fa
Feedback
⚖️Shields Law🇪🇹 የህግ አገልግሎት / Legal service ⚖️

⚖️Shields Law🇪🇹 የህግ አገልግሎት / Legal service ⚖️

رفتن به کانال در Telegram

⚖️ Shields Law ⚖️. ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች እዚሁ ያገኛሉ። Here on our channel, we provide Free legal Aid. You could alsk get access to laws, cassation decisions, job opportunity updates. ለማስታወቂያ 👉@alexyoba21

نمایش بیشتر
7 738
مشترکین
-224 ساعت
-117 روز
+1830 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+68
در 7 کانال‌ها
ژوئن '26
+108
در 7 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+88
در 7 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+76
در 6 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+53
در 5 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+75
در 5 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+105
در 4 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+139
در 10 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+103
در 2 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+163
در 9 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+84
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+74
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+121
در 6 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+66
در 2 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+85
در 8 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+89
در 6 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+132
در 6 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+63
در 4 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+150
در 5 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+200
در 7 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+561
در 3 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+377
در 6 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+262
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+406
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+554
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+432
در 4 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+373
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+603
در 3 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+332
در 5 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+390
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+517
در 2 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+415
در 2 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+159
در 3 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+140
در 2 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+69
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+137
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+265
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+254
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+197
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+92
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+181
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+60
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+131
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+92
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+119
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+255
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+194
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+619
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
25 ژوئیه+2
24 ژوئیه+1
23 ژوئیه+1
22 ژوئیه+2
21 ژوئیه0
20 ژوئیه+1
19 ژوئیه+1
18 ژوئیه+1
17 ژوئیه0
16 ژوئیه+13
15 ژوئیه+4
14 ژوئیه+1
13 ژوئیه+7
12 ژوئیه0
11 ژوئیه0
10 ژوئیه+2
09 ژوئیه+4
08 ژوئیه+1
07 ژوئیه+3
06 ژوئیه+6
05 ژوئیه+1
04 ژوئیه+3
03 ژوئیه+5
02 ژوئیه+5
01 ژوئیه+4
پست‌های کانال
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ የኢፌዲሪ የፍትሕ ሚኒስቴር በሕግ የተጣለበትን ኃላፊነት በላቀ ለመወጣት ይችል ዘንድ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በማውጣት የአሰራር እና የአደረጃጀት ማሻሻያዎችን አድርጓል። በአዲሱ አደረጃጀት መሠረት ባሉ የተለያዩ ማስተባበሪያዎች፣ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች፣ ዳይሬክቶሬቶች ተመድበው ለመስራት ፍላጎቱ እና ተነሳሽነቱ ያላቸው እና ከዚህ በታች የተመላከቱ መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሕግ ባለሙያዎችን በዐቃቤ ሕግነት ለመቅጠር ይህ ማስታወቂያ ወጥቷል። በመሆኑም ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 30 ቀናት ውስጥ በተወዳዳሪነት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን። አስፈላጊ የሆኑ መስፈርቶች፡ ኢትዮጵያዊ የሆነ/የሆነች እና በኢትዮጵያ የሚኖር /የምትኖር ፤ ለሕገ መንግስቱ እና ለሕግ የበላይነት ተገዢ የሆነ/የሆነች ፤ የየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆነ/ያልሆነች ፤ በታታሪነቱ/ቷ ፣ በታማኝነቱ/ቷ ፣ በሥነ-ምግባሩ/ሯ መልካም ስም ያተረፈ/ች መሆኑን/ኗን ይማርበት/ ትማርበት ከነበረበት ዩኒቨርሲቲ ወይም ከሚኖሩበት አካባቢ ካለ የመንግስት ተቋም ማስረጃ ማቅረብ የሚችል /የምትችል ፤ የወንጀል ቅጣት ሪከርድ የሌለበት/ባት ፤ የፌዴራል መንግስቱን የሥራ ቋንቋ የሚችል/የምትችል ፤ እንደ አስፈላጊነቱ የሚሰጠውን የጽሁፍም ይሁን የቃል ወይም ሁለቱንም ፈተና መውሰድ እና ማለፍ የሚችል /የምትችል፤  የሥራ መደብ፡ (ዐቃቤ ሕግ) ዐቃቤ ሕግ ደረጃ ሦስት  ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋም በሕግ ትምህርት በመጀመሪያ ዲግሪ በ2018 ዓ.ም የተመረቀ /የተመረቀች፤ የመመረቂያ ነጥብ (Cumulative GPA) 3.6 ከዚያ በላይ ያለው/ ያላት፣ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት 85 ፐርሰንታይል እና ከዛ በላይ በማምጣት ፈተናውን ያለፈ/ያለፈች፤ ብዝሃነት፣ ሴት እና አካል ጉዳተኛ ተወዳዳሪዎችን እናበረታታለን፤  የሥራ ልምድ - 0 አመት ብዛት -25 የምዝገባ ሁኔታ፡-  http://www.justice.gov.et በሚለው የተቋሙ ዌብሳይት ክፍት የሥራ ቦታ በሚለው ሥራ ባለው ማስፈንጠሪያ ወይም https://forms.gle/rWi1n6wi8HYYZubc7 በመጠቀም የሚጠይቀውን መረጃ በመሙላት እና ማስረጃዎችን በማያያዝ መመዝገብ ይቻላል። የምዝገባ ቀን፡- ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ፤ ማስታወሻ፡- ተወዳዳሪዎች ሲመዘገቡ ሊያሟሏቸው የሚገባቸው ሰነዶች፡- 1. ኢትዮጵያዊ መሆናችሁን የሚገልጽ መታወቂያ/ፓስፖርት እና ብሔራዊ መታወቂያ በpdf scan የተደረገ፤ 2. ዋና የትምህርት ማስረጃ (student copy) ጨምሮ በpdf scan የተደረገ ፤ አጠቃላይ የመመረቂያ አማካይ ውጤት CGPA እና የመውጫ ፈተና ውጤትን Exit Exam የሚገልጽ የትምህርት ማስረጃ፣ 3. ከሚኖሩበት አካባቢ ካለ የመንግስት ተቋም ወይም ከተመረቁበት የትምህርት ተቋም የመልካም ሥነ ምግባር ማስረጃ፣  ለበለጠ መረጃ ፡- በስራ ሠዓት በስልክ ቁጥር ፡- +251-15-15-7432 በመደወል፤ እንዲሁም በኢሜል አድረራሻ፡- mojprosecutorsadministration@justice.gov.et ወይም mojpublicprosecutorsa@gmail.com ላይ በመፃፍ ማግኘት ይችላሉ።  የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር

2
ቅጣትን የማቅለል እና ከቅጣት ነፃ ማድረግ ደንብ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ    መግቢያ ወንጀል ግላዊ ባህሪ ያለው በመሆኑ በወንጀል አድራጊዎች ላይ የሚጣለው ቅጣት እንደነገሩ ሁኔታ ሊከብድ ወይም ሊቀል ይችላል። ይህም የሚሆነው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ ስለ ቅጣት ማቅለያ እና ማክበጃ ምክያቶች ያስቀመጣቸውን ድንጋጌዎች መሠረት በማድረግ ነው። በዚህ ጽሑፍ የወንጀል ቅጣት ዓላማዎች፣ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ ቅጣት የሚወሰንበት አግባብ፣ ቅጣት የሚቀልበት ሁኔታ እና ከቅጣት ነፃ የማድረግ ሁኔታ በአጭሩ ይዳሰሳሉ።    የወንጀል ቅጣት ዓላማዎች በኢትዮጵያ የወንጀል ቅጣት ዓላማዎችን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 1 መገንዘብ ይቻላል። ይህም የወንጀል ሕግ ግብ ወንጀል እንዳይፈፀም መከላከል ሲሆን ይህንን የሚያደርገው ስለወንጀሎችና ስለቅጣታቸው በቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት፣ ማስጠንቀቂያነቱ በቂ ባልሆነበት ጊዜ ወንጀል አድራጊዎች ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠቡና ለሌሎች ማስተማሪያ እንዲሆኑ ወይም እንዲታረሙ በማድረግ ወይም ተጨማሪ ወንጀሎችን እንዳይፈፅሙ እርምጃዎች እንዲወሰዱባቸው በማድረግ ነው። በመሆኑም ቅጣቶች በአጠቃላይ ወንጀለኛው እንዲታረም (rehabilitative)፣ ወንጀል እንዳይፈፅም መከላከል (prevention, incapacitation) ወይም መቀጣጫ እንዲሆን (deterrence) የማድረግ ዓላማን ለማሳካት ተፈፃሚ ይሆናሉ።    ቅጣት የሚወሰንበት ሁኔታ  ፍርድ ቤቶች ቅጣቶችን የሚወስኑት የወንጀል ሕጉን ጠቅላላ ክፍል ድንጋጌዎች እንዲሁም ስለወንጀሎችና ስለቅጣታቸው የሚደነግጉትን የልዩ ክፍሉን ድንጋጌዎች መሠረት በማድረግ ነው። በወንጀል ሕግ አንቀጽ 88(2) እንደተደነገገው ቅጣቱ ሊወሰን የሚገባው የወንጀል አድራጊውን ግላዊ የአደገኝነት መጠን፣ ያለፈ የሕይወት ታሪኩን፣ ወንጀል ለማድረግ ያነሳሱትን ምክንያቶችና የአሳቡን ዓላማ፣ የግል ኑሮውን ሁኔታ፣ የትምህርቱን ደረጃ እንዲሁም የወንጀሉን ከባድነትና የአፈፃፀሙን ሁኔታ በማመዛዘን ነው። በመሆኑም የወንጀል ሕጉ ልዩ ክፍል ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆኖ ፍርድ ቤቶች እጅግ ቀላል ከሆነ ቅጣት አንስቶ እስከ ከባዱ ድረስ ያለውን በጥንቃቄ በመመርመር ለእያንዳንዱ ጉዳይ ተገቢ የሆነውን ቅጣት እንዲወስኑ የሚጠበቅባቸው ሲሆን በጣም ቀላል የሆኑ ወንጀሎች ባጋጠሙ ጊዜ በወንጀል ሕጉ ስለማስጠንቀቂያ ወይም ስለተግሳጽ ወይም ስለደንብ መተላለፍ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች በመከተል ሊወስኑ ይችላሉ።     ቅጣትን የማቅለል   ጠቅላላ የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶች በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 82 የተደነገጉ ሲሆን ልዩ የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶች ደግሞ በአንቀጽ 83 ስር ይገኛሉ። ጠቅላላ የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶች የሚባሉት   ወንጀለኛው ወንጀሉን እስካደረገበት ጊዜ ድረስ የዘወትር ጠባዩ መልካም መሆን   ወንጀሉ ከፍ ባለ ሀይማኖታዊ፣ ሞራላዊ ወይም ማሕበራዊ እምነት በመነሳሳት የተፈፀመ መሆን   ወንጀሉ በከፍተኛ ቁሳዊ እጦት፣ የሕሊና ስቃይ፣ ከፍ ያለ አደጋ የሚያመጣ ነገር እንደተቃጣ በማሰብ፣ መሠረት ባለው ፍርሐት ወይም ሊታዘዝለት በሚገባው ወይም በሥልጣኑ ሥር በሚያስተዳድረው ሰው ተፅዕኖ ምክንያት የተፈፀመ መሆን   ወንጀሉ ብርቱ ፈተና ላይ በሚጥል የተበዳዩ ሰው ጠባይ፣ በከባድ ፀብ ቀስቃሽነት ወይም በአፀያፊ ስድብ ምክንያት ወይም ደም በሚያፈላ ንዴት፣ ስቃይ ወይም ብስጭት ወይም ከፍ ባለ አስገዳጅነት ባለው ስሜትን በሚለውጥ ሁኔታ ወይም ምክንያት ባለው የመንፈስ ሁከት የተፈፀመ መሆን   የወንጀል ፈፃሚው ወንጀሉን ከፈፀመ በኋላ መፀፀት፣ በተለይ ለተበዳዩ አስፈላጊውን እርዳታ በማድረግ፣ ጥፋቱን በመገንዘብ ራሱን ለፍትህ አካላት በማቅረብ ላደረሰው ጉዳት በተቻለ መጠን በመካስ መፀፀትን ማሳየት እና ፍርድ ቤት በቀረበም ጊዜ በክስ ማመልከቻው ላይ የተመለከውን የወንጀል ዝርዝር በሙሉ ማመን ናቸው፡፡      በተጨማሪም በአንቀጽ 86 መሠረት በአንቀጽ 179 ቅጣትን ለማቅለል የሚያስችል በሕግ በግልፅ ያልተፃፈ ሌላ በቂ ምክንያት ሲገኝና ይህንኑ ፍርድ ቤቱ የሚቀበለው ሲሆን ለምን እንደተቀበለው ገልፆ ቅጣቱን ሊያቀል ይችላል። አንቀጽ 179 መደበኛ የቅጣት ማቅለያ ደንብ የሚደነግግ ሲሆን ፍርድ ቤት በዚህ አንቀጽ መሠረት ቅጣትን ለማቅለል እንደሚቻል በሕግ በተደነገገ ጊዜ ሁሉ ቅጣትን ማቅለል የሚገባ ሆኖ ሲያገኘው፡-  በሞት ቅጣት ምትክ ከ20 ዓመት እስከ ዕድሜ ልክ የሚደርስ ጽኑ እሥራት  በዕድሜ ልክ ጽኑ እሥራት ምትክ ከ10 ዓመት እስከ 20 ዓመት ጽኑ እሥራት ቅጣት  የጽኑ እሥራት ቅጣት መነሻ ከፍ ብሎ በሕጉ ልዩ ክፍል ተደንግጎ ሲገኝ በዚህ ቅጣት ምትክ በሕጉ ጠቅላላ ክፍል መነሻ ሆኖ ከተደነገገው ከ1 ዓመት ጀምሮ የጽኑ እሥራት ቅጣት  መነሻው 1 ዓመት በሆነ ጽኑ እስራት ምትክ ከ6 ወር እስከ 5 ዓመት የሚደርስ የቀላል እስራት ቅጣት  የቀላል እስራት ቅጣት መነሻ ከፍ ብሎ በሕጉ ልዩ ክፍል ተደንግጎ ሲገኝ በዚህ ቅጣት ምትክ ከ10 ቀን የማያንስ የቀላል እስራት ቅጣት እንዲሁም  ከ10 ቀን በማያንስ የቀላል እስራት ቅጣት ምትክ የግዳጅ ሥራ ወይም መቀጮ ይወስናል። እንዲሁም ፍርድ ቤት ቅጣትን በመሰለው ማቅለል አለበት ወይም ይችላል ተብሎ በተደነገገ ጊዜ የወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል በሚደነግገው የቅጣት ዓይነት ወይም መነሻ ቅጣት ሳይወስን መነሻ ከሆነው ቅጣት ዝቅ አድርጎ ወይም ቀለል ያለ ሌላ ዓይነት ቅጣት ተክቶ ለመወሰን ሥልጣን አለው። ይሁንና ፍርድ ቤቱ የሚወስነው ማናቸውም ዓይነት ቅጣት በወንጀል ሕጉ ጠቅላላ ክፍል ለየቅጣቱ ዓይነት ከተደነገገው መነሻ ዝቅ ሊል አይችልም (የወንጀል ሕግ አንቀጽ 180)።     ከቅጣት ነጻ ማድረግና ቅጣትን መተው ፍርድ ቤት ጥፋተኛውን ከማናቸውም ቅጣት ነፃ ማድረግና በሙሉ ወይም በከፈል ቅጣትን መተው የሚችለው በሕጉ ላይ በግልፅ ተደንግጎ ሲገኝ ብቻ እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 182 ተደንጓል። ለምሳሌ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 454 መሠረት በሐሰተኛ ምስክርነት ወይም ልዩ አስተያየት፣ በሐሰት በመተርጎም ወይም በማስተርጎም የተከሰሰ ሰው በሌላ ሰው ላይ ጉዳት ከመድረሱና የመጨረሻ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት ጥፋተኛው በገዛ ፈቃዱ ቃሉን አቃንቶ ወይም ለውጦ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን በተለየ ሁኔታ የሚያቀልለት ሲሆን ወንጀሉ ወይም ወንጀሉ የሚያስከትለው አደጋ ቀላል ሆኖ የማቃናቱ ወይም የመለወጡ ተግባር የተፈጸመው በሐቀኝነት እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ ጥፋተኛውን በመገሰጽና ማስጠንቀቂያ በመስጠት ፍርድ ቤቱ ከማናቸውም ሌላ ቅጣት ነፃ ሊያደርገው እንደሚችል ተደንግጓል። እንዲሁም ከወንጀል ሕጉ አንቀጽ 28 ድንጋጌ መረዳት እንደሚቻለው ወንጀል አድራጊ ሊፈፅመው የነበረውን ወንጀል በሐቀኝነት ወይም ከፍ ባለ የሕሊና ስሜት በመነሳሳት መፈፀሙን ከተወ ፍርድ ቤት ከቅጣት ነፃ ሊያደርገው ይችላል።    ማጠቃለያ የወንጀል ቅጣት ውሳኔዎች ወጥ፣ ተመጣጣኝ እና ተገማች መሆን ያለባቸው ቢሆንም እንደወንጀሉ አደገኝነት እና እንደወንጀል አድራጊው ግላዊ ሁኔታ የወንጀል ሕጉን ድንጋጌዎች መሠረት በማድረግ ቅጣት ሊቀል እንዲሁም በሕግ በግልፅ በተደነገገ ግዚም ከቅጣት ነፃ የማድረግ ውሳኔ ሊሰጥ ይችላል።                              እንኳን ደስ አለችሁ ሰለነበበቹህ
1 721
3
የስራ ስንበት ክፍያ እና የካሳ ምንነት የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ በተለምዶ የአገልግሎት ክፍያ እየተባለ ለሚታወቀው የስራ ስንብት ክፍያ ትርጉም ያልሰጠ ቢሆንም በተለያዩ ፅሁፎች ከተሰጠው ትርጉም መረዳት እንደሚቻለው የሥራ ስንብት ክፍያ ማለት አሠሪው ከቅጥሩ በኋላ ወይም ቅጥሩ ሲጠናቀቅ ለሠራተኛው የሚሰጠው ማካካሻ እና/ወይም ጥቅማጥቅሞች ነው። በአዋጁ ስለስራ ስንበት ክፍያ ከተቀመጡ አጠቃላይ ድንጋጌዎች የሚወሰደው ግንዛቤ ከዚህ ትርጉም ጋር የሚጣጣም ሆኖ ይገኛል። በተመሳሳይ አዋጁ ስለካሳ ምንነት ትርጉም ያልሰጠ ሲሆን ከድንጋጌዎቹ አጠቃላይ መንፈስ መረዳት እንደሚቻለው በአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ካሳ ማለት በአሰሪው ጥፋት የስራ ውል ተቋርጦ ወደ ስራ እንዲመለስ ለሠራተኛ ፍርድ ቤት ወስለት ሠራተኛው ወደ ስራ ለመመለስ ፍቃደኛ ካልሆነ በስራ መቋረጥ ምክንያት አሰሪ ለሠራተኛው ገንዘብ በካሳ መልክ የሚከፍልበት የክፍያ አይነት ነው። አዋጁ ለስራ ስንብት ክፍያ እና ካሳ ትርጉም ያልሰጠ ቢሆንም ክፍያዎቹ የሚከፈሉበትን ሁኔታ እና የክፍያ ስሌቱን በዝርዝር አስቀመቀጧል። የስራ ስንበት ክፍያ የሚከፈልባቸው ሁኔታዎች በአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 39 ስር የስራ ስንብት ክፍያ የሚከፈልባቸው ሁኔታዎች ተዘርዝረው ይገኛሉ። ይኸውም የሙከራ ጊዜውን የጨረሰ እና አግባብነት ባለው የጡረታ ሕግ መሠረት የጡረታ አበል ለመቀበል ብቁ ያልሆነ ሠራተኛ በሚከተሉት ሁኔታዎች የስራ ስንብት ክፍያ ይከፈለዋል። ድርጅቱ በመክሰሩ ወይም በሌላ ምክንያት ለዘለቄታው በመዘጋቱ የሥራ ውሉ ሲቋረጥ ( በአዋጁ አንቀጽ 24/4 ተመልክቷል )፣ በሕግ ከተደነገገው ምክንያት ውጪ በአሰሪው አነሳሽነት የሥራ ውሉ ሲቋረጥ ( የስራ ውል በአሠሪ አነሳሽነት ሊቋረጥ የሚችልባቸው ህጋዊ አግባቦች በአዋጁ አንቀጽ 26 ተመልክተዋል)፣ በአዋጁ በተመለከቱት ሁኔታዎች መሠረት ሠራተኛው ከስራ ሲቀነስ (የሠራተኛ የስራ ቅነሳ በአንቀጽ 29 ተመልክቷል) በአሰሪው ወይም በሥራ መሪ ወሲባዊ ጥቃት ወይም ትንኮሳ የተፈጸመበት እንደሆነ ወይም ድርጊቱ በሌላ ሠራተኛ እንደተፈጸመ ሪፖርት ተደርጎለት አሰሪው ተገቢውን እርምጃ ባለመውሰዱ ሠራተኛው የሥራ ውሉን ያቋረጠ እንደሆነ (ያለማስጠንቀቂያ የስራ ውል በሠራተኛው አነሳሽነት ሊቋረጥ የሚችልባቸው ሁኔታዎች በአዋጁ አንቀጽ 32(1)ለ ተመልክቷል)፣አሠሪው በሠራተኛው ላይ ሰብዓዊ ክብሩንና ሞራሉን የሚነካ ወይም በወንጀል ሕጉ መሠረት የሚያስቀጣ አድራጎት በመፈጸሙ የተነሣ ሠራተኛው የሥራ ውሉን ያቋረጠ እንደሆነ ( በአንቀጽ 32(1)ሀ ስር ተመልክቷል)፣ አሠሪው ለሠራተኛው ደኅንነት ወይም ጤንነት የሚያሰጋ አደጋ እንዳይደርስ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት እርምጃ ባለመውሰዱ የተነሳ ሠራተኛው የስራ ውሉን ሲያቋርጥ (ያለመስጠንቀቂያ የስራ ውል በሠራተኛው አንሳሽነት ሊቋረጥ የሚችልበት ምክንያት እንደሆነ በአዋጁ አንቀጽ 32(1)ሐ ተመልክቷል)፣ ሙሉ ወይም ዘላቂ የአካል ጉዳት በመድረሱ ሠራተኛው ሥራ ለመሥራት አለመቻሉ በሕክምና ተረጋግጦ የሥራ ውሉ ሲቋረጥ(በአዋጁ አንቀጽ 24(5) ተመልክቷል)፤ ቢያንስ አምስት ዓመት በአሠሪው ዘንድ የሥራ አገልግሎት ኖሮት በህመም ወይም በሞት የሥራ ውሉ ሲቋረጥ ወይም በሥራው ላይ የሚያስቆይ ከሥልጠና ጋር የተያያዘ ለአሠሪው የውል ግዴታ ሳይኖርበት ሥራውን በገዛ ፈቃዱ ሲለቅ፤ በኤችአይቪ/በኤድስ ህመም ምክንያት በራሱ አነሳሽነት የሥራ ውሉን ያቋረጠ እንደሆነ፤ ከአሰሪው የስራ ስንብት ክፍያ የማግኘት መብት አለው። አንድ ሠራተኛ የስራ ስንብት ክፍያ ከማግኘቱ በፊት ቢሞት የሥራ ስንብት በአንቀጽ 110/2 ለተመለከቱት ጥገኞቹ ማለትም የሟች የትዳር ጓደኛ፤ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ የሟች ልጆች እና በሟች ድጋፍ ይረዱ የነበሩ የሟች ወላጆች ይከፈላል። ለሟቹ ጥገኞች የሚከፈለው የስራ ስንብት ክፍያ በአዋጁ አንቀጽ 110 በሚከፈለው የካሳ አከፋፈል መሠረት የሚፈፀም ይሆናል። የስራ ውል ሲቋረጥ ካሳ የሚከፈልባቸው ሁኔታዎች አንድ አሰሪ ወይም ሠራተኛ የስራ ውልን ሲያቋርጥ በአዋጁ ወይም አግባብ ባለው ሌላ ሕግ የተወሰኑትን አስፈላጊ ሁኔታዎች ያላሟላ እንደሆነ የሥራ ውሉ መቋረጥ ህገ-ወጥ እንደሆነ የአዋጁ አንቀጽ 42 ይደነግጋል። ህገ-ወጥ የስራ ውል መቋረጥ ከሚያስከትላቸው ውጤቶች መካከል ወደ ስራ ከመመለስ ባሻገር የካሳ ክፍያ አንዱ ነው። በአዋጁ አንቀጽ 43/1 ስር እንደተደነገገው በአዋጁ አንቀጽ 26(2) በተመለከቱት ምክንያቶች አሰሪው የስራ ውሉን ቢያቋርጥ ሠራተኛውን ወደ ስራ የመመለስ ግዴታ ያለበት ሲሆን ሠራተኛው ወደ ስራ ለመመለስ ካልፈለገ ግን ካሳ እንዲከፈለው የመጠየቅ መብት አለው። በአዋጁ አንቀጽ 26(2) ስር እንደተደነገገው የሚከተሉት የሥራ ውልን ለማቋረጥ ተገቢ ምክንያቶች ሆነው ሊቆጠሩ የማይችሉ በመሆኑ የስራ ውል ሲቋረጥ ሠራተኛው ከስራ ስንብት ክፍያ በተጨማሪ የካሳ ክፍያ የማግኘት መብት አለው። እነሱም፡- ሀ) ሠራተኛው በሠራተኞች ማኅበር አባል መሆኑ ወይም በማኅበሩ ሕጋዊ ተግባሮች ተካፋይ መሆኑ፤ ለ) ሠራተኛው የሠራተኞች ተጠሪ ሆኖ ለመሥራት መፈለጉ ወይም መሥራቱ፤ ሐ) ሠራተኛው በአሠሪው ላይ ቅሬታ ማቅረቡ ወይም በፍርድ ቤት በቀረበ ክስ ወይም በሌላ ሰው ክስ ተካፋይ መሆኑ፤ መ) የሠራተኛው ብሔር፣ ጾታ፣ ሐይማኖት፣ የፖለቲካ አመለካከት፣ የጋብቻ ሁኔታ፣ ዘር፣ ቀለም፣ የቤተሰብ ኃላፊነት፣ የዘር ሐረግ፣ እርግዝና፣ አካል ጉዳተኝነት፣ ወይም ማኅበራዊ አቋም፡፡ በመሆኑም በእነዚህ ምክንያቶች የስራ ውልን ያቋረጠ አሰሪ ሠራተኛውን ወደ ስራ የመመለስ ወይም የካስ ክፍያ የመፈፀም ግዴታ አለበት። በተጨማሪ በአንቀጽ 32(1) (ያለማስጠንቀቂያ የስራ ውልን ማቋረጥ) መሠረት የስራ ውልን የሚያቋርጥ ሠራተኛ በአንቀጽ 40 (የስራ ስንብት ክፍያ መጠን) ከተመለከተው የስራ ስንብት ክፍያ በተጨማሪ የመጨረሻ ሣምንት አማካይ የቀን ደሞዙ በ30 ተባዝቶ ካሳ ይከፈለዋል። ይህ ክፍያ አግባብ ባለው የጡረታ ሕግ በተሸፈነ ሠራተኛ ላይም ተፈፃሚ እንደሚሆን አዋጁ ይደነግጋል። ሆኖም ሠራተኛው የስራ ውሉን ያቋረጠው በአንቀጽ 32(1)ለ ላይ በተመለከተው ምክንያት የሆነ እንደሆነ ከሥራ ስንብት ክፍያው በተጨማሪ የቀን ደመወዙ በ90 ተባዝቶ የሚከፈለው ሲሆን ይህ ክፍያ አግባብ ባለው የጡረታ ሕግ በተሸፈነ ሠራተኛ ላይም ተፈጻሚ እንደሚሆን በአዋጁ አንቀጽ 41(2) ስር ተደንግጎ ይገኛል። በሌላ በኩል ሠራተኛው ለአሰሪው ካሳ የመክፈል ኃላፊነት የሚኖርበት ሁኔታ በአዋጁ የተመለከተ ሲሆን ይህም በአንቀጽ 31(በማስጠንቀቂያ የስራ ውል ስለማቋረጥ) ወይም በአንቀጽ 35(2) (የማስጠንቀቂያ ጊዜ) ስለማስጠንቀቂያ የተጠቀሱትን አስፈላጊ ሁኔታዎች ያላሟላ ሠራተኛ ለአሠሪው ካሣ ይከፍላል። በዚህ መሠረት የሚከፈለው ካሣ አሰሪው ለሠራተኛው ከሚከፍለው ቀሪ ክፍያ ውስጥ ከ30 ቀናት የበለጠ መሆን እንደሌለበት በአዋጁ አንቀጽ 45 ላይ ተደንግጎ ይገኛል። በአጠቃላይ የስራ ስንብት እና የካሳ ክፍያ የሚከፈልባቸው ሁኔታዎች በአዋጁ የተመለከቱ በመሆኑ ሠራተኛው በሕግ አግባብ ክፍያዎቹን የመጠየቅ እና የማግኘት መብት አለው። አሠሪም እንደዚሁ።    
1 748
4
ክልከላ እና ገደብ የተደረገባቸው የቴክኖሎጂ ምርቶች የትኞቹ ናቸው? ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ክልከላ የተደረገባቸውና ገደብ የተደረገባቸው ምርቶች ዝርዝር ይፋ አድርጓል። በ+3
ክልከላ እና ገደብ የተደረገባቸው የቴክኖሎጂ ምርቶች የትኞቹ ናቸው? ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ክልከላ የተደረገባቸውና ገደብ የተደረገባቸው ምርቶች ዝርዝር ይፋ አድርጓል። በዚህም ክልከላ የተደረገባቸው የሚባሉት በምንም ዓይነት ሁኔታ ወደ ሀገር እንዳይገቡ፣ ከሀገር እንዳይወጡ ወይም ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ሙሉ በሙሉ የተከለከሉ የተደረገባቸው ናቸው። ገደብ የተደረገባቸው ምርቶች ደግሞ ወደ ሀገር ሊገቡ፣ ሊወጡ ወይም ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉት  የደህንነት ማረጋገጫ ፈቃድ ሲሰጣቸው ብቻ ይሆናል። ተቋሙ፥ ማንኛውም አስመጪ፣ ላኪ ወይም ተጠቃሚ የቴክኖሎጂ ምርቶችን ከማስገባቱ ወይም ከማስወጣቱ በፊት ምርቶቹ በየትኛው ምድብ ውስጥ እንደሚወድቁ የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለበት አስታውቋል። @TikvahethMagazine
1 695
5
ግን5አመት ህግ ተምረን እውነት ውትድርና ግቡ ማለት ግን ምን ማለትነው ለምን ዩኒቨርሲቲውን አይዘጉትም ግን ኧረ ቢያንስ በተስፋ እንኑር?
1
6
የቅጥር ማስታወቂያ በመከላከያ ፍርድ ቤቶች ውስጥ በዳኝነት, በጠበቃነት እና በሪጅስትራርነት መስራት ለምትፈልጉ ሁሉ። የኢ.ፊ.ዲ.ሪ የሀገር መከላከያ ሚኒስተር Join us Your Trusted Lega+2
የቅጥር ማስታወቂያ በመከላከያ ፍርድ ቤቶች ውስጥ በዳኝነት, በጠበቃነት እና በሪጅስትራርነት መስራት ለምትፈልጉ ሁሉ። የኢ.ፊ.ዲ.ሪ የሀገር መከላከያ ሚኒስተር Join us Your Trusted Legal Info Centre @Law_School_Media @Law_School_Media @Law_School_Media
3 009
7
✅ Global Bank Ethiopia S.C - Junior Attorney Vacancy Position: Junior Attorney (Qty: 2) Place of Work: Head Office Requirements: - LLB Degree - Fresh Graduates of 2024, 2025 & 2026 academic years - Minimum CGPA: 2 and above - Must have passed the exit exam - No prior experience required Salary: As per the Bank’s Salary Scale Application Deadline: July 17, 2026 (5 working days) How to Apply: Interested applicants should submit their non-returnable applications along with CV and photocopies of other relevant documents in person to: Global Bank Ethiopia S.C. Head Office Human Capital Management Department National Tower Building 9th floor (behind Ethiopia Hotel) Or by post to: Global Bank Ethiopia S.C Human Capital Management Dep’t P.O. Box 100743
2 606
8
👉 በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 94 መሠረት ጋብቻ መኖሩን ማስረዳት የሚቻለው በጋብቻ የምስክር ወረቀት መሆኑ የተደነገገ ሲሆን የምስክር ወረቀቱ በሌለ ጊዜ የትዳር ሁኔታ መኖርን በማስረዳት ጋብቻ እንዳለ ማረጋገጥ እንደሚቻል ከሕጉ አንቀጽ 96 እና 97 ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡ 👉ነገር ግን በተያዘው ጉዳይ አመልካችና ተጠሪ ፎቶ ግራፍ ተነስተዋል የተጠሪ እህትም እራት ጋብዘዋል መባሉ በህጉ በሚታወቁት ጋብቻዎች ሥርዓት ጋብቻ ተፈጽሟል የሚያሰኝ አይደለም፡፡ 👉በዚህ መልኩም የትዳር ሁኔታ መኖሩን አሳይተዋል ሊባልም አይችልም፡፡ 👉ከመነሻውም የአሁን ተጠሪ አስቀድመው ካቀረቡት አቤቱታና በዚህ ፍርድ ቤት ከሰጡት መልስ መገንዘብ የሚቻለው እራሳቸው ተጠሪ ከአመልካች ጋር የነበራቸው ግንኙነት ጋብቻ የፈፀሙ ባልና ሚስት ሳይሆን እንደባልና ሚስት ግንኙነት መሆኑን እንደሚቆጥሩት እና የተጠሪ ቤተሰቦችም ባልና ሚስት ናቸው በማለት ያልተቀበላቸው እንደነበር የሚያሳይ ነው። 👉 ይህ አይነቱ ሁኔታ ደግሞ በቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 96 መሠረት በመካከላቸው የትዳር ሁኔታ መኖሩን የሚያስገነዝብ አይደለም፡፡ በቤተሰብ ህጉ በአንቀጽ 97/1/ መሠረትም ግምት መውሰድ የሚቻልበት አይደለም። 👉 የሰ/መ/ቁ. 246124 ጥቅምት 6 ቀን 2015
2 430
9
ህፃናት ወራሾች በሆኑበት የንብረት ክርክር ይርጋ የሚቆጠረው 18 አመት ከሞላቸው በ10 አመት ውስጥ እንደሆነ በ10 አመት ውስጥ ካላቀረቡ ይርጋ እንደሚያልፍባቸው በቅፅ 27 ሰ/መ/ቁ 239453 ውሳኔ ተሰጥቶበቷል
1
10
የጠፋው ሰው በሕይወት መመለስ እና ውጤቱ የመጥፋት ውሳኔ የተሰጠበት ሰው በሕይወት መመለስ የመጥፋት ውሳኔ ቀሪ ከሚሆንባቸው ምክንያቶች ውስጥ አንዱ እንደሆነ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 170 ሥር ተደንግጎ የምናገኘው ጉዳይ ነው። ጠፋ የተባለው ሰው መመለስ ደግሞ የራሱ ውጤቶችን እንደሚያስከትል በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 171 ሥር የተመለከተ ሲሆን እነዚህም፡- • ጠፋ የተባለው ሰው የተወሰዱ ንብረቶችን በሚገኙበት አኳኋን ይወስዳል። ንብረቶቹ ተሽጠው ከሆነ ደግሞ የተሸጡበትን ዋጋ ይወስዳል፣ ስለሆነም ንብረቶቹን የያዙ ግለሰቦች በዚህ አግባብ ለተመለሰው ሰው የማስረከብ ግዴታ አለባቸው። (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 171)። ንብረቱን የያዙ ግለሰቦች በተንኮል ወይም በመጥፎ አስተዳደር ላጠፉት ነገር ካሳ የመክፈል ኃላፊነት አለባቸው (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 171(3))። • ጋብቻን በተመለከተ ግን በመጥፋት ውሳኔው የፈረሰው ጋብቻ መመለሱ ሕይወት እንዲዘራ ወይም እንደገና እንዲጸና የማድረግ ውጤት የለውም (የፍትሐብሔር ሕግ  ሰ/መ/ቁ. 74791 ቅጽ 14፣ ሰ/መ/ቁ. 213917 ቅጽ 27)። ማጠቃለያ የመጥፋት ውሳኔ በሕይወት መኖሩ ባልታወቀ ሰው ምክንያት በቤተሰብ እና በንብረት መብት ላይ የሚፈጠርን ክፍተት ለመሙላት የተቀረጸ ጠቃሚ የሕግ መሣሪያ ነው። ሕጉ በአንድ በኩል የጠፋውን ሰው በሕይወት የመመለስ ተስፋና ንብረት ለመጠበቅ የጊዜ ገደቦችንና የዋስትና ግዴታዎችን የሚያስቀምጥ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የቀሩት ቤተሰቦችና ወራሾች ሕይወታቸውን እንዲቀጥሉና ንብረቱን እንዲያስተዳድሩ መብት ይሰጣል። በመሆኑም ሕጉ እንደሚደነግገው ያለ ፍርድ ቤት መደበኛ የመጥፋት ውሳኔ ማስታወቂያና ማረጋገጫ በሰዎች ንብረትና መብት ላይ መወሰን በሕግ ፊት ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ ማኅበረሰቡ ይህንን ሥርዓት ተገንዝቦ በሕጋዊ መንገድ መብቱን ማስከበር ይኖርበታል። @ንቃተ ሕግና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
2 151
11
+5
639-2009 የፍትሃብሄር ህግ ማሻሻያ አዋጅ.pdf
3 062
12
የወንጀል ጉዳች ልዩ ዕትም-.pdf
3 156
13
የፌደራል የታክስ አስተዳደርን ለማሻሻል የወጣው አዋጅ ይዟቸው የመጡ አዳዲስ ለውጦች ምንድናቸው? የፌደራል የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008ን ለማሻሻል የወጣው ማሻሻያ አዋጅ በርካታ መሠረታዊ ለውጦችንና አዳዲስ አሰራሮችን ይዞ ቀርቧል። ዋና ዋናዎቹ ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፡- 1. አዳዲስ ትርጓሜዎችና የተቋም ስም ለውጥ 👉🏽 መስማማት (Settlement)፡ የታክስ አለመግባባቶችን በውይይትና በስምምነት ለመፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በትርጓሜ ደረጃ ተካቷል። 👉🏽 የታክስ ማጭበርበር፡ ታክስን ለመሰወር የሚደረጉ እንደ ሐሰተኛ ደረሰኝ ማቅረብና ገቢን መደበቅ ያሉ ተግባራት በዝርዝር ተተርጉመዋል። 2. የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ሥርዓት ይህ  አዋጁ ይዞት የመጣው ትልቁ ለውጥ ሲሆን፣ ክርክሮችን በፍርድ ቤት ወይም በይግባኝ ኮሚሽን ከመጨረስ ይልቅ በባለሥልጣኑና በታክስ ከፋዩ መካከል በሚደረግ ስምምነት እንዲቋጩ የሚያስችል ነው። 👉🏽 የአስማሚ ሚና፡ የታክስ ባለሥልጣኑ ነጻና ገለልተኛ "አስማሚ" በመመደብ ሂደቱን ያመቻቻል። 👉🏽 ሂደቱ፡ መስማማት የሚቻለው በታክስ ውሳኔ ላይ ቅሬታ ከቀረበ በኋላ ሲሆን፣ በዚህ ወቅት ለይግባኝ የተቀመጡ የጊዜ ገደቦች ታግደው ይቆያሉ። 👉🏽 ውጤቱ፡ የሚደረሰው ስምምነት በጽሁፍ ሆኖ በሁለቱም ወገኖች ከተፈረመ አስገዳጅና ተፈጻሚነት ይኖረዋል። 3. በአዲስ ማስረጃ አቀራረብ ላይ የተጣለ ገደብ 👉🏽 ታክስ ከፋዮች የታክስ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ በቅሬታ ወይም በይግባኝ ወቅት አዲስ ማስረጃ የማቅረብ መብታቸው ተገድቧል። 👉🏽 አዲስ ማስረጃ ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው ማስረጃው የታወቀው ከውሳኔ በኋላ ከሆነ ወይም አቅም በላይ በሆነ ምክንያት ካልቀረበ ብቻ ነው። 👉🏽 በዚህ መልክ የሚቀርብ አዲስ ማስረጃ በታክስ ዕዳው ላይ 20% ቅጣት እንዲከፈል ያደርጋል። 4. የታክስ ስሌት ማሻሻያና የይርጋ ጊዜ 👉🏽 የማጭበርበር ድርጊት፡ ባለሥልጣኑ የታክስ ማጭበርበር መኖሩን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ካገኘ፣ የታክስ ስሌቱን የማሻሻያ ጊዜ (ይርጋ) እስከ 10 ዓመት እንዲራዘም ተደርጓል። 👉🏽 መደበኛው የታክስ ስሌት ማሻሻያ ጊዜ ግን በነበረበት 5 ዓመት ቀጥሏል። 5. በሁኔታ ላይ የተመሰረተ የታክስ ክሊራንስ 👉🏽 የታክስ ዕዳ ያለባቸው ነገር ግን በክርክር ላይ ያሉ ወይም የክፍያ ስምምነት የፈጸሙ ታክስ ከፋዮች የንግድ ፈቃድ ለማደስ፣ በጨረታ ለመሳተፍና ብድር ለማግኘት የሚያስችላቸው "በሁኔታ ላይ የተመሰረተ የታክስ የምስክር ወረቀት" ማግኘት የሚችሉበት አሰራር ተዘርግቷል። 6. የታክስ ከፋዮች ምደባ 👉🏽 የታክስ ከፋዮች ምዝገባ ኢትዮጵያ በተቀበለችው የዓለም አቀፍ የኢንዱስትሪ ምደባ ደረጃ (ISIC) መሠረት እንዲከናወንና ታክስ ከፋዮች በተለያዩ ምድቦች እንዲመደቡ ተደንግጓል። 7. የቅጣት ማስተካከያዎች 👉🏽 ደረሰኝ አለመስጠት፡ የታክስ ደረሰኝ ሳይሰጥ ሲቀር የሚጣለው አስተዳደራዊ ቅጣት በእያንዳንዱ ደረሰኝ ብዛት ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) እንዲሆን ተሻሽሏል። 👉🏽 የድርጅት ኃላፊዎች ተጠያቂነት፡ አንድ ድርጅት የታክስ ወንጀል ሲፈጽም የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ወይም የፋይናንስ ኃላፊ ወንጀሉ መፈጸሙን ካወቁ ወይም ካዘዙ ተጠያቂ ይሆናሉ።
2 850
14
Vacancy / የስራ ማስታወቂያ
Vacancy / የስራ ማስታወቂያ
2 445
15
ለፖሊስ እጅ መስጠት የቅጣት ማቅለያ ይሆናልን?===========================https://t.me/Shields_Law ወንጀል ፈጽሞ ለፖሊስ እጅ መስጠትን በቅጣት ማቅለያነት የመያዝ ህጋዊ እይታ እና የሰበር አቋም! ​አንድ ተከሳሽ የወንጀል ድርጊት ከፈጸመ በኋላ እራሱን ለህግ አካል (ለፖሊስ) ማስረከቡ በቅጣት ማቅለያነት ሊያዝለት ይገባል ወይስ አይገባም? በሚለው ጭብጥ ላይ በዳኞች ዘንድ ሁለት የተለያዩ ህጋዊ አቋሞች ይስተዋላሉ፡ ​የመጀመሪያው እይታ (የማቅለያነት መብትን የሚቃወም)፦ ተከሳሹ እጁን ለፖሊስ የሰጠው ከልቡ ተጸጽቶ ሳይሆን፣ ከተጎጂው ወገኖች ሊሰነዘርበት የሚችለውን የበቀል ወይም የአጸፋ እርምጃ ለመሸሽ (ለራሱ ደህንነት ሲል) በመሆኑ፣ ይህ ድርጊት በቅጣት ማቅለያነት ሊወሰድለት አይገባም የሚል ነው። ​ሁለተኛው እይታ (የማቅለያነት መብትን የሚደግፍ)፦ የወንጀል ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ በራስ ፍላጎት ለህግ አካል እጅ መስጠት በራሱ እንደ ቅጣት ማቅለያ መቆጠር አለበት የሚል አቋም ነው። ​የሰበር መደበኛ ውሳኔ እና የመጨረሻ አቋም፦ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይህንን ክርክር የቋጨው ሁለተኛውን አቋም በመደገፍ ነው። ሰበር በሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም መሠረት፤ አንድ ተከሳሽ ወንጀል ፈጽሞ እጁን ለፖሊስ ወይም ለሚመለከተው የህግ አካል ካስረከበ፣ ይህ ድርጊቱ በቅጣት ማቅለያነት ሊያዝለት ይገባል በማለት ወስኗል። https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law
2 739
16
በ0 አመት Centre for Justice Vacancy - Interns ● Deadline: July 7, 2026 Centre for Justice (CJ) is one of Ethiopia’s main independent civil society organizations. ✅ Position 1: Legal Aid Service Provider Intern ■ Required Qualifications: LL.B Degree in Law (Must be a recent graduate or pending graduation confirmation). ✅ Position 2: Projects Intern ■ Required Qualifications: LL.B Degree in Law (Must be a recent graduate or pending graduation confirmation). How to Apply?? 👇👇👇 https://effoysira.com/centre-for-justice-project-interns/ NB: you have to prepare the following documents in single pdf. 1. Cover letter 2. Detailed CV 3. Copies of Academic credentials Join Us For More Accessibility of Laws https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law
2 280
17
በወንጀል የተከሰሰ ሰው የግል ተበዳይን በመከላከያ ምስክርነት ያቀረበና የግል ተበዳይም ድርጊቱ ያለመፈጸሙን በመግለጽ የምስክርነት ቃል የሰጠ ከሆነ ዓ/ህግ የግል ተበዳይ የምስክርነት ቃል በደላላ ወይም በጥቅም የተገኘ መሆኑን ለማረጋገጥ እስከ አልቻለ ድረስ ተከሳሽ ክሱን አልተከላከለም ሊባል የማይገባ ስለመሆኑ፡፡ ሰ.መ.ቁ 137545 ቅፅ  22
2 408
18
ፀደቀ‼️ የታክስ ቅሬታ አጣሪው ተቀየረ፤ የታክስ ቅጣትም በግማሽ ተቀነሰ‼️ *ሰኔ 23/2018 ዓ/ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ላይ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን አድርጎ በዛሬው ዕለት አጽድቋል። ማሻሻያው በተለይም ለታክስ ከፋይ ተቋማት የፍትህ አድማሱን የሚያሰፋና የቅጣት ጫናን የሚቀንስ ነው። በአዋጁ የተካተቱት ዋና ዋና ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፦ ከዚህ ቀደም በታክስ ባለሥልጣኑ በራሱ ይሰየም የነበረው የታክስ "አስማሚ" (Mediator)፣ ከአሁን በኋላ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚሰየም ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን ይተካል፡፡ ይህም የታክስ ክርክሮች ፍትሃዊ እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲታዩ ያስችላል። ታክስ ከፋዮች በታክስ አወሳሰን ወቅት ያልቀረቡ ነገር ግን በኋላ ላይ የዕዳ መጠን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ማስረጃዎችን ሲያቀርቡ ይጠብቃቸው የነበረው 20 በመቶ ቅጣት፣ በግማሽ ተቀንሶ ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል። የታክስ ህግን በመተላለፍ ወንጀል የሚፈጽሙ ድርጅቶች ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ድንጋጌ ተካቷል። በዚህም መሰረት ወንጀሉ በተፈጸመበት ወቅት በስልጣን ላይ የነበሩ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጆች ወይም የፋይናንስ ኃላፊዎች ለወንጀሉ በግል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ህጉ በግልጽ አስቀምጧል። ይህ ማሻሻያ የታክስ አስተዳደርን ይበልጥ ግልጽ፣ ፍትሃዊ እና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
2 669
19
የዓለም አቀፍ ስምምነቶች በኢትዮጵያ ሕግ ደረጃ 1. ዓለም አቀፍ ሕግ በብሔራዊ ሕግ ሥርዓት ውስጥ፡ መሠረታዊ ንድፈ-ሐሳቦች በዓለም አቀፍ ደረጃ አንድ አገር የዓለም አቀፍ ሕግጋትንና የራሷን የውስጥ (ብሔራዊ) ሕግጋት የምታይበት መንገድ በሦስት ዋና ዋና ንድፈ-ሐሳቦች ይከፈላል። ሀ. አህዳዊ ንድፈ-ሐሳብ (Monism) ይህ ንድፈ-ሐሳብ ዓለም አቀፍ ሕግና ብሔራዊ ሕግ የአንድ ወጥ የሕግ ሥርዓት ክፍሎች ናቸው ብሎ ያምናል። ባህሪው፦ አንድ አገር ዓለም አቀፍ ስምምነትን እንዳፀደቀች፣ ስምምነቱ በራሱ (Automatically) የብሔራዊ ሕጉ አካል ይሆናል። ተጨማሪ የውስጥ ሕግ አያስፈልገውም። ተከታዮች፦ አብዛኛውን ጊዜ የሲቪል ሎው (Civil Law) ተከታይ የሆኑ የአውሮፓ አገራት (ለምሳሌ፦ ፈረንሳይ፣ ጀርመን) ይህንን ይከተላሉ። ግጭት ሲፈጠር፦ አብዛኛውን ጊዜ ዓለም አቀፍ ሕግ ከብሔራዊ ሕግ (አንዳንድ ጊዜ ከሕገ-መንግሥትም ጭምር) የበላይነት ይሰጠዋል። ለ. መንታዊ ንድፈ-ሐሳብ (Dualism) ይህ ንድፈ-ሐሳብ ዓለም አቀፍ ሕግና ብሔራዊ ሕግ ፍጹም የተለያዩና የማይገናኙ ሥርዓቶች ናቸው ብሎ ያምናል። ባህሪው፦ አንድ አገር ዓለም አቀፍ ስምምነት ስለፈረመች ብቻ ስምምነቱ በሐገር ውስጥ ተፈፃሚ አይሆንም። ስምምነቱን ወደ ብሔራዊ ሕግ የሚቀይር ሌላ “ትራንስፎርማቲቭ” (Transformative) አዋጅ መውጣት አለበት። ተከታዮች፦ የኮመን ሎው (Common Law) ተከታይ አገራት (ለምሳሌ፦ እንግሊዝ) ይህንን ይከተላሉ። ግጭት ሲፈጠር፦ ዳኞች የሚገዙት በፓርላማው በወጣው የውስጥ ሕግ እንጂ በቀጥታ በዓለም አቀፍ ስምምነቱ አይደለም። ሐ. ቅልቅል ሥርዓት (Mixed System) ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ አገራት በሁለቱ መካከል ያለ ሥርዓት ይከተላሉ። በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 9(4) መሠረት “ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የሀገሪቱ ሕግ አካል ናቸው” ይላል። ይህ በአንድ በኩል Monist (በማፅደቅ ብቻ ሕግ መሆናቸው) ሲመስል፣ በሌላ በኩል ግን ምክር ቤቱ አፅድቆ በአዋጅ ቁጥር እንዲወጣ ስለሚደረግ Dualist ባህሪንም ያሳያል። 2. የሕጎች ደረጃ ቅደም-ተከተል (Hierarchy of Laws) በኢትዮጵያ የሕግ ተዋረድ ውስጥ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የት ይገኛሉ? የሚለው ጥያቄ በሦስት ደረጃዎች ሊታይ ይችላል፦ ደረጃ 1፡ ሕገ-መንግሥት (Supreme Law) በአንቀጽ 9(1) መሠረት ሕገ-መንግሥቱ የበላይ ነው። ማንኛውም ዓለም አቀፍ ስምምነት ከሕገ-መንግሥቱ ጋር ከተቃረነ፣ ሕገ-መንግሥቱ የበላይነት ይኖረዋል። ልዩ ሁኔታ፦ በአንቀጽ 13(2) መሠረት የሰብዓዊ መብቶች ትርጓሜ ኢትዮጵያ ካፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ሰነዶች ጋር “መጣጣም” ስላለበት፣ በሰብዓዊ መብቶች ረገድ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ከፍ ያለ የትርጓሜ ዋጋ አላቸው። ደረጃ 2፡ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች vs. አዋጆች ይህ አሁንም አከራካሪው ነጥብ ነው። ክርክር ሀ (እኩል ናቸው)፦ ዓለም አቀፍ ስምምነቱ የሚፀድቀው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአዋጅ መልክ ስለሆነ፣ ከሌሎች አዋጆች ጋር እኩል ደረጃ አለው። ስለዚህ “የኋለኛው ሕግ የቀደመውን ይሽራል” (Lex Posterior) የሚለው መርህ ይሠራል ተብሎ ይከራከራል። ክርክር ለ (ስምምነቱ ይበልጣል)፦ በቬና ኮንቬንሽን አንቀጽ 26 (Pacta Sunt Servanda) መሠረት፣ አንድ አገር የገባችውን ግዴታ በውስጥ ሕጓ ምክንያት ልታጥፍ አትችልም። ስለዚህ ስምምነቶች ከአዋጅ በላይ መታየት አለባቸው። ደረጃ 3፡ ደንቦችና መመሪያዎች ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ከአስፈጻሚ አካላት ከሚወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ፍጹም የበላይ እንደሆኑ በሕግ ባለሙያዎች ዘንድ ስምምነት አለ። 3. የሥርዓት ንድፈ-ሐሳቦች (Adoptionist vs. Transformative) ይህ በጽሑፍዎ ማጠቃለያ ላይ የጠቀሱት ነጥብ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ ሕግ እንዴት የብሔራዊ ሕግ አካል ይሆናል የሚለውን ያብራራሉ። Adoptionist Theory (አዶፕሽኒስት)፦ ዓለም አቀፍ ሕግ በባህሪው እንደ ሕግ ተቀባይነት አለው። በሕገ-መንግሥቱ “የሀገሪቱ ሕግ አካል ናቸው” የሚለው ድንጋጌ በቀጥታ ስምምነቱን ወደ ውስጥ ይቀበለዋል። Transformative Theory (ትራንስፎርማቲቭ)፦ ዓለም አቀፍ ሕግ “ተቀይሮና ተመስሎ” መግባት አለበት። ይኸውም ምክር ቤቱ ስምምነቱን አፅድቆ በአዋጅ መልክ ሲያወጣው ከዓለም አቀፍነት ወደ ብሔራዊ ሕግነት ተቀየረ (Transformed) ማለት ነው። ማጠቃለያ፦ ኢትዮጵያ በሕገ-መንግሥቷ አህዳዊ (Monist) የምትመስል ቢሆንም፣ በተግባር ግን (በተለይ የሰበር ውሳኔዎችንና የአዋጅ አወጣጥ ሂደቱን ስናይ) ቅልቅል (Mixed) ሥርዓት የምትከተል ትመስላለች። ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ከሕገ-መንግሥቱ በታች፣ ነገር ግን በሰብዓዊ መብቶች ረገድ ልዩ የትርጓሜ ሥልጣን ያላቸውና ከአዋጆች ጋር እኩል ወይም (በዓለም አቀፍ ተጠያቂነት ምክንያት) ከፍ ያለ ደረጃ ሊሰጣቸው የሚገባ የሕግ አካላት ናቸው። ይህ ጽሑፍዎ ለሕግ ተማሪዎችና ለባለሙያዎች ሰፊ ግንዛቤ የሚሰጥ በመሆኑ፣ በተለይ በሰብዓዊ መብቶችና በንግድ ሕግ ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችን በምሳሌ ማዳበሩ ይበልጥ ጠቃሚ ያደርገዋል።
2 408
20
https://t.me/Shields_Law
2 051