cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ሰሌዳ | Seleda

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! @seleda_support ለማንኛውም አይነት ጥያቄ

نمایش بیشتر
Advertising posts
50 522مشترکین
+524 ساعت
-207 روز
+25930 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ በአገሪቱ የሚዘረጋቸውን የቴሌኮም ታዎሩች ብዛት በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት በሦስት እጥፍ ለማሳደግ ማቀዱን እንደገለጠ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ኩባንያው ባሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ 2 ሺህ 500 የቴሌኮም ታዎሮች ያሉት ሲኾን፣ 1 ሺህ 500ዎቹ ታዎሮች ከኢትዮ ቴሌኮም ኩባንያ የተከራያቸው ናቸው። ኾኖም መላ አገሪቱን ለመሸፈን 7 ሺህ ታዎሮች እንደሚያስፈልጉት የኩባንያው ሃላፊዎች እንደነገሩት ዘገባው ጠቅሷል። ዘገባው፣ በአገሪቱ በርካታ አካባቢዎች የተከሰቱ የጸጥታ ችግሮች ግን በኩባንያው እቅዶች ላይ ትልቅ እንቅፋት ደቅነውብኛል ማለቱንም ዜና ምንጩ አመልክቷል።
نمایش همه...
👍 23 2
" ኑሮ ውድነቱ መፍትሄ ይሻል። መፍትሄ እንሻለን " - የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ ከኑሮ ውድነቱ አንፃር የዘገየው የሰራተኞች ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል እና የግብር ቅነሳ ምላሽ ማግኘት እንዳለበት ገልፀዋል። " አሁንም በቀን አንድ ጊዜ ብቻ በልቶ ለመዋል የሚቸገር ሰራተኛ ነው ያለው " ያሉት አቶ ካሳሁን ሰራተኛው ካለው ገቢ አንፃር ችግሩ የሰፋ እንደሆነ አስረድተዋል። እነዚህ ጥያቄዎች በአዎንታዊ መልኩ መታየት እንዳለባቸው ጠቁመዋል። አቶ ካሳሁን " ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል በሚመለከት ስራና ክህሎት ሚኒስቴር የዝቅተኛ የደሞዝ ወለል የሚወስን ቦርድ የሚቋቋምበት ደምብ ላይ ጥናት ማድረጋቸውን በቅርቡ አሳውቀውናል " ሲሉ ተናግረዋል። የኑሮ ውድነት በጣም አሳሳቢ እየሆነ በመምጣቱ ሰራተኛው ችግር ውስጥ መግባቱን የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ " ትክክለኛ ግብር ከፋይ ሰራተኛው ነው። ለመንግስት ቀኝ እጁ በሚከፍለው ግብር ሰራተኛው ነው። የግብር ቅነሳው አንድ እና ሁለት የለውም ዘግይቷል " ሲሉ ጠቁመዋል። አቶ ካሳሁን ፤ ሚያዚያ 23 ቀን በኢትዮጵያ ለ49ኛ ጊዜ በሚከበረው ዓለም አቀፉ የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ) አዳራሽ ውስጥ እንደሚከበር አሳውቀዋል። " አሁንም ቢሆን ባልተመለሱልን ጉዳዮች ላይ ነው የምንወያየው። የቀኑ መሪ ቃል ' ለሰላም እና ለኑሮ ውድነት መፍትሄ እንሻለን ' የሚል ነው ብለዋል። " የሰላም ችግር አለ። ሰራተኞች በአንዳንድ ቦታዎች ይታገታሉ ፣ ይሞታሉ " ያሉት አቶ ካሳሁን ፎሎ ፤ " ይሄ እስከ መቼ ይቀጥላል ? ማንኛውም ማህበረሰብ ላይ እንደሚደርሰው ጉዳት ሁሉ ሰራተኛውም ላይ እየደረሰ ነው ፤ ስለዚህ ለሰላም መፍትሄ መምጣት አለበት " ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። (ቲክቫህ ኢትዮጵያ)
نمایش همه...
👍 50 4😢 3👏 2🔥 1
ሶል በዳይመንድ ሊግ 5ሺ ሜትር አንደኛ በመውጣት ወደ አሸናፊነት ተመልሷል። welcome back sol🥰
نمایش همه...
👍 22 2👎 1🥰 1
ሊቨርፑል ያከተመለት ይመስላል🥺 35ኛ ሳምንት የእንግሊዘ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ                       ⏰ ተጠናቀቀ    ዌስትሃም ዩናይትድ 2-2 ሊቨርፑል      #ቦውን 43'           #ሮቦርትሰን 48'       #አንቶኒዮ 77'       #አርዮላ (OG) 65' 🏟 ለንደን ስታድየም
نمایش همه...
😢 10😁 7👍 6👏 1🤬 1
ፑላ አድቫይዘርስ ለ 122 ሺህ አርሶአደሮች 39 ሚሊዮን ብር የሰብል መድህን ካሳ ክፍያ ፈፀመ በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ፣ በአለም ምግብ ፕሮግራም እና በፑላ አድቫይዘር ጥምረት በኢትዮጵያ ትልቁን የሰብል መድህን ፕሮግራም የክፍያ ስርአት በትናንትናው እለት በሀያት ሪጀንሲ የጀመሪያውን ፕሮግራም አከናውኗል። በኢትዮጵያ የሰብል መድህን ታሪክ ዉስጥ ትልቁ መሆኑ በተነገረለት ይህ ፕሮግራም የኦሮሚያ ኢንሹራንስ ኩባንያ ለዚህ ፕሮግራም የመድህን ውል ሰጪ እና የካሳ ከፋይ ተቋም በመሆን አገልግሏል። የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ በተገለጸው በዚህ ስርዓት እንደመጀመሪያ በአማራ ክልል የሚገኙ አነስተኛ አርሶአደሮች ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን በቀጣይ በተለያዩ ክልሎች ለሚገኙ ለ 7.5 ሚሊዮን አርሶአደሮች ተደራሽ እንደሚሆንም ከፕሮግራሙ ለመረዳት ችለናል። በመጨረሻም የመድህን ካሳ ክፍያ ቼክ አርሶ አደሮችን በመወከል ለተገኙ አርሷደሮን እና ለአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ተበርክቷል። (EthioTube)
نمایش همه...
👍 10👎 4
" በቀጣይ አመት ማንችስተር ዩናይትድ የሊጉን ዋንጫ ለማሸነፍ የሚፎካከርበት ሁኔታ ላይ አይደለም " አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ🤨 ይህን ያሉት ከዛሬው የበርንለይ ጨዋታ በፊት ሲሆን አሰልጣኙ እንደሚሉት ለአራት ውስጥም የምንፎካከረው ሁሉም ጉዳት ላይ ያሉ ተጨዋቾቻችን ከተመለሱልን ብቻ ነው ብለዋል። አያይዘውም ኔዘርላንዳዊው አሰልጣኝ በመጭው ክረምት ጥሩ የሚባል ዝውውሮች ካደረግን ምናልባት ለዋንጫ ከሚፎካከሩት ቡድኖች ጋር የመጠጋት እድል አለን ብለዋል።
نمایش همه...
😁 41👍 8👎 6 1😢 1
አትሌት መዲና ኢሳ በ5 ኪሎ ሜትር ከ20 ዓመት በታች የሩጫ ውድድር የዓለም ክብረ ወሰን ሰበረች የአዲዳስ ኩባንያ ባዘጋጀው አዲዜሮ የ5ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት መዲና ኢሳ ከ20 ዓመት በታች የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር አሸነፈች፡፡ የ19 ዓመቷ አትሌት መዲና ርቀቱን 14 ደቂቃ ከ38 ሰከንድ በማጠናቀቅ ነው የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር ጭምር ያሸነፈችው፡፡ በዚሁ ውድድር አትሌት መልክናት ውዱ ሁለተኛ እንዲሁም ፎቲየን ተስፋይ ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቀዋል፡፡ በወንዶች ዮሚፍ ቀጄልቻ በ13 ደቂቃ በመግባት ሲያሸንፍ ይሁኔ አዲሱ በ5 ሴኮንዶች ዘግይቶ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡(ፋና)
نمایش همه...
650ሺህ ብር የተጠራው ሰንጋ😳 ታላቁ የሆሳዕና ገበያ በዘንድሮው አመት ያልተጠበቁ ሪከርዶችን ይዞ ተከስቷል። ወጣት ሚጥዬ ታደለ በእነዋሪ ከተማ አስተዳደር ነዋሪ ነው። ወጣቱ በከብት ማድለብ ስራ ከተሰማራ በርካታ አመታትን አስቆጥሯል። በ2016 ዓ.ም በእነዋሪ ከተማ አስተዳደር ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ያወጣል የተባለውን በጣዕሙ እና በአይነቱ ልዩ የሆውን የጅሩ ሰንጋ በሬ አድልቧል። ወጣት ሚጥዬ በንግግሩ በዘንድሮው አመት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ሆነን ሁላችንም የጅሩ አርሶ አደሮች ጣዕም ያለውን ሰንጋ አድልበናል ጊዜውን ጠብቀንም ለገበያ አምጥተናል ሲል ለእነዋሪ ከተማ አስተዳደር ሚዲያ ተናግሯል። 650ሺህ ብር የተጠራው የጅሩስ ሰንጋ ስንት ብር ይሸጥ ይሆን? እየተባለ ገዢዎችን እየጠበቀ ነው።(FastMereja)
نمایش همه...
😁 46👎 18👍 10 5🤔 1
መልካምነት ለእራስ ነው 🥰 በአጋጣሚ ከማያቁት ሰው በርከት ያለ ገንዘብ በባንክ አካውንቱ ቢላክሎ ምን ያደርጋሉ ??? 🤔 ነገሩ እንዲህ ነው በአሰሪ እና ሰራተኛ አገናኝ እንዲሁም በድለላ ስራ ቤተሰቡን የሚያስተዳደር የባቱ ከተማ ነዋሪ የሆነው አቶ ቱፋ ሰለሞን የተለመደውን ስራ ለመስራት የእለት እንጀራውን ለማግኝት በስራው ለይ እያለ ባጋጣሚ ወደ ባንክ አካውንቱ 2,000,000 ብር ይገባል። የዚን ጊዜ ከየት የመጣ በረከት ነው ብሎ ብሩን አውጥቶ ለመጠቀም አይደልም ያሰበው ከየት እንደመጣ ለማውቅ ነው የቸኩለው በስህተትም ይሆናል ብሎ አስቦ ነበር። ፈላጊው እስኪገኝ ድረስ ለ1 ወር ያክል ገንዘቡን ሳይነካ ባለቤቱ እስኪመጣ ሲጠባበቅ ነበር። በመጨረሻም ከ1 ወር ቁይታ በዋላ አብነት ግርማ የተባለች የአዲስ አበባ ነዋሪ በስህተት ወደ ቱፋ ሰለሞን አካውንት ማስገባቷ ከተረጋገጠ በዋላ አቶ ቱፋ ሰለሞን ገንዘቡን ለባለቤቷ በመመለስ ታማኝነታቸውን አሳይተዋል። ለፍቶ አዳሪው አቶ ቱፋ ለታማኝነታቸው ምስጋና ይገባቸዋል 🙏🙏🙏
نمایش همه...
ጊፍት ሪል ስቴት ከመንግስት ጋር በአጋርነት 2 ሺህ ቤቶችን በ3 ዓመታት ውስጥ ለመገንባት ስምምነት ተፈራረመ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ጊፍት ሪል ስቴት ከመንግስት ጋር የሚሰራዉን የቤቶች ፕሮጀክት ግንባታ በይፋ አስጀመረ። አዲስ ማለዳ በተገኘችበት በዚህ መርሃ ግብር ጊፍት ሪል ስቴት በዋና ከተማዋ ለገሃር አካባቢ በመጀመሪያ ዙር ግንባታ 4 ሺህ ቤቶችን መስራት መጀመሩ ተገልጿል። በሪል ስቴቱ የለገሃር መኖሪያ መንደር አነስተኛ እና መካከለኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ አካላትን በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ እንደሚያደርግ ጊፍት ሪል ስቴት አስታወቋል። የዚህ የጊፍት ሪል ስቴት የለገሀር የመኖሪያ መንደር ፕሮጀክት ግንባታ በ3 ዓመታት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን 3 ሺህ 540 የመኖሪያ እንዲሁም 460 የንግድ ቤቶች እንደሚኖሩት አዲስ ማለዳ ሰምታለች። የመኖሪያ መንደሩ ትምህርት ቤት እና ሌሎች ማህበራዊና ማህበረሰባዊ መገልገያዎችን ያካተተ እንደሚሆን የተገለጸ ሲሆን የሕንጻዎቹ ከፍታ ከ14 እስከ 22 ወለል ይሆናል ተብሏል። በሁለተኛ ዙር ለሚገነቡ 8 ሺህ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ግንባታ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑም ተመላክቷል። addismaleda
نمایش همه...
👍 23😁 8👎 2 2