ሰሌዳ | Seleda
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Seledanewsbot
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ሰሌዳ | Seleda
کانال ሰሌዳ | Seleda (@seledadotio) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 52 943 مشترک است و جایگاه 4 925 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 594 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 52 943 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 30 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -152 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -11 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 18.90% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.62% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 10 007 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 8 268 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 70 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን
@Seledanewsbot”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 01 ژوئیه | 0 |
| 2 | የሊቢያው ኦላ ኢነርጂ የቶታልኤነርጂስን የኢትዮጵያ ንብረቶች በሙሉ ጠቀለለ
የሊቢያው ኦላ ኢነርጂ ግሩፕ በኢትዮጵያ የሚገኙትን የፈረንሳዩ ቶታልኤነርጂስ ንብረቶች በሙሉ ለመጠቅለል የሚያስችለውን የግዢ ስምምነት በፓሪስ ተፈራረመ።
ይህ ስምምነት ኦላ ኢነርጂ በኢትዮጵያ የነዳጅ ማከፋፈል ገበያ ውስጥ ትልቁ የውጭ ኩባንያ ያደርገዋል።
ይህ ግዙፍ የአክሲዮን ግዢ በኢትዮጵያ የሚገኙ ወደ 120 የሚጠጉ የነዳጅ ማደያዎችን፣ የ13 ሺህ ሜትር ኩብ አቅም ያለውን የነዳጅ ማከማቻ ተርሚናል እና ተያያዥ የንግድ እንቅስቃሴዎችን ያጠቃልላል።
በስምምነቱ ላይ የሊቢያ ዘይትና ጋዝ ሚኒስትር ከሊፋ አብዱልሳዲቅ እና የቶታልኤነርጂስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፓትሪክ ፑያን ጨምሮ የሁለቱም ወገኖች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ግዢው ሊቢያ በአፍሪካ አህጉር ያላትን የኢኮኖሚ ተፅዕኖ እና የውጭ ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት የምታደርገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 3 843 |
| 3 | ፀደቀ‼️
የታክስ ቅሬታ አጣሪው ተቀየረ፤ የታክስ ቅጣትም በግማሽ ተቀነሰ‼️
*ሰኔ 23/2018 ዓ/ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ላይ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን አድርጎ በትናንትናው ዕለት አጽድቋል። ማሻሻያው በተለይም ለታክስ ከፋይ ተቋማት የፍትህ አድማሱን የሚያሰፋና የቅጣት ጫናን የሚቀንስ ነው።
በአዋጁ የተካተቱት ዋና ዋና ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፦
ከዚህ ቀደም በታክስ ባለሥልጣኑ በራሱ ይሰየም የነበረው የታክስ "አስማሚ" (Mediator)፣ ከአሁን በኋላ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚሰየም ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን ይተካል፡፡ ይህም የታክስ ክርክሮች ፍትሃዊ እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲታዩ ያስችላል።
ታክስ ከፋዮች በታክስ አወሳሰን ወቅት ያልቀረቡ ነገር ግን በኋላ ላይ የዕዳ መጠን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ማስረጃዎችን ሲያቀርቡ ይጠብቃቸው የነበረው 20 በመቶ ቅጣት፣ በግማሽ ተቀንሶ ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
የታክስ ህግን በመተላለፍ ወንጀል የሚፈጽሙ ድርጅቶች ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ድንጋጌ ተካቷል። በዚህም መሰረት ወንጀሉ በተፈጸመበት ወቅት በስልጣን ላይ የነበሩ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጆች ወይም የፋይናንስ ኃላፊዎች ለወንጀሉ በግል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ህጉ በግልጽ አስቀምጧል።
ይህ ማሻሻያ የታክስ አስተዳደርን ይበልጥ ግልጽ፣ ፍትሃዊ እና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል። | 5 234 |
| 4 | "የሕወሃት አመራር ወደ አዲስ አበባም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ የመጓዝ ፍላጎት የለውም!" -ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር
የፌዴራል መንግሥቱ በአሁኑ ወቅት ወታደሮቹን ከምዕራብ ትግራይ ወደ ምስራቅ ትግራይ እያሠማራ መሆኑን የሕወሃት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር በዛሬው ማምሻ ጋዜጣዊ መግለጫቸው አስታውቀዋል። በትግራይ ቴሌቪዥን በተላለፈው በዚህ መግለጫ ላይ ኃላፊዋ አሜሪካ በ"አክራሪ" የሕወሃት አመራሮችና አባላት ላይ የጣለችውን የቪዛ እገዳ አስመልክተው የተናገሩ ሲሆን፥ እገዳው በግለሰቦች ላይ ሳይሆን በሕወሃት "መርሆች" ላይ ያነጣጠረ ነው ብለዋል። ይሁን እንጂ ሕወሃት በመሠረታዊ መርሆዎቹ ላይ ፈጽሞ እንደማይደራደር አጽንዖት ሰጥተዋል።
ፈትለወርቅ አክለውም፥ የሕወሃት አመራር ወደ አዲስ አበባም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ የመጓዝ ፍላጎት እንደሌለው ለአሜሪካ ማሳወቃቸውን ገልጸዋል። የትግራይ ሕዝብና የድርጅቱ ጥያቄ ራስን በራስ የማስተዳደርና የራስን ዕጣ ፈንታ በራስ የመወሰን መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊዋ፥ የአሜሪካ ጥቅም ሊረጋገጥ የሚችለው ሕወሃትን በማስፈራራት ሳይሆን አብሮ በመስራት ብቻ እንደሆነ አስገንዝበዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 5 274 |
| 5 | #ሀሰተኛ - ይህ ከላይ በምስሉ የሚታየው " ፂም ያለው እና ሽማግሌ የሚመስል ሕጻን በጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ ተወለደ " እየተባለ የሚነገረው ሀሰት ነው።
በርካቶች መረጃውን ሳያረጋግጡ በችኮላና አንዳንዶች ደግሞ ሆን ብለው የሰዎችን እይታ ለማግኘት ሲሉ ብቻ " በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጋሞ ዞን፣ ቦረዳ ወረዳ ጭላሼ ቀበሌ ልዩ ስሙ ወቆ በተባለ ሥፍራ፣ ሙሉ ፂም ያለውና መልኩ ሽማግሌ የሚመስል ሕፃን ተወለደ " ሲሉ ሀሰተኛ መረጃ አሰራጭተዋል። | 7 751 |
| 6 | መምህሩና አዲስ ተመራቂ ባለቤታቸው ከምረቃ መልስ በደረሰ አደጋ ሕይወታቸው አለፈ::
* መምህር አብሪሃም ግዛው እና
* ባለቤቱ መምህርት ራሄል አክሊ
በካፋ ዞን ሺሾ እንዴ ወረዳ በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ የአንድ መምህርና ከኮሌጅ የተመረቀች ባለቤታቸው ህይወት ማለፉ ተሰማ።
አደጋው የደረሰው ከቦንጋ ወደ ሺሺንዳ በመጓዝ ላይ በነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ላይ መሆኑ ተገልጿል።
የሺሾ እንዴ ወረዳ እና የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቁት፣ የሰሌዳ ቁጥሩ 00582 የሆነው የዶልፊን የሕዝብ ማመላለሻ መኪና ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፋዱ 5 ሰዓት ከ30 ገደማ ሲሆን ዋና ቦላ በተባለ ቀበሌ ላይ መንገድ ስቶ ወደ ገደል ገብቷል።
ተሽከርካሪው በግምት 50 ሜትር ወደሚሆን ገደል በመግባቱ ምክንያት በውስጡ ተሳፍረው ከነበሩት መካከል ሁለት ሰዎች ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።
ህይወታቸው ያለፈው እነዚህ ተሳፋሪዎች መምህሩ እና የኮሌጅ ምረቃዋን አጠናቃ በደስታ ወደ ቤት እየተመለሰች የነበረችው ባለቤታቸው መሆናቸው ተረጋግጧል።
በዚሁ አደጋ ምክንያት ሌሎች የተለያዩ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች በአቅራቢያው በሚገኘው በዲንቢራ ጤና ጣቢያ ገብተው አስፈላጊው የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ከመንግስት ኮሙኒኬሽን የወጣው ይፋዊ መረጃ ያመላክታል።gursha
ነብስ ይማር 💔 | 7 840 |
| 7 | በ #ሱዳን በተፈጸሙ አስከፊ ወንጀሎች ውስጥ እጃቸው አለበት የተባሉ ከፍተኛ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣የ #ኢትዮጵያ እና የቀጠናው ባለሥልጣናት ላይ በዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ምርመራ እንዲደረግ ተጠየቀ‼️
ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች እና የሕግ ድርጅቶች ጥምረት፤ በሱዳን ዳርፉር ክልል በተቀሰቀሰው ግጭት ለተፈጸሙ አስከፊ ወንጀሎች ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ረገድ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ፣ የኢትዮጵያን ጨምሮ የቻድ፣የሶማሊያ፣ የሊቢያ እና የኬኒያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ላይ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ምርመራ እንዲያደርግ ጠየቀ።
ሚድል ኢስት አይ ባወጣው ዘገባ መሠረት፤ ይህ ጥሪ ሰኞ ዕለት የቀረበው፤ ራውል ዋለንበርግ የሰብአዊ መብቶች ማዕከል (RWCHR) ከተለያዩ የሕግ፣ የምርመራ እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጥምረት ጋር በመሆን የቀረበ ነው። አቤቱታው የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ዓቃቢያነ ሕግ የውጭ አገር ባለሥልጣናትና አሸማጋዮች በሱዳን ተፋላሚ ወገኖች የተፈጸሙ ወንጀሎችን ሆን ብለው በማገዝ ወይም በማበረታታት ረገድ የተሳተፉ መሆኑን እንዲመረምሩ ይጠይቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 7 511 |
| 8 | 📣LinkedIn ካለዎት ገቢ አለዎት!
🤝 ለ 2 ዓመታት አብሮ በዘለቀ አጋርነታችን፤ ለቢዝነስ አላማ የLinkedIn አካውንቶችን በመከራዬት ላይ ነን!
📱 የLinkedIn አካውንትዎን በማከራዬት በሳምንት ጠቀም ያለ ገንዘብ መስራት እንደሚችሉ ያውቃሉ?
⛔ መስፈርቶች ፦
📱 100+ Connections
🗓 ከተከፈተ 3 ወር እና ከዛ በላይ
💬 በውስጥ መስመር ➡️
@linkedin_ethiop ያግኙን
📱 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ➡️https://t.me/+0xQ8zF1gYpgyMmI0
😀ስልክ ፦ +251934848429
⚠️ ያስተውሉ ፦ አሁን ካለው ከገበያው ዋጋ በላይ ክፍያዎችን እያቀረብን እንገኛለን።
🤝 Stable • Trusted • Long-Term Collaboration. | 1 961 |
| 9 | “የነዳጅ ዋጋን በአስቸኳይ ቀንሱ!”፤ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በነዳጅ አከፋፋዮችና ማደያዎች ላይ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ አስተላለፉ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀገሪቱ የሚገኙ የነዳጅ ችርቻሮ ነጋዴዎችና ማደያዎች የሚሸጡትን የነዳጅ ዋጋ በአስቸኳይ እና ያለምንም መዘግየት እንዲቀንሱ ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት ይፋዊ መልእክት፤ በአሁኑ ወቅት አንድ ባሬል ድፍድፍ ዘይት በዓለም ገበያ በ68 ዶላር አካባቢ እየተሸጠ ባለበትና የገበያው አቅጣጫም ወደ ታች እያቆለቆለ በሚገኝበት ሁኔታ ላይ፣ ቸርቻሪዎች የሚያስከፍሉት ዋጋ እጅግ በጣም ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ነጋዴዎቹ ለዚህ መግለጫ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ትክክለኛውን ነገር ማድረግ እንዳለባቸው ያሳሰቡት ፕሬዝዳንት ትራምፕ፤ “ለታላቁ የአሜሪካ ሕዝብ ስትሉ ዋጋችሁን በአስቸኳይ ቀንሱ!” በማለት ትዕዛዝ ሰጥተዋል። ከትእዛዙ ጋር በተያያዘም ፍጹም ሕገ-ወጥ የሆነውንና ሕዝብን በዋጋ ጭማሪ መበዝበዝ የሚባለውን አሠራር እንደማይታገሡትና ቸርቻሪዎቹ ይህንን ትእዛዝ ካልፈጸሙ ወደፊት ትልቅና ከባድ ችግር እንደሚጠብቃቸው አስጠንቅቀዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሀገሪቱ የአንድ ጋሎን ነዳጅ ዋጋ 2 ዶላር ከ50 ሳንቲም አካባቢን ኢላማ በማድረግ እንዲቀነስ የጠየቁ ሲሆን፣ ይህም የዜጎችን የኑሮ ውድነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያቃልል አስገንዝበዋል።
በተያያዘም ፕሬዝዳንቱ በከፍተኛ ታክስ ምክንያት የነዳጅ ዋጋ ሰማይ በነካባት የካሊፎርኒያ ግዛት ላይ ያላቸውን ከባድ ቅሬታ ሰንዝረዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 7 519 |
| 10 | ⁉️ የምስራቁ ጦርነት የኑሮአችንን ዋጋ እንዴት እያናጋው ነው? 💥
🚨የኃያላን መንግስታት ፍጥጫ እና የድንበር ጦርነቶች ከሩቅ የሚታዩ የዜና አርዕስቶች ብቻ አይደሉም፤ የኢትዮጵያን ገበያ እና የኪሳችንን አቅም በቀጥታ የሚፈትኑ ማዕበሎች እንጂ።
የሀገር ውስጥ ወቅታዊ ፈተናዎችን እና አጠቃላይ የአህ👇ችንን እና የዓለምን ዜናዎች አቀናጅቶ የሚያቀርብላችሁን ስፑትኒክን አሁኑኑ ይከተሉ 👇
🔗 https://t.me/+EUyJimhjCeY2ZTVi
📣 @sputnik_ethiopia | 7 042 |
| 11 | ዱባይ ለኢትዮጵያውያን ማስጠንቀቂያ‼️
የዱባይ ፖሊስ በኢትዮጵያውያን ላይ የመጨረሻ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጠ‼️
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዲጂታል መድረኮች በሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች ላይ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። ይህ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው በትውልድ ኢትዮጵያውያን መካከል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተደረጉ ያሉ አንዳንድ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ነው።
የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በጋራ ባዘጋጁት መድረክ እንደተገለጸው፣ በአረብ ኤምሬቶች የሳይበር ወንጀል ህግ መሰረት የሚከተሉት ድርጊቶች ከፍተኛ ቅጣት እንደሚያስከትሉ ተገልጿል፦
📌 የጥላቻ ንግግር: በማህበረሰቡ መካከል መከፋፈልን፣ ጥላቻን እና ንቀትን የሚያንጸባርቁ የብሄር ፖለቲካ ቅስቀሳዎችን ሶሻል ሚዲያ ላይ መለጠፍ።
📌 ስድብ እና ስም ማጥፋት: ግለሰቦችን ወይም ተቋማትን በቪዲዮ፣ በጽሁፍ ወይም በኮሜንት መዝለፍ እና ስም ማጥፋት ህግ የተከለከለ ነው።
📌 ያለ ፈቃድ መረጃ ማውጣት: የግለሰቦችን ግላዊነት የሚነኩ ምስሎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም መረጃዎችን ያለ ፈቃድ ማሰራጨት በህግ የሚያስቀጣ ነው።
📌 የገንዘብ ማሰባሰብ: ያለ መንግስት ፈቃድ በማህበራዊ ሚዲያ በኩል በስምምነት ገንዘብ ማሰባሰብ በኢምሬትስ ህግ የተከለከለ ነው።
@Seledadotio
@Seledadotio | 8 137 |
| 12 | እራሴን ችዬ እዋጋለሁ-እስራኤል‼️
የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ከኢራን ጋር ዳግም ወደ ጦርነት በቀናት ውስጥ ልንገባ እንችላለን አሉ።
አይ ዲ ኤፍ ዝግጅት እንዲያደርግም ትዕዛዝ ተሰጥቶታል ብለዋል ሚኒስትሩ እስራኤል ካትዝ።
ኢራን ምንም ዓይነት ሚሳኤል ወደ እስራኤል ካስወነጨፈች አፀፋው የማያወላዳ ይሆናል ያሉት ካትዝ በቀናት ውስጥ “ምናልባትም ነገ”ወደ ጦርነቱ ልንመለስ እንችላለን በሚል አሳስበዋል።
ከአሜሪካ ጋር እየተደራደረች ወደ እስራኤል ጥቃት የማድረስ ፍላጎት ኢራን አላት ብለዋል እስራኤል ካትዝ።
"ኢራን ጥቃት ካደረሰች፤ሶስተኛው የኢራን ጦርነት ይሆናል፤ነገሩ እጅግ ግልፅም ነው”በሚል አፅንዖት ሰጥተዋል።
እስራኤል ሚሳዔል ሲወነጨፍባት አደገኛ ምላሽ ሳትሰጥ አታልፈውም የሚል መረጃም ሚኒስትሩ አጋርተዋል።
በኢራን ላይ ያለማንም ደጋፊ ፣ራሳችንን ችለን ጥቃት ለማድረስ እንዲሁም ሰማያዊ እና ነጭ ዘመቻ(ብሉ ኤንድ ዋይት) ኢራን ውስጥ ለማድረግ ጦሩ እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ ሰጥቻለሁ ብለዋል።
ብሉ ኤንድ ዋይት ዘመቻ በእስራኤል ጦርና ፖለቲከኞች ራስን ችሎ ማጥቃት የሚል ትርጓሜ ይሰጠዋል መባሉን ፎክስ ኒውስን ጠቅሰው ኤን ቢሲ ዘግቧል ። | 8 267 |
| 13 | በጋምቤላ ክልል ህፃናትን መጠጥ ቤት እንዲገቡ ማድረግ 5 ሺህ ብር ያስቀጣል ተባለ
ለአቅመ አዳም ያልደረሱና ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ወደ መጠጥ ቤቶች እንዳይገቡ ለመጠጥ ቤት ባለቤቶች ጥብቅ መመሪያ መስጠቱን በጋምቤላ ክልል አኙዋ ብሔረሰብ ዞን የአቦቦ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት አስታውቋል። የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ አዊሊ ኡጁሉ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት መመሪያውን ተላልፈው በሚገኙ የመጠጥ ቤት ባለቤቶች ላይ የ5 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተላልፋል ።
በተጨማሪም ወላጆች ህፃናትን ጫትና የአልኮል መጠጦችን ለመግዛት ወደ ተለያዩ የንግድ ቦታዎች እንዳይልኩ ጥብቅ መመሪያ መተላለፉን ኃላፊዋ ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል። ህፃናት ለጤናቸው ሲባል የትኛውንም አይነት የአልኮል መጠጥ ሙሉ ለሙሉ ማስወገድ እንዳለባቸው ተነግሯል ።
አልኮል የሚጠጣ ሰው ጤና አደጋ ላይ የሚወድቀው ከእያንዳንዱ መጠጥ የመጀመሪያ ጠብታ ጀምሮ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ ።የአልኮል መጠጥ የጉበት ካንሰርን ጨምሮ ጉበት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ፣የልብና የደም ሥር ችግሮች ፣የደም ግፊት ፣የልብ ህመም እንዲሁም የካንሰር ተጋላጭነትን እንደሚጨምር ጥናቶች ይጠቁማሉ።
| 8 010 |
| 14 | ኢትዮጵያ በጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የባህር ትራንስፖርት መስመሮች ጀመረች
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በበጀት ዓመቱ ወደ ጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የጉዞ መስመሮችን በመክፈት የንግድ ትስስሩን እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል።
የተቋሙ የኮርፖሬት ማርኬቲንግ መምሪያ ኃላፊና የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ተወካይ አቶ ደምሰው በንቲ፣ በኢንዶኔዥያና በጃፓን መስመሮች ላይ ከባድ ማሽነሪዎችን፣ ተሽከርካሪዎችንና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎችን የማጓጓዝ ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ለጋዜጣ ፕላስ ገልጸዋል።
ኃላፊው አክለውም፣ ወደፊትም የደንበኞችንና የሀገሪቱን ጥቅም ማዕከል ያደረጉ አዳዲስ መዳረሻዎችን የማስፋፋት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
እነዚህ አዳዲስ የባህር መስመር ጉዞዎች መጀመራቸው የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ያሻሽላል ያሉት አቶ ደምሰው፣ የወደብ ጭነቶች በአጭር ጊዜ ወደተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ በማስቻል ጊዜንና ወጪን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቆጥብ አስገንዝበዋል።
@Addis_News
@Addis_News | 8 209 |
| 15 | "የፌዴራል መንግሥት የትግራይን ሕዝብ ሊያድን ይገባል!"
የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከዚህ ቀደም ያደርገው ከነበረው የወርቅ ንግድ በአሁኑ ወቅት የትግራይ ወጣቶችን ወደ መሸጥና ወደ ማገት መሸጋገሩን የወለዶ ትግራይ ፖለቲካ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ ጉዕሽ ግደይ ገለጹ።
ቡድኑ ታሪካዊውን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በተግባር በማፍረስና ከሀገር ውጭ ካሉ ጠላቶች ጋር "ፅምዶ" በሚል ስያሜ በመተባበር ለሌላ ጦርነት እየተዘጋጀ እንደሚገኝና በትግራይ ክልል ሁሉንም ሰላማዊ የፖለቲካ መንገዶች ዘግቶ በጉልበት እያስተዳደረ መሆኑን አስረድተዋል። የትግራይ ወጣቶችን እያገተና ወላጆችን እያሰረ ትውልድን ለማጥፋት እየሠራ ነው ያሉት ቡድኑ፤ የትግራይን ሕዝብ ጥቅም ወደ ጎን በመተው ለታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጥቅም እየሠራ እንደሚገኝና ሕዝቡም በፈቃደኝነት ከእሱ ጋር እንደማይዋጋ በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን አጋልጠዋል።
አቶ ጉዕሽ የፌዴራል መንግሥት እስካሁን ላሳየው የሰላም ትዕግሥትና ጥረት ምስጋና አቅርበው፣ አሁን ላይ ግን የቡድኑ እንቅስቃሴ ወደ አደገኛ ደረጃ በመሸጋገሩ የትግራይን ሕዝብ ለማዳንና የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ሕገ-መንግሥታዊና ፖለቲካዊ እርምጃዎችን መውሰድ እንዳለበት በማሳሰብ፣ መላው የትግራይ ሕዝብ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጎን ቆሞ ይህንን ኋላቀር ቡድን እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 8 456 |
| 16 | ኢትዮጵያ ያለባትን የ1 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ለመክፈል ከአበዳሪዎቿ ጋር ስምምነት ላይ ደረሰች!
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የግል አበዳሪዎች ተበድራው የነበረውን 1 ቢሊዮን ዶላር (ዩሮቦንድ) በወቅቱ መክፈል አቅቷት የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ዕዳውን የምታቀልበት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኢትዮጵያ ከነበረባት 1 ቢሊዮን ዶላር ላይ የ12% ቅናሽ የተደረገላት ሲሆን በዚህ መሰረት የምትከፍለው ዕዳ ወደ 880 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ብሏል።
ይህንን 880 ሚሊዮን ዶላር እስከ 2029 ድረስ በ6.15% ወለድ በየደረጃው እንድትከፍል ጊዜ የተሰጣት ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ሳትከፍል ያሳለፈችውን 99.4 ሚሊዮን ዶላር የወለድ ዕዳ ትከፍላለች።
ስምምነቱ ወደፊት ኢትዮጵያ ብድር ባስፈለጋት ጊዜ እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ድረስ በድጋሚ የመበደር መብት ወይም ዕድልን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ዋናዎቹ አበዳሪ ሀገራት (ቻይና እና ፈረንሳይ) ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ገፅታ የሚያሻሽልና ተጨማሪ የውጭ ብድርና 1እርዳታ በቀላሉ እንድታገኝ በር የሚከፍት በመሆኑ .በገበያው ላይ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።
በየአብሥራ ተፈራ
@YeneTube @FikerAssefa | 8 929 |
| 17 | የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ (ሰኔ 23) ይጀምራል‼️
የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገራችን በ607 የፈተና ማዕከላት በስድስት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል::
ለፈተናው በድምሩ 563 ሺህ 501 ተፈታኞች የተመዘገቡ ሲሆን፣ 306 ሺህ 456 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 257 ሺህ 45 የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው:: | 8 925 |
| 18 | የጓደኛውን ሞባይል በመጠቀም ገንዘብ ወደ ራሱ አካውንት ያስተላለፈው ግለሰብ ክስ ተመሰረተበት።
አብርሃም ፈቃዱ የተባለ ተጠርጣሪ በእምነት ያዝልኝ ተብሎ በተሰጠው ስልክ ብር ወደ ራሱ አካውንት በማስተላለፍ የተጠረጠረው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 11:30 በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሾላ አካባቢ ነው።
የግል ተበዳይ ከጓደኛው ጋር ከነበሩበት ምግብ ቤት ካርድ ልግዛ ብሎ ስልኩን ሰጥቶ በወጣበት አጋጣሚ ተጠርጣሪው የግል ተበዳይን የሞባይል ባንኪንግ ሚስጥር ቁጥር በስራ አጋጣሚ ያውቀው ስለነበር 48ሺህ ብር ወደ ራሱ አካውንት ማስተላለፉን በየካ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የአድዋ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የግል ተበዳይ ጉዳዩን እንዳወቀ ለፖሊስ ያመለከተ ሲሆን ፖሊስም ምርመራውን በመጀመር ወደ ተጠርጣሪው የተላከውን ገንዘብ በማስወጣትና በኤግዚቢትነት በመያዝ መዝገቡ ተደራጅቶ ለአቃቤ ህግ መላኩን ፖሊስ መምሪያው ጠቁሟል።
የተጠናቀረውን የወንጀል መዝገብ የተመለከተው አቃቤ ህግም በተጠርጣሪ አብርሃም ፍቃዱ ላይ ክስ መመስረቱንም ማወቅ ተችሏል።
የባንክ የይለፍ ቁጥሮችን ጨምሮ የግል ሚስጥሮችን በአግባቡ መጠበቅ ከመሰል የወንጀል ድርጊት ራስን ማዳን ስለሚያስችል ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ምንጭ:-አአ ፖሊስ
@Seledadotio
@Seledadotio | 8 936 |
| 19 | ህወሃት ምላሽ ሰጠ‼️
‹‹በትግራይ ዙሪያ የድሮን ክትትሉ ቀጥሏል›› ሕወሓት‼️
ሕወሓት ወታደራዊ ግዳጅ እየፈጸመ መሆኑን ካደ፡፡ ቡድኑ የአውሮፓ ህብረት ያወጣውን ማሳሰቢያ ተከትሎ ባወጣው መግለጫ፣ መሬት ላይ ያሉ እውታዎችን በመካድ፤ የፌዴራል መንግስቱ ላይ ተጨማሪ ክሶችን አቅርቧል፡፡
ህወሓት በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ በትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያወጣውን መግለጫና የሰነዘረውን ወቀሳ ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ ጠንከር ያለ ይፋዊ ምላሽ ሰጥቷል። የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ ህወሓት "ትይዩ ክልላዊ ምክር ቤት አቋቁሟል" እና "የግዳጅ ውትድርና ምልመላ እያካሄደ ነው" በማለት የሰነዘረውን ወቀሳ ያጣጣለው ድርጅቱ፣ ሕብረቱ መሬት ላይ ያለውን ነባራዊ እውነታ ወደ ጎን በመተው በተሳሳተ መረጃ ላይ የተመሠረተ መግለጫ አውጥቷል ሲል ኮንኗል።
ህወሓት በትግራይ ውስጥ "ትይዩ ክልላዊ ምክር ቤት" አቋቁሟል የሚለው ወቀሳ ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ ነው ብሏል። በትግራይ ሕዝብ ስም የተቋቋመ ሌላ አዲስ ምክር ቤት እንደሌለ የገለጸው ድርጅቱ፣ ቀደም ሲል በሕግ የተመረጠው ብቸኛው የትግራይ ክልላዊ ምክር ቤት ከከተሞች እስከ ገጠር ማኅበረሰብ ሰፊ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ወደ መደበኛ ሥራው መመለሱንና ይህም በታችኛው መዋቅር በኩል ጭምር ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን አስታውቋል።
ድርጅቱ አስገዳጅ ምልመላ እያካሄደ ነው መባሉ ግልጽ ያልሆነና በማስረጃ ያልተደገፈ ክስ ነው ሲል አጣጥሎታል። ይሁን እንጂ በትግራይ ዙሪያ ከፍተኛ የወታደራዊ ኃይል ስምሪት፣ ቀጣይነት ያለው የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃቶችና የአየር ላይ ክትትሎች ባሉበት ነባራዊ ሁኔታ፣ የክልሉ ባለሥልጣናት ሕዝቡን ከዳግም ጭፍጨፋና ከህልውና አደጋ የመጠበቅና ራሱን የመከላከል ሞራላዊና ሕጋዊ ኃላፊነት እንዳለባቸው አስገንዝቧል።
@Seledadotio | 8 558 |
| 20 | አሜሪካ ተማሪዎቿን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲያነቡ ልታስደርግ ነው።
የቴክሳስ ግዛት ተማሪዎችን የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን እንዲያነቡ ሊያስገድድ መሆኑ ተዘግቧል።
በአሜሪካ የቴክሳስ ግዛት የትምህርት ምክር ቤት በግዛቲቱ ያሉ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን እንዲያነቡ የሚያስገድድ አዲስ የንባብ ዕቅድ በ9 የድጋፍ በ5 የተቃውሞ ድምፅ አጽድቋል።
ከሦስት ዓመት በኋላ ተግባራዊ የሚሆነው ይህ እቅድ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን ብቻ ሳይሆን የቻርልስ ዲከንስ “Great Expectations” እና የዊሊያም ሼክስፒር “The Tragedy of Julius Caesar” የመሳሰሉ ታዋቂ የእንግሊዝ ሥነ-ጽሑፍ ሥራዎችንም ያካትታል ነው የተባለው።
ውሳኔው በአሜሪካ ውስጥ በሃይማኖትና በመንግሥት መለያየት ላይ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።
ደጋፊዎቹ የአይሁድ-ክርስትና እሴቶችና ባህሎች በአሜሪካ ታሪክና ምሥረታ ውስጥ ትልቅ ሚና እንዳላቸው በመግለጽ ተማሪዎች ሊያውቋቸው ይገባል ይላሉ።
የቴክሳስ የትምህርት ቦርድ አባል ብራንደን ሆል “መጽሐፍ ቅዱስን ከ60 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትምህርት ቤቶች እየመለስን ነው” ብለዋል።
በሌላ በኩል ተቃዋሚዎች እቅዱ የሃይማኖት ነፃነትን የሚጎዳ፣ ክርስትናን ከሌሎች ሃይማኖቶች በላይ የሚያቆም እና የአሜሪካን ባህላዊ ብዝሃነት የሚያቀል መሆኑን ይናገራሉ።
የ“Freedom Network” ዋና ዳይሬክተር ፌሊሺያ ማርቲን እቅዱ ሌሎች ሃይማኖቶችን፣ የቀደምት አሜሪካውያንን እና የተለያዩ ማህበረሰቦችን አስተዋፅኦ ችላ እንደሚል ተችታለች።
ተማሪዎች ከአዲስ ኪዳን ውስጥ ስለ ኢየሱስ የሚናገሩ ክፍሎችን እና “የጠፋው ልጅ” የሚባለውን ምሳሌ እንዲማሩ በእቅዱ ተካትቷል።
እንዲሁም የቴክሳስ መምህራን ማህበር እቅዱ በጣም ሰፊ መሆኑን እና መምህራን ለተማሪዎቻቸው ተገቢ የሆኑ መጽሐፍትን የመምረጥ ነፃነታቸውን ሊያሳንስ እንደሚችል ገልጿል።
ይህ ውሳኔ በቴክሳስ ውስጥ ክርስቲያናዊ እሴቶችን በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ ለማጠናከር ከተወሰዱ ተከታታይ እርምጃዎች አንዱ ሲሆን፤ ባለፈው ዓመትም በትምህርት ክፍሎች ውስጥ የአሥርቱ ትዕዛዛት እንዲሰቀሉ የሚያስገድድ ሕግ ተላልፎ ነበር፤ ይህም በፌዴራል ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ድጋፍ አግኝቷል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ውሳኔውን በመደገፍ በአሜሪካ ውስጥ የሃይማኖት እሴቶችን ለማጠናከር የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ገልጸው፣ “ሃይማኖት ከቀድሞው የበለጠ ጠንካራ ሆኖ ወደ አገራችን ተመልሷል” ብለዋል።
በአጠቃላይ ውሳኔው በአሜሪካ የትምህርት፣ የሃይማኖት ነፃነት እና የመንግሥት-ሃይማኖት ግንኙነት ላይ ሰፊ ውይይት እንዲቀጥል አድርጓል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 7 691 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
