ሰሌዳ | Seleda
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Seledanewsbot
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ሰሌዳ | Seleda
کانال ሰሌዳ | Seleda (@seledadotio) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 52 954 مشترک است و جایگاه 4 913 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 591 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 52 954 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 29 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -159 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -8 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 18.84% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.53% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 9 978 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 8 224 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 67 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን
@Seledanewsbot”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 30 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 30 ژوئن | 0 | |||
| 29 ژوئن | +9 | |||
| 28 ژوئن | +1 | |||
| 27 ژوئن | 0 | |||
| 26 ژوئن | +1 | |||
| 25 ژوئن | +11 | |||
| 24 ژوئن | +2 | |||
| 23 ژوئن | +5 | |||
| 22 ژوئن | +2 | |||
| 21 ژوئن | +11 | |||
| 20 ژوئن | +2 | |||
| 19 ژوئن | 0 | |||
| 18 ژوئن | +10 | |||
| 17 ژوئن | +1 | |||
| 16 ژوئن | 0 | |||
| 15 ژوئن | +4 | |||
| 14 ژوئن | +23 | |||
| 13 ژوئن | +1 | |||
| 12 ژوئن | +16 | |||
| 11 ژوئن | 0 | |||
| 10 ژوئن | +4 | |||
| 09 ژوئن | +58 | |||
| 08 ژوئن | +2 | |||
| 07 ژوئن | +5 | |||
| 06 ژوئن | +6 | |||
| 05 ژوئن | +3 | |||
| 04 ژوئن | 0 | |||
| 03 ژوئن | +13 | |||
| 02 ژوئن | +14 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
| 2 | 📣LinkedIn ካለዎት ገቢ አለዎት!
🤝 ለ 2 ዓመታት አብሮ በዘለቀ አጋርነታችን፤ ለቢዝነስ አላማ የLinkedIn አካውንቶችን በመከራዬት ላይ ነን!
📱 የLinkedIn አካውንትዎን በማከራዬት በሳምንት ጠቀም ያለ ገንዘብ መስራት እንደሚችሉ ያውቃሉ?
⛔ መስፈርቶች ፦
📱 100+ Connections
🗓 ከተከፈተ 3 ወር እና ከዛ በላይ
💬 በውስጥ መስመር ➡️
@linkedin_ethiop ያግኙን
📱 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ➡️https://t.me/+0xQ8zF1gYpgyMmI0
😀ስልክ ፦ +251934848429
⚠️ ያስተውሉ ፦ አሁን ካለው ከገበያው ዋጋ በላይ ክፍያዎችን እያቀረብን እንገኛለን።
🤝 Stable • Trusted • Long-Term Collaboration. | 586 |
| 3 | “የነዳጅ ዋጋን በአስቸኳይ ቀንሱ!”፤ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በነዳጅ አከፋፋዮችና ማደያዎች ላይ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ አስተላለፉ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀገሪቱ የሚገኙ የነዳጅ ችርቻሮ ነጋዴዎችና ማደያዎች የሚሸጡትን የነዳጅ ዋጋ በአስቸኳይ እና ያለምንም መዘግየት እንዲቀንሱ ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት ይፋዊ መልእክት፤ በአሁኑ ወቅት አንድ ባሬል ድፍድፍ ዘይት በዓለም ገበያ በ68 ዶላር አካባቢ እየተሸጠ ባለበትና የገበያው አቅጣጫም ወደ ታች እያቆለቆለ በሚገኝበት ሁኔታ ላይ፣ ቸርቻሪዎች የሚያስከፍሉት ዋጋ እጅግ በጣም ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ነጋዴዎቹ ለዚህ መግለጫ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ትክክለኛውን ነገር ማድረግ እንዳለባቸው ያሳሰቡት ፕሬዝዳንት ትራምፕ፤ “ለታላቁ የአሜሪካ ሕዝብ ስትሉ ዋጋችሁን በአስቸኳይ ቀንሱ!” በማለት ትዕዛዝ ሰጥተዋል። ከትእዛዙ ጋር በተያያዘም ፍጹም ሕገ-ወጥ የሆነውንና ሕዝብን በዋጋ ጭማሪ መበዝበዝ የሚባለውን አሠራር እንደማይታገሡትና ቸርቻሪዎቹ ይህንን ትእዛዝ ካልፈጸሙ ወደፊት ትልቅና ከባድ ችግር እንደሚጠብቃቸው አስጠንቅቀዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሀገሪቱ የአንድ ጋሎን ነዳጅ ዋጋ 2 ዶላር ከ50 ሳንቲም አካባቢን ኢላማ በማድረግ እንዲቀነስ የጠየቁ ሲሆን፣ ይህም የዜጎችን የኑሮ ውድነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያቃልል አስገንዝበዋል።
በተያያዘም ፕሬዝዳንቱ በከፍተኛ ታክስ ምክንያት የነዳጅ ዋጋ ሰማይ በነካባት የካሊፎርኒያ ግዛት ላይ ያላቸውን ከባድ ቅሬታ ሰንዝረዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 3 210 |
| 4 | ⁉️ የምስራቁ ጦርነት የኑሮአችንን ዋጋ እንዴት እያናጋው ነው? 💥
🚨የኃያላን መንግስታት ፍጥጫ እና የድንበር ጦርነቶች ከሩቅ የሚታዩ የዜና አርዕስቶች ብቻ አይደሉም፤ የኢትዮጵያን ገበያ እና የኪሳችንን አቅም በቀጥታ የሚፈትኑ ማዕበሎች እንጂ።
የሀገር ውስጥ ወቅታዊ ፈተናዎችን እና አጠቃላይ የአህ👇ችንን እና የዓለምን ዜናዎች አቀናጅቶ የሚያቀርብላችሁን ስፑትኒክን አሁኑኑ ይከተሉ 👇
🔗 https://t.me/+EUyJimhjCeY2ZTVi
📣 @sputnik_ethiopia | 3 144 |
| 5 | ዱባይ ለኢትዮጵያውያን ማስጠንቀቂያ‼️
የዱባይ ፖሊስ በኢትዮጵያውያን ላይ የመጨረሻ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጠ‼️
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዲጂታል መድረኮች በሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች ላይ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። ይህ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው በትውልድ ኢትዮጵያውያን መካከል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተደረጉ ያሉ አንዳንድ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ነው።
የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በጋራ ባዘጋጁት መድረክ እንደተገለጸው፣ በአረብ ኤምሬቶች የሳይበር ወንጀል ህግ መሰረት የሚከተሉት ድርጊቶች ከፍተኛ ቅጣት እንደሚያስከትሉ ተገልጿል፦
📌 የጥላቻ ንግግር: በማህበረሰቡ መካከል መከፋፈልን፣ ጥላቻን እና ንቀትን የሚያንጸባርቁ የብሄር ፖለቲካ ቅስቀሳዎችን ሶሻል ሚዲያ ላይ መለጠፍ።
📌 ስድብ እና ስም ማጥፋት: ግለሰቦችን ወይም ተቋማትን በቪዲዮ፣ በጽሁፍ ወይም በኮሜንት መዝለፍ እና ስም ማጥፋት ህግ የተከለከለ ነው።
📌 ያለ ፈቃድ መረጃ ማውጣት: የግለሰቦችን ግላዊነት የሚነኩ ምስሎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም መረጃዎችን ያለ ፈቃድ ማሰራጨት በህግ የሚያስቀጣ ነው።
📌 የገንዘብ ማሰባሰብ: ያለ መንግስት ፈቃድ በማህበራዊ ሚዲያ በኩል በስምምነት ገንዘብ ማሰባሰብ በኢምሬትስ ህግ የተከለከለ ነው።
@Seledadotio
@Seledadotio | 5 924 |
| 6 | እራሴን ችዬ እዋጋለሁ-እስራኤል‼️
የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ከኢራን ጋር ዳግም ወደ ጦርነት በቀናት ውስጥ ልንገባ እንችላለን አሉ።
አይ ዲ ኤፍ ዝግጅት እንዲያደርግም ትዕዛዝ ተሰጥቶታል ብለዋል ሚኒስትሩ እስራኤል ካትዝ።
ኢራን ምንም ዓይነት ሚሳኤል ወደ እስራኤል ካስወነጨፈች አፀፋው የማያወላዳ ይሆናል ያሉት ካትዝ በቀናት ውስጥ “ምናልባትም ነገ”ወደ ጦርነቱ ልንመለስ እንችላለን በሚል አሳስበዋል።
ከአሜሪካ ጋር እየተደራደረች ወደ እስራኤል ጥቃት የማድረስ ፍላጎት ኢራን አላት ብለዋል እስራኤል ካትዝ።
"ኢራን ጥቃት ካደረሰች፤ሶስተኛው የኢራን ጦርነት ይሆናል፤ነገሩ እጅግ ግልፅም ነው”በሚል አፅንዖት ሰጥተዋል።
እስራኤል ሚሳዔል ሲወነጨፍባት አደገኛ ምላሽ ሳትሰጥ አታልፈውም የሚል መረጃም ሚኒስትሩ አጋርተዋል።
በኢራን ላይ ያለማንም ደጋፊ ፣ራሳችንን ችለን ጥቃት ለማድረስ እንዲሁም ሰማያዊ እና ነጭ ዘመቻ(ብሉ ኤንድ ዋይት) ኢራን ውስጥ ለማድረግ ጦሩ እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ ሰጥቻለሁ ብለዋል።
ብሉ ኤንድ ዋይት ዘመቻ በእስራኤል ጦርና ፖለቲከኞች ራስን ችሎ ማጥቃት የሚል ትርጓሜ ይሰጠዋል መባሉን ፎክስ ኒውስን ጠቅሰው ኤን ቢሲ ዘግቧል ። | 6 041 |
| 7 | በጋምቤላ ክልል ህፃናትን መጠጥ ቤት እንዲገቡ ማድረግ 5 ሺህ ብር ያስቀጣል ተባለ
ለአቅመ አዳም ያልደረሱና ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ወደ መጠጥ ቤቶች እንዳይገቡ ለመጠጥ ቤት ባለቤቶች ጥብቅ መመሪያ መስጠቱን በጋምቤላ ክልል አኙዋ ብሔረሰብ ዞን የአቦቦ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት አስታውቋል። የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ አዊሊ ኡጁሉ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት መመሪያውን ተላልፈው በሚገኙ የመጠጥ ቤት ባለቤቶች ላይ የ5 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተላልፋል ።
በተጨማሪም ወላጆች ህፃናትን ጫትና የአልኮል መጠጦችን ለመግዛት ወደ ተለያዩ የንግድ ቦታዎች እንዳይልኩ ጥብቅ መመሪያ መተላለፉን ኃላፊዋ ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል። ህፃናት ለጤናቸው ሲባል የትኛውንም አይነት የአልኮል መጠጥ ሙሉ ለሙሉ ማስወገድ እንዳለባቸው ተነግሯል ።
አልኮል የሚጠጣ ሰው ጤና አደጋ ላይ የሚወድቀው ከእያንዳንዱ መጠጥ የመጀመሪያ ጠብታ ጀምሮ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ ።የአልኮል መጠጥ የጉበት ካንሰርን ጨምሮ ጉበት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ፣የልብና የደም ሥር ችግሮች ፣የደም ግፊት ፣የልብ ህመም እንዲሁም የካንሰር ተጋላጭነትን እንደሚጨምር ጥናቶች ይጠቁማሉ።
| 6 298 |
| 8 | ኢትዮጵያ በጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የባህር ትራንስፖርት መስመሮች ጀመረች
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በበጀት ዓመቱ ወደ ጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የጉዞ መስመሮችን በመክፈት የንግድ ትስስሩን እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል።
የተቋሙ የኮርፖሬት ማርኬቲንግ መምሪያ ኃላፊና የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ተወካይ አቶ ደምሰው በንቲ፣ በኢንዶኔዥያና በጃፓን መስመሮች ላይ ከባድ ማሽነሪዎችን፣ ተሽከርካሪዎችንና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎችን የማጓጓዝ ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ለጋዜጣ ፕላስ ገልጸዋል።
ኃላፊው አክለውም፣ ወደፊትም የደንበኞችንና የሀገሪቱን ጥቅም ማዕከል ያደረጉ አዳዲስ መዳረሻዎችን የማስፋፋት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
እነዚህ አዳዲስ የባህር መስመር ጉዞዎች መጀመራቸው የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ያሻሽላል ያሉት አቶ ደምሰው፣ የወደብ ጭነቶች በአጭር ጊዜ ወደተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ በማስቻል ጊዜንና ወጪን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቆጥብ አስገንዝበዋል።
@Addis_News
@Addis_News | 6 748 |
| 9 | "የፌዴራል መንግሥት የትግራይን ሕዝብ ሊያድን ይገባል!"
የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከዚህ ቀደም ያደርገው ከነበረው የወርቅ ንግድ በአሁኑ ወቅት የትግራይ ወጣቶችን ወደ መሸጥና ወደ ማገት መሸጋገሩን የወለዶ ትግራይ ፖለቲካ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ ጉዕሽ ግደይ ገለጹ።
ቡድኑ ታሪካዊውን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በተግባር በማፍረስና ከሀገር ውጭ ካሉ ጠላቶች ጋር "ፅምዶ" በሚል ስያሜ በመተባበር ለሌላ ጦርነት እየተዘጋጀ እንደሚገኝና በትግራይ ክልል ሁሉንም ሰላማዊ የፖለቲካ መንገዶች ዘግቶ በጉልበት እያስተዳደረ መሆኑን አስረድተዋል። የትግራይ ወጣቶችን እያገተና ወላጆችን እያሰረ ትውልድን ለማጥፋት እየሠራ ነው ያሉት ቡድኑ፤ የትግራይን ሕዝብ ጥቅም ወደ ጎን በመተው ለታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጥቅም እየሠራ እንደሚገኝና ሕዝቡም በፈቃደኝነት ከእሱ ጋር እንደማይዋጋ በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን አጋልጠዋል።
አቶ ጉዕሽ የፌዴራል መንግሥት እስካሁን ላሳየው የሰላም ትዕግሥትና ጥረት ምስጋና አቅርበው፣ አሁን ላይ ግን የቡድኑ እንቅስቃሴ ወደ አደገኛ ደረጃ በመሸጋገሩ የትግራይን ሕዝብ ለማዳንና የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ሕገ-መንግሥታዊና ፖለቲካዊ እርምጃዎችን መውሰድ እንዳለበት በማሳሰብ፣ መላው የትግራይ ሕዝብ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጎን ቆሞ ይህንን ኋላቀር ቡድን እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 7 378 |
| 10 | ኢትዮጵያ ያለባትን የ1 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ለመክፈል ከአበዳሪዎቿ ጋር ስምምነት ላይ ደረሰች!
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የግል አበዳሪዎች ተበድራው የነበረውን 1 ቢሊዮን ዶላር (ዩሮቦንድ) በወቅቱ መክፈል አቅቷት የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ዕዳውን የምታቀልበት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኢትዮጵያ ከነበረባት 1 ቢሊዮን ዶላር ላይ የ12% ቅናሽ የተደረገላት ሲሆን በዚህ መሰረት የምትከፍለው ዕዳ ወደ 880 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ብሏል።
ይህንን 880 ሚሊዮን ዶላር እስከ 2029 ድረስ በ6.15% ወለድ በየደረጃው እንድትከፍል ጊዜ የተሰጣት ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ሳትከፍል ያሳለፈችውን 99.4 ሚሊዮን ዶላር የወለድ ዕዳ ትከፍላለች።
ስምምነቱ ወደፊት ኢትዮጵያ ብድር ባስፈለጋት ጊዜ እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ድረስ በድጋሚ የመበደር መብት ወይም ዕድልን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ዋናዎቹ አበዳሪ ሀገራት (ቻይና እና ፈረንሳይ) ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ገፅታ የሚያሻሽልና ተጨማሪ የውጭ ብድርና 1እርዳታ በቀላሉ እንድታገኝ በር የሚከፍት በመሆኑ .በገበያው ላይ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።
በየአብሥራ ተፈራ
@YeneTube @FikerAssefa | 8 037 |
| 11 | የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ (ሰኔ 23) ይጀምራል‼️
የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገራችን በ607 የፈተና ማዕከላት በስድስት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል::
ለፈተናው በድምሩ 563 ሺህ 501 ተፈታኞች የተመዘገቡ ሲሆን፣ 306 ሺህ 456 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 257 ሺህ 45 የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው:: | 8 237 |
| 12 | የጓደኛውን ሞባይል በመጠቀም ገንዘብ ወደ ራሱ አካውንት ያስተላለፈው ግለሰብ ክስ ተመሰረተበት።
አብርሃም ፈቃዱ የተባለ ተጠርጣሪ በእምነት ያዝልኝ ተብሎ በተሰጠው ስልክ ብር ወደ ራሱ አካውንት በማስተላለፍ የተጠረጠረው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 11:30 በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሾላ አካባቢ ነው።
የግል ተበዳይ ከጓደኛው ጋር ከነበሩበት ምግብ ቤት ካርድ ልግዛ ብሎ ስልኩን ሰጥቶ በወጣበት አጋጣሚ ተጠርጣሪው የግል ተበዳይን የሞባይል ባንኪንግ ሚስጥር ቁጥር በስራ አጋጣሚ ያውቀው ስለነበር 48ሺህ ብር ወደ ራሱ አካውንት ማስተላለፉን በየካ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የአድዋ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የግል ተበዳይ ጉዳዩን እንዳወቀ ለፖሊስ ያመለከተ ሲሆን ፖሊስም ምርመራውን በመጀመር ወደ ተጠርጣሪው የተላከውን ገንዘብ በማስወጣትና በኤግዚቢትነት በመያዝ መዝገቡ ተደራጅቶ ለአቃቤ ህግ መላኩን ፖሊስ መምሪያው ጠቁሟል።
የተጠናቀረውን የወንጀል መዝገብ የተመለከተው አቃቤ ህግም በተጠርጣሪ አብርሃም ፍቃዱ ላይ ክስ መመስረቱንም ማወቅ ተችሏል።
የባንክ የይለፍ ቁጥሮችን ጨምሮ የግል ሚስጥሮችን በአግባቡ መጠበቅ ከመሰል የወንጀል ድርጊት ራስን ማዳን ስለሚያስችል ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ምንጭ:-አአ ፖሊስ
@Seledadotio
@Seledadotio | 8 262 |
| 13 | ህወሃት ምላሽ ሰጠ‼️
‹‹በትግራይ ዙሪያ የድሮን ክትትሉ ቀጥሏል›› ሕወሓት‼️
ሕወሓት ወታደራዊ ግዳጅ እየፈጸመ መሆኑን ካደ፡፡ ቡድኑ የአውሮፓ ህብረት ያወጣውን ማሳሰቢያ ተከትሎ ባወጣው መግለጫ፣ መሬት ላይ ያሉ እውታዎችን በመካድ፤ የፌዴራል መንግስቱ ላይ ተጨማሪ ክሶችን አቅርቧል፡፡
ህወሓት በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ በትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያወጣውን መግለጫና የሰነዘረውን ወቀሳ ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ ጠንከር ያለ ይፋዊ ምላሽ ሰጥቷል። የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ ህወሓት "ትይዩ ክልላዊ ምክር ቤት አቋቁሟል" እና "የግዳጅ ውትድርና ምልመላ እያካሄደ ነው" በማለት የሰነዘረውን ወቀሳ ያጣጣለው ድርጅቱ፣ ሕብረቱ መሬት ላይ ያለውን ነባራዊ እውነታ ወደ ጎን በመተው በተሳሳተ መረጃ ላይ የተመሠረተ መግለጫ አውጥቷል ሲል ኮንኗል።
ህወሓት በትግራይ ውስጥ "ትይዩ ክልላዊ ምክር ቤት" አቋቁሟል የሚለው ወቀሳ ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ ነው ብሏል። በትግራይ ሕዝብ ስም የተቋቋመ ሌላ አዲስ ምክር ቤት እንደሌለ የገለጸው ድርጅቱ፣ ቀደም ሲል በሕግ የተመረጠው ብቸኛው የትግራይ ክልላዊ ምክር ቤት ከከተሞች እስከ ገጠር ማኅበረሰብ ሰፊ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ወደ መደበኛ ሥራው መመለሱንና ይህም በታችኛው መዋቅር በኩል ጭምር ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን አስታውቋል።
ድርጅቱ አስገዳጅ ምልመላ እያካሄደ ነው መባሉ ግልጽ ያልሆነና በማስረጃ ያልተደገፈ ክስ ነው ሲል አጣጥሎታል። ይሁን እንጂ በትግራይ ዙሪያ ከፍተኛ የወታደራዊ ኃይል ስምሪት፣ ቀጣይነት ያለው የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃቶችና የአየር ላይ ክትትሎች ባሉበት ነባራዊ ሁኔታ፣ የክልሉ ባለሥልጣናት ሕዝቡን ከዳግም ጭፍጨፋና ከህልውና አደጋ የመጠበቅና ራሱን የመከላከል ሞራላዊና ሕጋዊ ኃላፊነት እንዳለባቸው አስገንዝቧል።
@Seledadotio | 7 808 |
| 14 | አሜሪካ ተማሪዎቿን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲያነቡ ልታስደርግ ነው።
የቴክሳስ ግዛት ተማሪዎችን የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን እንዲያነቡ ሊያስገድድ መሆኑ ተዘግቧል።
በአሜሪካ የቴክሳስ ግዛት የትምህርት ምክር ቤት በግዛቲቱ ያሉ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን እንዲያነቡ የሚያስገድድ አዲስ የንባብ ዕቅድ በ9 የድጋፍ በ5 የተቃውሞ ድምፅ አጽድቋል።
ከሦስት ዓመት በኋላ ተግባራዊ የሚሆነው ይህ እቅድ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን ብቻ ሳይሆን የቻርልስ ዲከንስ “Great Expectations” እና የዊሊያም ሼክስፒር “The Tragedy of Julius Caesar” የመሳሰሉ ታዋቂ የእንግሊዝ ሥነ-ጽሑፍ ሥራዎችንም ያካትታል ነው የተባለው።
ውሳኔው በአሜሪካ ውስጥ በሃይማኖትና በመንግሥት መለያየት ላይ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።
ደጋፊዎቹ የአይሁድ-ክርስትና እሴቶችና ባህሎች በአሜሪካ ታሪክና ምሥረታ ውስጥ ትልቅ ሚና እንዳላቸው በመግለጽ ተማሪዎች ሊያውቋቸው ይገባል ይላሉ።
የቴክሳስ የትምህርት ቦርድ አባል ብራንደን ሆል “መጽሐፍ ቅዱስን ከ60 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትምህርት ቤቶች እየመለስን ነው” ብለዋል።
በሌላ በኩል ተቃዋሚዎች እቅዱ የሃይማኖት ነፃነትን የሚጎዳ፣ ክርስትናን ከሌሎች ሃይማኖቶች በላይ የሚያቆም እና የአሜሪካን ባህላዊ ብዝሃነት የሚያቀል መሆኑን ይናገራሉ።
የ“Freedom Network” ዋና ዳይሬክተር ፌሊሺያ ማርቲን እቅዱ ሌሎች ሃይማኖቶችን፣ የቀደምት አሜሪካውያንን እና የተለያዩ ማህበረሰቦችን አስተዋፅኦ ችላ እንደሚል ተችታለች።
ተማሪዎች ከአዲስ ኪዳን ውስጥ ስለ ኢየሱስ የሚናገሩ ክፍሎችን እና “የጠፋው ልጅ” የሚባለውን ምሳሌ እንዲማሩ በእቅዱ ተካትቷል።
እንዲሁም የቴክሳስ መምህራን ማህበር እቅዱ በጣም ሰፊ መሆኑን እና መምህራን ለተማሪዎቻቸው ተገቢ የሆኑ መጽሐፍትን የመምረጥ ነፃነታቸውን ሊያሳንስ እንደሚችል ገልጿል።
ይህ ውሳኔ በቴክሳስ ውስጥ ክርስቲያናዊ እሴቶችን በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ ለማጠናከር ከተወሰዱ ተከታታይ እርምጃዎች አንዱ ሲሆን፤ ባለፈው ዓመትም በትምህርት ክፍሎች ውስጥ የአሥርቱ ትዕዛዛት እንዲሰቀሉ የሚያስገድድ ሕግ ተላልፎ ነበር፤ ይህም በፌዴራል ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ድጋፍ አግኝቷል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ውሳኔውን በመደገፍ በአሜሪካ ውስጥ የሃይማኖት እሴቶችን ለማጠናከር የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ገልጸው፣ “ሃይማኖት ከቀድሞው የበለጠ ጠንካራ ሆኖ ወደ አገራችን ተመልሷል” ብለዋል።
በአጠቃላይ ውሳኔው በአሜሪካ የትምህርት፣ የሃይማኖት ነፃነት እና የመንግሥት-ሃይማኖት ግንኙነት ላይ ሰፊ ውይይት እንዲቀጥል አድርጓል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 7 237 |
| 15 | 📣LinkedIn ካለዎት ገቢ አለዎት!
🤝 ለ 2 ዓመታት አብሮ በዘለቀ አጋርነታችን፤ ለቢዝነስ አላማ የLinkedIn አካውንቶችን በመከራዬት ላይ ነን!
📱 የLinkedIn አካውንትዎን በማከራዬት በሳምንት ጠቀም ያለ ገንዘብ መስራት እንደሚችሉ ያውቃሉ?
⛔ መስፈርቶች ፦
📱 100+ Connections
🗓 ከተከፈተ 3 ወር እና ከዛ በላይ
💬 በውስጥ መስመር ➡️
@linkedin_ethiop ያግኙን
📱 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ➡️https://t.me/+0xQ8zF1gYpgyMmI0
😀ስልክ ፦ +251934848429
⚠️ ያስተውሉ ፦ አሁን ካለው ከገበያው ዋጋ በላይ ክፍያዎችን እያቀረብን እንገኛለን።
🤝 Stable • Trusted • Long-Term Collaboration. | 7 913 |
| 16 | ተማሪዎች ውጤታቸው መመልከት ይችላሉ።
በ2018 የትምህርት ዘመን በ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና 95.85% ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤትን ይፋ ተደርጓል።
ተማሪዎች ውጤታቸውን ይህንን ማስፈንጠሪያ https://aa.ministry.et/#/result በመጫን መመልከት ይችላሉ። | 7 553 |
| 17 | በአዲስ አበባ ከተማ የሲጋራ ቁራጭ መንገድ ላይ መጣል 2 ሺህ ብር ያስቀጣል ተባለ
የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን የሲጋራ ቁራጭ በመንገድ፣ በአደባባይ ወይም በማንኛውም የህዝብ መገልገያ ቦታ ላይ የሚጥል ግለሰብ በ2 ሺህ ብር እንደሚቀጣ ገልጿል።ይህ እርምጃ የከተማዋን ንፅህና፣ የህዝብን ጤና ለመጠበቅ እና የትምባሆ ተጠቃሚነትን ለመቀነስ የሚደረገው የቁጥጥር አካል መሆኑ ተገልጿል።
የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ሙሉእመቤት ታደሰ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ቅጣቱ የሚተገበረው በከተማ አስተዳደሩ ደንብ ቁጥር 167/2016 መሠረት ነው።ደንቡ የትምባሆ ምርቶችን አጠቃቀም ለመቆጣጠርና ከጭስ ነፃ የሆነ የከተማ አካባቢን ለመፍጠር የወጣ መሆኑን ጠቁመዋል።
ባለሥልጣኑ በአዲስ አበባ ከተማ 79 በመቶ የሚሆኑት የህዝብ መገልገያ ተቋማት ከጭስ ነፃ መሆናቸውን ገልጿል።በከተማዋ የአጫሾች መጠን ከ5.3 በመቶ ወደ 4.6 በመቶ መቀነሱን በመግለጽ እየተወሰዱ ያሉ የቁጥጥርና የግንዛቤ ማስጨበጫ እርምጃዎች ውጤት እያሳዩ መሆናቸውን አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 7 931 |
| 18 | የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50 በመቶ ሆኖ ተወሰነ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50 በመቶ እንዲሆን ተወሰነ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በ2018 የትምህርት ዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ ከፍተኛ ዉጤት መመዝገቡን ጠቅሰው የተመዘገበው ውጤት አበራታች መሆኑን ተናግረዋል።
ዶክተር ዘላለም አያይዘውም በ2018 ዓ.ም የሒሳብና እንግሊዘኛ ትምህርትን ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረገው ስትራቴጂ በተማሪዎች ውጤት መረጋገጡን ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ዘርፉ ላይ ባደረገው ትኩረት ውጤቱ መመዝገቡን ተናግረው፤ፈተናውን በአጭር ጊዜ በማረም ውጤቱ ይፋ እንዲሆን ቀን ከሌት ሲሰሩ ለቆዩ የፈተና ክፍል ባለሙያዎችና ሂደቱን ሲደግፉ ለነበሩ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ በበኩላቸው፤በከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም 85 ሺህ7መቶ37 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡ | 7 411 |
| 19 | የአውሮፓ ሕብረት ተደጋጋሚ መግለጫ ስለ ትግራይና ስለ ህወሓት
የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ ልዑክ በሰሜን ኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል እየታየ ባለው ወቅታዊ ውጥረት ላይ ያለውን ከፍተኛ ስጋት ገልጿል።
ሕብረቱ ባወጣው መግለጫ መሠረት የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በቅርቡ የወሰዳቸውን እርምጃዎች ማለትም ትይዩ የሆነ የክልል ምክር ቤት ማቋቋሙንና በክልሉ ውስጥ በአንድ ወገን የሚደረገውን የውትድርና ምልመላ በጥብቅ ኮንኗል።
እነዚህ ተግባራት እ.ኤ.አ በ2022 በፕሪቶሪያ የተፈረመውን ዘላቂ ግጭት ማቆም ስምምነት ደንቦችንና ግዴታዎችን በግልጽ የሚጥሱ መሆናቸውን ልዑኩ አስገንዝቧል።
ስምምነቱ ወደ ነበረበት እንዲመለስና በተግባር ላይ እንዲውል ሁሉም ወገኖች አስቸኳይ ውይይት እንዲጀምሩ ጠይቋል።
የአፍሪካ ሕብረት ከፍተኛ ተወካይ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ በክልሉ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚያደርጉትን የሽምግልና ጥረት ሕብረቱ ሙሉ በሙሉ እንደሚደግፍም አስታውቋል።
@Addis_News
@Addis_News | 7 579 |
| 20 | የ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይሆናል
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ሰኔ 22 ቀን ከሰዓት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ነጥቡ ላይ ውይይት ካደረጉ በኃላ ይፋ ይደረጋል ሲል ቢሮው ማስታወቁን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።
የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ ያስችላል። የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 11 እና 12 /2018 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለ56,737 ተማሪዎች መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
@Addis_News
@Addis_News | 8 012 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
