ሰሌዳ | Seleda
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Seledanewsbot
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ሰሌዳ | Seleda
کانال ሰሌዳ | Seleda (@seledadotio) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 52 960 مشترک است و جایگاه 4 913 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 591 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 52 960 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 29 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -159 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -8 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 18.84% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.53% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 9 978 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 8 224 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 67 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን
@Seledanewsbot”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 30 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 29 ژوئن | +9 | |||
| 28 ژوئن | +1 | |||
| 27 ژوئن | 0 | |||
| 26 ژوئن | +1 | |||
| 25 ژوئن | +11 | |||
| 24 ژوئن | +2 | |||
| 23 ژوئن | +5 | |||
| 22 ژوئن | +2 | |||
| 21 ژوئن | +11 | |||
| 20 ژوئن | +2 | |||
| 19 ژوئن | 0 | |||
| 18 ژوئن | +10 | |||
| 17 ژوئن | +1 | |||
| 16 ژوئن | 0 | |||
| 15 ژوئن | +4 | |||
| 14 ژوئن | +23 | |||
| 13 ژوئن | +1 | |||
| 12 ژوئن | +16 | |||
| 11 ژوئن | 0 | |||
| 10 ژوئن | +4 | |||
| 09 ژوئن | +58 | |||
| 08 ژوئن | +2 | |||
| 07 ژوئن | +5 | |||
| 06 ژوئن | +6 | |||
| 05 ژوئن | +3 | |||
| 04 ژوئن | 0 | |||
| 03 ژوئن | +13 | |||
| 02 ژوئن | +14 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
| 2 | የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ (ሰኔ 23) ይጀምራል‼️
የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገራችን በ607 የፈተና ማዕከላት በስድስት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል::
ለፈተናው በድምሩ 563 ሺህ 501 ተፈታኞች የተመዘገቡ ሲሆን፣ 306 ሺህ 456 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 257 ሺህ 45 የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው:: | 5 235 |
| 3 | የጓደኛውን ሞባይል በመጠቀም ገንዘብ ወደ ራሱ አካውንት ያስተላለፈው ግለሰብ ክስ ተመሰረተበት።
አብርሃም ፈቃዱ የተባለ ተጠርጣሪ በእምነት ያዝልኝ ተብሎ በተሰጠው ስልክ ብር ወደ ራሱ አካውንት በማስተላለፍ የተጠረጠረው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 11:30 በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሾላ አካባቢ ነው።
የግል ተበዳይ ከጓደኛው ጋር ከነበሩበት ምግብ ቤት ካርድ ልግዛ ብሎ ስልኩን ሰጥቶ በወጣበት አጋጣሚ ተጠርጣሪው የግል ተበዳይን የሞባይል ባንኪንግ ሚስጥር ቁጥር በስራ አጋጣሚ ያውቀው ስለነበር 48ሺህ ብር ወደ ራሱ አካውንት ማስተላለፉን በየካ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የአድዋ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የግል ተበዳይ ጉዳዩን እንዳወቀ ለፖሊስ ያመለከተ ሲሆን ፖሊስም ምርመራውን በመጀመር ወደ ተጠርጣሪው የተላከውን ገንዘብ በማስወጣትና በኤግዚቢትነት በመያዝ መዝገቡ ተደራጅቶ ለአቃቤ ህግ መላኩን ፖሊስ መምሪያው ጠቁሟል።
የተጠናቀረውን የወንጀል መዝገብ የተመለከተው አቃቤ ህግም በተጠርጣሪ አብርሃም ፍቃዱ ላይ ክስ መመስረቱንም ማወቅ ተችሏል።
የባንክ የይለፍ ቁጥሮችን ጨምሮ የግል ሚስጥሮችን በአግባቡ መጠበቅ ከመሰል የወንጀል ድርጊት ራስን ማዳን ስለሚያስችል ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ምንጭ:-አአ ፖሊስ
@Seledadotio
@Seledadotio | 6 173 |
| 4 | ህወሃት ምላሽ ሰጠ‼️
‹‹በትግራይ ዙሪያ የድሮን ክትትሉ ቀጥሏል›› ሕወሓት‼️
ሕወሓት ወታደራዊ ግዳጅ እየፈጸመ መሆኑን ካደ፡፡ ቡድኑ የአውሮፓ ህብረት ያወጣውን ማሳሰቢያ ተከትሎ ባወጣው መግለጫ፣ መሬት ላይ ያሉ እውታዎችን በመካድ፤ የፌዴራል መንግስቱ ላይ ተጨማሪ ክሶችን አቅርቧል፡፡
ህወሓት በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ በትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያወጣውን መግለጫና የሰነዘረውን ወቀሳ ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ ጠንከር ያለ ይፋዊ ምላሽ ሰጥቷል። የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ ህወሓት "ትይዩ ክልላዊ ምክር ቤት አቋቁሟል" እና "የግዳጅ ውትድርና ምልመላ እያካሄደ ነው" በማለት የሰነዘረውን ወቀሳ ያጣጣለው ድርጅቱ፣ ሕብረቱ መሬት ላይ ያለውን ነባራዊ እውነታ ወደ ጎን በመተው በተሳሳተ መረጃ ላይ የተመሠረተ መግለጫ አውጥቷል ሲል ኮንኗል።
ህወሓት በትግራይ ውስጥ "ትይዩ ክልላዊ ምክር ቤት" አቋቁሟል የሚለው ወቀሳ ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ ነው ብሏል። በትግራይ ሕዝብ ስም የተቋቋመ ሌላ አዲስ ምክር ቤት እንደሌለ የገለጸው ድርጅቱ፣ ቀደም ሲል በሕግ የተመረጠው ብቸኛው የትግራይ ክልላዊ ምክር ቤት ከከተሞች እስከ ገጠር ማኅበረሰብ ሰፊ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ወደ መደበኛ ሥራው መመለሱንና ይህም በታችኛው መዋቅር በኩል ጭምር ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን አስታውቋል።
ድርጅቱ አስገዳጅ ምልመላ እያካሄደ ነው መባሉ ግልጽ ያልሆነና በማስረጃ ያልተደገፈ ክስ ነው ሲል አጣጥሎታል። ይሁን እንጂ በትግራይ ዙሪያ ከፍተኛ የወታደራዊ ኃይል ስምሪት፣ ቀጣይነት ያለው የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃቶችና የአየር ላይ ክትትሎች ባሉበት ነባራዊ ሁኔታ፣ የክልሉ ባለሥልጣናት ሕዝቡን ከዳግም ጭፍጨፋና ከህልውና አደጋ የመጠበቅና ራሱን የመከላከል ሞራላዊና ሕጋዊ ኃላፊነት እንዳለባቸው አስገንዝቧል።
@Seledadotio | 5 971 |
| 5 | አሜሪካ ተማሪዎቿን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲያነቡ ልታስደርግ ነው።
የቴክሳስ ግዛት ተማሪዎችን የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን እንዲያነቡ ሊያስገድድ መሆኑ ተዘግቧል።
በአሜሪካ የቴክሳስ ግዛት የትምህርት ምክር ቤት በግዛቲቱ ያሉ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን እንዲያነቡ የሚያስገድድ አዲስ የንባብ ዕቅድ በ9 የድጋፍ በ5 የተቃውሞ ድምፅ አጽድቋል።
ከሦስት ዓመት በኋላ ተግባራዊ የሚሆነው ይህ እቅድ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን ብቻ ሳይሆን የቻርልስ ዲከንስ “Great Expectations” እና የዊሊያም ሼክስፒር “The Tragedy of Julius Caesar” የመሳሰሉ ታዋቂ የእንግሊዝ ሥነ-ጽሑፍ ሥራዎችንም ያካትታል ነው የተባለው።
ውሳኔው በአሜሪካ ውስጥ በሃይማኖትና በመንግሥት መለያየት ላይ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።
ደጋፊዎቹ የአይሁድ-ክርስትና እሴቶችና ባህሎች በአሜሪካ ታሪክና ምሥረታ ውስጥ ትልቅ ሚና እንዳላቸው በመግለጽ ተማሪዎች ሊያውቋቸው ይገባል ይላሉ።
የቴክሳስ የትምህርት ቦርድ አባል ብራንደን ሆል “መጽሐፍ ቅዱስን ከ60 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትምህርት ቤቶች እየመለስን ነው” ብለዋል።
በሌላ በኩል ተቃዋሚዎች እቅዱ የሃይማኖት ነፃነትን የሚጎዳ፣ ክርስትናን ከሌሎች ሃይማኖቶች በላይ የሚያቆም እና የአሜሪካን ባህላዊ ብዝሃነት የሚያቀል መሆኑን ይናገራሉ።
የ“Freedom Network” ዋና ዳይሬክተር ፌሊሺያ ማርቲን እቅዱ ሌሎች ሃይማኖቶችን፣ የቀደምት አሜሪካውያንን እና የተለያዩ ማህበረሰቦችን አስተዋፅኦ ችላ እንደሚል ተችታለች።
ተማሪዎች ከአዲስ ኪዳን ውስጥ ስለ ኢየሱስ የሚናገሩ ክፍሎችን እና “የጠፋው ልጅ” የሚባለውን ምሳሌ እንዲማሩ በእቅዱ ተካትቷል።
እንዲሁም የቴክሳስ መምህራን ማህበር እቅዱ በጣም ሰፊ መሆኑን እና መምህራን ለተማሪዎቻቸው ተገቢ የሆኑ መጽሐፍትን የመምረጥ ነፃነታቸውን ሊያሳንስ እንደሚችል ገልጿል።
ይህ ውሳኔ በቴክሳስ ውስጥ ክርስቲያናዊ እሴቶችን በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ ለማጠናከር ከተወሰዱ ተከታታይ እርምጃዎች አንዱ ሲሆን፤ ባለፈው ዓመትም በትምህርት ክፍሎች ውስጥ የአሥርቱ ትዕዛዛት እንዲሰቀሉ የሚያስገድድ ሕግ ተላልፎ ነበር፤ ይህም በፌዴራል ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ድጋፍ አግኝቷል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ውሳኔውን በመደገፍ በአሜሪካ ውስጥ የሃይማኖት እሴቶችን ለማጠናከር የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ገልጸው፣ “ሃይማኖት ከቀድሞው የበለጠ ጠንካራ ሆኖ ወደ አገራችን ተመልሷል” ብለዋል።
በአጠቃላይ ውሳኔው በአሜሪካ የትምህርት፣ የሃይማኖት ነፃነት እና የመንግሥት-ሃይማኖት ግንኙነት ላይ ሰፊ ውይይት እንዲቀጥል አድርጓል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 5 568 |
| 6 | 📣LinkedIn ካለዎት ገቢ አለዎት!
🤝 ለ 2 ዓመታት አብሮ በዘለቀ አጋርነታችን፤ ለቢዝነስ አላማ የLinkedIn አካውንቶችን በመከራዬት ላይ ነን!
📱 የLinkedIn አካውንትዎን በማከራዬት በሳምንት ጠቀም ያለ ገንዘብ መስራት እንደሚችሉ ያውቃሉ?
⛔ መስፈርቶች ፦
📱 100+ Connections
🗓 ከተከፈተ 3 ወር እና ከዛ በላይ
💬 በውስጥ መስመር ➡️
@linkedin_ethiop ያግኙን
📱 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ➡️https://t.me/+0xQ8zF1gYpgyMmI0
😀ስልክ ፦ +251934848429
⚠️ ያስተውሉ ፦ አሁን ካለው ከገበያው ዋጋ በላይ ክፍያዎችን እያቀረብን እንገኛለን።
🤝 Stable • Trusted • Long-Term Collaboration. | 5 430 |
| 7 | ተማሪዎች ውጤታቸው መመልከት ይችላሉ።
በ2018 የትምህርት ዘመን በ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና 95.85% ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤትን ይፋ ተደርጓል።
ተማሪዎች ውጤታቸውን ይህንን ማስፈንጠሪያ https://aa.ministry.et/#/result በመጫን መመልከት ይችላሉ። | 6 269 |
| 8 | በአዲስ አበባ ከተማ የሲጋራ ቁራጭ መንገድ ላይ መጣል 2 ሺህ ብር ያስቀጣል ተባለ
የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን የሲጋራ ቁራጭ በመንገድ፣ በአደባባይ ወይም በማንኛውም የህዝብ መገልገያ ቦታ ላይ የሚጥል ግለሰብ በ2 ሺህ ብር እንደሚቀጣ ገልጿል።ይህ እርምጃ የከተማዋን ንፅህና፣ የህዝብን ጤና ለመጠበቅ እና የትምባሆ ተጠቃሚነትን ለመቀነስ የሚደረገው የቁጥጥር አካል መሆኑ ተገልጿል።
የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ሙሉእመቤት ታደሰ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ቅጣቱ የሚተገበረው በከተማ አስተዳደሩ ደንብ ቁጥር 167/2016 መሠረት ነው።ደንቡ የትምባሆ ምርቶችን አጠቃቀም ለመቆጣጠርና ከጭስ ነፃ የሆነ የከተማ አካባቢን ለመፍጠር የወጣ መሆኑን ጠቁመዋል።
ባለሥልጣኑ በአዲስ አበባ ከተማ 79 በመቶ የሚሆኑት የህዝብ መገልገያ ተቋማት ከጭስ ነፃ መሆናቸውን ገልጿል።በከተማዋ የአጫሾች መጠን ከ5.3 በመቶ ወደ 4.6 በመቶ መቀነሱን በመግለጽ እየተወሰዱ ያሉ የቁጥጥርና የግንዛቤ ማስጨበጫ እርምጃዎች ውጤት እያሳዩ መሆናቸውን አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 6 708 |
| 9 | የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50 በመቶ ሆኖ ተወሰነ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50 በመቶ እንዲሆን ተወሰነ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በ2018 የትምህርት ዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ ከፍተኛ ዉጤት መመዝገቡን ጠቅሰው የተመዘገበው ውጤት አበራታች መሆኑን ተናግረዋል።
ዶክተር ዘላለም አያይዘውም በ2018 ዓ.ም የሒሳብና እንግሊዘኛ ትምህርትን ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረገው ስትራቴጂ በተማሪዎች ውጤት መረጋገጡን ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ዘርፉ ላይ ባደረገው ትኩረት ውጤቱ መመዝገቡን ተናግረው፤ፈተናውን በአጭር ጊዜ በማረም ውጤቱ ይፋ እንዲሆን ቀን ከሌት ሲሰሩ ለቆዩ የፈተና ክፍል ባለሙያዎችና ሂደቱን ሲደግፉ ለነበሩ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ በበኩላቸው፤በከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም 85 ሺህ7መቶ37 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡ | 6 396 |
| 10 | የአውሮፓ ሕብረት ተደጋጋሚ መግለጫ ስለ ትግራይና ስለ ህወሓት
የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ ልዑክ በሰሜን ኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል እየታየ ባለው ወቅታዊ ውጥረት ላይ ያለውን ከፍተኛ ስጋት ገልጿል።
ሕብረቱ ባወጣው መግለጫ መሠረት የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በቅርቡ የወሰዳቸውን እርምጃዎች ማለትም ትይዩ የሆነ የክልል ምክር ቤት ማቋቋሙንና በክልሉ ውስጥ በአንድ ወገን የሚደረገውን የውትድርና ምልመላ በጥብቅ ኮንኗል።
እነዚህ ተግባራት እ.ኤ.አ በ2022 በፕሪቶሪያ የተፈረመውን ዘላቂ ግጭት ማቆም ስምምነት ደንቦችንና ግዴታዎችን በግልጽ የሚጥሱ መሆናቸውን ልዑኩ አስገንዝቧል።
ስምምነቱ ወደ ነበረበት እንዲመለስና በተግባር ላይ እንዲውል ሁሉም ወገኖች አስቸኳይ ውይይት እንዲጀምሩ ጠይቋል።
የአፍሪካ ሕብረት ከፍተኛ ተወካይ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ በክልሉ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚያደርጉትን የሽምግልና ጥረት ሕብረቱ ሙሉ በሙሉ እንደሚደግፍም አስታውቋል።
@Addis_News
@Addis_News | 6 594 |
| 11 | የ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይሆናል
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ሰኔ 22 ቀን ከሰዓት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ነጥቡ ላይ ውይይት ካደረጉ በኃላ ይፋ ይደረጋል ሲል ቢሮው ማስታወቁን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።
የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ ያስችላል። የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 11 እና 12 /2018 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለ56,737 ተማሪዎች መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
@Addis_News
@Addis_News | 7 093 |
| 12 | መረጃን የደበቀ የመንግሥት ኃላፊን 5 ዓመት የሚያሳስረው አዋጅ ጸደቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነጻ መረጃ ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል።
-ዓላማው:- ሙስናን፣ ሕገ-ወጥ አሠራርን ወይም የሥራ ብቃት ማነስን ለመሸሸግ ሲሉ መረጃና ሰነድ የሚደብቁ ወይም እንዲጠፉ የሚያደርጉ የመንግሥት ኃላፊዎችን ተጠያቂ ማድረግ ነው።
- ቅጣቱ፦ ጥፋቱ በፍርድ ቤት የተረጋገጠበት የማንኛውም የመንግሥት ወይም የግል ድርጅት የበላይ ኃላፊ፣ የመረጃ ኃላፊ ወይም ትዕዛዝ ሰጪ አካል እስከ 5 ዓመት በሚደርስ እስራት ይቀጣል ይላል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 7 666 |
| 13 | አሜሪካ በሩዋንዳ ወርቅ ማጣሪያ ላይ ማዕቀብ ጣለች
አሜሪካ በሩዋንዳ የሚገኘውን ጋሳቦ ጎልድ ሪፋይነሪ ጨምሮ ከሶስት የሩዋንዳ ማዕድን ኩባንያዎች እና ከፍተኛ አመራሮቻቸው ላይ አዲስ ማዕቀብ መጣሏን የውጭ ሀብት ቁጥጥር ቢሮ አስታውቋል።
ማዕቀቡ የተጣለባቸው የኩባንያው ሊቀመንበር ዣን ማሊክ ካሊማ እና ዋና ስራ አስኪያጁ ቦስኮ ካዮቦትሲ ሲሆኑ፣ ከእነርሱ ጋር በተያያዘ ቡጋምቢራ ማይንስ፣ዎልፍራም ማይኒንግ እና ርዊንክዋቩ ማይኒንግ ኮርፖሬሽን የተባሉ ተቋማትም በዝርዝሩ ውስጥ ተካተዋል።
እንደ አሜሪካ የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ፣ ማጣሪያው በምስራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኤም23 አማፂያን ቁጥጥር ስር ካሉ አካባቢዎች የሚመጣውን ወርቅ በህገ-ወጥ መንገድ በማሸሽ እና በህጋዊ የንግድ ስርዓት ውስጥ በመደበቅ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል።
በፈረንጆቹ 2026 መጀመሪያ ላይ ብቻ ከ60 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ በህገ-ወጥ መንገድ መተላለፉ የተጠቆመ ሲሆን፣ ሂደቱም በአንዳንድ አጋጣሚዎች በሩዋንዳ መከላከያ ሰራዊት ጥበቃ ታጅቦ እንደነበር የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
ይህ እርምጃ ለአማፂ ቡድኑ የሚፈሰውን የገቢ ምንጭ በማድረቅ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሰላም ስምምነት ለማጠናከር ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
ማዕቀቡ በኢኮኖሚው ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ከፍተኛ እንደሚሆን የሚጠበቅ ሲሆን፣ የአሜሪካ ዜጎችና ኩባንያዎች ከተጠቀሱት አካላት ጋር የንግድ ግንኙነት እንዳያደርጉ ታግደዋል።
ሩዋንዳ በበኩሏ በአማፂያኑ ላይ ድጋፍ እንደምታደርግ ወይም ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ እንደምታመቻች የሚነገረውን ክስ በይፋ አስተባብላለች። | 8 031 |
| 14 | በሳዑዲ አረቢያ እና በፈረንሳይ በደረሱ ሁለት አሰቃቂ የአየር ላይ አደጋዎች የ25 ሰዎች ሕይወት አለፈ
በዓለም አቀፍ ደረጃ በዛሬው ዕለት በተከሰቱ ሁለት ተከታታይ የአየር ላይ አደጋዎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በሳዑዲ አረቢያ እና በፈረንሳይ የደረሱት እነዚህ አደጋዎች በዓለም አቀፉ ሚዲያ ትኩረት የሳቡ ዋነኛ ክስተቶች ሆነዋል።
የመጀመሪያው አደጋ የተሰማው ከሳዑዲ አረቢያ ሲሆን፣ የሀገሪቱ የነዳጅ ግዙፍ ኩባንያ ሳዑዲ አራምኮ (Saudi Aramco) የሆነ ሄሊኮፕተር በሀገሪቱ ምስራቃዊ የባህር ዳርቻ ራስ ታኑራ በተባለችው ቁልፍ የነዳጅ ማዕከል አካባቢ ተከስክሷል።
በሄሊኮፕተሩ ተሳፍረው የነበሩ 14 የሳዑዲ ዜጎች በሙሉ ወዲያውኑ ሕይወታቸው አልፏል።
በሌላ በኩል በፈረንሳይ በተመሳሳይ ዕለት በደረሰ የሲቪል አውሮፕላን አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተረጋግጧል።
አውሮፕላኑ ጥቂት ሰዎችን አሳፍሮ በመብረር ላይ በነበረበት ወቅት የተከሰከሰ ሲሆን፣ በአደጋው ሳቢያ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት ተሳፋሪዎች በሙሉ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
የሀገሪቱ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ከአደጋው የተረፈ ሰው አለመኖሩን ያረጋገጡ ሲሆን፣ የተጎጂዎችን ሙሉ ማንነት ለማወቅ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።
በአሁኑ ወቅት በሁለቱም ሀገራት የደረሱትን የእነዚህን አስደንጋጭ አደጋዎች ትክክለኛ መንስኤ ለማወቅ የሚመለከታቸው የሲቪል አቪዬሽን እና የደህንነት ባለስልጣናት ጥልቅ ምርመራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 9 046 |
| 15 | የአሜሪካና ኢራን ጥቃት‼️
አዳሩን አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ ዳርቻ ላይ በሚገኘው የኢራን ቴሌኮሙኒኬሽን ተቋምና እና ሌሎች ወታደራዊ ማዕከላት ላይ ጥቃት መፈፀሟን ተከትሎ ኢራን በባህሬን እና በኩዬት በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ቤዝ ላይ ጥቃት በመፈፀም ከባድ ጉዳት አድርሳለች። ትራምፕ ኢራንን ከምድረገፅ አጠፋታለሁ የሚል ፅሁፍ ያሰፈሩ ሲሆን የኑክሌር ቦንብ ሊጠቀሙ ይሆን? የሚል ስጋት ደቅኗል። | 9 305 |
| 16 | የሆሳዕናው የውሻ ግድያ 2 ህጻናት ተማሪዎች በእብድ ውሻ በሽታ መሞታቸውን ተከቶሎ የተፈፀመ ነው‼️
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በራቢስ (የእብድ ውሻ) በሽታ ምክንያት ከአንድ ቤት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን ጨምሮ የሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ፣ በነዋሪዎችና በእድር አማካኝነት ሰፊ የውሻ ግድያ ዘመቻ መጀመሩ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል። በከተማዋ አስተዳደር ግብርና ጽሕፈት ቤት መረጃ መሠረት በሆሳዕና ከተማ ውስጥ በአጠቃላይ ከ 10,500 በላይ ውሾች የሚገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 7,500 የሚሆኑት ባለቤት ያላቸው ሲሆኑ 7,200 ያህሉ የተከተቡ ናቸው።
ይሁን እንጂ ቀሪዎቹ 3,000 የሚጠጉት ውሾች ባለቤት የሌላቸውና በየአደባባዩ የሚገኙ በመሆናቸው ለበሽታው መስፋፋትና ለሕዝብ ስጋት ዋነኛ ምክንያት መሆናቸው ተገልጿል።
የሰው ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ በተፈጠረ ድንጋጤ ነዋሪዎች ጤነኛ የሆኑና የተከተቡ የቤት ውሾችን ጭምር በገመድ በማነቅና በተለያዩ መሣሪያዎች በጭካኔ እየገደሉ መሆኑን የገለጹት የከተማው ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ለፋሞ፣ ይህ ዓይነቱ ድርጊት የእንስሳትን ጤናና ደህንነት ለመጠበቅ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1376/2017 የሚጻረርና በሕግ የሚያስጠይቅ በመሆኑ ድርጊቱን የማስቆም ሥራ እየተሠራ መሆኑንና ከጸጥታ አካላት ጋር በመሆን ጥፋተኞችን ለመለየት መረጃ እየተሰበሰበ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 9 361 |
| 17 | “ኢራን ከዚህ በኋላ አትኖርም” ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የተኩስ አቁም ስምምነቱ አደጋ ውስጥ ከገባ በኃላ ኢራን ዳግም አትኖርም ሲሉ መዛታቸው ተሰምቷል፡፡
ኢራንና አሜሪካ የተኩስ አቁም ስምምነትን በመጣስ እርስ በእርሳቸው ጥቃት መሰንዘራቸውን ተከትሎ፤ መወቃቀሳቸውን ቀጥለዋል፡፡
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አገራቱ ስምምነቱን ከፈጸሙ ከጥቂት ቀናት በኋላ የአሜሪካ ማዕከላዊ ኮማንድ በቴህራን በርካታ ኢላማዎችን መመታቸውን አስታውቀዋል።
ጥቃቱን ለመሰንዘሩ ኢራን ስምምነቱን የሚጥስ ተግባር በመፈጽሟ ነው ብለዋል፡፡
ትራምፕ በቱርዝ ሶሻል ሚዲያ ባጋሩት መልዕክት ኢራን በጭራሽ መማር የማትችል ናት ብለዋል፡፡
ቴህራን የሰላም ስምምነቱን መጣስ ካላቆመች ከዚህ በኃል አትኖርም ሲሉ ዝተዋል፡፡
ኢራን በበኩሏ ፤አሜሪካ ስምምነቱን በመጣሷ በዮርዳኖስ፣ ባህሬን እና ኩዌት በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት መሰንዘሯን አስታውቃለች፡፡ | 10 309 |
| 18 | ኢትዮጵያ፣ አውሮፓ ኅብረት ወደ አገራቸው ሊባረሩ የማይችሉ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ለመላክ ከመረጣቸው አገራት መካከል አንዷ መኾኗን ሂውማን ራይትስ ዎች ገለጠ።
ተቋሙ፣ ኅብረቱ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሦስተኛ አገራት ለመላክ አዲስ ስልቶችን እየቀየሠ ይገኛል በማለት ወቅሷል።
ጀርመን፣ ኦስትሪያ፣ ዴንማርክ፣ ግሪክ እና ኔዘርላንድስ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ለመላክ ከመረጧቸው አገራት መካከል፣ ኢትዮጵያ፣ ኡጋንዳ፣ ሩዋንዳ፣ ቱኒዚያ፣ ግብጽ፣ ሊቢያ እና ሞሪቴኒያ እንደሚገኙበት ተቋሙ ጠቅሷል።
ተቋሙ፣ ተቀባይ አገራት የጥገኝነት ጠያቂዎቹን ሰብዓዊ መብት ያከብሩ፣ ወደ ትውልድ አገራቸው ይመልሷቸው ወይም ያስሯቸው እንደኾነ ግልጽ አይደለም ሲል ስጋቱን ገልጧል።
የኅብረቱ አገራት ይህንኑ እቅድ እንዲተውት ያሳሰበው ተቋሙ፣ ይህ ካልሆነ ግን እቅዱ ተግባራዊ ከመኾኑ በፊት ኅብረቱ ቢያንስ በተቀባይ አገራት የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ጥብቅ ግምገማ እንዲያደርግ እቅዱን የሚቃወሙት የፈረንሳይና ስፔን መሪዎች ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 9 279 |
| 19 | ትራምፕ በምስላቸው ያጌጠ አዲስ ፓስፖርት ይፋ አደረጉ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የሀገሪቱን 250ኛ የነጻነት በዓል ለማዘከር የተዘጋጀ ልዩና ውስን የፓስፖርት ዲዛይን ይፋ አድርገዋል።
“አርበኛዊ ባዊ ፓስፖርት” (Patriotic Passport) የተሰኘው ይህ ፓስፖርት፣ በትራምፕ የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ የቀረበ ሲሆን የፕሬዝዳንቱን ምስል እና ፊርማ አካትቷል።
በጀርባው ላይ ደግሞ የ1776ቱ የነጻነት አዋጅ ፊርማ ስነ-ስርዓት ምስል እና “Welcome, but be good!” (እንኳን ደህና መጡ፣ ግን መልካም ሁኑ!) የሚል መልዕክት ተጽፎበታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በትራምፕ የታሪፍ ዛቻ ዙሪያ ከአውሮፓ ህብረት ጠንከር ያለ ምላሽ ተሰጥቷል።
ህብረቱ ትራምፕ ታሪፍ ከጣሉ ፈጣንና ወሳኝ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 9 475 |
| 20 | የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች:-
✅ ከጠዋቱ 4፡00-ቀኑ 9፡30
👉 ሜክስኮ፣ ብሔራዊ ፣ ሰንጋተራ 40/60 ኮንዶሚኒየም፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፣ ኩባ ፓርክ፣ ተ/ሃይማኖት፣ በርበሬ በረንዳ፣ ዲአፍሪካ እና አካባቢያቸው ፣
✅ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 8፡00
👉ጎፋ ካምፕ፣ ጀርመን አደባባይ፣መከኒሳ አረቄ ፋብሪካ፣ላፍቶ፣ ቄራ፣ቆሼ፣ ዘነበወርቅ፣ጎፋ እና አካባቢያቸው ፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00-10፡30
👉ሸገር ዳቦ፣ ኤሞሌስ ፋብሪካ፣ ለገ ጣፎ ከተማ ፣ የካሰዴ፣የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም፣ወሰን ግሮሰሪ፣ ሲኤምሲ ሚካኤል፣ ካራሎ፣ለገጣፎ፣ ሲዲሲ ፣ ኮሰሮ፣ ለገዳዲ፣ ሰንዳፋ፣ 44 ማዞሪያ፣ ሲሬ ጎዩ፣ የካ ሰዴ፣ድሬ ሰኩር እና አካባቢያቸው፣
👉 ጁኒፐር ግላስ፣ ደጋ ውሃ፣ ቻንግልዶንግራን፣ ፊበላ፣ ቦልት ማልት፣ ሃዋ ትሬዲንግ፣ ብራውን ፉድ ፣ ማማ ዱኬት ፋብሪካዎች እና አካባቢያቸው ፣
✅ ከለሊቱ 6፡00-ቀኑ 6፡00
👉 ድሬደዋ ውሃ፣ ፓይነር ሲሚንቶ፣ ቱሬ ሲሚንቶ፣ ሀረር ውሃ፣ ማረሚያ፣ ኩርቱ፣ በለዋ፣ ቃልቻ፣ ቢሻን በሄ፣ ሃሎብሳ፣ ለጎዳ፣ አሳሊሶ፣ ኢንዱስትሪ ኮንዶሚኒየም፣ ሻሎም ኢንጂነሪንግ፣ መልካ፣የኢንዱስትሪ እና አካባቢያቸው፣
✅ ከጠዋቱ 1፡30-5፡00
👉አዳማ ከወንጂ ቀበሌ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢያቸው ፣
✅ ከጠዋት 12፡00-12፡00
👉በአሰላ፣ አዳሚቱሉ፣ ቡታጅራ፣ ወራቤ እና አካባቢው
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ውድ ደንበኞቻችን፤ የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስከሚመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን ትብብራችሁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት | 10 629 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
