አርምሞ🧘🏽♂
📈 تحلیل کانال تلگرام አርምሞ🧘🏽♂
کانال አርምሞ🧘🏽♂ (@armemo_offical) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 11 234 مشترک است و جایگاه 8 229 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 971 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 11 234 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 09 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 103 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -9 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.46% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.84% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 2 749 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 994 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 43 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ጥ ቂ ት ም ና ኔ. .🧘🏽♂️”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 10 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 10 ژوئن | 0 | |||
| 09 ژوئن | 0 | |||
| 08 ژوئن | 0 | |||
| 07 ژوئن | 0 | |||
| 06 ژوئن | +4 | |||
| 05 ژوئن | 0 | |||
| 04 ژوئن | +8 | |||
| 03 ژوئن | +3 | |||
| 02 ژوئن | +17 | |||
| 01 ژوئن | +9 |
ውጥንቅጡ የወጣ ደስታ እየተሰማኝ ነው። ምንም ካለማድረግ ምንም ማድረግ ይሻላል። አላገኘውም ለዛም ነው የማጣው ነገር እንደሌለኝ የተረዳውት። በዚህ ሰሞን ያለፍኩት ቴራፒ ከኖርኩት ሎጂክ በላይ ብዙ ትርጉም በህይወቴ አምጥቷል። ሰላም እደሩ 🍸| 2 | በደስታ እና በተስፋ ጠኔ ልሞት ስል «ምን አግኝቶ ነው?» ብለው ሲያወሩ ሰማው። እኔ ምንም አላገኘውም ይልቅስ ሸክሜን ነው ያራገፍኩት፣ እድፌን ነው ያጸዳውት፤ መንጻት የሚቻለው በአንድ ነገር ብቻ ነው። እሱም በቅዱስ ደም ውስጥ ያለ የራስን ሰውነት የማጠብ ሂደት ነው።
ከመጠበቅ በላይ ተቀብሎ መኖር፣ ከማማረር ይልቅ ዝምታን መርጦ ማለፍ፣ ወድቆ ከመቅረት ይልቅ ደጋግሞ እየወደቁ መራመድ ዋጋ አለው። እግዚአብሔር ይመስገን ለሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን 😊 | 954 |
| 3 | «አንዳንዴ ሌላ ህይወት አልማለሁ። ለሰዎች ማን መሆኔን የማላስረዳበት። ከእንግዲህ ምንም አለመጻፍ፤ በተሰበረ መስታወት እራሴን ማየት አልፈልግም። ሙሉ ለሙሉ ብቻዬን የምሆንበትን ቦታ አልማለሁ። ማለቂያ የሌለው ምድረበዳ ላይ እንደተዘረጋ ባህር እኔ እና ድመቴ በዝምታ ተቀምጠን አልማለሁ። ህልም ግን ህልም ነው። በአዕምሮአችን በኩል ያለከልካይ ከፍተን የምንዘጋው በር ነው። አብዛኛው ሰው ከህልሙ ይሸሻል። እውን እንዳይሆን በፍርሃት የታጠረ የሃሳብ ምስል ብቻ ሆኖ ይቀራል። እኔ ግን አየዋለሁ፣ እኖረዋለሁ፣ የኖርኩትን ጽፌ ቀስ አድርጌ እለቀዋለሁ..»
―ቻርለስ ቡኮውስኪ
@Imagination_officially | 1 341 |
| 4 | የትኛው የበለጠ ይሻላል? | 1 117 |
| 5 | Old profile | 1 107 |
| 6 | አዲሱ ፕሮፋይል ከአስር ስንት? | 1 151 |
| 7 | پیام صوتی | 112 |
| 8 | The king has returned, and I brought my own drama. Did you miss me? I know you did don't lie. Sorry I’m late, the world wasn't chaotic enough without me. Social media detox is over, and I'm back to ruin everyone’s feed again 🍸😑 | 1 249 |
| 9 | #የመጨረሻ_ፖስት
እስከዛሬ የእኔን ጽሁፍ እያነበባችሁ የነበራችሁ ሰዎች። አንድ ነገር ልለመናችሁ። ትዕግስት የሌላችሁ ጠላትና ወዳጆቼ በጠቅላላ ይህን ጽሁፍ እስከመጨረሻው አንብቡት። ምክንያቱም የመጨረሻ ፖስቴ ነው።
«በሰው ስልክ የተጻፈ» 🤳
ቻው ቻው ሲኞር ሲኞሬ መቃኔን ዘጋው ቤት ባይኖረኝም ዛሬ። ማንበብን የመሰለ ገጸበረከት መጻፍን ያህል መርገም ያሸክመናል። ያኔ ነው ከሰው ተራ የምንወጣው። ከስምንት አመት በላይ በስነጽሁፍ ህይወት ውስጥ ጸሃፊ ሆኜ ኖሪያለሁ። ታድያ ምን አተረፍኩ? ስም። ከሰፈርና ሶሻል ሚድያ የተሰጠኝ የስሞች ብዛት፦
«ጉሩ»
«ፕሮፌሰሩ»
«ሞሳድ»
«ምሁር»
«ደራሲው»
ስም ልብስ አይደለም። ስም አርቴፊሻል አበባ ነው። የሳሎን ጌጥ!። ከስምንት አመት በላይ እጄ ላይ የቆዩት ስልኮች ሁለት ናቸው። ስልክ በጥንቃቄ በመያዝ እታወቃለሁ። አንዱ ቆሽቋሻ ህዋዊ ሲሆን ከዛ በኋላ ግን ለረጅም ግዜ እስከዛሬ የተጠቀምኩት ይሄ በምስሉ ላይ ያለውን ZTE ነው። በእነዚህ ስልኮች ሦስት ቴሌግራም ከፍቻለሁ፦
¹«አርምሞ» 11,270 ሰብስክራይብ
²«Imagination» 7,273 ሰብስክራይብ
³«Thought pending» 2,075 ሰብስክራይብ
ይህ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ማለትም ከማንም ጋር ማስታወቂያ ሳልሰራ የገነባውት Real members ነው። እንደሱም ሆኖ በአሳብ አለመግባባት ሌፍት ያሉት ለቁጥር ያዳግታሉ። ፌስቡክ ላይም 19,200 ፎልወር ሰብስቢያለሁ።
ታድያ አርምሞ ቻናል ላይ ከ3500 በላይ አርቲክል፤ imagination ቻናል ላይ ደግሞ ከ2,400 በላይ አርቲክል። Thought ላይ ደግሞ ከ1ሺህ በላይ አርቲክሎችን ጽፊያለሁ። ፌስቡክም በተመሳሳይ ከ1k በላይ ጽፊያለሁ።
በድምር ወደ 7ሺህ አርቲክል። አጫጭር አባባሎች 2 ሺህ ብለን መንጥረን ብናወጣ Long article ወደ5ሺህ ይጠጋል። እድሜዬ 23 ነው። እና በዚህ እድሜዬ ይህ ሁሉ መጻፍ እጅግም ትርፍ ነው።
ቢሆንም አዳዲስ የሶሻል ሚድያ ፕላትፎርሞችን ለመቀላቀል ስልኩ እጅግ በጣም የማይረባ ሆነብኝ። ስለዚህ ከኮረና ጀምሮ ቲክቶክ እና ዩቲዩብ ለመቀላቀል ሰንፌ ቀርቻለሁ። ካሜራው ትንሽ እራሱ ጥራት የለውም!። እንደዛም ሆኖ በሌሎች ሰዎች ስልክ ቪድዮ ለመስራት እስከ ልመና ደርሼ ሞክሪያለሁ። ዛሬ ቢኖሩም ነገ አይኖሩም። ካሜራ የለም፣ ካሜራው ቢገኝ የሚቀርጸኝ አካል አላገኝም!።
በጥልቀት መጻፍ የጀመርኩት በፈረንጆች አቆጣጠር 2019 ዓ.ም ላይ ነው። እጅግ በጣም ብዙ ጽሁፍ የጻፍኩት ደግሞ 2022 እስከ 2024 አካባቢ ነው። ከዚህ ያተረፍኩት የሰውነት መክሳት ነው። በፊት የሚያውቁኝ ሰዎች ሲያገኙኝ ይደነግጣሉ። በሽታ ይዞኝ ነው የሚመስላቸው!። በዛ ላይ የአዕምሮ ቀውስ በተደጋጋሚ አጋጥሞኛል። ቅርቤ ባሉ ሰዎች ስነጽሁፍ ላይ ያለኝ ፍቅር ወደተረባ ተቀይሮ ቀስ በቀስ ስድብ እየሆነ መጣ። ለሊት ለሊት በቅዠት እሰቃያለሁ መተኛት አልችልም!። እጅግ በጣም ጭንቀት አለብኝ እጅግ በጣም!። ብዙ መዳኒቶችን እስከመጠቀም ያደረሰ የአዕምሮ ጭንቀት!። እንደዛም ሆኖ መጻፍ አላቆምኩም። ልተወው አልቻልኩም!።
ጸጸት፣ እራስን መውቀስ፣ ከሃይማኖት ቦታዎች መራቅ፣ ብቻን መቀመጥ፣ ከፍተኛ የመርሳት ችግር፣ ምግብ በቀን አንድ ወይም ሁለቴ መብላት፣ ማይግሪንና ወሬ የመቀላቀል አባዜ ዋጠኝ!። የምር እብድ ነው የምመስላቸው!።
ይህ ሁሉ መልፋቴ ትርፍ ባይኖረውም ነገር ግን ዛሬ አንድ ነገር ተፈጠረ ስልኬ እስከነጭራሹም መስራት አቆመ። ለብዙ አመታት እየጋለ፣ ባትሪው አብጦና ቶሎ እያለቀ ቻርጅ ሰክቼ የታገልኩለት ስልክ ዛሬ ተሰናበተኝ!። ቻው ቻው ሲኞር ሲኞሬ!።
ምንም ካለማድረግ ምንም ማድረግ ይሻላል። ለዛም ነው ይህ ሁሉ አመታት የጻፍኩት!። በተለይ ማታ ማታ የምሞት ስለሚመስለኝ የምጽፈው «የዕውነት ማስታወሻዎች» በተደጋጋሚ አጋርቻለሁ።
ስልኬ ከእንግዲህ የለም። ከዚህ በኋላ መጻፍ ቀረ!። መጻፍ ሲቀር ማሰብ ይቆማል!። «አንተ በምትጽፈው ወይ አያልፍህ ወይ እናትህን አታሳልፍላት እንደእብድ ትቸከችካለ!» ብሎ የተናገረኝ የሰፈር ልጅ ዛሬ ላይ ቆሜ አጨበጭብለታለሁ!።
ከዚህ በፊት ስልክ ለመግዛት በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ሶሻል ሚድያ ላይ ገንዘብ አሰባስቢያለሁ። የሚገርመው ግን ካሰብኩት በታች ነበር ያገኘውት። እያናናቅኩ አይደለም። ያገኘውት 2,543 ብር ነው። እንደውም ሦስተኛው ቻናሌን 700 ብር ስለሸጥኩት የሞላ ድምር ነው። አርምሞ ላይ ያሉት 11 ሺህ ሜምበር ውስጥ መቶ መቶ ብር ቢያወጡ 10 ሺህ ይሞላል የሚል እምነት ነበረኝ። ቢያንስ ከአርምሞ 5 ሺህ ከImagination 5ሺህ ከሦስተኛው ቻናሌ ደግሞ 1 ሺህ ባገኝ አጠቃላይ 11 ሺህ ብር ሆኖ ትንሽ ጨምሬበት እኔም የቲክቶክና የዩቱዩብ ቪድዮዎችን በመልቀቅ ኢንፊሉዌንስ ካፒታሌን ልገነባ አስቤ የነበረ ቢሆንም የተላከልኝ ገንዘብ 3 ሺህ ብር እራሱ አይሞላም!።
በመጨረሻም ማስተላለፍ የምፈልገው ነገር ስልክ ቦታ የምተሰሩ ሰዎች አንድ የተሻለ ስልክ ስፖንሰር የምታደርጉኝ ከሆነ ለስድስት ወራትና ከዛ በላይ ከስራዬ ጎን ላስተዋወቅ ቃል እገባለሁ። ወይም ከስር ባለው የአዋሽ አካውንትና የቴሌ ብር ያለንን ገንዘብ በማስገባት አመቱን ሙሉ ፈልጌ ካጣውት የስልክ ርሃብና የታሰሩ አሳቦቼን ለማሳካት አስችሉኝ!።
ይህ ጽሁፍ ምንም ቀመር የለውም። ቃል ለምድር ለሰማይ በዚህ ሰዓት የሚያስፈልገኝ ስልክና ስልክ ብቻ ነው። ስለዚህ የሚመጣው ገንዘብ ወደስልክ ነው የምቀይረው። እስካሁን የተላከውን 2ሺህ አምስት መቶ ብር አላጠፋውትም እኔም የእራሴን እጨምራለሁ እናንተም በዚህ እንድትረዱኝ በትህትና እጠይቃለሁ።
ይህን ማድረግ የማትችሉ ደግሞ ላይክ፣ ኮመንት እና ሼር በማድረግ ተባበሩኝ አመሰግናለሁ።
ከነገ ጀምሮ ከስምንት አመታት በኋላ ያለስልክ እና ያለኢንተርኔት የምቆይበት የአርምሞ ግዜ ይሆናል። ይህ ነገር እንደሚሳካ አውቃለሁ። ሲሳካልኝ ግን ገንዘብ መስራት እንደምጀምር 100% እርግጠኛ ሆኜ አወራለሁ። በየመሃሉ በሰው ስልክ መግባቴ አይቀርም። ነገር ግን ግዜ ወስዶ ለመጻፍ አይመችም ይደብራል ጭምር!። ዛሬ አለው ከነገ ጀምሮ ኢንቦክስ ቴክስት ልካችሁ የማልመልስ ከሆነ ተናግሪያለሁ እኔ የለውም!። ሰላሙን እመኝላችኋለሁ።
በሶሻል ሚድያ የማውቃችሁ በመሃል ከዚህ ምድር ካለፋችሁና ካለፍን ነፍስ ይማር ለጥፋታችን ለእኔም ለእናንተም። እወዳችኋለሁ። የበለጠ የተረዳኝ ብሎም ቦታ የሰጠኝ እዚህ ስጽራ ያለው ማህበረሰብ። የአሳብ ሰዎች ቻው ቻው ሲኞር ሲኞሬ👋🏼
የስልኩ ግዢ ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ 👇🏽
አዋሽ፦013201281880800
ቴሌብር፦0961275503
Moges beyene
@Armemo_offical | 3 |
| 10 | بدون متن... | 1 |
| 11 | #የመጨረሻ_ፖስት
እስከዛሬ የእኔን ጽሁፍ እያነበባችሁ የነበራችሁ ሰዎች። አንድ ነገር ልለመናችሁ። ትዕግስት የሌላችሁ ጠላትና ወዳጆቼ በጠቅላላ ይህን ጽሁፍ እስከመጨረሻው አንብቡት። ምክንያቱም የመጨረሻ ፖስቴ ነው።
«በሰው ስልክ የተጻፈ» 🤳
ቻው ቻው ሲኞር ሲኞሬ መቃኔን ዘጋው ቤት ባይኖረኝም ዛሬ። ማንበብን የመሰለ ገጸበረከት መጻፍን ያህል መርገም ያሸክመናል። ያኔ ነው ከሰው ተራ የምንወጣው። ከስምንት አመት በላይ በስነጽሁፍ ህይወት ውስጥ ጸሃፊ ሆኜ ኖሪያለሁ። ታድያ ምን አተረፍኩ? ስም። ከሰፈርና ሶሻል ሚድያ የተሰጠኝ የስሞች ብዛት፦
«ጉሩ»
«ፕሮፌሰሩ»
«ሞሳድ»
«ምሁር»
«ደራሲው»
ስም ልብስ አይደለም። ስም አርቴፊሻል አበባ ነው። የሳሎን ጌጥ!። ከስምንት አመት በላይ እጄ ላይ የቆዩት ስልኮች ሁለት ናቸው። ስልክ በጥንቃቄ በመያዝ እታወቃለሁ። አንዱ ቆሽቋሻ ህዋዊ ሲሆን ከዛ በኋላ ግን ለረጅም ግዜ እስከዛሬ የተጠቀምኩት ይሄ በምስሉ ላይ ያለውን ZTE ነው። በእነዚህ ስልኮች ሦስት ቴሌግራም ከፍቻለሁ፦
¹«አርምሞ» 11,270 ሰብስክራይብ
²«Imagination» 7,273 ሰብስክራይብ
³«Thought pending» 2,075 ሰብስክራይብ
ይህ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ማለትም ከማንም ጋር ማስታወቂያ ሳልሰራ የገነባውት Real members ነው። እንደሱም ሆኖ በአሳብ አለመግባባት ሌፍት ያሉት ለቁጥር ያዳግታሉ። ፌስቡክ ላይም 19,200 ፎልወር ሰብስቢያለሁ።
ታድያ አርምሞ ቻናል ላይ ከ3500 በላይ አርቲክል፤ imagination ቻናል ላይ ደግሞ ከ2,400 በላይ አርቲክል። Thought ላይ ደግሞ ከ1ሺህ በላይ አርቲክሎችን ጽፊያለሁ። ፌስቡክም በተመሳሳይ ከ1k በላይ ጽፊያለሁ።
በድምር ወደ 7ሺህ አርቲክል። አጫጭር አባባሎች 2 ሺህ ብለን መንጥረን ብናወጣ Long article ወደ5ሺህ ይጠጋል። እድሜዬ 23 ነው። እና በዚህ እድሜዬ ይህ ሁሉ መጻፍ እጅግም ትርፍ ነው።
ቢሆንም አዳዲስ የሶሻል ሚድያ ፕላትፎርሞችን ለመቀላቀል ስልኩ እጅግ በጣም የማይረባ ሆነብኝ። ስለዚህ ከኮረና ጀምሮ ቲክቶክ እና ዩቲዩብ ለመቀላቀል ሰንፌ ቀርቻለሁ። ካሜራው ትንሽ እራሱ ጥራት የለውም!። እንደዛም ሆኖ በሌሎች ሰዎች ስልክ ቪድዮ ለመስራት እስከ ልመና ደርሼ ሞክሪያለሁ። ዛሬ ቢኖሩም ነገ አይኖሩም። ካሜራ የለም፣ ካሜራው ቢገኝ የሚቀርጸኝ አካል አላገኝም!።
በጥልቀት መጻፍ የጀመርኩት በፈረንጆች አቆጣጠር 2019 ዓ.ም ላይ ነው። እጅግ በጣም ብዙ ጽሁፍ የጻፍኩት ደግሞ 2022 እስከ 2024 አካባቢ ነው። ከዚህ ያተረፍኩት የሰውነት መክሳት ነው። በፊት የሚያውቁኝ ሰዎች ሲያገኙኝ ይደነግጣሉ። በሽታ ይዞኝ ነው የሚመስላቸው!። በዛ ላይ የአዕምሮ ቀውስ በተደጋጋሚ አጋጥሞኛል። ቅርቤ ባሉ ሰዎች ስነጽሁፍ ላይ ያለኝ ፍቅር ወደተረባ ተቀይሮ ቀስ በቀስ ስድብ እየሆነ መጣ። ለሊት ለሊት በቅዠት እሰቃያለሁ መተኛት አልችልም!። እጅግ በጣም ጭንቀት አለብኝ እጅግ በጣም!። ብዙ መዳኒቶችን እስከመጠቀም ያደረሰ የአዕምሮ ጭንቀት!። እንደዛም ሆኖ መጻፍ አላቆምኩም። ልተወው አልቻልኩም!።
ጸጸት፣ እራስን መውቀስ፣ ከሃይማኖት ቦታዎች መራቅ፣ ብቻን መቀመጥ፣ ከፍተኛ የመርሳት ችግር፣ ምግብ በቀን አንድ ወይም ሁለቴ መብላት፣ ማይግሪንና ወሬ የመቀላቀል አባዜ ዋጠኝ!። የምር እብድ ነው የምመስላቸው!።
ይህ ሁሉ መልፋቴ ትርፍ ባይኖረውም ነገር ግን ዛሬ አንድ ነገር ተፈጠረ ስልኬ እስከነጭራሹም መስራት አቆመ። ለብዙ አመታት እየጋለ፣ ባትሪው አብጦና ቶሎ እያለቀ ቻርጅ ሰክቼ የታገልኩለት ስልክ ዛሬ ተሰናበተኝ!። ቻው ቻው ሲኞር ሲኞሬ!።
ምንም ካለማድረግ ምንም ማድረግ ይሻላል። ለዛም ነው ይህ ሁሉ አመታት የጻፍኩት!። በተለይ ማታ ማታ የምሞት ስለሚመስለኝ የምጽፈው «የዕውነት ማስታወሻዎች» በተደጋጋሚ አጋርቻለሁ።
ስልኬ ከእንግዲህ የለም። ከዚህ በኋላ መጻፍ ቀረ!። መጻፍ ሲቀር ማሰብ ይቆማል!። «አንተ በምትጽፈው ወይ አያልፍህ ወይ እናትህን አታሳልፍላት እንደእብድ ትቸከችካለ!» ብሎ የተናገረኝ የሰፈር ልጅ ዛሬ ላይ ቆሜ አጨበጭብለታለሁ!።
ከዚህ በፊት ስልክ ለመግዛት በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ሶሻል ሚድያ ላይ ገንዘብ አሰባስቢያለሁ። የሚገርመው ግን ካሰብኩት በታች ነበር ያገኘውት። እያናናቅኩ አይደለም። ያገኘውት 2,543 ብር ነው። እንደውም ሦስተኛው ቻናሌን 700 ብር ስለሸጥኩት የሞላ ድምር ነው። አርምሞ ላይ ያሉት 11 ሺህ ሜምበር ውስጥ መቶ መቶ ብር ቢያወጡ 10 ሺህ ይሞላል የሚል እምነት ነበረኝ። ቢያንስ ከአርምሞ 5 ሺህ ከImagination 5ሺህ ከሦስተኛው ቻናሌ ደግሞ 1 ሺህ ባገኝ አጠቃላይ 11 ሺህ ብር ሆኖ ትንሽ ጨምሬበት እኔም የቲክቶክና የዩቱዩብ ቪድዮዎችን በመልቀቅ ኢንፊሉዌንስ ካፒታሌን ልገነባ አስቤ የነበረ ቢሆንም የተላከልኝ ገንዘብ 3 ሺህ ብር እራሱ አይሞላም!።
በመጨረሻም ማስተላለፍ የምፈልገው ነገር ስልክ ቦታ የምተሰሩ ሰዎች አንድ የተሻለ ስልክ ስፖንሰር የምታደርጉኝ ከሆነ ለስድስት ወራትና ከዛ በላይ ከስራዬ ጎን ላስተዋወቅ ቃል እገባለሁ። ወይም ከስር ባለው የአዋሽ አካውንትና የቴሌ ብር ያለንን ገንዘብ በማስገባት አመቱን ሙሉ ፈልጌ ካጣውት የስልክ ርሃብና የታሰሩ አሳቦቼን ለማሳካት አስችሉኝ!።
ይህ ጽሁፍ ምንም ቀመር የለውም። ቃል ለምድር ለሰማይ በዚህ ሰዓት የሚያስፈልገኝ ስልክና ስልክ ብቻ ነው። ስለዚህ የሚመጣው ገንዘብ ወደስልክ ነው የምቀይረው። እስካሁን የተላከውን 2ሺህ አምስት መቶ ብር አላጠፋውትም እኔም የእራሴን እጨምራለሁ እናንተም በዚህ እንድትረዱኝ በትህትና እጠይቃለሁ።
ይህን ማድረግ የማትችሉ ደግሞ ላይክ፣ ኮመንት እና ሼር በማድረግ ተባበሩኝ አመሰግናለሁ።
ከነገ ጀምሮ ከስምንት አመታት በኋላ ያለስልክ እና ያለኢንተርኔት የምቆይበት የአርምሞ ግዜ ይሆናል። ይህ ነገር እንደሚሳካ አውቃለሁ። ሲሳካልኝ ግን ገንዘብ መስራት እንደምጀምር 100% እርግጠኛ ሆኜ አወራለሁ። በየመሃሉ በሰው ስልክ መግባቴ አይቀርም። ነገር ግን ግዜ ወስዶ ለመጻፍ አይመችም ይደብራል ጭምር!። ዛሬ አለው ከነገ ጀምሮ ኢንቦክስ ቴክስት ልካችሁ የማልመልስ ከሆነ ተናግሪያለሁ እኔ የለውም!። ሰላሙን እመኝላችኋለሁ።
በሶሻል ሚድያ የማውቃችሁ በመሃል ከዚህ ምድር ካለፋችሁና ካለፍን ነፍስ ይማር ለጥፋታችን ለእኔም ለእናንተም። እወዳችኋለሁ። የበለጠ የተረዳኝ ብሎም ቦታ የሰጠኝ እዚህ ስጽራ ያለው ማህበረሰብ። የአሳብ ሰዎች ቻው ቻው ሲኞር ሲኞሬ👋🏼
የስልኩ ግዢ ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ 👇🏽
አዋሽ፦013201281880800
ቴሌብር፦0961275503
Moges beyene
@Armemo_offical | 1 330 |
| 12 | بدون متن... | 1 034 |
| 13 | የምሰራበት ስራ ቦታ አለ። ያው መዋያ ስለሌኝ እንጂ ደሞዙ የሻይ ነው። ግን እዛ ስራ ቦታ የአለቆች አለቃ የሆነች mastermind women አለች። እና እሷ በምትመራው ስራ ውስጥ ሁለት ማህበራት አሉ። ሁለት ማህበራት ውስጥ ደግሞ አርባ አርባ ሰዎች ተቀምጠዋል።
እና አንዱ ማህበር አንድ ሳምንት ሲሰራ ቀጣዩን ሳምንት ደግሞ ሌላኛው ማህበር ነው የሚሰራው። ከዚህ በፊት አንድ ማህበር የነበረ ቢሆንም። ስራው ሲቀዛቀዝ ሌላ ተቀናቃኝ ማህበር ጨምራባቸው በሳምንት ፈረቃ ነበር የሚሰሩት።
ታድያ ከመኪና ባራገፋችሁት ልክ ነው የምታገኙት የሚል ህግ ወጥቶ በዛ ህግጋት ዙርያ ነው የሚንቀሳቀሱት። ግን ይሄ ፌበር እንደሆነ የነቃውት እኔ እና እኔ ብቻ ነኝ። በስራው ላይ ባልኖርበትና ባያገባኝም። አብሮአደግ ጓደኞቼ ስላሉ የምትጠቀመውን የጭንቅላት ጨዋታ ነግሬያቸው ነበር። እና ቢያምጹ። ሎጃኪሊ ቢከራከሩ ይህቺ ሴት የዋዛ አይደለችም። በጣም የተማረችና የምትሰራውን ጠንቅቃ የምታውቅ ሴት ነች!።
እንዲህ እያለ ለሁለት አመት ከሰሩ በኋላ ምን ብታደርግ ጥሩ ነው? አንዱን ማህበር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አባረረች። አመጽ ቢያስነሱ፣ ቢከራከሩ በጥበቃ አትገቡም የሚል እገዳ ተጣለባቸው። ለምን?
የእሷ ስራ እየተቀዛቀዘ ነበር። ስለዚህ አንድ ነገር ማድረግ ነበረባት። ያሰበችውን እዛ ማህበር ውስጥ ያሉ ሰዎች ባይገነዘቡትም እኔ ግን ጥንቅቅ ባለ ሁኔታ ገብቶኛል።
መጀመርያ አንድ ማህበር ማለትም አርባዎችሁ ነበር ከአመት እስከአመት የሚሰሩት ታድያ ግን ገንዘብ ከልክ አልፎ ጠገቡ። እነሱ አይገቡም ሌላ መቅጠርና ስራ መቅረት ጀመሩ። ያኔ ነው ሌላ ተፎካካሪ አርባ ማህበር አደራጅታ ያስገባችው። ይሄኔ ግን እንደድሮ አመቱን ሙሉ መስራት አልቻሉም። ይልቅስ ከእነዚህ ማህበር ጋር በፈረቃ መሸቀል ጀመሩ። ስለዚህ የለመዱትን ገንዘብ ለማግኘት ጠንከረው መስራት ጀመሩ። አዲስ የገባውም ማህበር እንደአዲስነቱ ስራውን ሰጥ'ለጥ ብሎ መስራት ተያያዘው። አመት ተቆጠረ። አሁንም አዲስ የገባው ማህበር ገንዘብ ጠገበ። ይህን ሳምንት ቢያጡም ቀጣይ ሳምንት እጥፍ ስለሚያገኙ ስራ መቅረትና ሰው ቀጥሮ ማሰራት ጀመሩ። ቅርብ ግዜ ግን አንድ ሀሳብ ብልጭ አለላት። የድሮውን ማህበር አባራረች!።
ይሄኔ አንዱ ማህበር ብቻ ቀረ። በአንዱ ብቻ መንቀሳቀስ ስለማይችል ሌላ አዲስ ማህበር በድጋሚ ተደራጅቶ ገባ። ስራ ቦታውም ለወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር ደረጃ አንደኛ ሆኖ በመንግስት ተመሰገነ።
እና ምን አደረገች ያባረረቻቸውን ማህበራት በይቅርታ አስገባች። አሁን ሦስት ማህበራት ሆኑ። ይሄም ማለት የመጀመርያው ማህበር አንድ ሳምንት፣ ሁለተኛው አንድ ሳምንት፣ ሦስተኛው አንድ ሳምንት። የመጀመርያው ማህበር አንድ ሳምንት ሰርቶ ገንዘብ የሚቀበለው በቀጣዩ ሳምንት ነው። ይሄም ማለት ሁለት ሳምንት ያለምንም ስራ ይቀመጣል።
ዋናው እቅዷ የሰራው እዚህ ጋር ነው። የተባረሩት ማህበራት ድጋሚ ላለመባረር ብሎም የለመዱትን የገንዘብ መጠን ለማግኘት ቀን ከሌት ያለና የሌለ ጉልበታቸውን አፍስሰው መስራት ጀመሩ። ቀስ በቀስ ቀጣይ ሳምንት የሚገቡት ሌላኛው ማህበር ጋር ስራ ጠፋ። ምክንያቱም አብዛኛው መኪና መጀመርያ በተባረረው ማህበር ተሰርቶ አልቋል። ስለዚህ ቀጣዮችሁም ጠንክረው መስራት ጀመሩ። እሷም የሚገባው የመኪና መጠን እንዲጨምር አዘዘች። ሶስቱም ማህበር መኪና በመጣ ቁጥር ከወትሮ በተለየ መልኩ በፍጥነትና በቅልጥፍና ይሰራሉ። እሷም አመታዊ ገቢዋ ምን ይሆናል?። ከዚህ በፊት ተሰርቶ የማያውቅ እጥፍ ድርብ ትርፍ የሚያመጣ ታክቲክ!። የሚገርመው ይህን ሁሉ ቀመር ማንም አላወቀም። 😊
@Armemo_offical | 2 172 |
| 14 | ከዛሬ ሦስትና አራት አመት በፊት ቴሌግራም ላይ የማወራው ነገር ዛሬ ሀላል ሲፈጸም ስመለከት «ብዬ ነበር» አላልኩም፤ ያስፈራልና ደነገጥኩ!። እንዲህ ያለ ነገር ሲገጥም ቃላት ብቻውን አይበቃም። ልቤ ድንጋይ ሆኖ ተፈረካክሶ ባለቀ የሚል ምኞት ነው ያደረብኝ። የማይገለጽ ሀዘን ውስጥ ነኝ ምክንያቱም ወገኔ ከአመት ወደአመት እንደቅጠል በገጀራ ተቆራርጦና በእሳት ተቃጥሎ ሲሞት ማየት ወደእብደት እያመራኝ ነው።
የእምነቴ ሰው ከጨዋታው ውጭህ ነህ። ዛሬ አገሪቷ በአንድ ብሔርና በአንድ ሃይማኖት ካፒታላይዜሽን ነው የምትንቀሳቀሰው። ቀስ በቀስ ቁጥርህ ወደታች አሻቅቦ ጎዳና አዳሪ እንደምትሆን ደሞ ዛሬ ልናገርና ከአመታት በኋላ ታረጋግጣለህ። ይህ በአንዱ ብቻ አይደለም በኢኮኖሚ፣ በግል መብት እና በፖለቲካ ጭምር ከጨዋታው እስከምትገለል የእነሱ ለማኝ ሆነ መቅረትህን ሳስበው ልብ የሚያቆስል በአፍ የሚመር ሀዘን ይወረኛል።
ቤተክርስቲያኖች ሲቃጠሉ እኛ የምናየው እሳቱን ነው፤ ነገር በዛ መቅደስ ውስጥ ብዙ ትውስታ አለ፣ ብዙ መፅሐፍቶችና ንዋየ ቅዱሳት አሉ። የቆሎ ተማሪና የትንንሽ ህፃናት ድምፅ በጥይት ሩምታ ጸጥ ሲል የሚጠፋው ድምፅ ብቻ አይደለም፤ የወደፊት የእኛ የምንለው ብሔራዊ ተስፋችንም ጭምር ነው። እናቶች ሲበተኑ እዕቶች ሲደፈሩ ትንሽ ጉዳት አይደለም። ይህ ከአውሬነትም ያለፈ የግፈኞች ሴራና የሀገር መፍረስ ምልክት ነው። «Grief is the price we pay for love»— Queen Elizabeth II
«ሁሉም ነገር ለበጎ ነው» የምትል ጥቅስ ሁሉንም ነገር ውጥንቅጡ እስከሚወጣ የክፉ መፈንጫ አደረገችን። ነገን መጠበቅ ዛሬን እንደማያኖር ምስክርነት ይሆን ዘንድ የእለት እንጀራውን ሊጠይቅ ቤተመቅደስ ፊት ለፊት ያቀረቀረው የልጆች አባት ዝቅ ባለበት አንገቱን በአክራሪዎች ገጀራ ተነርቶ ሞተ!። ይፈርዳል እያልን ፈራጁ በዛብን። የሰማይ ቤትን በማሰብ የምድር መብታችንን ተነጠቅን። ይጠግባሉ ብለን ጠቦትና ግልገሎቻችንን ለአውሬ ሰጠን፤ ይህ አውሬ ግን ሊበላን እኛኑ በእሳት አስቀመጠን!።
የምንጠብቀው ብርሃን የለም፤ ደመናዋ በንጹህ ደም ቀልታለች። ጨለማውም ቤቱን ሰርቷል። ዝምታችን ለመቃብራችን የተመቻቸ ቃላት ሆኗል!። እረኞች እንደድሮ ታማኝ አይደሉም፤ በጎቻቸውን ለተኩላ አሳልፈው ሰጥተዋል!።
ሆድ አደር አባቶች በልጆቻቸው ሞት ሰርግ ደግሰው አርብን ገደፉ፤ አልቀናል ስንል ክርስቲያን ምትል ጥቅስ እየጻፉ!። ኦርቶዶክስ መታጠቅ አለባት!። ኦርቶዶክስ የራሷን ሰራዊት ማቋቋም አለባት። ቤተክርስቲያን ዝም ብሎ አይቃጠልም። እንዲቃጠል ያዘዘው አካል ጅል አይደለም። አገሪቷ ካከማቸችው ሃብቶች ከ50% በላይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ተቀምጧል። ከዘረፉ በኋላ ነው የሚያቃጥሉት። የሚያቃጥሉትም ዘረፋ ሳይሆን አመጽ እንደሆነ ለማሳወቅ ነው!። ዝም ብሎ መግደል አያስደስትም!። በግብር ያልጠገበ በዝርፊያ ይሰማራል። ከፊት ሱፍ አጊጦ ከጀርባ እንደወንበዴ ክላሽ ይዞ ይመዘብራል።
እኔ በመንግስት እና ባልታወቁ አካላት ላይ አልፈርድም የምፈርደው የሰው ጅብ በሆኑ አባቶቻችን ላይ ነው። የእራሳቸው ስልጣን ሲነካ ማይክ ለሚጨብጡ የንጹህ ደም ሲፈስ አፍ የሚለጉሙ እራስ ወዳድ፣ ስግብግብ፣ የአስቆሮቱ ቀሳውስት!። በቀሚሱ እጣ ጥለው የሚነግዱ፤ የሚውሉበት መቅደስ ከመብዛታቸው ቁማር ቤት ለመሰላቸው በጠቅላላ እግዜር ይፈርዳል አልልም!። የእግዚአብሔር ፍርድ ገና ነው።
እንደሀገር ለመቆም ሃይማኖትህን፣ ሃብትህን፣ መፅሐፍቶችህን እና ትውፊትህን ለመጠበቅ ኦርቶዶክስ ሆይ ታጠቅ!። ኦርቶዶክስ ሆይ ታጠቂ፤ ማንነትሽን ምንነትሽን ጠብቂ!። ለራስሽ ራስሽ!።
@Armemo_offical | 2 125 |
| 15 | بدون متن... | 1 735 |
| 16 | ብቸኝነትን ወይም መሰላቸትን መቋቋም የማይችል ትውልድ ሳይኮሎጂካል ኢማቹሪቲ፣ ኢሞሺናል ኢማቹሪቲ ያለበት Infantile Generation ነው። ሰው መሰላቸት ሲሰማው ከዛ ለመውጣት የሚያደርገው ነገር ሌላ ችግር ይዞበት ነው የሚመጣው። ስልካችን ለምን ያህል ግዜ ከእጃችን እርቆ ይቀመጣል?። ስልካችን እጃችን ላይ ቢሆን እራሱ ማህበራዊ ሚድያ ሳንገባ ምን ያህል ቀናት እንቆያለን?።
አለማችን ውስጥ በወጣትነት ወይም በጎልማሳነት እድሜ ሕፃናዊ ባህሪ ያላቸው ሴት እና ወንዶች እንደአሸን በዝተዋል። እነዚህ childish generation በአስተሳሰብና በስሜት ቀለል ያሉ ቢመስሉም የተረጋጋ ልቦና የሚጠይቁ የሕይወት ዘገምተኛ እና ተፈጥሯዊ ጫናዎች መሸከም የማይችሉ ደካማ ሰዎች ናቸው።
ለጥቂት ሰከንድ የዝምታ ወይም የባዶነት ቅጽበት ውስጥ ሲገቡ ከውሃ እንደወጣ ዓሣ መተንፈስ ይቸገራሉ። ስለዚህ የፈጠነ ወደ ስክሪኖች ጫጫታ ለመመለስ ይሯሯጣሉ። የተፈጠረባቸውን ችግር ከመፍታት ይልቅ ፈጣን መዝናኛዎችና ጊዜያዊ ደስታዎች ውስጥ መደበቅ ይመርጣሉ።
አንድ ሰው የሚያሰለቸውን ነገር የመቋቋም ችሎታ እያጣ ሲመጣ የውስጡን ጥንካሬ አብሮ ነው የሚቀዘቅዘው። ታድያ ቀስ በቀስ ጭር ያሉ የዝምታ ጊዜዎችን የማይታገስ ይሆናል። ያኔ ነው የሌሎች ፍላጎቶች እና የራሱ ፈጣን ምኞቶች ባርያ የሚሆነው። ከራሱ ጋር ቆሞ ለመኖር ወይም ስለ ሕይወቱ ትርጉም በጥልቀት ለማሰብ አቅም ያጣ ልፍስፍስ ሰው ይሆናል።
ነገር ግን ይህ የመሰልቸት ባህሪን ለጥቂት ቅጽበታት ካስተዋልነው የለውጥ መንገድ ይሆነናል። ሐሳቦቻችንን እንደገና እንድናደራጅ የሚረዳን ዕድል ፈንታ ይሰጠናል። ራሳችንን በጥልቀት እንድናውቅ፣ እንዲሁም ለታላላቅ ፈጠራዎችና ጥልቅ ሐሳቦች የተሰጠን ያደርገናል። የምሬን ነው የመሰላቸትን እውነተኛ ዋጋ እንደገና ማግኘት ከቻልን ወደ እውነተኛው ተፈጥሯችን ብሎም ወደ ውስጣዊ ሚዛናችን ይመልሰናል። ያኔ ከማያልቀው ሽሽት እርቀን ሕይወትን በቀጥታ ለመጋፈጥ የሚያስችለንን ጥንካሬ እንደገና እንገነባለን። መሰለቸት የአንድ ነገር ድግግሞሽ ምልክት ሲሆን፤ ይህ ስሜት ከዚህ ውጣና አዲስ ነገር ፍጠር የሚል መልዕክት በውስጡ ተሸክሟል!።
@Armemo_offical | 1 960 |
| 17 | °°ሞኝ በጥንካሬው ሲኮራ ብልህ ከድክመቱ ይማራል.. | 1 875 |
| 18 | ኸረ ቲክቶክ ላይ ፎሎ አድርጉ ሞራል አትግደሉ፤ ከስር ያለውን username search ባሩ ውስጥ ከጻፋችሁ ወዲያው እከሰታለሁ 👇🏽
@imaging_gurus | 3 628 |
| 19 | Check out Guru's video! #TikTok https://vm.tiktok.com/ZS92fkKfCX6kE-p7NxD/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite | 1 |
| 20 | ሙሉውን ዘፈን ኮመንት ላይ አስቀምጡ👇🏽
@Armemo_offical | 2 417 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
