fa
Feedback
ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ

رفتن به کانال در Telegram

✨Philosophy For Higher Consciousness✨

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ

کانال ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ (@zephilosophy) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 31 998 مشترک است و جایگاه 2 106 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 088 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 31 998 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 03 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 380 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 24 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 28.34% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.87% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 9 069 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 198 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 133 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
✨Philosophy For Higher Consciousness✨

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

31 998
مشترکین
+2424 ساعت
+1147 روز
+38030 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '26
سپتامبر '26
+49
در 0 کانال‌ها
اوت '26
+466
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '26
+407
در 2 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '26
+409
در 5 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+283
در 6 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+184
در 2 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+134
در 3 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+149
در 5 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+171
در 3 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+177
در 2 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+234
در 2 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+229
در 1 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+633
در 2 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+444
در 5 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+281
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+289
در 3 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+376
در 4 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+307
در 11 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+384
در 6 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+340
در 3 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+753
در 5 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+2 069
در 10 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+994
در 6 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+1 978
در 6 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+1 137
در 4 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+1 133
در 9 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+924
در 6 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+170
در 2 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+772
در 7 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+811
در 5 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+352
در 2 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+2 121
در 11 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+305
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+437
در 3 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+229
در 4 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+116
در 2 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+118
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+224
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+247
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+232
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+183
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+279
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+196
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+183
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+1 205
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+271
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+346
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+387
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+325
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+2 113
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+947
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+424
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+1 160
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+568
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+602
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+510
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+743
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+817
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+1 004
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+1 462
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+1 602
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+299
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+219
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+280
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+269
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+420
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+232
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+248
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+1 240
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
04 سپتامبر0
03 سپتامبر+24
02 سپتامبر+11
01 سپتامبر+14
پست‌های کانال
የስነ ልቦና ህክምና ዋና አላማው ግለሰቦችን ማከም እና ወደ ማህበረሰቡ መደበኛ የእለት ተእለት እንቅስቃሴ መመለስ ነው። ነገር ግን አንድ ግለሰብ ሊላመደው የሚገደደው ማህበረሰብ ራሱ በበሽታ የተበከለ ቢሆንስ? ችግሩ ያለው ስቃይ ላይ ባለው ግለሰብ አእምሮ ውስጥ ሳይሆን እብደቱን እና ስቃዩን በማምረት ላይ ባለው የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መዋቅር ውስጥ ከሆነስ? ​እንደ Michel Foucault እና Erich Fromm ያሉ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያዎች እንደሚከራከሩት ዘመናዊው ማህበራዊ መዋቅር ሰዎችን ከተፈጥሮአዊ ማንነታቸው ከእውነተኛ ፍላጎቶቻቸው እና ከሌሎች ሰዎች ጋር ካላቸው ጥልቅ ግንኙነት ይነጥላቸዋል። ማህበረሰቡ ለውድድር፣ ለቁሳቁስ መሰብሰብ፣ ለውጫዊ ስኬት እና ማለቂያ የሌለው ድካም የሚሰጠው አክብሮት ሰዎችን ማሺን እንዲሆኑ ያስገድዳቸዋል። ​በዚህ አስከፊ የውድድር ሂደት ውስጥ የአእምሮ ጭንቀት ፣ ድብርት እና የባዶነት ስሜት መፈጠሩ ተፈጥሮአዊ ምላሽ እንጂ የግለሰቡ ጉድለት አይደለም። አእምሮው ለሚደርስበት መዋቅራዊ ጫና የሚሰጠው ጤናማ ተቃውሞ ሲሆን የ ስነ ልቦና ህክምናው ግን ይህንን ተቃውሞ እንደ በሽታ በመቁጠር ግለሰቡን መድኃኒት አሸክሞ እንደገና ለዚያው ጎጂ ስርዓት ብቁ ለማድረግ ይጥራል። ህንዳዊ ፈላስፋው ጂዱ ክሪሽናሙርቲ እንዳለው በጣም በታመመ ማህበረሰብ ውስጥ  መላመድ ወይም እንደነሱ መሆን የጤናማነት ምልክት አይደለም። ​ይሁን እንጂ ጉዳዩን ሙሉ በሙሉ በማህበረሰቡ ላይ ብቻ መጫንም ሌላኛው አደገኛ እይታ ነው። በአንድ በኩል የሰው ልጅ ባዮሎጂያዊና አእምሮአዊ የኬሚካል መዛባቶች  ወይም የዘር ውርስ ተፅዕኖዎች በግል ህክምናና መድኃኒት መታገዝ እንዳለባቸው የማይካድ እውነታ ነው። ​ነገር ግን ዋናው ችግር የሚፈጠረው የህክምናው ዘርፍ ሁሉንም የሰው ልጅ የስነ ልቦና ስቃይ ወደ ባዮሎጂያዊ ምክንያት ብቻ ሲያሳንሰው ነው።  ብቸኝነት የኢኮኖሚ ውጥረት፣ የመደብ ልዩነት እና ትርጉም አልባ ልፋት ሰዎችን አእምሯዊ ስቃይ ውስጥ ሲከቷቸው መፍትሔው ማህበራዊ ሁኔታዎችን መቀየር እንጂ ግለሰቡን ብቻ ማስተካከል ሊሆን አይችልም።  ዘመናዊ የምንለው  ማህበረሰብ አእምሮአዊ ህመምን የሚያመርቱ ሁኔታዎችን እያፋጠነ በሌላ በኩል ደግሞ ከሲስተሙ ጋር ያልተግባቡትን ወይም ሲስተሙን ያልተቀበሉትን ሰዎች እንደ ጨለል መረዳቱ የተለመደ ነገር ሆኗል። መሆን ያለበት  ግለሰቡን እንደ ጨለል ማየቱን አቁመን የሚያበሳጨውንና እና የሚያናድደውን ማህበራዊ መዋቅር ለመፈተሽ ስንደፍር ብቻ ነው። ማህበረሰቡ ራሱ ህመምተኛ በሆነበት አለም ውስጥ ጤናማ መሆን እና አጉል ነገሮችን አልቀበልም ማለት ለሁኔታው የምንሰጠው ምላሽ እንጂ እ ብ ደ ት አይደለም። ያሬድ ግርማ @zephilosophy

2
بدون متن...
2 901
3
"የአንድ የሞራል ልሽቀት የገጠመው ትውልድና ማህበረሰብ ምልክት ለሀገርና ለህዝብ የሚጠቅም የምርምርና የእውቅት ብርሃን ከሚያበሩለት እንዲሁም የበጎ ስራ ከሚሰሩ ብልህ ልሂቃን ይልቅ በቀልድና በማይረባ ወሬ ግዜው እየገደሉ ለሚጫወቱበት የበለጠ ክብርና ትኩረት ሲሰጥ ሲታይ ነው።" ፊዮዶር ዶስቶቪስኪ @zephilosophy
4 075
4
"እነሆ አንቺ ውብ ነሽ። እንደመኖር ታስፈሪያለሽ። እንደ ትርጉም ታማልያለሽ። ጸጉርሽ ከኪዮራን ቃላት ይጠቁራል። አይንሽ ከመሆን ጥያቄ ይጠልቃል፣ ከዳንቴ ሃሳብ ይርቃል። ከንፈርሽ ከሶፎ ስንኝ ይጥማል። አንደበተሽ ከሼክስፒር ተውኔት ይረቃል። አዕምሮሽ እንደ ራንድ ነጻነት ኃያል፣ እንደ ራስል አመክንዮ የጠራ፣ እንደ ሶቅራጥስ ጥያቄም እረፍት አልባ ነው። መገኘትሽ እንደኒቼ ገደል ጥልቅ፣ ዝምታሽም እንደ ቡድሃ መንፈስም የሰከነ ነው።...አንቺ የፕላቶ ውበት፣ የኢፒኩረስ ደስታ፣ የሆሜር ግጥም፣ የቤቶቨን ሙዚቃ ነሽ።...." ✍️ ዮንታን አቢስ @zephilosophy
5 462
5
መማር ከማሰብ ጋር እኩል አይደለም ....  የኢትዮጵያ “ምሁራን” ፈተና አንዳንድ ጊዜ የአንድን ሕዝብ የአስተሳሰብ ደረጃ ለመለካት የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ማየት ብቻ ይበቃል። ዓለም በArtificial Intelligence፣ በኳንተም ኮምፒውቲንግ፣ በሮቦቲክስ፣ በጂን ቴክኖሎጂ፣ በንጹሕ ኃይልና በሕዋ ምርምር ስለሚመጣው ሃምሳ ዓመት ሲያስብ፣ እኛ ግን በ2026 ቆመን “ይህች ከተማ የማን ናት?”፣ “ይህ መሬት በፊት የማን ነበር?”፣ “የማን አያት ቀድሞ ኖረበት?” ብለን ወደ ኋላ እያየን ነው። የትናንትን ቁስል ማወቅ አስፈላጊ ነው፤ በቁስሉ ውስጥ ቤት ሠርቶ መኖር ግን የወደፊት ፖለቲካ አይደለም። ዛሬ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቁ ችግር የሐሳብ እጥረት ነው። በተለይም የተማረው ክፍል ከሕዝቡ አንድ እርምጃ ወደፊት መሆን ሲገባው፣ አንዳንዴ ከሕዝቡ አንድ ምዕተ ዓመት ወደኋላ ቆሞ ይታያል። PhD ይኖረዋል፤ የሚያስበው ግን ስለ ጎሳ ድንበር ነው። ፕሮፌሰር ይሆናል፤ ጥያቄው ግን “የማን መሬት?” ላይ ይቆማል። በአውሮፓና በአሜሪካ ዘመናዊ ተቋማት ውስጥ ይሠራል፤ ለኢትዮጵያ ሲያስብ ግን የ21ኛውን ክፍለ ዘመን መሣሪያ ይዞ የ19ኛውን ክፍለ ዘመን ጦርነት ይዋጋል። ዲግሪ አእምሮን በራሱ አያሰፋውም፤ ሰፊ አስተሳሰብ የሚጀምረው ከጎሳ አጥር ባሻገር ማየት ስንችል ነው። አስቡት። በ2050 የተወለደ ኢትዮጵያዊ ልጅ በ2075 ወደዚህ ዘመን ታሪክ ቢመለስ ስለ እኛ ምን ይላል? “እነዚህ ሰዎች አገሪቱ 120 ሚሊዮን ሕዝብ ስትሆን፣ ወጣቶች ሥራ ሲፈልጉ፣ ገበሬው ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ሲፈልግ፣ ሕፃናት ጥሩ ትምህርት ሲፈልጉ፣ አገሪቱ ኢንዱስትሪና ሳይንስ ስትፈልግ፣ ምን ላይ ነበር የሚከራከሩት?” ብሎ ሲጠይቅ፣ መልሳችን “አዲስ አበባ የማን ናት ብለን ነበር” ከሆነ፣ ታሪክ ለእኛ የሚሰጠው ፍርድ ከባድ ይሆናል። አብርሃም ሊንከንን ዛሬ የምናስታውሰው የዘመኑን ትንሽ ፖለቲካ ተከትሎ ስለኖረ አይደለም። ከዘመኑ በላይ ማየት ስለቻለ ነው። ታላላቅ መሪዎች የሕዝብን የዛሬ ቁጣ ብቻ አይሰሙም፤ ገና ያልተወለደውን ትውልድ ዝምታም ይሰማሉ። የኢትዮጵያም መሪ፣ ምሁር፣ ጋዜጠኛ፣ አክቲቪስትና ወጣት ዛሬ ራሱን መጠየቅ ያለበት፦ “ለሚቀጥለው ምርጫ ምን ይጠቅመኛል?” ሳይሆን “ለሚቀጥሉት ሁለት ትውልዶች ምን አገር እተዋለሁ?” የሚለውን ነው። TikTok ላይ 60 ሰከንድ በሚቆይ ቪዲዮ ሕዝብን ማስቆጣት ቀላል ነው። Facebook ላይ አንድ ብሔር ሌላውን እንዲጠራጠር የሚያደርግ ሐረግ መጻፍም ቀላል ነው። ከባዱ ነገር ግን የተቆጣን ሕዝብ ወደ ማሰብ፣ የተከፋፈለን ሕዝብ ወደ መነጋገር፣ በትናንት የተያዘን ትውልድ ወደ ነገ ማዞር ነው። የኢትዮጵያ ምሁራን ሥራ የማኅበራዊ ሚዲያውን ቁጣ በትልቅ ቃላት ማስተጋባት ሳይሆን ሕዝቡ ገና ያላየውን አድማስ ማሳየት ነው። ስለዚህ ዛሬ ለኢትዮጵያ አዲስ ጥያቄዎች እንጠይቅ። በ2050 የኢትዮጵያ ልጅ በዓለም ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች ከሚማሩ ልጆች ጋር እንዴት ይወዳደራል? ኢትዮጵያ 150 ወይም 200 ሚሊዮን ሕዝብ ሲኖራት እንዴት ትመግበዋለች? ውሃዋን እንዴት ታስተዳድራለች? ሥራ እንዴት ትፈጥራለች? AI የሚቀይረውን የሥራ ዓለም እንዴት ትቀበላለች? አዲስ አበባን ከዘር ፖለቲካ ውድድር አውጥተን የአፍሪካ ዋና የፈጠራ፣ የዲፕሎማሲና የንግድ ማዕከል እንዴት እናደርጋታለን? እነዚህ ለትልቅ አገር የሚመጥኑ ትልልቅ ጥያቄዎች ናቸው። የሚቀጥለው ታላቅ የኢትዮጵያ ፖለቲከኛ ስለ ትናንት ብዙ የሚያውቅ ብቻ አይሆንም፤ ሌሎች ገና ያላዩትን ነገ የሚያይ ሰው ይሆናል። የሚቀጥለው ታላቅ ምሁርም ለብሔሩ የተሻለ ክርክር የሚያቀርብ ሳይሆን ብሔሮች ሳይፈሩ አብረው የሚኖሩበትን ሥርዓት የሚያስብ ይሆናል። ከ50 ዓመት በኋላ ዛሬ የምንጣላባቸው ብዙ ነገሮች የታሪክ ግርጌ ማስታወሻ ብቻ ሊሆኑ ይችላሉ። ዛሬ የምንገነባቸው ተቋማት፣ ትምህርት፣ ሕግ፣ ኢኮኖሚና የጋራ ማንነት ግን የልጅ ልጆቻችንን ሕይወት ይወስናሉ። ስለዚህ ጥያቄው “ኢትዮጵያ የማን ናት?” መሆን የለበትም። ጥያቄው፦ “ለልጆቻችን ምን ዓይነት ኢትዮጵያ እንተዋለን?” የሚል መሆን አለበት። ትንሽ ፖለቲካ የሚጠይቀው፦ “የማን ነው?” ታላቅ ፖለቲካ የሚጠይቀው፦ “ምን እንገንባ?” ኢትዮጵያ በቂ ታሪክ አላት። አሁን የሚያስፈልጋት የወደፊት ሐሳብ ነው። ፀሀፊ-መኮነን ቢሩ @zephilosophy
8 147
6
"ፍርሀትን ራሱን ማርበድበድ" ያዕቆብ ብርሀኑ ይህችን ዓለም አንቀጥቅጦ የሚገዛት ፍቅር፣ ገንዘብ፣ ሞት፣ ስልጣን ወይስ ፍርሃት? መልሱ ሙዝ የመላጥ ያህል ቀላል ነው፡፡ ይህችን ዓለም በበላይነት የሚያስተዳድራት ፍርሃት ነው፡፡ ከስልጣን መውረድን መፍራት፣ ውርደትን መፍራት፣ እጦትን መፍራት....ፍርሃት፣ ፍርሃት፣ ፍርሃት... ብዙ መልኮች ያሉት ፍርሃት፡፡ ራሳችሁን ነፃ አድርጋችሁ ይህችን ግብስብስ ዓለም ብትመለከቷት፣ ሰብዓዊያን በሙሉ ይህን የፍርሃት ነውጥ በመሸሽ፣ እንደ ዶሮ ጫጩት ሲተራመሱ ማየት ትችላላችሁ፡፡ ሌላው ቢቀር የኤሊ ቆዳ ሻካራነት ስያሜ ማጣት ቢያሳስበን መልስ ለመሻት ‹‹በድሮ ጊዜ ኤሊ ከአእዋፋት ጋር ለግብዣ ሰማይ ቤት ተጠርታ...›› የሚል ለዛ ቢስ ተረት መፈጠሩን ወደድን፡፡ እንዲህ ከሆነ የዚህች ዓለም ጌታን ማንነት ጥያቄ ለመመለስ አዕላፍት መላምታዊ መልሶች ቢፈጠሩ የሚደንቅ አይሆንም። ለሕይወት የዋህ አረዳድ ያለው አዕምሮአችን እንጂ ኃያል አስመስሎ የሚያሳየን፣ የሰው ልጅ እኮ ፈሪና ድንጉጥ ፍጡር ነው፡፡ ንጉሥ ቄሳር ካሊጉላ፣ በተውኔቱ መሃል በአንድ ቃለ ተውኔቱ ላይ፡- "ፍርሃት በካባው ውስጥ ያለውን ሰው ማንነት ያሳያል፡፡" ይላል፡፡ ለመሆኑ የምንፈራው ምንድን ስለምንስ ነው? ኢየሱስ በዚያች የጸሎተ ሐሙስ አመሻሽ ‹‹አባት ሆይ ፈቃድህ ቢሆን ይህቺ ጽዋ ከእኔ ትለፍ፡፡›› እንዲል ወደ አብ እንዲጮህ የገፋፋው ምክንያት በእርግጥ እርሱ ፍርሃት አልነበረምን? ያለ የጅራፉ ንቅሳት፣ ያለ የችንካሩ ሕማም አዳኝነቱስ የሚቻል ነውን? እንደ አቡነ አትናቲዎስ፤ (ከ327-373 ዓ.ም ግብፅ አቡነ ሰላማን ቀብተው የላኩት) መላውን ዓለምን መቃወሙስ ይቅር፡፡ እንዴት ሰው በማያምንበት ነገር ላይ የቅርብ አለቆችን እንኳን መቃወም ይሳነዋል? በ325 ዓ.ም በኒቂያ ጉባኤ “ክርስቶስ ሰው እንጂ አምላክ አይደለም” የሚለው የአርዮስ አስተሳሰብ ተወገዘ፡፡ ከሁለት ዓመታት በኋላ የጳጳሱ አቡነ እስክንድርን ህልፈት ተከትሎ፣ አቡነ አትናቲዮስ መንበረ ስልጣኑን ተረከቡ፡፡ ጥቂት ዓመታት ቆይቶ አርዮስ የነገሥታቱን ይሁኝታ በማግኘት አቡነ አትናቲዮስን ለብቻቸው በደሴት ውስጥ አሳሠራቸው፡፡ በዚህ ወቅት ከአንድ ወዳጃቸው ‹‹The whole world is against you›› በሚል ለተላከላቸው መልእክት ሲመልሱ ‹‹If the world goes against the truth, then Athunasius will goes against the world›› ብለዋል፡፡ ‹‹ዓለም እውነቱን መቃወምን ከመረጠ አትናትዮስ ዓለምን ይቃወማል›› እንደማለት፡፡ የብርሃኑ ድንቄ አልቦ ዘመዳዊ ‹‹እምቢ አሻፈረኝን ካልተለማመድክ መኖርን አታውቃትም፡፡›› ገደምዳሜ ምክር እዚች ጋ በገቢር ይሠራል፡፡ ግን ስንቶቻችን መላው ዓለም ቀርቶ በቅርብ አለቆቻችን፣ አስሮ ባስቀረን ፍርሃታችን ላይ እምቢ አሻፈረኝ እንላለን? መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ሰው ሰው የመሆን ህሊናውን ያገኘው በመተላለፉ አመጽ ውስጥ በበለስ ፍሬዎች መካከል ነበር፡፡ ለዚህም አሻፈረኝ ባይነቱ ማርና ወተት ከሚፈስባት ኤደን ገነት ወደ እሾህና አሜኬላ የሚበቅልባት ምድር ተግዟል፡፡ እዚች ጋ ቆም ብለህ የጆን ስትዋርት ሚልን ‹‹lt is better to be a human being dissatisfied than a pig satisfied. Better to be Socrates dissatisfied than a fool satisfied. ›› የምትል አባባል አስበህ እንኳንም አትልም! ፍርሃት ግን መልኩ ገጹ፣ መከሰቻ ግብሩ እልፍ ትዕንግርት ነው፡፡ ቪንሰንት ቫንጎ በጥቅምት 2፣ 1884 እ.ኤ.አ ለወንድሙ ቲዮ በጻፈለት ደብዳቤ ላይ እንዲህም አለ የሚያስብል የሠዓሊንን የልሙጥ ሸራ ፍርሃት አንስቷል፡፡ <<<If one wants to be active, one mustn't be afraid to do something wrong sometimes, not afraid to lapse into some mistakes.... Many painters are afraid of the blank canvas, but the blank canvas IS AFRAID of the truly passionate painter who dares and who has once broken the spell of «you can't.» Life itself likewise always turns towards one an infinitely meaningless, discouraging, dispiriting blank side on which there is nothing, any more than on a blank canvas.» በእርግጥም ደፍረው የመጀመሪያውን የብሩሽ ጥፊ እስኪያሳርፉበት ውጥሩ ሸራ እንኳን አተያዩ የጠበኛ፣ የወደረኛ ዓይነት ይሆናል፡፡ የሥነ ተረቱ ሰው ጆሴፍ ካምቤል ‹‹ሕይወት ራሷ የምትጀምረው ከአመጽ (act of disobidence) ነው›› ይላል፡፡ ትልቁ ጠላታችን ያለው እኛነታችን ውስጥ ነው፡፡ የማንነታችን አክናፍ በእጆቻችን እንዳንሠራ መሰናክል የሆነን ትልቁ አውሬ ያሸመቀው እኛነታችን ተጣብቆ ነው፡፡ መፍራትስ ሺኅ የገደለውን አይደለም፡፡ ፍርሃቱን ያሸነፈውን እንጂ...ፍርሃቱን ጠፍንጎ አስሮ ለራሱ ለፍርሃት ላስረከበ ለእርሱ እንኳን ውጥሮ ሸራ ምድር ትርበታበታለች፡፡ በማይናወጡ ጽኑ ዓይኖች አንበሳውን መማተር የሚችሉ የማሳያ ጎሳዎች ያለምንም መሰንዘር ከአንበሳው መንጋጋ ስጋን ያስጥላሉ፡፡ ስብሃት ከሕልፈቱ በፊት እንደከተበልን በተለፈፈላት መልዕክቱ ‹‹ተዘጋጀህም አልተዘጋጀህም ጥሪው እንደሁ አይቀርልህ..›› ብሏል፡፡ እናስ ድፈር እንጂ ባይሆን የምር ኖረህ ሞትህ የጀግና ማድረግ ነው፡፡ ራሱ አልበርት ካሙ በ‹‹Happy death ልብወለዱ እንደነገረን አንዳንድ ጊዜ ራስን ከማጥፋት ይልቅ ራስን ማሰንበት የበለጠ ጀግንነት ይፈልጋል፡፡ @zephilosophy
10 227
7
አገራዊ ሰርግ ተዘጋጅቷል። ሞት የሚወለድበት ድግስ ተደግሷል። ድንቁርናና መንበር ተጋብተው ሞትን ወለዱ። አሁንም አላዋቂነትና ስልጣን ተጋብተው በላይ በላዩ ሞትን ይወልዳሉ። ዛሬም ብሔራዊ ድግስ አለ፥ መንበርና ድንቁርና ዳግመኛ ይጣመራሉ። ከሰርጉ በኋላ ሞት ይወለዳል። "እናት አባት ሲሞት በአገር ይለቀሳል እህት ወንድም ሲሞት በአገር ይለቀሳል አገር የሞተ ቀን ወዴት ይደረሳል" ማልቀስ እፈልጋለሁ። ትውልዴን የሚወክል እንባ ማፈሰስ እመኛለሁ። አንች ከፈቀድሽልኝ ማቅ እለብሳለሁ ፥ ደረት እደቃለሁ፥ ፀጉር እነጫለሁ፥አመድ በላዬ ነስንሼ "ወየው" እላለሁ። ማልቀስ ፍቀጂልኝ። በእኔ ላይ ያለሽን ስልጣን ተጠቅመሽ እንዳለቅስ እዘዢ። "እየፈረሰች ስላለች አገርህ አልቅስ ፥ ስለዘመመው ብሔራዊ ጎጆ እንባህን አፍስሰ" በዪኝ። ተመልከች አገሩን ስካር ከጠመንጃ ተባበሩ። መንበርና ጥላቻ ተዳመሩ። ተጣምሪዎቹ በእጃቸው ያለውን ስል ሰይፍ ለሞት አዳይ መልዓክ አቀበሉ። የሞት መልዓክ ለማንም አልራራም። ሰይፉን ከሰገባው መዘዘ። አሰላሳይ አንጎል የተሸከሙ አንገቶች ተቀሉ። ሰው ረከሰ፥ ሰውነት ፈረሰ። በየሜዳው ሬሳ ተከመረ። ተመልከች አገሩን። በኛና በፖለቲከኞቻችን መካከል ያለው ግኑኝነት የዲዳና የእውር ነው። ችግራችንን እንዳናስረዳቸው መናገር የተሳነን ነን። ሁኔታችንን አይተው እንዳይገነዘቡ ማየት የማይችሉ ናቸው። ዝናብ አልነበረም፥ ሰፈራችን ግን ጨቅይቷል። መሬታችንን ያጨቀየው የሰው ደም ነው። የደም ኩሬ ሲፈጠር ፥ ሬሳ እንደ ቆሻሻ ሲከመር ፥ ሰው ከቁስ በታች ሲሆን ማልቀስ የለብኝም? ማልቀስ እፈልጋለሁ። ደረት እየደቃሁ ፥ ፀጉር እየነጨሁ ፥ ልብሴን እየቀደድኹ ማልቀስ እፈልጋለሁ። ብዕሬን ያነሳሁት ናፍቀሽኛል ልልሽ ነበር። አይንሽን ካየሁት ስንት ዘላለም ሆነኝ? ጡትሽን አይቼ ከተገረምኩ ስንት ዘላለሞች ነጎዱ? በደቂቃ ሽራፊና በዘላለም መካከል ያለሽው ልዩነት አንቺ ነሽ። ካንቺጋ ስሆን ዘላለም ጥቂት ነው። ያላንቺ የማሳልፈው አንድ ቀን ከዘላለም ክምር ትኬሻ ይለካካል። ድምፅሽን ከሰማሁት ስንት ዘላለም አለፈ? አይንሽን ካየሁት ስንት ዘላለም ተቆጠረ? በጡትሽ ከተገረምኩ ስንት ዘላለም ነጎደ? በፀጉርሽ ከተደነቅኹ ስንት ዘላለም ሆነ? "ናፍቀሽኛል" ልልሽ ብዕር ባነሳም ናፍቆቴን ልነግርሽ አቅም አጣሁ። በየሜዳው የወደቁ ታናናሾቼ አጥንት መንፈሴን ወጋ። ሀዘን ሸነታተረኝ። ስለ ውብ ጡቶችሽ እያሰብኩ ፈገግ ባልኩበት አፍታ ፥ ደመ ከልብ የሆኑ እኩዮቼ በአይኔ ተሳሉ። ፈገግታዬ ከሰመ፥ አይኔን እንባ ጋረደው። እውድሽ አይደል? ዘመን ነው ጠላታችን። እንዲህ ባለ ደም አፍቃሪ ዘመን መፈጠር አልነበረብኝም። ዘመኔ ሌላ ቢሆን ኖሮ ሰማይ በሚያክል ብራና መወድስ እፅፍልሽ ነበር። ያለነው ሰው በረከሰበት ዘመን ባይሆን፥ ለሰማይ አዕፋት ስላንቺ እተርካለሁ። "የውዴን ድምፅ ስሰማ እታደሳለሁ፥ ድምጿ መድሃኒቴ ነው" ብዬ እናገር ነበር። በዛፎች መካከል ተገኝቼ ስለ ፀጉርሽ እተርክ ነበር። ነበር... ዘመን ነው ጠላቴ። ፍቅሬን ልነግርሽ ብዕር ባነሳሁበት አፍታ፥ በየሜዳ የወደቁ ታናናሾቼን እያሰብኩ እንዳለቅስ ያደረገኝ ዘመን ጠላቴ ነው። ለከንፈርሽ መወድስ ላቀርብ ስዘጋጅ ፥ በየሜዳ የፈሰሰ ደም አስባለሁ። ተመልከች አገሩን ጎበዙ እንደዘበት በወጣበት ቀርቷል። ወላጅ ጧሪ ልጁን በዋዛ ቀብሯል። የሀዘን ስል ካራ እናትን ገደለ። የመሞትን ተራ አባት ተከተለ። ተመልከች አገሩን በአገሩ ድግስ አለ። ብሔራዊ ሰርግ ነው። ስልጣን ከድንቁርና ተጋብተዋል። የሞት መልዓክ ከሙሽሮቹ መግደያ ፍቃድ አግኝቷል። ገዳዩ ሰይፍን ከአፎቱ መዟል። ብርቱ ይቀጠፋል፥ አዛውንት ይወድቃል፥ ጎበዙ ይረግፋል ፥አዳጊ ይቀጫል። እባክሽ አለሜ ፥ ከዚህ ሁሉ መዓት አድኚኝ። መሄጃ የለኝም። መሸሸጊያዬ አንቺ ነሽ። በእቅፍሽ ስሆን እድናለሁ። እቅፍሽ የሀዘኔን ተራራ ይንደዋል።የፍርሄቴን አለት ይሰብረዋል። ከመከራ ይከልለኛል። ፍልሚያ እና መቀጠፍ ፥ በበዛበት ሐገር መሸሸጊያ ሁኚኝ ፥ በእቅፍሽ ልሰወር አለሜዋ፥ እንደማህተም በልብሽ እንደማህተም በክንድሽ አኑሪኝ። ፍቅር ከሞት የበረታች ናት Via ተስፋአብ ተሾመ https://t.me/Tfanos
10 418
8
ጥቂት ነጥቦች ስለአልኬሚ የረቂቁ አልኬሚ ፍልስፍና መስራች ስሙ ሐርሜስ ትሪስሜጊስተስ (Hermes Trismegistus) ይባላል፡፡ እግዚአብሔራዊ አረዳዳችን ላይ ከቀኖና የተሻገረ ረቂቅ አምልኮአዊ ፍልስፍና ካረቀቁ ሰዎች ቀዳሚው እሱ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ግብጻዊ ቢሆንም ግሪካዊያን የሚጠቀሙባቸውን 42 የሚደርሱ መጻሕፍት የጻፋቸው እርሱ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ሰውዬው ፍጹም የላቀ ሰው ነበር፡፡ የሳይንስ፣ የሐይማኖታዊ ዕሳቤዎች፣ ሒሳብ፣ ጂኦሜትሪ፣ አልኬሚ፣ ሕክምና፣ ፍልስፍና እና አስማት የመሣሠሉ ጥበባት ሁሉ መስራች መሆኑ ይነገርለታል፡፡ ሙሴ በእስራኤል ታሪክ ታላቁ ነብይ ሆኖ እስራኤላዊያንን ከአራት መቶ ዘመናት አገዛዝ ቀንበር ነጻ ከማውጣቱ በፊት ከኢትዮጵያዊው ዮቶር ሌላ በዚሁ ጥቁር ግብጻዊ ሐርሜስ ትሪስሜጊስተስ ክትትል እና አስተምህሮ ስር እንዳደገ የሚነገር ታሪክ አለ፡፡ በሌላ በኩል በመጽሐፍ ቅዱሳዊ አቆጣጠር፣ ከአዳም ስደት በኋላ ከጥፋት ውኃ  በፊት በግብጽ እንደኖረ የሚተረክም ሌላ የታሪክ ፈርጅ አለ፡፡ አንዳንዶች ትሪስሜጊስተስ ከጥፋት ውኃ በፊት የኖረው የመጽሐፍ ቅዱሱ ሔኖክ (የቅዱስ ቁርዓኑ እድሪስ) ነው ይላሉ፡፡ ሌሎች በአንጻሩ ሔርሜስ ትሪስሜጊስተለ ፈጠራ፣ ስያሜው ራሱ ከግሪኩ የጣዖት አምላክ ሔርሜስ እና ከግብጹ ቶት ተዳቀሎ የተገኘ ፍጹም ምናብ ወለድ ሰው ስለመሆኑ ይከራከራሉ፡፡ የዚህ ታላቅ ሰው ማንነት ላይ ዛሬም ድረስ ስምምነት የለም፡፡ የአልኬሚ ግርድፍ ጽንሰ ሀሳብ ይሄው ነው፡፡ ብረትን ሁሉ ወደ ወርቅ ምትቀይረውን ፈሳሽ መፈለግ፣ ዘለዓለማዊ ወጣት ለመሆን የምታስችለውን እጽ ማሰስ፡፡ ከኢየሱስ መወለድ በፊት ለሺህ ዘመናት የተፈራረቁት አልኬሚስቶች የሞትን መድኃኒት፣ ወይ ብረትን ሁሉ ወደ ወርቅ የምትቀይረውን ተዓምረኛ ድንጋይ ይፈልጉ ዘንድ ቃተቱ፡፡ ከእርሱ በፊት የፈለቁት የመጀመሪያዎቹ የአልኬሚ ጠቢባን ሁሉም ጽድቁም፣ ኩነኔውም፣ ጋኔሉም ያለው ውስጣችን መሆኑን ያወቁት አይመስልም፡፡ በኋለኛው ዘመን ብቅ ያሉ ክርስቲያናዊ የአልኬሚ ጠበብት እነ ሜይስተር ኤክሃርት ደግሞ መዳን ረቂቅ የአልኬሚ ሽግግር መሆኑን በተግባር ያሳየው ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ሰበኩ፡፡ እንደ እነዚሁ ክርስቲያናዊ ሚስቲኮች አስተምህሮ ፍጽምናውን መቀዳጀት የሚቻልበትን እውነተኛ መንገድ የቀየሰ መሲሁ ብቻ ነው፡፡ በእርግጥም እንደመጽሐፍ ቅዱስ ትረካዎች ኢየሱስ ራሱ አልኬሚስት ነበር፡፡ ከእናቱ ጋር በቃና ዘገሊላ በታደመበት ሰርግ ለሰርገኛው የሚቀርብ ወይን በተሟጠጠ ጊዜ ውኃውን ወደ ወይን ቀይሯል፡፡ በሌላ ጊዜ ጥቂት ቁራሽ ዳቦዎችንና ጥቂት ዓሶችን በበረከት አባዝቶ ሺዎችን መግቧል፡፡ አሁንም እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ትረካዎች ሽባዎችን፣ ድውያንን ፈውሷል፡፡ ይህ ለሺህ ዘመናት የተንከራተቱ አልኬሚስቶች ሁሉ ምኞት ነበር፡፡ ብረትን ወደ ወርቅ፣ ውኃን ወደ ወይን፣ ሞትን ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት መቀየር.. ከኢየሱስ መወለድ በኋላ በመካለኛው ዘመን በተለይ በአውሮፓ የነበሩ የአልኬሚ ጠበብት ሞትን ድል የምታደርገውን ዕጽ ሀሰሳውን እርግፍ አድርገው ትተው የክርስቶስን አብነት ተከተሉ፡፡ ለእነርሱ ብረት የሆነ ሀጥያትን ሁሉ ወደ ወርቅ የሆነ ጽድቅ የሚቀይረው መንገድ እርሱ እንደሆነ አመኑ፡፡ እኛ ግን እንጠይቅ! ኢየሱስ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዳይካተቱ ከተገፈተሩት መጻሕፍት አንዱ በሆነው የቶማስ ወንጌል ላይ በውስጣችሁ ያለውን እሱን ካወጣችሁት ያድናችኋል፡፡ በውስጣችሁ ያለውን ያንን ማውጣት ካልቻላችሁ ግን መጥፊያችሁ ይሆናል፡፡» ሲለን ምን ማለቱ ነበር? (When you bring forth that within you, then that will save you. If you do not, then that will kill you.) በውስጣችን ያለው ያ ስናሰለጥነው ሊያድነን፣ ልናወጣው ባንችል ግን ሊገድለን የሚችል እርሱ ምንድን ነው? ይህ ኃይለቃሉ በራሳችን እና በዙሪያችን የከበበን የነተበ ፈሪሳዊ ዓለም ላይ እንድናምጽ እያተጋን አልነበረምን? የራሳችን መስቀል ተሸክመን ወደ ራሳችን ቀራኒዮ እንድንዘምት፣ ልክ እንደተጋዳሊ (Hero) ከራስ ለሚልቅ ዓላማ እንድንሰለፍ እያነቃን? ዋሻ ውስጥ ተጋድሞ የጸሐይቷን መውጣት ሲጠብቅ እንቅልፍ ጥሎት ዘመናት እንደሚፈራረቁበት፣ ሳር እንደሚበቅልበት ዘንዶ በውስጣችን ያንቀላፋውን ያንን ስናነቃው፣ ስናሰለጠነው ሊያጀግነን የሚችል ደራጎን ማስደንበር እንችል ዘንድ እያተጋን? ደራገን (Dragon - Serpent) ከአልኬሚ ጽንሰ ሐሳብ ጋር ተያይዞ የሚነሳ እሳት እንደሚተፋ፣ በክንፍ እንደሚበር የሚታሰብ የእባብ ዝርያ ነው፡፡ ነገርግን ደራጎኖች የሰው ልጅ ስነልቦናን እንደጥናት ዘርፍ ከመመስረቱ ሺህ ዘመናት በፊት ለጭቁኑ አእምሮው (shadow) መገለጫ ይሆኑት ዘንድ የፈጠራቸው ምናባዊ መመሰያዎች እንጂ በሕልውና የነበሩ ፍጥረታት እንዳልሆኑ ይታመናል፡፡ ደራጎኖች ውስጣችን የታመቀው ስናነቃው፣ ስናሰለጥነው ሊያመጥቀን ሊያስፈነጥረን የሚችል ንጹህ ንቁ ኃይል አመልካቾች ናቸው፡፡ ደራጎኖች ከመገራታቸው ከመታረቃቸው በፊት ስግብግቡን አኔነት (ego) ይሸከማሉ፡፡ ደራጎኖች መጀመሪያ ከሸለብታቸው ሲቀሰቀሱ አፍራሽ፣ አደፍራሽ ናቸው፡፡ ከተገሩ በኋላ ግን የነቃውን አነ (divinity) ይመስሉታል፡፡ ሽግግሩ ዘመናትን ሊወስድ በአብዛኛው ላይቋጭም ቢችልም ቅሉ.. የደራጎኑ ጌታ ገበሬም ይሁን ሐያሲ የደራጎኑን ቁጣ ማስከን መግራቱን እስኪሰለጥንበት ሁሉንም ማተረማመሱ፣ ማፈራረሱ አይቀርም፡፡ ይህ በድራጎን የተመሰለ እምቅ ኃይል በሁላችንም ውስጥ ይገኛል፡፡ የሰው ልጅ አካል ከአፈር፣ ከአየር፣ መሬት እና እሳት ኃይለ ባህሪያት (form of energies) ተሰራ ብለናል፡፡ ደራጎኖች በአካል ላይ የሚሰለጡኑ ገዥ ኃይላት እንደመሆናቸው አካል የተሰራንባቸውን አራት ባህሪያት (ውኃ፣ እሳት፣ መሬት፣ አየር) ይወርሳሉ፡፡ በዚህም አግባብ በሰው ልጆች እዝነ ልቦና ውስጥ አራት ዓይነት የድራገን ኃይለ ስሪቶች ይኖራሉ፡፡ ሆኖም ምንጊዜም አንደኛው ኃይለ ስሪት ገዥ (dominant) ሆኖ መውጣቱ ግዴታ ይሆናል፡፡ ገዥውን ስነ ባህሪይ ለይቶ ማወቅ ብሎም ማሰልጠን ደግሞ የተተስካከለ ስብዕና የላቀ ኃይል ያላብሳል፡፡ 📖ብርሀን ጨልጦ መስከር ደራሲ-ያዕቆብ ብርሀኑ @zephilosophy
9 921
9
بدون متن...
10 883
10
"የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር መቃቃር የጀመረው  ራሱን ከተፈጥሮ ሁሉ የበላይ አድርጎ መመልከት ሲጀመር ነው።ለዚህም መነሻ ምክንያት የክርስትና አስተምህሮ ነው።" ብሩህ አለምነህ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ሰፊ ዘመናትን የያዙት የባርያ ንግድ፣ ቅኝ ግዛት፣ የተለያዩ ዓይነት ባርነቶችና የሴቶች ጭቆናዎች ሁሉ መንስኤያቸው የሰው ልጅ መቆጣጠርንና ጥቅምን ዓላማው ባደረገ አስተሳሰብ መመራቱ ነው፡፡ አንድን ነገር “መቆጣጠር” ካሰብክ ራስህን የዚያ ነገር አካል አድርገህ ማሰብህን አቁመሃል፡፡ “መቆጣጠር” የሚለው ሀሳብ የሚመጣው ራስህን ከዚያ ነገር ለይተህ ስታየው ነው፡፡ እናም አውሮፓውያን በዚህ መንገድ ተጉዘው ራሳቸውን ከተፈጥሮ ገነጠሉ፤ ራሳቸውን ከተፈጥሮ መገንጠል ብቻ ሳይሆን ተፈጥሮን ለሰው ልጅ መጠቀሚያ ብቻ የተፈጠረ አድርገው እንዲቆጥሩት አድርጓቸዋል፡፡ በዚህ አስተሳሰብ ላይ ተመስርተውም የፈጠሩት ሃይማኖት (ክርስትና)፣ የካፒታሊዝም ስልተ ምርት፣ ፍልስፍናና ሳይንስም ተፈጥሮን ይበልጥ እንደመጠቀሚያ እና ሜካኒካል በሆኑ ክስተቶች የተሞላ አድርገው እንዲያስቡት አድርጓቸዋል፡፡ ለምሳሌ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሄር ምድርን የሠራት፣ እንስሳትንና እጽዋትንም የፈጠራቸው ለሰው መጠቀሚያነት እንደሆነ ይናገራል፤ “እግዚአብሄርም አለ፡- ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር፤ የባሕር አሣዎችንና የሰማይ ወፎችን፤ እንሳሳትንና ምድርን ሁሉ፤ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ፤” (ዘፍ 1፥ 26) ​"አላህ በሰማያትና በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ ያስገዛላችሁ፤ ግልጽና ድብቅ የሆኑትንም ጸጋዎቹን በፊታችሁ ላይ ያፈሰሰላችሁ መሆኑን አታዩምን?" (ቁርአን 31፥20) እንደዚህ አይነት መንፈሳዊ አስተምህሮ እንደ ታሪክ ምሁሩ Lynn White, Jri አመለካከት፣ "የሰውን ልጅ ራሱን ከተፈጥሮ የተገነጠለና የተለየ፤ የፍጥረታት ሁሉ ማዕከልና የሁሉም የበላይ አድርጎ እንዲመለከት በማድረግ ትልቅ ሚና ተጫውቷል፡፡ " በሃይማኖታዊ አስተምህሮው ከተፈጥሮ ራሱን የገነጠለው አውሮፓ “ተፈጥሮን መቆጣጠርና ማስገበር ” በሚል መርህ ወደሚመራው ካፒታሊስታዊ ስልተምርት ተሸጋገረ፡፡ ካፒታሊዝምም የገበያ ውድድርን በማፋፋምና ከፍላጎት በላይ የሚጠቀም ማህበረሰብን በመፍጠር ተፈጥሮ ላይ የመጨከኑና ከመጠን በላይ የመበዝበዙን መንገድ አጠናክሮ ገፋበት፡፡ እንደ አዲሶቹ ማርክሲስቶች አመለካከት ግን የካፒታሊዝም ጦስ የሰውን ልጅ ከተፈጥሮ በመገንጠል ብቻ አያበቃም፤ "ካፒታሊዝም የሰውን ልጅ ከተፈጥሮ ብቻ ሳይሆን ከራሱ ሰውነትም ገንጥሎታል፡፡ ካፒታሊዝም የሰውን ልጅ ሃይል በገበያ ብዙ ትርፍ ሊያመጣ እንደሚችል ኢንቨስትመንት በመቁጠር ሰውነትን ወደ ሸቀጥነት ቀይሮታል፡፡" እናም ወደ ሸቀጥነት የተቀየረው ሰው ለተፈጥሮ የሚያዝንበት ህሊና አጣ፡፡ የጥንቱና የምዕራብያውያን ፍልስፍና ዋነኛ ትኩረቱ ሰው ከሚኖርበት አካባቢና ከዲበ አካላዊው (ከሰማያዊው) ዓለም ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያስስ ነበር፡፡ እውነትንና እውቀትን፤ ውበትንና የሕይወት ትርጉምን ሁሉ በዚህ ሂደት ውስጥ ለማግኘት ይሞክር ነበር፡፡ ይሄም ሂደት  ከተፈጥሮ ጋር የነበረውን ጥብቅ ቁርኝት የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ የጥንቱ አውሮፓዊነት ከተፈጥሮ ጋር መቃቃር የጀመረው ግን ራሱን ከተፈጥሮ ሁሉ የበላይ አድርጎ መመልከት ሲጀመር ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነት ትምክህታዊ አመለካከት እንዲይዝ ካደረጉት አስተምህሮቶች ውስጥ ዋነኛው ደግሞ ክርስትና ነው፡፡ " የሰማያት ሰማይ ለእግዚአብሔር ነው፤ ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት።" መዝሙረ ዳዊት 115፥16 ክርስትና (እና እስልምና) እግዚአብሄር ምድርን ለሰው ልጅ መጠቀሚያ እንደፈጠረ በማስተማር የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር የነበረውን ህብረትና ጓደኝነት ቆረጡት፡፡ አውሮፓዊነትም በዚህ የክርስትና አስተምህሮ ተጠልፎ ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ግንኙነት ከሁለንተናዊ ህብርነት ወደ ገዥና ተገዥ፣ ጨቋኝና ተጨቋኝ፣ መለኮታዊና አለማዊ ወደሆነ “ቁጥጥር እና ጥቅም”ን ታሳቢ ወዳደረገ የሁለትዮሽ ግንኙነት ተቀየረ፡፡ የኒውተን ሜካኒክስ እንዲሁም የሆብስ፣ የላሜትሪ እና የዴካርት ፍልስፍናዎች መሰረታቸው ይሄው በሰውና በተፈጥሮ መካከል ያለው የበላይነትና የበታችነት የሁለትዮሽ ግንኙነት ነው፡፡ እነሱ የሚመኩበት “የምክንያታዊነት” እና “ተፈጥሮን በመቆጣጠር የማስገበር” አካሄድ መጨረሻ ላይ የምድራችንንና አጠቃላይ የሰውን ልጅ ህልውና የከፋ አደጋ ላይ ጣለው፡፡ አውሮፓዊነት ከተፈጥሮ ጋር የነበረውን የስሜት ቁርኝት ትቶ የተጓዘበት መንገድ መጨረሻው ተፈጥሮን በማምከን የሰውን ልጅ ለከፋ አደጋ ዳረገው፡፡ 📖ፍልስፍና -2 ✍️ ብሩህ አለምነህ @zephilosophy
10 935
11
ድንቅ ሀሳቦችና አባባሎች 1.የሰው ዘር ጠቅላላ ፍለጎት ማቆሚያ የሌለው እና ፋታ የማይሰጥ የስልጣን ወይም የክብር ጥማት ነው።መደምደሚያውም ሞት ብቻ ነው።" ቶማስ ሆብስ 2."ሰው ነፃ ሆኖ ቢወለድም በሄደበት ቦታ ሁሉ በሰንሰለት ተጠፍንጓል።አንዳንዱ ራሱን የሌሎች አለቃ አድርጎ ያስባል።ሆኖም ከእነሱ በባሰ ባርነት ውስጥ ነው።ይህ ለውጥ እንደምን መጣ አላውቅም። ምን ጉዳይ ህጋዊነቱን ያፀድቅለታል ? እርሱን መመለስ እንደምችል አሰባለሁ።" ዣን ዣክ ሩሶ 3."ሰዎች ዲሞክራሲያዊውን መሪ ሁልጊዜም የፍላጎታቸው ወኪል አድርገው ወደ ታላቅነት ምኩራብ ተንከባክበው ያወጡታል።ይህ እንግዲህ የአምባገነንነት ዛፍ የሚያጎናቁልበት ግልፅ ስር ነው።" አፍላጦን 4.«ከሰዎች መሃል የሚበዙቱ ስለራሳቸውን ብቻ ሲያስቡ ፤ የሚመሩባቸው ፍላጐቶችም በአንድ ምልከታ በቀላሉ የሚገመቱ እና በወቅቱ ባሉበት ሁኔታ ዙርያ የሚሽከረከሩ ናቸው።" ጆን ስትዋርት ሚል 5"በህይወት ያለ ነገር ሁሉ ለአንድ ነገር ሊታዘዝ ግድ ነው! እናም ለራስህ መታዘዝ ካልቻልክ ሌላው  ሰው ያዝሀል። ኃያላን ራሳቸውን ይታዘዛሉ .. ሌሎችንም  ያዛሉ! እነዚያ ለራሳቸው የታዘዙት ደካማ የሆኑትን እንዲያዝዙ ግድ ይሆናል።" ፍሬድሬክ ኒቼ 6."ሰዎች በተፈጥሯቸው ነፃ፣ እኩል እና ራሳቸውን የቻሉ በመሆናቸው ማንም ከራሱ ፍቃድ ውጭ መብቱ ተነጥቆ በሌላው ፖለቲካዊ ሉዓላዊ ስልጣን ስር ሊውል አይገባውም።" ጆን ሉክ 7."አንድ ነገር መረዳት ማለት ከባህሪይ እና ከውስጣዊ ማንነቱ ጋር መተዋወቅ ነው።" ጀርም ቤንታም 8."የአገር መልካምነት (በምግባር ልዕልና መላቅ) በመንግስት ስርዓቷ የሚሳተፉ ዜጎቿ መልካምነት ድምር ውጤት ነው።" አሪስጣጢሎስ 9."መልካም አርበኛ እና እውነተኛ ፖለቲከኛ በአገሩ ያለውን እሴት እንዴት አሟጦ እንደሚጠቀም ያሰላስላል።" ኢድመንድ በርክ 10."ብዙውን ጊዜ መንግስታት የዛሬውን እውነታ ለመጋፈጥ ሲደፍሩ አይስተዋልም። ከዚህም የተነሳ ለሚመጣው ዝግጁ አይደሉም።ለዜጎቻቸው የሚያቀርቡትም የማይጨበጥ ምናባዊ ደስታን ይመስላል።" ጀርም ቤንታም 11. "ታላላቆቹ የፖለቲካ እሰጥ አገባዎች እና ግጭቶች በሀይማኖት ፣በብሄር ፣በመብት ፣በነፃነት ስም የሚደረጉ ይመስላሉ።ሀቁ ከዚህ ይለያል።ከውብ መፈክሮች ጀርባ ድብቅ የግል ጥቅምን የማስጠበቅ እኩይ ጠባያት አሉ።" ኢድመንድ በርክ የትኛውን አባባል የበለጠ ወደዳችሁት? @zephilosophy
11 502
12
«የዓለም ታሪክ ነፃነት ለማወቅ ከሚደረግ ሒደት ውጭ ምንም አይደለም።» ፍሬድሪክ ሄግል ታላቁ ጀርመናዊ ፈላስፋ ፍሬድሪክ ሔግል "philosophy of history" በተሰኘው መፅሀፍ ላይ የዓለም ታሪክ አጋጣሚ ያከታተላቸው ኹነቶች ትርዒት ሳይሆን በተቃራኒው ምክንያታዊ እና የታሰበበት ዕቅድ ውጤት ነው ይለናል። ይህ ቅጥ አምባር በየትኛውም ቦታ እና ጊዜ ቁልጭ ብሎ ይታያል። የፖለቲካ ጥናትም የተሟላ የሚሆነው ተቋማት እና ሰብዕናዎች በትልቅ ዓላማ ያነገበ የታሪክ እድገት ማዕቀፍ ውስጥ ከተከወነ ብቻ ይሆናል፡፡  ለዚህ ሒደት ወይም ቅጥ አምባር (ፓተርን) ሔግል ስያሜ አውጥቶለታል። ታላቁ ኃሳብ ወይም ፍፁማዊ እውቀት (The ldea) ሲል ይጠራዋል። ሔግል በፖለቲካ ሒደት ውስጥ ኃሳብ ላለው ትልቅ ፋይዳ አፅንኦት ስለሚሰጠው ስያሜው የተገባ ይመስላል። ቁሳዊው የሰዎች እና የተቋማት ዓለም ለሔግል ብዙም ጉዳዩ አይደለም። ይልቁን ለቁሳዊው ዓለም አቅጣጫ እና ግብ የሚሰጠው መንፈስ ወይም ኃሳብ ላይ ማተኮርን ይመርጣል። ታላቁ ኃሳብ በማህበረሰብ ውስጥ አስፈላጊ የሆኑ እንደ ፍትህ ፤ ነፃነት ያሉ ረቂቅ እሳቤዎችን ሁሉ ጠቅልሎ የሚይዝ ማዕቀፍ ነው። «ነፃነት ይላል ሔግል በሰዎች ተግባር ውስጥ ሳይሆን በሰዎች ግንዛቤ ውስጥ ይገኛል። ፖለቲካን ለመረዳትም ማጥናት ያለብን የሰዎችን ድርጊት አይደለም፡፡ ድርጊታቸውን እንዲፈፅሙ የሚገፋፋቸውን መንፈስ እንጅ። የሰው ዘር ታሪክ በንቃት የተተለመ የሆነ ግብ ይዞ አልተጀመረም። ማህበራዊ ደመ ነብስ ንቁ የሆነ ለህይወት እና ለንብረት ደህንነት መሻትን ያመላክታል። እናም ማህበረሰብ በሚቋቋምበት ጊዜ ይህ ዓላማ ይበልጥ ጠቅላይ ሆኗል። የዓለም ታሪክ የሚጀምረው ጠቅላይ ግብን በመረዳት ነው። የመንፈስ ኃሳብ በስውር  ቅርፁ ንቁ ደመነብስ ይሆናል።» ይለናል። በታሪክ ማዕከል ውስጥ ከህቡዕ ልቦና ወደ ንቁ ልቦና ወይንም ካለመንቃት ወደ ንቃት የተደረገው ሽግግር አለ። ይህም ወደ ፍልስፍናዊ ነፃነት የሚያደርሰው ሒደት ነው። አስተያየቱን ሲቀጥልም፦ «የነፃነት ዋና ተፈጥሮ ራሱን ወደማወቅ መምጣቱ ነው። በዚህም ህልውናውን ይገነዘባል።ሰዎች ከታላቁ ኃሳብ ጋር መኖርን ማወቅ አለባቸው። ሊያመልጡት አይቻላቸውምና። ሰዎች እና ተቋማት ነፃነትን ለማወቅ ከፈለጉ በትልቁ የታሪክ ሒደት ውስጥ ትክክለኛ ቦታቸውን ለማወቅ ጥረት ማድረግ አለባቸው፡፡ ታሪክ በእርሱ አመለካከት መሠረት በነፃነት አቅጣጫ የሚደረግ ተቋማዊ የለውጥ ሒደት ነው። ሰዎች ነፃነትን እንዲጨብጡ የህልውናቸውን ምክንያት ወደማወቅ ከፍታ ማንሰራራት አለባቸው፡፡ ስለዚህ ነፃነት ከእውቀት ወይም ንቃተ ልቦና (consciousness) ተለይቶ ሊታይ አይችልም። ነፃ የሆነ ሰው ለድርጊቱ እና ለባህርዩ የክልከላ አጥር ያልተበጀለት ሰው ሳይሆን በታሪክ መስክ ላይ ትክክለኛ እና ልዩ ስፍራውን ጠንቅቆ ያወቀ ነው፡፡ ይህንን ነፃነት የሚያጐናፅፈው ታላቁ ኃሳብ ብቻ ነው።" በፖለቲካ ንፍቀ ክበብ ውስጥ ብዙ ሰዎች ፍዝ ናቸው። የመረዳትም የመሳተፍም ንቃት የላቸውም፡፡ እጣ ፈንታቸውን ያለ ተቃውሞ እና ያለ አመፃ ይቀበላሉ። እነዚህ ሰዎች ሳያውቁት በጦርነት ይፈጃሉ ፤ በረሃብ ያልቃሉ ፤ በአምባገነን ጭቆና ይቆረቁዛሉ። በእያንዳንዱ ዘመን አልፎ አልፎ ግን ብቅ የሚሉ ልዩ ሰብዕናን የታደሉ ፤ የነቁ እና አብዮተኛ ግለሰቦች አይጠፉም። የአንድ መደብ አባላት አይደሉም። ልዩ መብት የታደሉ ወይንም የተነፈጉም አይደሉም። ከየትኛውም አቅጣጫ ሊወጡ የሚችሉ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ - ይላል ሔግል የፖለቲካዊ ተግባር ሰዎች ናቸዉ። የራሳቸውን ግብ እና ፍላጐት ሰንቀው በአንድ ኃሳብ ይጓዛሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች የዲያሌክቲካዊው ሒደት ዋነኛ መሳርያ ናቸው። በግልፅ ባይታወቃቸውም የተቃርኖ (አንቲቴሲስ) ኃሳብን በመድረስ ነባሩን ስርዓት ይሞግታሉ። አብዮትን በመለኰስ ታሪክን ይፅፋሉ። ሔግል የእነዚህ ሰዎች ወዳጅ ነው። ለሰው ዘር እድገት ያበረከቱትን አስተዋፅኦ ማክበር ይገባናል"  ይለናል @zephilosophy
9 707
13
ስለጊዜ ሳስብ ገደል አፋፍ ላይ ሆነው የለቀቋት እፉዬ ገላን አስታውሳለሁ። ከዓይን እስከምትሰወር ድረስ ብቻ የምንከተላት። ከአለፈች በኋላ ምስሏ ብቻ በአዕምሯችን መዝገብ ሳይ የሚሰፍር። በ "ጊዜ" ውስጥ ቁጥር አይደለም ያለው። ጊዜ ስንል ሰዓት ፣ደቂቃ ሰከንድ እያልን አይደለም። ጊዜ ሰኞና ሀሙስ አልያም ጥቅምትና ሰኔ አይደሉም። ትላንትና ብለን ዛሬ ከዛሬም ደግሞ ነገ ተከታዩ አይደሉም የጊዜ መስፈሪያዎች...እኛው ነን!! ጊዜ የሚሰፈረው በእኛ ነው።  በስጋና በነፍሳችን ውስጥ ነው ጊዜ የሚሽከረከረው። በሽክርክሪቱ መሀል የምንቆጠረው እኛ ነን።24 ሰዓታት የምንላቸው ፍካሬያቸው ከውልደት እስከ ሞት ድረስ ያለው ህልውናችንን ለመወከል ነው። እያንዳንዷ የገላችን ክፍል ጊዜ ነው። ህዋሳቶቻችን እንደ ኑግ ክምር ከስጋዎቻችን ላይ ሰፍረዋል። በየሰከንድ ውስጥ ከዚህ ክምር ቅንጣት ህዋስ ትንሸራተታለች።ጊዜ ቁጥር አይደለም። ጊዜ ስጋችን ነው ታሪካችን ነው...ህይወታችን ነው ጊዜ እኛው ነን። 📖📖📖📖📖📖 ይህ የኛ ጊዜ ግን መከረኛ ትውልድ ተገልጦበታል።ዘመኑ የመከራ ክርታስ ሆኗል። በዚህ ክርታስ ውስጥ ሞት... ስደት.... ጦርነት... ድህነት... የተባሉ ጥሬ ሀቆች ታጭቀውበታል። ይህንንም የክርታስ ቋጠሮ በእያንዳንዱ የትውልዴ አንገት ላይ እንደ ሜዳሊያ ተንጠልጥሏል።ለዚያም ነው ሁሉም የጎበጠው። ለዚህም ነው የድባቴ አየር ብቻ የሚነፍሰው። ይህ ትውልድ በ "ጊዜው ላይ ተሸንፏል። ቢያኮርፍ እንኳ የሚያባብለው የለም። ታላላቆቹ ጥይት በማንጣጣት ተጠምደዋል ለረሀቡ ዳቦ ለእንባው ደሞ መሀረብ የሚያቀብለው ታላቅ የለውም። የኑሮ ትርምስና ውጣ ውረድ ሽባ አድርጎታል። ለመሳለም ጎንበስ ሲሉለት ኩርኩም አናቱን ያቀምሱታል። ለመማር ከእግራቸው ስር ቢደፋ ከንፅህና የራቀ እግራቸው ይሰነፍጠዋል። ይህ እግራቸው መዋል በሌለባቸው ስፍራ ስለመገኘታቸው እንደ ምልክት ሆኖ ይጮሀል። ትውልዱ ባክኗል! ታላላቆቹ ለሚጫወቱት ቁማር ማስያዣ ሆኗል። ህይወቱ የራሱ አይደለችም። በአራጣ ተይዛለች...... አህመድ ሁስ 📖ጥሪ ወደ ሞት @zephilosophy
11 494
14
የእግዜር አሽሙር ምድርን በዘረጋው፣ ሰማይን ባቆመው           ጥበበኛ እጁ ተጨንቆ ቢሰራን፤ እኛ ግን ከንቱ ነን! ከእርግብ መደብ ተክሎን            የእባብ ነፍስ አፈራን። ፍርድ ያውቅበት የለ? የሕይወትን ትርጉም – በአሽሙሩ ሲያራራው፧ ለሞቱ ያልመጠነን- “ኗሪ!' ብሎ ጠራው። ባባ ጣሂር 📖የመንፈስ ከፍታ @zephilosophy
10 963
15
بدون متن...
12 346
16
"ፍትህ የሌለው ሉአላዊ ስልጣን የተደራጀ ዝርፊያ እንጂ ሌላ ምንድን ነው?" አውግስቲን @zephilisophy
"ፍትህ የሌለው ሉአላዊ ስልጣን የተደራጀ ዝርፊያ እንጂ ሌላ ምንድን ነው?" አውግስቲን @zephilisophy
11 208
17
The Republic The Republic የአፍላጦን ዋነኛ ተጠቃሽ ስራው ነው። የመጀመሪያው ብስል የፖለቲካዊ ፍልስፍና ስራም ነው። ስለመንግስት አስተዳደር ያለውን አስተያየት ጠቅልሎ አካቶበታል። ከፍተኛ ስነ ፁሁፋዊ ለዛ ያረፈበትን ይህን ታላቅ ዲያሎጉን (በውይይት መልኩ የሚቀርብ ሀተታ) የፃፈው ድርሰትን በሚገባ በተካነበት እና ኃሳብን የመግለፅ ጥበብን አሳምሮ ባወቀ! ወቅት በመሆኑ በፍልስፍናው አበክሮ የሚያወጣ የሚያወርዳቸውን ጉዳዮች በሚደንቅ ህብር አስሮ ለማቅረብ እስችሎታል። ፍፁም ነው የሚለውን ሐሳባዊ የጋራ ብልፅግና ሲተነትን (ይህም በስነፅሁፍ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው ዩቶፒያ-- እንከን አልባ ምናባዊ ዓለም-- ተደርጎ ይቆጠራል።) በህይወቱ  ያተኮረበትን ተግባራዊ ፖለቲካ ያስዳስሳል። በሳል የህይወት ተሞክሮውን እና እውቀቱን ተጠቅሞ ለዓይነተ ብዙ ችግሮች (ከስነ ፅሁፍና ሙዚቃ ግልጋሎት እስከ የሴቶች እኩልነት፤ ከጋራ መኖሪያዎች እስከ የህዝብን ዕድገት በመቆጣጠር ምርጥ ዘር የመፍጠር ሳይንስ ወይም ኢዩጄኒክስ ድረስ) አስተያየቱን ለግሷል። በትምህርት እና በመንግስት መካከል ያለውን የጠለቀ ግንኙነት ካስተዋሉት የመጀመሪያዎቹ ጠቢባን መሃልም አንዱ ነው። ወጣቶችን ስለማስተማር፤ ስለማነፅ እና ስለማሰልጠን የሰጠው አፅንኦት በበርካቶች በአድናቆት ታይቷል። ዣን ዣክ ሩሶ «በዓለም ላይ በትምህርት ላይ የተሰራው እጅግ ምርጡ የምርምር ፅሁፍ » ሲል The Republicን ማወደሱን ልብ ይሏል። በአስር ቅፆች (መፅሃፍት) የተደራጀ ስራ ነው The Republic። በመጀመርያው ቅፅ ፍትህ የሰው ልጆች ነብስ በትክክል ስራዋን እንድትከውን የሚያስችል ጠበል ነው ይለናል። ህይወትን በአግባቡ የሚኖር ሰው የተባረከ እና ደስተኛ ነው ሲል ያክላል። በሁለተኛው ቅፁ መግቢያ ላይም ፍትህ ለራሱ ሲባል (መልካም እሴት ስለሆነ) እንዲሁም የሚያስገኘው ውጤት በጎ ስለሆነ ልንተገብረው እንደሚገባ ይመክረናል። በአራተኛው ቅፅ ደግሞ ፍትህን የሚተገብር ግለሰብ ሌሎቹን የምግባር እሶቹን በሙሉ እያስተባበረ እንደሆነ ያስረዳል። ፍትህን የማይተገብር ሰው በአንፃሩ ደፋርም አይደለም፡፡ ብልህም አይደለም። ትክክለኛም አይደለም፡፡ ከላይ ከላይ ሲያዩት የዲያሎጉ ዓላማ «ፍትህ ምንድን ነው? የሚለውን ጥያቄ መመለስ ቢመስልም ፍትህ (juctice) የሚለውን አቻ ትርጓሜ የሚያስገኝልን የግሪክ ቃል ከፖለቲካዊ እና ህጋዊ እኩልነት የዘለለ ፍቺ በውስጡ ያመቀ በመሆኑ ጉዳዩን አስፍተን እንድንመለከተው ይጋብዘናል። የምግባር ልዕልናን (virtue) የመፈንጠቅ ትክክለኛነት የሚል ትርጉምም አለው፡፡ አፍላጦን ይባትል የነበረው ትክከለኛውን ህይወት (ሰዎች እና አገራት ሰናይ ተፈጥሯቸውን አሟጠው እንዲያወጡ የሚያደርጉ መርሆችን) ፍለጋ ነው። The Republic በወቅቱ በነበረው ስርዓተ ፖለቲካ ላይ የቀረበ ኂስም ክስም ነው። አፍላጦን ከሰው ልጆች ተሞክሮ የሚልቅ ዘላለማዊ ህልውና አለ ብሎ ያምን ስለነበር ግብረ ገብ እና መልካሙ ህይወት የዚህ ህልውና መገለጫዎች ናቸው። መንግስታት እነኝህን እሴቶች ማበረታታት አለባቸው ይላል። ይህ አመለካከቱን ለማሳየት ባጠናቀረው አንድ ተረክ ላይ ሰዎች ዋሻ ውስጥ ፊቶቻቸውን ወደ ግድግዳ አዙረው በሰንሰለት ተጠፍንገዋል። ለብርሃኑ ጀርባቸውን ሰጥተዋል። ስለዚህ ያተኮሩበት ግድግዳ ላይ የሚታያቸው ትዕይንት ከጀርባቸው የሚከወነው እውነታ ነፀብራቅ ወይንም ጥላው ብቻ ነው። ለአፍላጦን ተራ ተርታው የዕለት ተዕለት ህይወት አታላይ ቅዠት ነው። በፖለቲካ ውስጥ የሚያቆጠቁጡት ክፋቶችም አውሬያዊ ደመ ነብስን የመከተል ውጤቶች ናቸው። ስለሆነም ከዚህ ክፉ ደመ ነብሳዊ ጥሪ ነፃ የወጡ ፈላስፎች የንግስናን መንበር ካልተቆናጠጡ ወይንም ነገስታቱ በቅንነት ሃቀኛ ፈላስፎች ሊሆኑ ካለቆረጡ በቀር ከክፋት መላቀቅ የለም። ፈላስፋ-ፖለቲከኛ ብቻ ነው ዜጎቹን ከታሰሩበት ፈትቶ ፊታቸውን ወደ ብርሃን ሊመራ የሚችለው ፤ ከዋሻውም አውጥቶ አምሳያውን ሳይሆን ትክክለኛውን እውነት የማሳየት ብቃት የታደለው። @zephilisophy
10 784
18
The Republic - Plato
7 356
19
بدون متن...
8 192
20
بدون متن...
8 376