cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ስንክሳር

ሁሌ ዝቅ ማለትን አብዝቶ መስማትን ገንዘብ እናድርግ። @Synaxarium "ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን" ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
771
Suscriptores
Sin datos24 horas
-17 días
+930 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን። ግንቦት 5 በእናቱ ማኅጸን ሳለ የተመረጠ ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤርምያስ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ ይኽም ዕውነተኛ የእግዚአብሔር ነቢይ የካህኑ ኬልቅዩ ልጅ ነው፡፡ የስሙ ትርጓሜ ‹‹እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል›› ማለት ነው፡፡ አባቱ ኬልቅዩ እግዚአብሔርን የሚያገለግል ካህን ሲሆን እናቱ ማርታ ትባላለች፡፡ ሀገሩ ይሁዳ ሲሆን ልዩ ስሙ አናቲት ይባላል፡፡ ነቢዩ ኤርምያስ ገና በእናቱ ማኅጸን ሳለ የተመረጠና የተቀደሰ ነቢይ ሲሆን የአሞጽ ልጅ የይሁዳ ንጉሥ ኢዮስያስ በነገሠ በ13 ዓመቱ ማስተማር ጀመረ፡፡ ከዚያም በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም ዘመን ዓሥራ አንዱ የሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥቱ እስኪፈጸም በ5ኛው ወር ኢየሩሳሌም እስከተማረከችበት ጊዜ ድረስ ያስተምር ነበር፡፡ ነቢዩም ስለራሱ ሲናገር ‹‹የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ መጣ፣ እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፡- ‹በእናትህ ማኅጸን ሳልፈጥርህ ወደድኩህ፣ ከእናትህም ማኅጸን ሳትወጣ መረጥኩህ፤ ለአሕዛብም መምህር አደረግሁህ› አለኝ፡፡›› ኤር 1፡4፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ኤርምያስ እንደነቢዩ ኢሳይያስ በበትር የምትመሰል የአምላክን እናት የቅድስት ድንግል ማርያምን ምሳሌ በለውዝ በትር አምሳል ተመልክቷታል፡፡ ኤር 1፡11፡፡ በተጨማሪም ከሁለት ደቀመዛሙርቱ ከባሮክና ከአቤሜሌክ የእመቤታችን ምሳሌ የሆነች ዐጽቀ በለስ በንስር አንገት የተላከለት ታላቅ ነቢይ ነው፡፡ ቅዱስ ኤርምያስ የእግዚአብሔርን አምልኮና ሕግ በመተዋቸው ‹‹ተጠበቁ፣ ንስሓም ግቡ፣ የእግዚአብሔር ቁጣው በላያችሁ እንዳይመጣ›› ብሎ የእስራኤልን ልጆች ገሠጻቸው፡፡ ሁለተኛም ‹‹ወደ ፈጣሪያችሁ እግዚአብሔር ካልተመለሳችሁ የከላዴዎንን ንጉሥ ናቡከደነጾርን በላያችሁ እርሱ ያስነሣዋል›› ብሎ ትንቢት ተናገረ፡፡ እንደቃሉም ሆነ፡፡ ዳግመኛም ሕዝቡ ተማርከው ሰባ ዘመን በምርኮ እንደሚኖሩ ትነቢት ተናገረ፡፡ ደግሞም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኩነተ ሥጋ እንደሚመጣና መከራ እንደሚቀበል፣ የአስቆሮቱ ይሁዳ እንደሚሸጠውና የሽያጩን ዋጋ 30 ብር እንደሚቀበል ተናገረ፡፡ ስለ ብዙ ሥራዎችም ትንቢትን በተናገረ ጊዜ አይሁድ ሊገድሉት ፈልገው ይዘው አሥረው ገርፈው ከጉድጓድ ውስጥ ጣሉት፡፡ እግዚዚአብሔርም አዳነው፡፡ ነቢዩ ግን ስለ አይሁድ ይለምንና ይማልድ ነበር፣ እግዚዚአብሔርም ‹‹ስለ እነርሱ ወደእኔ አትማልድ፣ እነርሱ ከክፋታቸው አይመለሱምና›› አለው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነጾርም የኢየሩሳሌምን ሕዝብ በማረከ ጊዜ ከእርሳቸው ጋራ አልማረከውም፡፡ ነገር ግን ከምርኮ የቀሩት ወደ ግብጽ አገር ወሰዱት፡፡ ነቢዩም የግብጽን ሰዎች ሲያጠፏቸው የነበሩ በወንዞች የሚኖሩ አራዊትን በጸሎቱ አጠፋቸው፡፡ ከዚያም ወደ ባቢሎን አገር ወሰዱት፡፡ በዚያም የእስራኤል ልጆች ከምርኮ እስኪመለሱ ትንቢት እየተናገረ ሕዝቡን ሲያስተምር ኖረ፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ኤርምያስ ነገረ ሥጋዌን ማለትም የጌታችንን ሰው መሆን በትንቢት ሲናገር ክፉዎች የእስራኤል ልጆች የትንቢቱ ወራት ሲፈጸም ‹‹የአምላክን ልጅ አምላክን አየሁት›› ይለናል ብለው በድንጋይ ወገሩትና በዚያው በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ ተረ ኤር 11፡54፤ ዕብ 11፡37፡፡ የነቢዩ የቅዱስ ኤርምያስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን አሜን። 🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃 ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ሁሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት 5️⃣ ቀን ስንክሳር ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን። ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል። እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ። ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር . ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼ ግንቦት 4️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም
Mostrar todo...
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን። ግንቦት 3 ጌታችን ከመረጣቸው ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ አንዱ የሆነውና ቅዱስ ጳውሎስ በጠርሴስ አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት የሾመው ሐዋርያው ቅዱስ ያሶን ዕረፍቱ ነው፡፡ ➥ ሰማዕቱ አባ ብሶይ ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ ➥ "የንጉሥ ወግና ሰገድ እናቱ የሆነች የተባረከች ንግሥት ወለተ ማርያም" ዕረፍቷ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳታል፡፡ እርሷም በምግባር፣ በሃይማኖትና በመንፈሳዊ ተጋድሎ የከበረችና የተመሰገነች ናት፡፡ 🔥 ሰማዕቱ አባ ብሶይ ይኽንንም ቅዱስ ክፉዎችና ጣኦት አምላኪዎች ይዘውት ሰውነቱን በማጣመምና በመቆልመም ብዙ አሠቃዩት፡፡ የእግዚአብሔርም መልአክ በእጁ አክሊል ይዞ "አትፍራ ጽና፣ እነሆ በእጄ ውስጥ አክሊል አለ" አለው፡፡ ደግሞም ብዙ ካሠቃዩት በኋላ ወደ እሳት ውስጥ ጨመሩት፡፡ ጌታችንንም በማመን እስከመጨረሻው ጸንቶ ተጋድሎውንም በዚኹ ፈጸመ፡፡ መልአኩም አስቀድሞ አሳይቶ ተስፋ እንደሰጠው የሰማዕትነት አክሊልን አቀዳጀው፡፡ የሰማዕቱ የቅዱስ ብሶይ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡ 🔥 ሐዋርያው ቅዱስ ያሶን ይኽም ቅዱስ ሐዋርያ ከከበሩ ሐዋርያት ጋራ ወንጌልን በሰበከ ጊዜ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን በጌታችን ስም ተቀበለ፡፡ በ50ኛው ቀን ከሐዋርያት ጋራ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሏልና ድንቅ ድንቅ የሆኑ ብዙ ተአምራትን አደረገ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ያሶን ትውልዱ ከጠርሴስ አገር ነው፡፡ ጠርሴስም ሰዎች አስቀድሞ በወንጌል ያመነው እርሱ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከተጠራና ካመነ በኋላ ወንጌልን ዞሮ ሲሰብክ ቅዱስ ያሶን ተከትሎት በብዙ አገሮች በወንጌል ትምህርት አገልግሎታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ያሶን በተሰሎንቄ ከተማ ወንጌልን ሲሰብኩ ክፉዎች ይዘዋቸው እየጎተቱ ወስደው ከተሰሎንቄ አገር ገዥ ፊት አቅርበዋቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ቅዱስ ያሶንን በጠርሴስ አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾመው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ያሶንም ቤተ ክርስቲያንን በመልካም አጠባበቅ ጠበቃት፡፡ ምእመናንን በቀናች ሃይማኖት ካጸናቸውና በበጎ ምግባር ካነጻቸው በኋላ ወደ ምዕራብ አገር ሄዶ በዚያ ወንጌልን ሰበከ፡፡ ስሟ ኮራኮራስ ወደምትባል ደሴትም ገብቶ በውስጧ ወንጌልን ሰብኮ ነዋሪዎቿን እግዚአብሔርን ወደማመን መለሳቸው፡፡ በደሴቷም ውስጥ በዲያቆናት አለቃ በሰማዕቱ በቅዱስ እስጢፋኖስ ስም ቤተ ክርስቲያን ሠራላቸው፡፡ የአገሪቱ ገዥም ይኽንን ባወቀ ጊዜ ቅዱስ ያሶንን ይዞ ከእሥር ቤት ጣለው፡፡ ሐዋርያው ግን በእሥር ቤት ያገኛቸውን ሰባት ኃይለኛ ወንበዴዎችን አስተምሯቸው ካሳመናቸው በኋላ አጠመቃቸው፡፡ እነርሱም በከሃዲው መኮንን ፊት በጌታችን ታመኑ፡፡ "በቅዱስ ያሶን አምላክ እናምናለን" ብለውም በጮኹ ጊዜ መኮንኑ ዝፍጥና ድን በተመላ ምጣድ ውስጥ አግብቶ አቃጠላቸው፡፡ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ ከዚኽም በኋላ መኮንኑ ቅዱስ ያሶንን ከእሥር ቤት አውጥቶ ብዙ አሠቃየው ነገር ግን ጌታችን መከራውን ያስታግስለት ነበርና ምንም እንዳልነካው ሆነ፡፡ በተአምራቱም ብዙዎችን አሳመናቸው፡፡ የንጉሡም ሴት ልጅ ከቤቷ መስኮት ሆና አይታ በክብር ባለቤት በጌታችን አመነች፡፡ ልብሶቿንና ጌጦቿንም ሁሉ አውጥታ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጠችና በሐዋርያው በቅዱስ ያሶን አምላክ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታመነች፡፡ ንጉሡ አባቷም ይኽንን በሰማ ጊዜ ይዞ አሠራት፡፡ ጌታችንንም በማመን ስለጸናች አባቷ ብዙ ሥቃጦችን አደረሰባት፡፡ በጢስ አፍኖ አሠቃያት፣ ልብሷን አውልቆ ካራቆታት በኋላ ሰውነቷን በፍለጻ ነደፋት እርሷም በዚሁ ሰማዕትነቷን ፈጽማ ነፍሷን ለእግዚአብሔር ሰጠች፡፡ ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማረን፡፡ ከዚኽም በኋላ ሐዋርያው ቅዱስ ያሶንን አሠቃይተው ይገድሉት ዘንድ ከአንድ መኮንንና ከሠራዊቱ ጋራ ወደ ደሴት ሰደደው፡፡ መኮንኑም በመርከብ ወደዚያ በሄደ ጊዜ እግዚአብሔር መኮንኑን ከነሠራዊቱ አሰጠመው፡፡ ቅዱስ ያሶንም ወንጌልን ተዘዋውሮ እየሰበከ ብዙ ዘመናት ኖረ፡፡ ሁለተኛም ሌላ መኮንን በተሾመ ጊዜ ቅዱስ ያሶንን ይዞ በምጣድ ውስጥ ድኝና ዝፍጥ ሰም መልቶ ነበልባሉ ወደላይ እስኪወጣ ድረስ ከሥሩ አነደደና ሐዋርያውን በውስጡ ጨመረው፡፡ ነገር ግን የክብር ባለቤት ጌታችን አገልጋዩን ያለምንም ጉዳት አዳነው፡፡ መኮንኑም ይኽንን ድንቅ ሥራ ባየጊዜ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አመነ፡፡ ቤተሰቦቹና የአገሪቱ ሰዎችም ሁሉ አብረው አመኑ፡፡ ቅዱስ ያሶንም አጠመቃቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ከሠራላቸው በኋላ የከበረች የወንጌልን ሕግና ትእዛዝ ሠራላቸው፡፡ እነርሱም በምግባር በሃይማኖት ጸኑ፡፡ ሐዋርያውም ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን አደረገላቸው፡፡ መልካም የሆነውን አገልግለቱንም ፈጽሞ በበጎ ሽምግልና ሆኖ በዚኽች ዕለት ዐረፈ፡፡ የሐዋርያው የቅዱስ ያሶን ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡ 🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃 ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ሁሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት 3️⃣ ቀን ስንክሳር ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን። ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል። እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ። ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር . ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼ ግንቦት 2️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም
Mostrar todo...
ስንክሳር

ሁሌ ዝቅ ማለትን አብዝቶ መስማትን ገንዘብ እናድርግ። @Synaxarium "ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን" ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

👍 1
. 🔥 ዓርብ - ቤተክርስቲያን 🔥 ዓርብ የእግዚአብሔር ቅድስት ማደሪያ በሆነችው ቤተ ክርስቲያን ተሰይማለች። ይህም ሁሉም ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የተፈጸመባት ዕለት በመሆኗ ነው። ዕለተ ዐርብ የሥራ መከተቻ፤ ምዕራብና መግቢያ በሚሉት ስያሜዎችም ትጠራለች፡፡ በክርስቶስ ደም ተዋጅታ ለተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዓርብ "ቤተ ክርስቲያን" ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ. 26-26-29 የሐ. ሥራ. 20-28 በዕለቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልዕልተ መስቀል ያደረገውን ተአምር በመስቀሉ ድኅነትን እንዳሳየ፤ በቀራንዮ የሕንጻዋ መሠረት እንደተተከለላትና ሥጋ መለኮት እንደተቆረሰላት፤ ልጆቿን ከማሕፀነ ዮርዳኖስና ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ የምትወልድበት ማየ ገቦ እንደፈሰሰላት ተገልጾባታል። (ኤፍ.፪፥፲፱፤ራዕ.፩፥፮-፰) ይህች ዕለትም እንደ ዕለተ ኀሙስ ሦስት ስያሜዎች አሏት፡፡ ይኸውም፡- ➛ አንደኛው ከሆሳዕና ቅዳሜ በፊት ያለችው ዓርብ የጌታችን ጾም የሚፈጸምባት፤ የጾመ ድጓው ቁመትም የሚያበቃባት፣ በመሆኗ በቤተ ክርስተያን "ተጽዒኖ" ስትባል፤ በሕዝቡም ዘንድ በሕማማትና ሰሙነ ትንሣኤው ከባዱን ሥራ ስለሚያቆምባት "የወፍጮ መድፊያ፣ የቀንበር መስቀያ" ትባላለች፡፡ ➛ ሁለተኛውም በመጀመሪያ የሰው አባትና እናት አዳምና ሔዋን ስለተፈጠሩባት፣ ኋላም በሐዲስ ኪዳን ጌታችን ለቤዛ ዓለም መከራ ተቀብሎ ስለተሰቀለባትና የማዳን ሥራውን ስለፈጸመባት " ዕለተ ስቅለት አማናዊቷ ዓርብ" ትባላለች። ➛ ሦስተኛው በሰሙነ ትንሣኤው ያለችው ደግሞ "ቤተ ክርስቲያን" ትባላለች ማለት ነው፡፡ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=2597592030394633&id=100004315844056&mibextid=Nif5oz
Mostrar todo...
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን። ግንቦት 2 በዘመኑ እንደ እርሱ ያለ ዕውነተኛ ደግ ሰው እንደሌለ እግዚአብሔር የመሰከረለት ጻድቁ ኢዮብ ዕረፍቱ ነው፡፡ ➛ የመንፈሳዊ ማኅበር አባት የሆነው የአባ ጳኩሚስ ረድእ የሆነው የከበረ አባ ቴዎድሮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ➛ አባ ኤሲ ከሃያ ሁለት ሰዎች ጋር በሰማዕትነት እንዳረፉ ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳቸዋል፡፡ 🔥 ቅዱስ ቴዎድሮስ ረድኡ ለአባ ጳኩሚስ የአባ ጳኩሚስ ረድእ የነበሩና እጅግ የከበሩ አባት ናቸው፡፡ በትሑትነትቸውና በታዛዥነታቸው ይታወቃሉ፡፡ በበጎ ሥራ ሁሉ ፍጹም ናቸው፡፡ ከታናሽነታቸው ጀምረው መንኩሰው ለአባ ጳኩሚስ ለፈጣሪያቸው እንደሚታዘዙት ሆነው ይታዘዟቸው ነበር፡፡ አባ ቴዎድሮስ ጠቢብና ሊቅ ናቸው፡፡ አባ ጳኩሚስም እጅግ ይወዷቸው ነበር፡፡ እርሳቸውም በአባ ቴዎድሮስ ላይ ያደረውን ጸጋ ዐውቀው ገና ታናሽ በብላቴና ሆነው ሳለ በመነኮሳቱ ሁሉ ላይ የበላይ አድርው ሾሟቸው፡፡ አባ ጳኩሚስም በሞት ካረፉ በኋለ በእሳቸው ፈንታ አበ ምኔት ሆነው ገዳሙን በጽድቅ በትሩፋት እያስተዳደሩ መርተዋል፡፡ ገዳሙንም በተለያየ መንገድ አገልግለዋል፡፡ አባ ቴዎድሮስ የዚኽን ዓለም ክብር እጅግ አድርገው ይሸሹና ይጸየፉ ነበር፡፡ ጻድቁ መልካም የሆነ አገልግሎታቸውን ፈጽመው እግዚአብሔርን ደስ አሰኝተው በዚኽ ዕለት በሰላም በክብር ዐርፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ 🔥 ጻድቁ ቅዱስ ኢዮብ ለዚኽም ጻድቅ በዘመኑ እንደ እርሱ ያለ ዕውነተኛ ደግ ሰው እንደሌለ በቅዱሳት መጻሕፍትም ስለእርሱ እንደተነገረ እግዚአብሔር መሰከረለት፡፡ የበጎ ነገር ሁሉ ጥንተ ጠላት ሰይጣንም ቀንቶበት በገንዘቡና በልጆቹ ላይ ያሰለጥነው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ፡፡ እግዚአብሔርም የጻድቅ ወዳጁን ትዕግሥት ስለሚያውቅ ሰይጣንን አሰለጠነው፡፡ የቅዱስ ኢዮብ ትዕግሥት ለመጪው ትውልድም አርአያና ምሳሌ ይሆን ዘንድ እግዚአብሔር ኢዮብ እንዲፈተን ፈቀደ፡፡ ስለዚኽም ነገር ሐዋርያው ሲጽፍ ‹‹እነሆ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደታገሠ ሰምታችኋል፣ ጌታም እንደፈጸመለት አይታችኋል፤ ጌታ እጅግ የሚምር የሚራራም ነውና›› ብሏል፡፡ ያዕ 5፡11፡፡ ከዚኽም በኋላ የቅዱስ ኢዮብ ገንዘቡን ሁሉ በአንዲት ቀን ጠፋ፡፡ እርሱም በሥጋ ደዌ ከራሱ እስከ እግሩ ድረስ ተመታ፡፡ በዚኽም በአስጨናቂ ደዌ ውስጥ እየኖረ እግዚአብሔርን ሁልጊዜ ያመሰግን ነበር፡፡ አንዲት ቃልን እንኳ በመናገር በእግዚአብሔር ላይ አላጉረመረመም፡፡ ይልቁንም እንስሶቹና ገንዘቡ ሁሉ በጠፋ ጊዜ ‹‹እግዚአብሔር ሰጠ እግዚአብሔርም ነሣ፣ የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን›› አለ፡፡ በመከራም በነበረበት ዘመን በተራራ ላይ ተጥሎ ሳለ የወዳጆቹና የሚስቱ ዘለፋ በዝቶበት ኖረ፡፡ ሚስቱም ‹‹እስከመቼ ድረስ በሞኝነት ትኖራለህ? እንግዲህስ እግዚአብሔርን ስደበውና ሙት፤ ዳግመኛ እግዚአብሔርን ደጅ እጠናዋለሁ፣ መከራውንም እታገሣለሁ የቀድሞ ኑሮዬን ተስፋ አደርጋለሁ ትላለህን? እንዲህስ እንዳትል እነሆ ከዚህ ዓለም ስም አጠራርህ ጠፋ፣ ሴቶችና ወንዶች ልጆቼ ሞቱ…. ከእንግዲህስ እግዚአብሔርን የማይገባ ቃል ተናግረኸው ሙት›› አለችው፡፡ ጻድቁ ቅዱስ ኢዮብም ‹‹ሥርዓት እንዳልተሠራባቸው ከአሕዛብ ሴቶች እንደ አንዲቱ ተናገርሽን? ከዚህ ቀደም በጎውን ነገር ከእግዚአብሔር እጅ ተቀበልን፤ ከዚህም በኋላ ደግሞ መከራውን አንታገሥምን?›› አላት፡፡ ጻድቁ ቅዱስ ኢዮብ ባገኘው እጅግ አሳዛኝ መከራ ሁሉ ጌታን የበደለው በደል የለም፡፡ እርሱም ወርቅ በእሳት እንዲፈተን ፈጽሞ ተፈተነ፡፡ የትዕግሥቱንም ጽናት ካየ በኋላ እግዚአብሔርም በደመና ውስጥ ተነጋገረው፡፡ ከደዌውም ፈወሰው፡፡ ጥሪቱንም ሁሉ ከቀድሞ እጥፍ አደረገለት፡፡ ሌሎች ልጆችንም ሴቶችንና ወንዶችን ሰጠው፡፡ ኢዮብም ከደዌው ከተፈወሰ በኋላ 170 ዘመን ኖረ፡፡ አጠቃላይ ዘመኑም 248 ዓመት ነው፡፡ እግዚአብሔርን አገልግሎ በበጎ ሽምግልና ሆኖ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡ 🔥 የኢዮብ አማላጅነት እግዚአብሔር ስለ ጻድቁ ስለ ኢዮብ ሃይማኖትና በጎ ምግባር ብቻ ሳይሆን ስለ ኢዮብ አማላጅነትም መስክሮለታል ። ጻድቁ ኢዮብ በታመመበት ወቅት በዙሪያው ቆመው በቁስሉ ላይጥዝጣዜን ሲጨምሩበት የነበሩት ሦስት ጓደኞቹ ላይ እግዚአብሔር ተቆጥቶ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ከሦስቱ የኢዮብ ወዳጆች ለአንዱ ለቴማናዊውኤልፋዝ፦ እንደ ባሪያዬ እንደ ኢዮብ ቅንን ነገር ስለ እኔ አልተናገራችሁምና ቍጣዬ በአንተና በሁለቱ ባልንጀሮችህ ላይ ነድዶአል አለው፡፡ እግዚአብሔር ቴማናዊውን ኤልፋዝን «እንደ ባሪያዬ እንደ ኢዮብ አንዲት ቅን ነገርን በፊቴ አልተናገራችሁምና አንተና ሁለ ቱ ባልንጀሮችህ በድላችኋል። አሁን እንግዲህ ሰባት ወይፈኖችንና ሰባት አውራ በጎችን ይዛችሁ ወደ ባሪያዬ ወደ ኢዮብ ዘን ድ ሂዱ፥ እርሱም የሚቃጠል መሥዋዕት ስለ ራሳችሁ ያሳርግላችሁ። ባሪያዬም ኢዮብ ስለ እናንተ ይጸልይ፥ እኔም ፊቱን እቀ በላለሁ። ስለ እርሱ ባይሆን ባጠፋኋችሁ ነበር። በባሪያዬ በኢዮብ ላይ ቅን ነገርን በፊቴ አልተናገራችሁምና።» ያለው ለዚህ ነው። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመዓዛ ቅዳሴው ላይ እመቤታችንን ‹‹የኢዮብ ደመና ማርያም ሆይ! በረድኤት ነይ›› በማለት አመስግኗታል፡፡ እግዚአብሔርን ጻድቁ ኢዮብን ከደዌው ፈውሶ ምሕረትን ሊሰጠው ሲል በደመና ተገልጦ ድኅነትን እንደሰጠው ሁሉ በዘመነ ሐዲስም እግዚአብሔር ደዌ ነፍስ ጸንቶባቸው የነበሩ ሰዎችን ለማዳን ሲል ከድንግል እናቱ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ተወልዶ ምሕረትን ለዓመለሙ ሁሉ ሰጥቷልና ነው ሊቁ ‹‹የኢዮብ ደመና ማርያም ሆይ! በረድኤት ነይ›› ያላት፡፡ (መዓዛ ቅዳሴ ዘአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ቁ 26፡፡) ዳግመኛም እመቤታችን በፍቅሯ በቃልኪዳኗ ከቁስለ ሥጋ ከቁስለ ነፍስ ከዘላለም ሞት የምንድንባት ነትና አባቶች ‹‹የኢዮብ የሰሜናዊው ምሥራቅ ዓምባ መጠጊያው ማርያም ይኽቺ ናት›› ዳግመኛም ‹‹በቁስለ ሥጋ በታመመ ጊዜ የኢዮብ የልመናው መቀበያ አንቺ ነሽ›› በማለት አማላጅነቷን አመስጥረው አመስግነዋታል፡፡ (መጽሐፈ ሰዓታት ገጽ 89፣ ዝኒ ከማሁ ገጽ 160፡፡) ዳግምት ሰማይ፤ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ መውጫ ምሥራቅ ፤ የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክ በድጋሚ ከልደቷ ረድኤት በረከት ትክፈለን፡፡ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በእመቤታችን ምልጃ ፤ በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡ ምንጭ፡- የግንቦት ❷ ስንክሳር 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።
Mostrar todo...
ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል። እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ። ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖ . ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼ ግንቦት ➊ ቀን 2011 ዓ.ም
Mostrar todo...
"ሔዋን በገነት ዛፎች መካከል ቆማ የሠራችውን የጥፋት ታሪክ ድንግል ማርያም በናዝሬት ገሊላ ቆማ አረመችው፡፡ ሔዋን በገነት ሳለች ማድረግ ያልተቻላትን ነገር ሁሉ ታናሽዋ ብላቴና አድርጋ አሳየቻት፡፡ የሰው ልጅን ከገነት ያስወጣው የእባቡና የሔዋን ቃለ ምልልስም ሰውን ወደ ገነት በመለሰው በገብርኤልና በማርያም ቃለ ምልልስ ተተካ፡፡ ሰይጣን በእባብ አድሮ የሠራውን ሰውን የማታለሉ የውድቀታችን ታሪክ 'እባብ ለሴቲቱ እንዲህ አላት' ተብሎ በየዕለቱ ሲተረክና የሰው ልጅን አንገት ሲያስደፋ እንዳልኖረ አሁን በተራችን የገብርኤልና የማርያምን ንግግር 'መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ እንዲህ አላት' እያልን በዘወትር ጸሎታችን ሳይቀር እየደጋገምን የምንጸልየውና የምንዘምረው የክብራችን ማስታወሻ ሆነ፡፡ በሴት ልጅ ይሁንታ ወደ ሞት ፍርድ የወረደውን የሰው ልጅ በሴት ልጅ ይሁንታ ወደ ሕይወት መመለሱን ፣ እየዘመርን የዲያብሎስን ሴራ መክሸፍ እናበሥራለን፡፡" የብርሃን እናት (ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ) ድንግል ሆይ ልደትሽ ልደታችን ነው
Mostrar todo...