ዕለታዊ ስንክሳር
Открыть в Telegram
ሁሌ ዝቅ ማለትን አብዝቶ መስማትን ገንዘብ እናድርግ። @Synaxarium "ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን" ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ
Больше1 458
Подписчики
+724 часа
+177 дней
+3430 день
Загрузка данных...
Похожие каналы
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июль '26
июль '26
+29
в 0 каналах
июнь '26
+37
в 0 каналах
Get PRO
май '26
+42
в 1 каналах
Get PRO
апрель '26
+58
в 0 каналах
Get PRO
март '26
+52
в 0 каналах
Get PRO
февраль '26
+82
в 0 каналах
Get PRO
январь '26
+79
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '25
+89
в 1 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+53
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '25
+27
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+51
в 1 каналах
Get PRO
август '25
+43
в 1 каналах
Get PRO
июль '25
+35
в 0 каналах
Get PRO
июнь '25
+102
в 0 каналах
Get PRO
май '25
+42
в 0 каналах
Get PRO
апрель '25
+43
в 1 каналах
Get PRO
март '25
+17
в 1 каналах
Get PRO
февраль '25
+25
в 1 каналах
Get PRO
январь '25
+39
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '24
+33
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+67
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '24
+46
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+61
в 0 каналах
Get PRO
август '24
+38
в 0 каналах
Get PRO
июль '24
+28
в 0 каналах
Get PRO
июнь '24
+3
в 0 каналах
Get PRO
май '24
+3
в 0 каналах
Get PRO
апрель '24
+31
в 0 каналах
Get PRO
март '24
+1
в 0 каналах
Get PRO
февраль '24
+6
в 0 каналах
Get PRO
январь '24
+7
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '23
+18
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+18
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '23
+11
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+22
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+46
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+20
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+14
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+36
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+7
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+13
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+122
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+22
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+11
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+22
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+19
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+42
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+119
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+44
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+20
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+16
в 0 каналах
Get PRO
апрель '22
+13
в 0 каналах
Get PRO
март '22
+12
в 0 каналах
Get PRO
февраль '22
+8
в 0 каналах
Get PRO
январь '22
+39
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '21
+20
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '21
+10
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '21
+14
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '21
+13
в 0 каналах
Get PRO
август '21
+34
в 0 каналах
Get PRO
июль '21
+23
в 0 каналах
Get PRO
июнь '21
+24
в 0 каналах
Get PRO
май '21
+27
в 0 каналах
Get PRO
апрель '21
+21
в 0 каналах
Get PRO
март '21
+440
в 0 каналах
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 11 июля | +1 | |||
| 10 июля | +7 | |||
| 09 июля | +4 | |||
| 08 июля | +6 | |||
| 07 июля | +2 | |||
| 06 июля | +2 | |||
| 05 июля | +2 | |||
| 04 июля | +1 | |||
| 03 июля | +1 | |||
| 02 июля | +1 | |||
| 01 июля | +2 |
Посты канала
| 2 | ግጻዌ አመ ፭ ለሐምሌ ለእመ ኮነ በሰንበት
💚💛❤ ❤💛💚
🇯 🇴 🇮 🇳 &🇸 🇭 🇦 🇷 🇪
✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ | 67 |
| 3 | መዝሙር ዘሰንበት
ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ
አሠርገዎሙ፤ ለሐዋርያት በሰማያት፤አሠርገዎሙ፤ ወንጌለ መንግሥት አወፈዮሙ፤አሠርገዎሙ ሰንበተ ክርስቲያን ለዕረፍት ሠርዓ ሎሙ፤አሠርገዎሙ ከመ ወርቅ በእሳት ፈተኖሙ፤አሠርገዎሙ ወከመ ጽንሐሐ መሥዋዕተ ተወክፎሙ፤ማ፦አሠርገዎሙ ፤ ለሐዋርያት በሰማያት
አመላለስ፦
አሠርገዎሙ አሠርገዎሙ ለሐዋርያት/፪/
ለሐዋርያት በሰማያት/፬/ | 101 |
| 4 | ✏️ ሌሊት ፡- በባህረ ሐሳብ አቆጣጠር ሌሊቱና ቀኑ የተለያየ አቆጣጠር አላቸው፤ ሌሊትን ለማግኘት 3 ነገሮችን እንደምራለን ፤
ሌሊት = አበቅቴ + ሠርቀ መዐልት + ሕጸጽ / 30
♠ ምሳሌ 1፡- የ2018 ዓ.ም ሐምሌ 5 ሌሊቱን ለማወቅ ፥-
✏️ ሌሊት = 12 + 5 + 6 = 23 ስለዚህ የ2018 ዓ.ም ሐምሌ 5 ሌሊቱ 23 ነው የሚያድረው ማለት ነው፡፡ ይህም የ2019 ዓ.ም አበቅቴ ነው።
✏️ ጨረቃ (ሠርቀ ወርኅ) ደግሞ 27 ነው ማለት ነው፡፡ ሌሊቱ የሚያገለግለን የቤተክርስቲያን አገልግሎት ምንጊዜም ከሌሊቱ ስለሚጀምር ነው።
✏️ ጨረቃ (ሠርቀ ወርኅ - 4) ፡- ልደተ ጨረቃ ማለት ጨረቃ የወጣችበት ዕለት ማለት ነው። ይህም ከሌሊቱ ላይ 4 በመደመር ይገኛል 4 የጨረቃ ተውሳክ ነው፡፡ ኪ.ወ.ክ ገጽ 404
✏️ ሠርቀ ወርኅ (ልደተ ጨረቃ - 4) አወጣጡ
ፀሐይ ከጨረቃ የምታተርፈው 11 ዕለት ብቻ አይደለም፡፡ 22 ኬክሮስ፣ 1ካልዒት፣ 37 ሣልሲት፣52 ራብዒት፣ 48 ኃምሲት አለ፡፡ ድሜጥሮስ ግን አጽዋማት በዓላት የሚውሉባቸው ዕለታትንና አውራኅን በፀሐይ መንገድ ለማግኘት 11ዱን ዕለታት ብቻ አበቅቴ አደረገ፡፡ የቀሩትን አልሻቸውም፡፡ ኋላ ግን አቡሻኽር ሠርቀ ሌሊትና ልደተ ወርኅ ባይተካከልለት ከላይ የዘረዘርናቸውን ከኬክሮስ እስከ ኃምሲት ያሉትን አጠራቅሞ ዕለታት አገኘ ስማቸውንም ትራፋተ ዓውድ አላቸው፤ ከአውደ አበቅቴ የተረፉ ማለት ነው፡፡ እኒህ ዕለታት እስከ ዛሬ ድረስ አራት (4) ዕለታት ሁነዋል፡፡ እኒህን አራት ዕለታት ካልጨመሩ እውነተኛ ልደተ ወርኅና ሠርቀ ሌሊት አይገኙም፡፡ ስለዚህ ባለው አበቅቴ ላይ አራት መጨመር ግድ ነው፡፡ (መርሐ ዕውር ገጽ 7 (367) | 111 |
| 5 | ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ አባት ይታይ ስለነበረ ታዴዎስን ወደ ሀገረ ስብከቱ ለማድረስ አብሮት ተጕዞ ነበር፡፡ ወደ ከተማዋ ሲጠጉም አንድ የሚያርሱ ሽማግሌ አገኙ፡፡ ሐዋርያቱ ወደ ሽማግሌው ጠጋ ብለው የእግዚአብሔር ሰላምታ ሰጧቸው፡፡ የሚበላ ነገር ያላቸው እንደሆነም ጠየቋቸው፡፡ ሽማግሌው ገበሬም ደግ ነበሩና ‹‹ከቤት እስካመጣላችሁ ድረስ በሬዎቼን ጠብቁልኝ›› ብለው ወደ መንደር ገቡ፡፡ ሐዋርያቱም ‹‹የተጠመዱትን በሬዎች ተቀምጦ መመልከት ሐፍረት ነው›› አሉና ታዴዎስ ማረስ ጀመረ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም የስንዴውን ዘር አነሣ፡፡ ‹‹ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! በረከትህ በዚህ እርሻ ላይ ትውረድ›› ብሎ ጸለየ፡፡ ታዴዎስም ‹‹የምድር በረከት በዚች እርሻ ይታይ ዘንድ አምላኬ ሆይ ፈቃድህ ይሁን›› አለ፡፡ 30 ትልም አረሱና የስንዴውን ቡቃያ ዕለቱን ወዲያው አበቀሉት፡፡ ወዲያውም ዕለቱን ዐይንን የሚማርክ የስንዴ እሸት ሆኖ ታየ፡፡ አረጋዊው ገበሬ ሲመለስ የእርሻውን መለምለም ተመልክቶ አደነቀና ‹‹ጌቶቼ እናንተ እነማን ናችሁ? በእውነት እናንተ ከሰማይ የወረዳችሁ አማልክት ናችሁ›› ብሎ በእግራቸው ሥር ወደቀ፡፡ ሐዋርያቱ ግን ‹‹እኛ የአምላክ ባሪያዎች እንጂ አማልክት አይደለንም›› ብለው የመጡበትን ምክንያት ነግረውት ወንጌልን አስተማሩት፡፡ ገበሬውም እየተደነቁ እሸቱን ታቅፈው ለቤተሰባቸው ሊያሳዩ ወደ ቤታቸው ሮጡ፡፡ የከተማዋ ሰዎችም ነገሩ ገርሟቸው ከበቧቸው፡፡ ሽማግሌው ገበሬም ያዩትንና የሰሙትን ሁሉ ተረኩላቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በማናቸውም ነገር ፈጣንና ቀልጣፋ ነበር፡፡ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ መሠረት ቅዱስ ጴጥሮስ በፍልስጤም፣ በሶርያ፣ በጳንጦን፣ በገላትያ፣ በቀጰዶቅያ፣ በቢታንያ እና በሮሜ ወንጌልን ሰብኳል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ አንድ ዓመት ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ካስተማረ በኋላ የሮሜ ክርስቲያኖች እየበዙ ከመምጣታቸውም በላይ የክርስትናው ጉዞ እስከ ሮማ ባለሥልጣናት ደረሰ፡፡ በትምህርቱና በተአምራቱ ካመኑት መካከል የሮማ ንጉሥ ባለሟልና የቅርብ ወዳጅ የሆነው አልታብዮስ ሚስቱ ክርስቲያን በመሆኗ በታላቅ ሀዘን ተለያዩ፡፡ በርካታ ሴቶችም አብረዋት ወደ ክርስትናው ዓለም ገቡ፡፡ የኔሮን የቅርብ ባለሥልጣናት የሆኑት የአልቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች ወደ ክርስትናው ገቡ፡፡ በዚህን ጊዜ ኔሮን ንጉሠ ሮማ በቅንዓት ተነሣባቸው፡፡ ኔሮን በሮም የነገሠው በ54 ዓ.ም ነው፡፡ በመንግሥቱ መጀመሪያ ደግ ሰው ነበረ፡፡ ነገር ግን በነገሠ በዓመቱ የጨካኝነት ዐመሉ ብቅ ማለት ጀመረና የአባቱን ልጅ አስገደለ፡፡ በ59 ዓ.ም ደግሞ እናቱን በመርዝ ገደለ፡፡ በ63 ዓ.ም እያስተማረ ያሳደገውን መምህሩን፣ በ62 ዓ.ም የልጅነት ሚስቱን አግታሺያን አስገደለ፡፡ ከእርሷም በኋላ ያገባትን ሚስቱን ፓፒያንም እንዲሁ ገደላት፡፡ ኔሮን በ64 ዓ.ም እርሱ ከከተማው ወጣ ብሎ በሚገኘው ቤተ መንግሥቱ ተቀምጦ የሮማን ከተማ እሳት ለቀቀባትና የሮም ሕዝብ በደረሰው አደጋ እጅግ መቆጣቱን ሲመለከት በክርስቲያኖች አመካኘ፡፡ በዚህም የተነሣ በሮማ ከተማ ሁለት ዓይነት ወሬ መናፈስ ጀመረ፡፡ ‹‹የሮማ አማልክት በክርስቲያኖች ሃይማኖት ስለተቆጡ በከተማዋ እሳት አዘነቡባት›› የሚለው የመጀመሪያው ሲሆን ‹‹ክርስቲያኖች ሆን ብለው ከተማዋን አቃጥለዋታል›› የሚለው ደግሞ ሁለተኛው ወሬ ነበር፡፡
የከተማው መጋየት ያበሳጨው የሮማ ሕዝብ፣ ክርስቲያን የሆነውን ሁሉ እያወጣ መግደሉን ተያያዘው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ሰዓት በእሥር ቤት ነበርና ተሰይፎ ዐረፈ፡፡ ይህን የሰሙት የአግቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች እነዚህም የሮም ባለሟሎች ነበሩና እነርሱም «ባይሆን አንተ ትረፍልን» ብለው ቅዱስ ጴጥሮስን በከተማዋ ግንብ በገመድ አሥረው በቅርጫት በማውረድ ቅጽረ ሮማን ለቅቆ እንዲወጣ አደረጉት፡፡ ሐዋርያው እንዳይታወቅ ራሱን ሰውሮ በኦፒየም ጎዳና ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ሮማን ለቆ እያዘገመ በሸመገለ ጉልበቱ ሲጓዝ አንድ ቀይ ጐልማሳ መስቀል ተሸክሞ ወደ እርሱ ሲመጣ አየ፡፡ እየቀረበ ሲመጣ ግን ጌታችን መሆኑን ተረዳ፡፡ ወዲያው በፊቱ ተደፋና «ጌታዬ ወዴት እየተጓዝክ ነው?» ብሎ ጠየቀው፡፡ ጌታችንም ‹‹ልሰቀል ወደ ሮም ከተማ እሄዳለሁ›› አለው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹ዳግመኛ ትሰቀላለህን?›› አለው፡፡ አስቀድሞ በምን ዓይነት ሞት ይሞት ዘንድ እንዳለው ሲነግረው ‹‹አንተ ጎልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደ ምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ፣ ሌላውም ያስታጥቅሃል፣ ወደማትወደውም ይወስድሃል›› ያለውን አስታውሶ እጅግ አዝኖ ወደ ሮም ከተማ ተመልሰ፡፡ የኔሮን ወታደሮችም እየፈለጉት ነበርና «እነሆኝ ስቀሉኝ» አላቸው፡፡ ያን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ይዘው አሠሩት፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላም ሮማውያን የመስቀያውን እንጨት ሲያቀርቡ ተመልክቶ ‹‹እኔ እንደጌታዬ ልሰቀል አይገባኝም እንደ ጌታዬ ሳይሆን ቁልቁል ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ›› ብሎ ለመናቸው፡፡ እነርሱም ፈቃዱን ፈጽመውለት ሐምሌ 5 ቀን 67 ዓ.ም ዘቅዝቀው ሰቅለውታል፡፡
የሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን።
ምንጭ፦ የሐምሌ 5️⃣ ስንክሳር
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
. ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼ | 98 |
| 6 | 👉 ሐምሌ 5 ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
🔥 ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ
በአራማይክ ኬፋ፣ በግሪክ ጴጥሮስ ማለት ‹‹ዓለት›› ማለት ነው፡፡ አንድም ጴጥሮስ ማለት የሃይማኖት መሠረት ማለት ነው፡፡ ማቴ 16፡18፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ የመጀመሪያ ስሙ ስምዖን ሲሆን ጌታችን ኬፋ ብሎ ሰይሞታል፡፡ በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው በቤተሳይዳ ተወለደ፡፡ ትውልዱ ከነገደ ሮቤል ሲሆን አባቱ ዮና ይባላል፡፡ የተወለደው በገሊላ አውራጃ በቤተ ሳይዳ ነው፡፡ ከአምስት ዓመቱ ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ነው፡፡ ጴርቴዋ የምትባል ሚስት የነበረችው ሲሆን የሚተዳደረው ዓሣ በማጥመድ ነበር፡፡ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር ዓሣ ከሚያጠምድበት ተጠርቶ ሐዋርያ ሆኗል፡፡
ለደቀመዛሙርነት ሲመረጥ ዕድሜው 53 ዓመት እንደነበረ ይነገራል፡፡ ወደ ጌታችን ያመጣውም ወንድሙ እንድርያስ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ፣ በርናባስ እና ወንጌላዊው ማርቆስ ቤተ ዘመድ ናቸው፡፡ የማርቆስ አባት አርስጦቡሎስ እና በርናባስ በእናት የሚገናኙ ወንድማማች ናቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ያገባው የበርናባስንና የአርስጦቡሎስን እኅት ስለነበር በጋብቻ ይዛመዳሉ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት ሲጠራ መተዳደሪያው የነበረውን መረቡንና ታንኳውን እንዲሁም አባቱን እርግፍ አድርጐ ትቶ ጌታውን የተከተለ ሐዋርያ ነው፡፡ የመጀመሪያ ስሙ ስምዖን ሲሆን ይህንንም እናቱ በነገዷ ስም ያወጣችለት ነው፡፡
በቂሳርያ ከተማ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ማን ትሉኛላችሁ?» ብሎ በጠየቀ ጊዜ «አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ» ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረውን ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን «አንተ ጴጥሮስ ነህ» ብሎታል ይህም በላቲን ቋንቋ ዓለት ማለት ነው፡፡ በአርማይክ ደግሞ ኬፋ ይባላል፡፡ በመቀጠልም ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን ሲመልስ ከጌታችን ዘንድ የተሰጠው መልስ ‹‹በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ስጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ፣ እኔም እልሃለሁ አንተ ጴጥሮስ ነህ፣ በዚህችም ዓለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሠራለሁ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም፡፡ የመንግስተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፣ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፤ በምድር የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል›› የሚል ነው፡፡ ይኸውም በወቅቱ የነበሩ ሐዋርያትና በኋላም በእርሱ እግር የሚተኩትን ካህናት አባቶችን ወክሎ የተቀበለው እጅግ አስደናቂና ቃልኪዳን ነው፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ ከአዕማድ ወይንም የምሥጢር ሐዋርያት ከሚባሉት ከእነ ዮሐንስ እና ያዕቆብ ጋር በመጀመሪያ የሚቆጠር ነው፡፡ ከሐዋርያት ሁሉ ቀደም ቀደም የማለት ባሕርይ ነበረው፡፡ ጌታችን በጥብርያዶስ ባሕር ላይ ሌሊት በእግሩ ሲመጣ ቢመለከት ‹‹ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ›› በማለት ካስፈቀደ በኋላ ወደ ጌታ ለመምጣት መንገድ ጀምሮ በመሐል ጥርጣሬ ገባውና መስጠም ስለጀመረ ጌታችን «ያመንክ እንጂ ያላመንክ አትሁን» ብሎ ገሥጾ ከመስጠም አድኖታል፡፡ ማቴ 14፡22-33፡፡ በቅፍርናሆም ጉባኤ ጌታችን ምሥጢረ ቍርባንን ሲያስተምር አይሁድ ስላልገባቸው ወደ ኋላ አፈገፈጉ፡፡ ከደቀ መዛሙርቱም «ብዙዎቹ ወደ ኋላ ተመለሱ» በዚህን ጊዜ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁ?» ብሎ ሐዋርያትን ጠየቃቸው፡፡ በዚህ ሰዓት «ጌታ ሆይ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘለዓለም የሕይወት ቃል አለህ፣ እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆንክ እናምናለን» በማለት ሐዋርያትን ወክሎ የመለሰ እርሱ ነው፡፡ ዮሐ 6፡66-68፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታችንን በጣም ይወድ ነበር፡፡ ፍቅሩ ግን ቅንዓት የተቀላቀለበት በመሆኑ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል። ማቴ 16፡23፡፡ በኋላም «ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም» ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር፡፡ ጌታችን «ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ» እያለው እንኳን «ከአንተ ጋር መሞት እንኳን የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም» በማለት ተከራክሯል፡፡ ማቴ 26፡34፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ አስቀድሞ የተናገረውን ቃል ለመጠበቅ ሞክሮ ነበር፡፡ ጌታችን ዛሬ «የሰው ልጅ ተላልፎ ይሰጣል» ብሎ አስተምሮአቸው ነበርና መከላከያ ይሆነኛል ብሎ ሠይፍ ደብቆ ይዞ ነበር፡፡ የሮም ጭፍሮችም ጌታችንን ለመያዝ ሲጠጉ የሊቀ ካህናቱን ባርያ (ማልኰስን) በሰይፍ ጆሮውን ቆረጠው፡፡ ዮሐ 18፡10፡፡ ጌታችን ግን ሞቱ በፍቃዱ ለድኅነተ ዓለም ነውና «ሰይፍህን ወደ ሰገባው መልስ›› ሲል ገሠጸው፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ የሚታወቅበት ሌላው ትልቁ ነገር ንስሓው ነው፡፡ ጌታችን በአይሁድ እጅ ከተያዘ በኋላ ጌታው አስቀድሞ ‹‹ትክደኛለህ›› ብሎ የነገረው መድረሱንና አምላኩን በመካድ መበደሉን እንዳወቀ ከግቢው ወጥቶ ተንሰቅስቆ አለቀሰ፡፡ በፍጹም ንስሓም ተመለሰ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በዕድሜው ታላቅነት በሐዋርያት ዘንድ እንደ አባት ይታይ ስለነበር ጌታችን ከተሰቀለ በኋላ ሐዋርያቱን ሊመግብ ወደሚያውቀው ሙያ ዓሳ ወደ ማስገሩ ተሠማራ፡፡ ጌታችንም አስቀድሞ የመረጠው እርሱ ነውና ቢክደው እንኳን በንስሐ በመመለሱ ንስሐውን መቀበሉን ዛሬም እንደሚወደው ይገልጽለት ዘንድ ዓሣ በሚያጠምድበት በጥብርያዶስ ባሕር ተገለጠለት፡፡ ሦስት ጊዜ ክዶት ነበርና ቀኖና ሰጠው፡፡ አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው ዐውቆአልና «ትወደኛለህን?» ተብሎ ሲጠየቅ «አንተ ታውቃለህ» ነበረ መልሱ፡፡ የራሱ ዕውቀት የት እንዳደረሰው ያውቃልና ጌታችንም በቀልን የሚተው ነውና ዛሬም እንደሚወደው በንስሓ ተመልሷልና ዛሬም ለእርሱ የሰጠውን ክብር እንደማያጐድልበት ሲነግረው (ግልገሎቼን አሰማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጐቼን አሰማራ» በማለት ምእመናንን ልጆቹን በአደራ አስረከበው፡፡ ዮሐ 21፡15-17፡፡ ከዚያም በሞቱ እንዴት አድርጐ እግዚአብሔርን እንደሚያከብረው ነግሮት ወደ ሰማያት ዐረገ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በይሁዳ ምትክ ሌላ ሐዋርያ እንዲመረጥ ሐሳብ ያቀረበ እርሱ ነበር። የሐዋ 1፡16-23፡፡ በበዓለ ሃምሳም ለደቀመዛሙርቱ መንፈስ ቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ ለተሰበሰቡት አይሁድ አፈ ጉባዔ ሆኖ ወንጌልን የሰበከ በአንዲት ዕለት ሦስት ሺህ ምእመናንንም አሳምኖ የመጀመሪያዋን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በኢየሩሳሌም የመሠረተ እርሱ ነው፡፡ የሐዋ 2፡14-37፡፡ አስቀድሞ ፈሪ የነበረውና በሊቀ ካህናት ቀያፋ ግቢ ጌታውን የካደው ቅዱስ ጴጥሮስ የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ካገኘ በኋላ ግን በአይሁድ ሸንጐ ድውይ ፈወስክ ተብሎ በተከሰሰ ጊዜ በድፍረት ስለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ መሰከረ፡፡ የሐዋ 4፡1-22፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ቆርነሌዎስን በማጥመቅ ወንጌልን ለአሕዛብ አስቀድሞ የሰበከው ሐዋርያ ነው።
የሐዋ 10፡1-11፡፡
ሐዋርያው ልዑል እግዚአብሔር ባደለው ጸጋ ጥላው እንኳን ድውያንን ይፈውስ ነበር፡፡ የሐዋ 5፡15፡፡ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 15 ላይ እንደተጠቀሰው በ50 ዓ.ም አካባቢ በኢየሩሳሌም በተደረገው የሐዋርያት ሲኖዶስ ከአንጾኪያ ክርስቲያኖች ለቀረበው ጥያቄ የመጀመሪያውን መልስ የሰጠው እርሱ ነበር፡፡ ስለ ቅዱስ ጴጥሮስ መልክና ቁመና ጥንታዊያን መዛግብት እንደሚከተለው ያቀርቡታል። «ፊቱ ሰፋ ያለ ሲሆን ሪዛምና መካከለኛ ቁመት የነበረው ራሰ በራ ነው። | 90 |
| 7 | Нет текста... | 89 |
| 8 | 🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀
ሥርዓተ ማኅሌት አመ ፭ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸
የሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ #ሥርዓተ_ማኅሌት ከሊቃውንቱ ጋራ አብረን ለማመስገን ይረዳን ዘንድ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል።
#ሥርዓተ_ነግሥ:-
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
#መልክዐ_ሥላሴ
ሰላም ለቃልክሙ መታሬ እሳት ነዳዲ፤ሥሉስ ቅዱስ ንዋያተ ዕፁብ ነጋዲ፤አመ በንስሐ ተወልዱ እምጸጋክሙ ወላዲ፤ተወፈየ መርኆ ሰማይ የማነ ጴጥሮስ ከሐዲ፤ወመምህረ ወንጌል ኮነ ጳውሎስ ሰዳዲ።
#ዚቅ
ጸጋ ዘአብ ኂሩት ዘወልድ፤ሱታፌ ዘመንፈስ ቅዱስ፤ተውህቦሙ ለሐዋርያት።
#ነግሥ
ሰላም ለመልክዕክሙ እመልክዐ አዳም ዘተቶስሐ፤እግዚአብሔር ፈጣሪ ዘኮነክሙ መርሐ፤፲ወ፪ቱ እለ ሰበክሙ ቃለ ንስሐ፤ሥረዩ ኃጢአትየ ወጌጋይየ ብዙኀ፤በእንተ ማርያም ድንግል በህሊናሃ ወድንግል በሥጋሃ።
#ዚቅ
ሐዋርያተ ሰላም ክቡራነ ስም፤ሥረዩ ኃጢአተ ዓለም፤በእንተ ኢየሱስ ክርስቶስ ወበእንተ ድንግል እም።
#መልክዐ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ
ሰላም ለመቃብሪከ በመካነ ሐዋዝ ሃሌ ሉያ፤ወለትንሣኤከ ድኅረ ዘይከውን በዕለተ ምርያ፤ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሞተከ ታብዕል ኢትዮጵያ፤ለጴጥሮስ በዓለ መርኆ ወለጳውሎስ ሐዋርያ፤ከመ ተዝካሮሙ ታብዕል ሮምያ።
#ዚቅ
ንግበር ተዝካሮሙ ለእለ እግዚእ ኃረዮ፤ዓጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ።
#መልክዐ_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ
ሰላም ለዝክረ ስምክሙ ዘአልባስጥሮስ አፈው፤ወለሥዕርትክሙ ጸሊም ዘድላሌሁ ፍትው፤ምቱረ ክሣድ ጳውሎስ ወጴጥሮስ ቅንው፤ተራወጸ ውስተ ልብየ ምስል መዓዛሁ ቅድው፤ደመ ስምክሙ ሐዋርያ ዘኅብሩ ከዋው።
#ዚቅ
ሃሌ ሉያ፤ከዋው እገሪሆሙ፤ለእለ ይዜንዉ ዜና ሠናየ፤ዘእግዚአብሔር ፈነዎ፤ቃለ እግዚአብሔር ይነግር።
#ሃሌ_ሉያ/፪/
ከዋው እገሪሆሙ/፪/
#ወረብ
ከዋው እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ዜና ሠናየ ለእለ ይዜንዉ/፪/
ዘእግዚአብሔር ፈነዎ ይነግር ቃለ እግዚአብሔር/፪/
#መልክዐ_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ
ሰላም ለአዕዛኒክሙ ለሰሚዓ ወንጌል ዘተሰብሐ፤ወለመላትሒክሙ ቀይሐት እምነ ሮማን ዘቄሃ፤መሥዋዕተ አምልኮት ኩኑ ወዘመሃይምናን ምክሐ፤ደምከ ጴጥሮስ ወልደ ዮና በጽዋዓ መስቀል ተቀድሐ፤ወደመ ጳውሎስ ሐዋርያ ሰማያተ ጸርሐ።
#ዚቅ
ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም እንተ ትቀትሎሙ ለነቢያቲሃ፤ወትዌግሮሙ ለሐዋርያቲሃ፤ሚ መጠን ዘተክዕወ ዲቤሃ፤እምደመ ጳውሎስ ሐዋርያ፤እስከ ደመ ጴጥሮስ ወልደ ዮና።
#ወረብ
ሚ መጠን ዘተክዕወ ዲቤሃ ለኢየሩሳሌም/፪/
እምደመ ጳውሎስ ሐዋርያ እስከ ደመ ጴጥሮስ ወልደ/፪/
#ዓዲ
በሀኪ ኦ ዓባይ ሀገር ሮሜ፤ሀገረ ነጐድጓድ ሀገረ እግዚአብሔር፤እንተ ተሰመይኪ ገነተ፤ደሞሙ ለሰማዕታትኪ ውኅዘ ከመ ማይ፤ድምፀ ነጐድጓዶሙ በጽሐ እስከ ሰማይ።
#መልክዐ_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ
ሰላም ለዘባናቲክሙ በምኲራባት እለ ተቀሥፋ፤ወለእንግድዓክሙ ዘሰፍሐ መልዕልተ ጠበብት ወፈላስፋ፤በእንተ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተጸፍአ ቅድመ ቀያፋ፤ሀበኒ ጴጥሮስ መስቀለከ ይኲነኒ ተስፋ፤ወጳውሎስ ዉቅየተከ እንተ ደም ለከፋ።
#ዚቅ
እስመ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ዘተሠውጠ ላዕለ ኲሎሙ ሐዋርያት፤በመንፈስ ቅዱስ ነበቡ በነገረ ኲሉ በሐውርት፤ይኲነነ አክሊለ መዊዕ ወተስፋ፤በረከቶሙ ለሳውል ወኬፋ።
#ወረብ
እስመ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ዘተሰውጠ ላዕለ ሐዋርያት/፪/
በመንፈስ ቅዱስ ነበቡ በነገረ ኲሉ በሐውርት/፪/
#መልክዐ_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ
ሰላም ዕብል ብርሃናተ ፪ኤተ፤በዓውደ ንጉሥ ኔሮን እለ ፈጸሙ ሩጸተ፤ጳውሎስ ወጴጥሮስ ዘያጸንዑ ፀበርተ፤አሐዱ በመስቀል ተሰቅለ ቊልቊሊተ፤ወካልዑ (ወአሐዱ) ተመትረ ክሣዱ ክብርተ።
#ዚቅ
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ብርሃናተ ዓለም ሐዋርያተ ሰላም ሱቱፋነ ሕማም፤አሥራበ ምሕረት ከዓዉ እምአርያም።
#ወረብ
ሐዋርያተ ሰላም "ብርሃናተ ዓለም"/፪//፪/
አሥራበ ምሕረት ከዓዉ ከዓዉ እምአርያም/፪/
#መልክዐ_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ
ተዘኪረከ ክርስቶስ ዘሐዋርያት ኲሎሙ፤ህየንተ ክቡር ደምከ እለ ከዓዉ ደሞሙ፤አክሊለ ስምዕ ሀበኒ ከመ እሳተፍ ገድሎሙ፤ወደምስስ ለአጽራርየ እመጽሐፈ ህይወት ዝክሮሙ፤ከመ ለይሁዳ ረሲዕ ተደምሰሰ ስሙ።
#ዚቅ
ስምዖን ጴጥሮስ ወአኃዊሁ ሱቱፋነ ሕማምከ፤እለ ከዓዉ ደሞሙ ህየንተ ደምከ፤ከመ ይኩን ተውሳከ ለሴጠ አሕዛብ በስብከተ ወንጌልከ፤በከመ ተቶስሐ መዓዛ ክህነትከ በክህነቶሙ፤ቶስሕ ስእለተነ በስእለቶሙ፤ጸግወነ ሎሙ ከመ ንድኃን ቦሙ።
#ወረብ
ስምዖን ጴጥሮስ ወአኃዊሁ "ሱቱፋነ ሕማምከ"/፪//፪/
እለ ከዓዉ ደሞሙ ደሞሙ ህየንተ ደምከ/፪/
#መልክዐ_ኢየሱስ
ሰላም ለእራኅከ መክፈልተ ሕማማት ሱቱፍ፤ወቅንዋቲሁ እኤምሕ በአፍ፤ኢየሱስ ክርስቶስ በላዕለ ቅዱሳን ዕሩፍ፤ይፀነስ ውስተ ከርሥየ ዘርአ ቃልከ መጽሐፍ፤ጸዳለ እምጸዳል ከመ ትፀንስ ዖፍ።
#ዚቅ
እግዚአ ውእቱ ለሰንበት ውእቱ፤አቡሃ ለምሕረት ውእቱ፤ኃያል ወብዙኅ ሣህል ውእቱ፤ዘባሕቲቱ በቅዱሳኒሁ ዕሩፍ።
#አንገርጋሪ
ይቤሎ ጴጥሮስ ለጳውሎስ ጥባዕኬ እኁየ ጳውሎስ ወኢትናፍቅ እምዝ ዳግመ ኢንመውት ዳግመ ወእምዝ ዳግመ ኢንመውት።
#ምልጣን
እምዝ ዳግመ ኢንመውት ዳግመ ወእምዝ ዳግመ ኢንመውት።
#አመላለስ፦
ወእምዝ ዳግመ /፪/
ዳግመ ኢንመውት/፬/
✅ ወረብ
ይቤሎ ጴጥሮስ ለጳውሎስ ጥባዕኬ እኁየ ጳውሎስ እኁየ/፪/
ወኢትናፍቅ ዳግመ እምዝ ዳግመ ኢንመውት/፪/
✅ እስመ ለዓለም
ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን፤አርድዕት ልዑላን አዕማደ ቤተ ክርስቲያን፤ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ፤ወኲሎሙ ሐዋርያት፤ፈድፋደ ቦሙ ሞገስ በኀበ ኲሎሙ ሕዝብ።
✅ ወረብ
ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን አዕማደ ቤተክርስቲያን/፪/
ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ/፪/
✅ ቅንዋት፦
ናስተበቊዓከ በእንተ ሐዋርቲከ፤እለ ፆሩ ወንጌለከ በሕማሞሙ፤እለ ሐረስዋ ለምድረ አእዛብ በዕርፈ መስቀልከ፤ወዘርዑ መዝገበ ቃልከ፤ውስተ ኵሉ ምድር።
✅ እስመ ለዓለም ዘሰንበት
ምሕሮሙ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ ለእለ መጽኡ ኀቤሁ በዕለተ ሰንበት፤ ወይቤሎሙ ለእመ ሰማዕክሙኒ ቃልየ፤ወተአገሥክሙ በሕግየ፤ወለእመ ሰማዕክሙኒ ዘንተ ትእዛዘ ዘእኤዝዘክሙ አነ፤ አዘንም ለክሙ በረከተ፤ እስመ አነ ውእቱ አምላክ ኄር፤ ዘእክል ረድኦ ወእክል አድኅኖ፤ እክለ ኅዳጣተ አብዝኆተ እክል ባርኮተ እክል ፣ይቤ እግዚአብሔር።
👉 ስህተት ቢኖር እናንተ በመንፈስ ያላችሁ አቃኑት
🇯 🇴 🇮 🇳 &🇸 🇭 🇦 🇷 🇪
✥┈┈•◦●◈◎❖◎◈●◦•┈┈✥
✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
#ይቀላቀሉ & #ለወዳጅዎ_ሼር_ያርጉ | 122 |
| 9 | Нет текста... | 92 |
| 10 | Нет текста... | 1 |
| 11 | ሥርዓተ ዋይዜማ አመ ፭ ሡ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
የሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ሥርዓተ ዋይዜማ
መኃትው አመ ሐሙሱ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሃሌ ሉያ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በሀገረ ፊሊጶስ ፈጸሙ ገድሎሙ፤መጽአ አፍራሰ እሳት ወመሠጦሙ፤ወሀለዉ ሕዝብ ይኔጽሩ ዕርገቶሙ፤ተመይጠ ጴጥሮስ መንገሌሆሙ፤ወይቤሎሙ ምንተኑ ትኔጽሩነ፤ከመ ዘበኃይልነ ገበርነ፤አዕርገነ ትእዛዙ ለአምላክነ፤ዕቀቡ ትእዛዞ ለአምላክክሙ።
#ዋዜማ_በ_6_ሃሌታ
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወረዱ ወቦዑ፤ሀገረ ፊልጶስ፤ቦኡ ልድያ ወበህየ ረከቡ ብእሴ፤ዘስሙ ኤንያ፤በሰላሣ ወሰምንተ ክረምተ ሐመ፤ፈወስዎ ወአሕየውዎ፤ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ።
#ምልጣን፦
ቦኡ ልድያ ወበህየ ረከቡ ብእሴ፤ ዘስሙ ኤንያ፤ በሰላሳ ወሰምንተ ክረምተ ሐመ፤ፈወስዎ ወአሕየውዎ፤ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ፤ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ
#አመላለስ፦
ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ/2/
ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ/4/
በ፭ ለእግዚአብሄር ምድር በምልዓ፦
አዕማድ እሙንቱ የማኖሙ ወድሙር ኲሉ ንዋዮሙ አዕማድ እሙንቱ የማኖሙ።
#እግዚብሔር_ነግሠ፦
ኃረየ ዐስርተ ወክልኤተ ሐዋርያተ ሤሞሙ ኖሎተ ይቤሎሙ ኢየሱስ ዘኪያክሙ ስምዓ ኪያየ ሰምዓ ስምዖ ለዘፈነወኒ።
#እግዚኦ_ጸራእኩ_ኃቤከ፦
ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን ለእንተ ይብልዋ ቅድስተ ቅዱሳን ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን
#ይትባረክ_እግዚአብሔር፦
አንትሙሰ ኅሩያን ፍጥረትክሙ ስብኩ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያት ሕዝብ ዘኃርየ ወጸውዐ ሎቱ ለርስቱ፤
ስቡሕኒ፦ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፤ዘኪያክሙ ስምዓ ኪያየ ስምዐ ስምዖ ለዘፈነወኒ።
#ጸሎተ_ዘሰለስቱ_ደቂቅ፦
ስምዖን ጴጥሮስ ወጳውሎስ፤ቦኡ ሀገሮ ለኤንያ ወበህየ ፈወሱ ዱያነ።
#ሰላም፦
ስምዖን ጴጥሮስ ወጳውሎስ፤ቦኡ ልድያ ሀገሮ ለኤንያ ወበህየ ፈወሱ ዱያነ ዘስሙ ለኢየሱስ ገብሩ ሰላመ።
#አመላለስ፦
ወበህየ ፈወሱ ዱያነ /2/
ዘስሙ ለኢየሱስ ገብሩ ሰላመ /4/
➾✍እመሒ ስሕተኩ አንትሙ እለ በመንፈስ አርትዕ(የተሳሳትኩት ቢኖር እናንተ በመንፈስ ያላችሁ አቃኑት)🙏
🅵🅾🅻🅻🅞🆆 // 🆂🅷🅰🆁🅴
ዜና ተዋሕዶ | 70 |
| 12 | Нет текста... | 87 |
| 13 | 💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ወረብ
ይቤሎ ጴጥሮስ ለጳውሎስ ጥባዕኬ እኁየ ጳውሎስ እኁየ/፪/
ወኢትናፍቅ ዳግመ እምዝ ዳግመ ኢንመውት/፪/
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
እስመ ለዓለም
ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን፤አርድዕት ልዑላን አዕማደ ቤተ ክርስቲያን፤ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ፤ወኲሎሙ ሐዋርያት፤ፈድፋደ ቦሙ ሞገስ በኀበ ኲሎሙ ሕዝብ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ወረብ
ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን አዕማደ ቤተክርስቲያን/፪/
ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ/፪/
💚💛❤ @Misbak_WeMahlet ❤💛💚
ቅንዋት፦
ናስተበቊዓከ በእንተ ሐዋርቲከ፤እለ ፆሩ ወንጌለከ በሕማሞሙ፤እለ ሐረስዋ ለምድረ አእዛብ በዕርፈ መስቀልከ፤ወዘርዑ መዝገበ ቃልከ፤ውስተ ኵሉ ምድር።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
እስመ ለዓለም ዘሰንበት
ምሕሮሙ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ ለእለ መጽኡ ኀቤሁ በዕለተ ሰንበት፤ ወይቤሎሙ ለእመ ሰማዕክሙኒ ቃልየ፤ወተአገሥክሙ በሕግየ፤ወለእመ ሰማዕክሙኒ ዘንተ ትእዛዘ ዘእኤዝዘክሙ አነ፤ አዘንም ለክሙ በረከተ፤ እስመ አነ ውእቱ አምላክ ኄር፤ ዘእክል ረድኦ ወእክል አድኅኖ፤ እክለ ኅዳጣተ አብዝኆተ እክል ባርኮተ እክል ፣ይቤ እግዚአብሔር።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
➾✍እመሒ ስሕተኩ አንትሙ እለ በመንፈስ አርትዕ(የተሳሳትኩት ቢኖር እናንተ በመንፈስ ያላችሁ አቃኑት)
🙏🙏🙏
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
🇯 🇴 🇮 🇳 &🇸 🇭 🇦 🇷 🇪
✥┈┈•◦●◈◎❖◎◈●◦•┈┈✥
✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
#ይቀላቀሉ & #ለወዳጅዎ_ሼር_ያርጉ | 6 |
| 14 | ምስባክ ወማኅሌት:
🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀
ሥርዓተ ማኅሌት አመ ፭ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸
የሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ #ሥርዓተ_ማኅሌት ከሊቃውንቱ ጋራ አብረን ለማመስገን ይረዳን ዘንድ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ሥርዓተ ነግሥ:-
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
መልክዐ ሥላሴ
ሰላም ለቃልክሙ መታሬ እሳት ነዳዲ፤ሥሉስ ቅዱስ ንዋያተ ዕፁብ ነጋዲ፤አመ በንስሐ ተወልዱ እምጸጋክሙ ወላዲ፤ተወፈየ መርኆ ሰማይ የማነ ጴጥሮስ ከሐዲ፤ወመምህረ ወንጌል ኮነ ጳውሎስ ሰዳዲ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዚቅ
ጸጋ ዘአብ ኂሩት ዘወልድ፤ሱታፌ ዘመንፈስ ቅዱስ፤ተውህቦሙ ለሐዋርያት።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ነግሥ
ሰላም ለመልክዕክሙ እመልክዐ አዳም ዘተቶስሐ፤እግዚአብሔር ፈጣሪ ዘኮነክሙ መርሐ፤፲ወ፪ቱ እለ ሰበክሙ ቃለ ንስሐ፤ሥረዩ ኃጢአትየ ወጌጋይየ ብዙኀ፤በእንተ ማርያም ድንግል በህሊናሃ ወድንግል በሥጋሃ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዚቅ
ሐዋርያተ ሰላም ክቡራነ ስም፤ሥረዩ ኃጢአተ ዓለም፤በእንተ ኢየሱስ ክርስቶስ ወበእንተ ድንግል እም።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
መልክዐ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
ሰላም ለመቃብሪከ በመካነ ሐዋዝ ሃሌ ሉያ፤ወለትንሣኤከ ድኅረ ዘይከውን በዕለተ ምርያ፤ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሞተከ ታብዕል ኢትዮጵያ፤ለጴጥሮስ በዓለ መርኆ ወለጳውሎስ ሐዋርያ፤ከመ ተዝካሮሙ ታብዕል ሮምያ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዚቅ
ንግበር ተዝካሮሙ ለእለ እግዚእ ኃረዮ፤ዓጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሰላም ለዝክረ ስምክሙ ዘአልባስጥሮስ አፈው፤ወለሥዕርትክሙ ጸሊም ዘድላሌሁ ፍትው፤ምቱረ ክሣድ ጳውሎስ ወጴጥሮስ ቅንው፤ተራወጸ ውስተ ልብየ ምስል መዓዛሁ ቅድው፤ደመ ስምክሙ ሐዋርያ ዘኅብሩ ከዋው።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዚቅ
ሃሌ ሉያ፤ከዋው እገሪሆሙ፤ለእለ ይዜንዉ ዜና ሠናየ፤ዘእግዚአብሔር ፈነዎ፤ቃለ እግዚአብሔር ይነግር።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
አመላለስ
ሃሌ ሉያ/፪/
ከዋው እገሪሆሙ/፪/
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ወረብ
ከዋው እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ዜና ሠናየ ለእለ ይዜንዉ/፪/
ዘእግዚአብሔር ፈነዎ ይነግር ቃለ እግዚአብሔር/፪/
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሰላም ለአዕዛኒክሙ ለሰሚዓ ወንጌል ዘተሰብሐ፤ወለመላትሒክሙ ቀይሐት እምነ ሮማን ዘቄሃ፤መሥዋዕተ አምልኮት ኩኑ ወዘመሃይምናን ምክሐ፤ደምከ ጴጥሮስ ወልደ ዮና በጽዋዓ መስቀል ተቀድሐ፤ወደመ ጳውሎስ ሐዋርያ ሰማያተ ጸርሐ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዚቅ
ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም እንተ ትቀትሎሙ ለነቢያቲሃ፤ወትዌግሮሙ ለሐዋርያቲሃ፤ሚ መጠን ዘተክዕወ ዲቤሃ፤እምደመ ጳውሎስ ሐዋርያ፤እስከ ደመ ጴጥሮስ ወልደ ዮና።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ወረብ
ሚ መጠን ዘተክዕወ ዲቤሃ ለኢየሩሳሌም/፪/
እምደመ ጳውሎስ ሐዋርያ እስከ ደመ ጴጥሮስ ወልደ/፪/
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዓዲ
በሀኪ ኦ ዓባይ ሀገር ሮሜ፤ሀገረ ነጐድጓድ ሀገረ እግዚአብሔር፤እንተ ተሰመይኪ ገነተ፤ደሞሙ ለሰማዕታትኪ ውኅዘ ከመ ማይ፤ድምፀ ነጐድጓዶሙ በጽሐ እስከ ሰማይ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሰላም ለዘባናቲክሙ በምኲራባት እለ ተቀሥፋ፤ወለእንግድዓክሙ ዘሰፍሐ መልዕልተ ጠበብት ወፈላስፋ፤በእንተ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተጸፍአ ቅድመ ቀያፋ፤ሀበኒ ጴጥሮስ መስቀለከ ይኲነኒ ተስፋ፤ወጳውሎስ ዉቅየተከ እንተ ደም ለከፋ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዚቅ
እስመ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ዘተሠውጠ ላዕለ ኲሎሙ ሐዋርያት፤በመንፈስ ቅዱስ ነበቡ በነገረ ኲሉ በሐውርት፤ይኲነነ አክሊለ መዊዕ ወተስፋ፤በረከቶሙ ለሳውል ወኬፋ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ወረብ
እስመ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ዘተሰውጠ ላዕለ ሐዋርያት/፪/
በመንፈስ ቅዱስ ነበቡ በነገረ ኲሉ በሐውርት/፪/
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሰላም ዕብል ብርሃናተ ፪ኤተ፤በዓውደ ንጉሥ ኔሮን እለ ፈጸሙ ሩጸተ፤ጳውሎስ ወጴጥሮስ ዘያጸንዑ ፀበርተ፤አሐዱ በመስቀል ተሰቅለ ቊልቊሊተ፤ወካልዑ (ወአሐዱ) ተመትረ ክሣዱ ክብርተ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዚቅ
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ብርሃናተ ዓለም ሐዋርያተ ሰላም ሱቱፋነ ሕማም፤አሥራበ ምሕረት ከዓዉ እምአርያም።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ወረብ
ሐዋርያተ ሰላም "ብርሃናተ ዓለም"/፪//፪/
አሥራበ ምሕረት ከዓዉ ከዓዉ እምአርያም/፪/
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ተዘኪረከ ክርስቶስ ዘሐዋርያት ኲሎሙ፤ህየንተ ክቡር ደምከ እለ ከዓዉ ደሞሙ፤አክሊለ ስምዕ ሀበኒ ከመ እሳተፍ ገድሎሙ፤ወደምስስ ለአጽራርየ እመጽሐፈ ህይወት ዝክሮሙ፤ከመ ለይሁዳ ረሲዕ ተደምሰሰ ስሙ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዚቅ
ስምዖን ጴጥሮስ ወአኃዊሁ ሱቱፋነ ሕማምከ፤እለ ከዓዉ ደሞሙ ህየንተ ደምከ፤ከመ ይኩን ተውሳከ ለሴጠ አሕዛብ በስብከተ ወንጌልከ፤በከመ ተቶስሐ መዓዛ ክህነትከ በክህነቶሙ፤ቶስሕ ስእለተነ በስእለቶሙ፤ጸግወነ ሎሙ ከመ ንድኃን ቦሙ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ወረብ
ስምዖን ጴጥሮስ ወአኃዊሁ "ሱቱፋነ ሕማምከ"/፪//፪/
እለ ከዓዉ ደሞሙ ደሞሙ ህየንተ ደምከ/፪/
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
መልክዐ ኢየሱስ
ሰላም ለእራኅከ መክፈልተ ሕማማት ሱቱፍ፤ወቅንዋቲሁ እኤምሕ በአፍ፤ኢየሱስ ክርስቶስ በላዕለ ቅዱሳን ዕሩፍ፤ይፀነስ ውስተ ከርሥየ ዘርአ ቃልከ መጽሐፍ፤ጸዳለ እምጸዳል ከመ ትፀንስ ዖፍ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዚቅ
እግዚአ ውእቱ ለሰንበት ውእቱ፤አቡሃ ለምሕረት ውእቱ፤ኃያል ወብዙኅ ሣህል ውእቱ፤ዘባሕቲቱ በቅዱሳኒሁ ዕሩፍ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
አንገርጋሪ
ይቤሎ ጴጥሮስ ለጳውሎስ ጥባዕኬ እኁየ ጳውሎስ ወኢትናፍቅ እምዝ ዳግመ ኢንመውት ዳግመ ወእምዝ ዳግመ ኢንመውት።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ምልጣን
እምዝ ዳግመ ኢንመውት ዳግመ ወእምዝ ዳግመ ኢንመውት።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
አመላለስ፦
ወእምዝ ዳግመ /፪/
ዳግመ ኢንመውት/፬/ | 4 |
| 15 | 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ሥርዓተ ዋይዜማ አመ ፭ ሡ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
የሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
መኃትው አመ ሐሙሱ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሃሌ ሉያ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በሀገረ ፊሊጶስ ፈጸሙ ገድሎሙ፤መጽአ አፍራሰ እሳት ወመሠጦሙ፤ወሀለዉ ሕዝብ ይኔጽሩ ዕርገቶሙ፤ተመይጠ ጴጥሮስ መንገሌሆሙ፤ወይቤሎሙ ምንተኑ ትኔጽሩነ፤ከመ ዘበኃይልነ ገበርነ፤አዕርገነ ትእዛዙ ለአምላክነ፤ዕቀቡ ትእዛዞ ለአምላክክሙ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ዋዜማ በ 6 ሃሌታ
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወረዱ ወቦዑ፤ሀገረ ፊልጶስ፤ቦኡ ልድያ ወበህየ ረከቡ ብእሴ፤ዘስሙ ኤንያ፤በሰላሣ ወሰምንተ ክረምተ ሐመ፤ፈወስዎ ወአሕየውዎ፤ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ምልጣን፦
ቦኡ ልድያ ወበህየ ረከቡ ብእሴ፤ ዘስሙ ኤንያ፤ በሰላሳ ወሰምንተ ክረምተ ሐመ፤ፈወስዎ ወአሕየውዎ፤ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ፤ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
አመላለስ፦
ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ/2/
ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ/4/
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
በ፭ ለእግዚአብሄር ምድር በምልዓ፦
አዕማድ እሙንቱ የማኖሙ ወድሙር ኲሉ ንዋዮሙ አዕማድ እሙንቱ የማኖሙ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
እግዚብሔር ነግሠ፦
ኃረየ ዐስርተ ወክልኤተ ሐዋርያተ ሤሞሙ ኖሎተ ይቤሎሙ ኢየሱስ ዘኪያክሙ ስምዓ ኪያየ ሰምዓ ስምዖ ለዘፈነወኒ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
እግዚኦ ጸራእኩ ኃቤከ፦
ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን ለእንተ ይብልዋ ቅድስተ ቅዱሳን ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ይትባረክ እግዚአብሔር፦
አንትሙሰ ኅሩያን ፍጥረትክሙ ስብኩ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያት ሕዝብ ዘኃርየ ወጸውዐ ሎቱ ለርስቱ፤
ስቡሕኒ፦ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፤ዘኪያክሙ ስምዓ ኪያየ ስምዐ ስምዖ ለዘፈነወኒ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ጸሎተ ዘሰለስቱ ደቂቅ፦
ስምዖን ጴጥሮስ ወጳውሎስ፤ቦኡ ሀገሮ ለኤንያ ወበህየ ፈወሱ ዱያነ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
ሰላም፦
ስምዖን ጴጥሮስ ወጳውሎስ፤ቦኡ ልድያ ሀገሮ ለኤንያ ወበህየ ፈወሱ ዱያነ ዘስሙ ለኢየሱስ ገብሩ ሰላመ።
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
አመላለስ፦
ወበህየ ፈወሱ ዱያነ /2/
ዘስሙ ለኢየሱስ ገብሩ ሰላመ /4/
💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
➾✍እመሒ ስሕተኩ አንትሙ እለ በመንፈስ አርትዕ(የተሳሳትኩት ቢኖር እናንተ በመንፈስ ያላችሁ አቃኑት)🙏💚💛❤ @Synaxarium ❤💛💚
join and share | 3 |
| 16 | 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
አመ ፭ሡ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ስርአተ ዋይዜማ
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
ዋዜማ በ6 ሃሌታ-
@Synaxarium
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ
ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወረዱ ወቦዑ፤ ሀገረ ፊልጶስ፤ ቦኡ ልድያ ወበህየ ረከቡ ብእሴ ፤ ዘስሙ ኤንያ ፤ በሰላሳ ወሰምንተ ክረምተ ሐመ ፤ፈወስዎ ወአሕየውዎ፤ ማ፦ ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ
@Synaxarium
ምልጣን፦
ቦኡ ልድያ ወበህየ ረከቡ ብእሴ ፤ ዘስሙ ኤንያ በሰላሳ ወሰምንተ ክረምተ ሐመ ፤ፈወስዎ ወአሕየውዎ፤ ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ፤ ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ
@Synaxarium
አመላለስ፦
ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ/፪/
ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ/፪/
@Synaxarium
ለእግዚአብሄር ምድር በምልዓ፦
አዕማድ እሙንቱ የማኖሙ ወድሙር ኩሉ ንዋዮሙ አዕማድ እሙንቱ የማኖሙ
@Synaxarium
እግዚያብሔር ነግሠ፦
ኃረየ ዐስርተ ወክልኤተ ሐዋርያተ ሤሞሙ ኖሎት ይቤሎሙ ኢየሱስ ዘኪያክሙ ስምዓ ኪያየ ስምዖ ለዘፈነወኒ
@Synaxarium
እግዚኦ ጸራእኩ ኃቤከ፦
ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን ለእንተ ይብልዋ ቅድስተ ቅዱሳን ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን
@Synaxarium
ይትባረክ እግዚያብሔር ፦
አንትሙሰ ኅሩያን ፍጥረትክሙ ስብኩ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያት ሕዝብ ዘኃርየ ወጸውዐ ሎቱ ለርስቱ
@Synaxarium
ስቡዕኒ፦
ዘኪያክሙ ስምዓ ኪያየ ስምዐ ስምዖ ለዘፈነወኒ
@Synaxarium
ጸሎተ ዘሰለስቱ ደቂቅ፦
ስምዖን ጴጥሮስ ወጳውሎስ ፤ ቦኡ ሀገሮ ለኤንያ ወበህየ ፈወሱ ዱያነ
@Synaxarium
ሰላም፦
ስምዖን ጴጥሮስ ወጳውሎስ ፤ ቦኡ ልድያ ሀገሮ ለኤንያ ወበህየ ፈወሱ ዱያነ በስሙ ለኢየሱስ ገብሩ ሰላመ
@Synaxarium
አመላለስ፦
ወበህየ ፈወሱ ዱያነ /2/
በስሙ ለኢየሱስ ገብሩ ሰላመ /4/
👇👇👇👇👇👇🇪🇹
👉@Synaxarium👈
👉@Synaxarium👈
👉@Synaxarium👈
🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹
@Synaxarium
# Join & share # | 4 |
| 17 | ግጻዌ ዘሐምሌ 4 | 82 |
| 18 | አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።
ሐምሌ 4 ስለክርስቶስ ትንቢታቸውን እንደፈሳሽ ውኃ ያጎረፉ የ12ቱ ደቂቀ ነቢያት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ነው፡፡
➛ ነቢዩ ቅዱስ ሶፎንያስ ዕረፍቱ ነው፡፡
➥ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ቅዱሳን የሆኑ ሰማዕታት የአቡቂርና የዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት ሆነ፡፡
🔥 ሰማዕት አቡቂር እና ሰማዕት ዮሐንስ
እነዚህም ቅዱሳን በሰማዕትነት ካረፉ በኋላ ሥጋቸውን ምእመናን በእስክንድርያ ሰሜናዊ ከተማ ውስጥ ባለች በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሥውር አኖሩ፡፡ እስከ ሊቀጳጳሳት አቡነ ቄርሎስ ዘመንም በዚያ ኖሩ፡፡ የታዘዘ መልአክ ለአቡነ ቄርሎስ ተገለጠለትና የቅዱሳኑን ሥጋቸውን አፍልሶ በባሕር ዳርቻ ወዳለች ሌላይቱ የቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እንዲወስድ ነገረው፡፡ ምእመናንም የሰማዕታቱን ሥጋቸውን አፍልሰው ታላቅ በዓልን አከበሩ፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ፡፡ አረማውያንም ተሰብስበው የተደረጉትን ታላላቅ ተአምራት አይተው በጌታችን አመኑ፡፡ አስቀድመው ያመልኩበት የነበረው የጣዖት ቤታቸውም በተአምራት አሸዋ ተከመረበትና ታላቅ ኮረብታ ሆነ፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ፣ ቅዱስ አቡቂር፣ ቅድስት አትናስያና ሦስቱ ደናግል ልጆቿ፡-
የቅድስት አትናስያ ልጆች ስማቸው ቴዎድራ፣ ቴዎፍና፣ ቴዎዶክስያ ይባላል፡፡ የስማቸውም ትርጓሜ በቅደም ተከተል ‹‹የእግዚአብሔር ስጦታ››፣ ‹‹የእግዚአብሔር ሃይማኖት›› እና ‹‹የእግዚአብሔር ምስጋና›› የሚል ነው፡፡ ቅዱስ አቡቂር ከታናሽነቱ ጀምሮ በገድል ተጠምዶ የሚኖር መነኮስ ነው፡፡ የከበረ ዮሐንስ ግን በንጉሥ ሠራዊት ውስጥ የሚያገለግል ነው፡፡ የእነርሱም ሀገራቸው እስክንድርያ ሲሆን የሚኖሩት ግን አንጾኪያ ነው፡፡ በዚያም እነዚህ ሦስት ቅዱሳት ደናግል ቴዎድራ፣ ቴዎፍና፣ ቴዎዶክስያ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ፊት ቆመው የጌታችንን ክብር መሰከሩ፡፡ ንጉሡም ከወዴት እንደሆኑ በጠየቃቸው ጊዜ ከእስክንድርያ እንደሆኑ ሲነገሩት ወደዚያ ወስደው ያሠቃዩአቸው ዘንድ አዘዘ፡፡
እነዚህም ሦስት ቅዱሳት ደናግል እስክንድርያ በደረሱ ጊዜ ዳግመኛ በመኮንኑ ፊት ቆመው የጌታችንን አምላክነት በመመስከር በጣዖት ማምለክን ረገሙ፡፡ በዚህም የተናደደው መኮንን ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸው፡፡ በመጨረሻም ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ እናታቸው የከበረች ቅድስት አትናስያም ደናግል ልጆቿን በጌታችን ስም ምስክር ሆነው በሰማዕትነት ከሞቱ ለሰማያዊው ሙሽራ ለክርስቶስ ሙሽሮቹ እንደሚሆኑ በመንገር ታጽናናቸው ነበር፡፡ ቅዱስ አቡቂርም በከበረች ሐዋርያዊት በቅድስት ቴክላ ላይ የደረሰውን መከራና ያገኘችውን ክብር ይገልጥላቸውና ያጽናናቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ወታደሮቹ ሦስቱን ቅዱሳት ደናግል ቴዎድራን፣ ቴዎፍናንና ቴዎዶክስያን በየተራ እያቀረቡ አንገታቸውን ሰየፏቸውና የሰማዕትነታቸው ፍጻሜ ሆነ፡፡ ቀጥለውም ጭፍሮቹ እናታቸው ቅድስት አትናስያን፣ ቅዱስ አቡቂርንና ቅዱስ ዮሐንስን ሁሉንም በየተራ ሰየፏቸውና ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ ምእመናንም ሥጋቸውን ወስደው የመከራው ዘመን እስከፈጸም ድረስ በክብር አስቀመጡት፡፡ በኋላም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ቅዱስ ሥጋቸውን በዚያ አኖሩ፡፡ ከቅዱሳኑም ሥጋ ብዙ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ የሰማዕታቱ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡
🔥 ነቢዩ ቅዱስ ሶፎንያስ
ይኸውም ቅዱስ ነቢይ የአማርያ ልጅ፣ የሴዴቅያስ ልጅ፣ የጎዶልያ ልጅ፣ የኩሲ ልጅ ነው፡፡ እርሱም በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ዘመን ትንቢትን ሲናገር የነበረ ነው፡፡ እግዚአብሔር ይህችን ዓለም ፈጽሞ እንደሚያጠፋት ሰዎችና ከብቶች የባሕር አሣዎችና የሰማይ ወፎችም ጭምር እንደሚጠፉ ትንቢት ተናገረ፡፡ ስለሞአብም መጥፋት ተናገረ፡፡ ዳግመኛም ስለ ፋርስና ስለ ነነዌ መጥፋት ሲናገር ‹‹እግዚአብሔር ‹የፋርስን ሰዎች አጠፋቸዋለሁ፣ ነነዌንም ፍርስራሽና ውኃ እንደሌለባት ምድረ በዳ አድርጋታለሁ› ብሏል›› አለ፡፡ ቅዱሱ ነቢይ እንደተናገረውም ይህች ከተማ በመቄዶናዊው እስክንድር እጅ ጠፍታለች፡፡
ቅዱስ ሶፎንያስ ዳግመኛም ስለጌታችን መምጣት ትንቢትን ሲናገር ‹‹ያን ጊዜም ሁሉ የእግዚአብሔርን ስም ይጠራ ዘንድ በአንድ ሕግም ይገዙልኝ ዘንድ የአሕዛብን ሁሉ አንደበት ወደ ሕግ እመልሳለሁ›› አለ፡፡ ደግሞም ቅዱሱ ነቢይ ስለ ሀገራችን ትንቢትን ሲናገር ‹‹ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ መሥዋዕቴን ያመጡልኛል›› አለ፡፡
ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡
ምንጭ፦ የሐምሌ 4️⃣ ስንክሳር
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሰኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
. ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium
ሐምሌ 3️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም | 126 |
| 19 | Нет текста... | 140 |
| 20 | ሊቀ ጳጳሳት ልኮ አባ ክልስቲያኖስን ወደ መንበሩ በክብር መለሰው፡፡ ሕዝቡም በታላቅ ክብር ተቀበለው፡፡ በዚያም ወራት ንጉሡ ከጦርነት በሰላም ተመለሰ፡፡ ቤተ ክርስቲያንም በሰላም ኖረች፡፡
ከዚህም በኋላ በዘመኑ የንስጥሮስ ክህደት በተገለጠ ጊዜ የከበሩ ቅዱሳን አባቶች የአንድነት ስብሰባ ሲያደርጉ አባ ክልስቲያኖስ ግን ከደዌውና ከእርጅናው የነተሣ ወደ ጉባኤው መሄድ ባይችልም ንስጥሮስን ከሚያወግዝ ደብዳቤ ጋራ ሁለት ሊቃውንት ቀሳውስትን ላከ፡፡ እርሱም የእረፍቱ ጊዜ በቀረበ ጊዜ አባ ዮናክንዲኖስና አባ አትናስዮስ ተገለጡለትና ‹‹ጌታችን ወደ ሕይወት ጠርቶሃልና አንተ ወደ እኛ ስለምትመጣ ሕዝቡን በሃይማኖት እንዲጸኑ አስጠንቅቃቸው›› አሉት፡፡ የእስክንድርያው ቅዱስ ቄርሎስ ዓምደ ሃይማኖትና የሀገረ ፃን ኤጲስቆጶስ አባ ሉቅያስም እንዲሁ ተገለጡለት፡፡ ወዲያውም ሕዝቡን ሁሉ ጠርቶ ‹‹ተኩላዎች ወደዚህች ከተማ ይገቡ ዘንድ አላቸውና ተጠንቀቁ፣ እስከመጨረሻው በሃይማኖት ጽኑ›› ብሎ ከመከራቸው በኋላ በሰላም ዐረፈ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይህን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎትና ምልጃ ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ምንጭ፦ የሐምሌ 3️⃣ ስንክሳር
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሰኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
. ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium
ሐምሌ 2️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም | 185 |
