es
Feedback
መጽሐፍቶችን በpdf📚

መጽሐፍቶችን በpdf📚

Ir al canal en Telegram

"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome! በpdf(በሶፍት ኮፒ) ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ! ፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ! ፨በዚህ ቻናል የተለያዩ መፅሐፎች፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አፕልኬሽኖች፣አነቃቂ ምስሎች ቀርቦላችኋል አውርደው ይጠቀሙ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram መጽሐፍቶችን በpdf📚

El canal መጽሐፍቶችን በpdf📚 (@pdfffb) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 407 suscriptores, ocupando la posición 2 377 en la categoría Libros y el puesto 2 192 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 407 suscriptores.

Según los últimos datos del 30 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 778, y en las últimas 24 horas de 15, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 16.23%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 5.45% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 2 501 visualizaciones. En el primer día suele acumular 839 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome! በpdf(በሶፍት ኮፒ) ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ! ፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ! ፨በዚህ ቻናል የተለያዩ መፅሐፎች፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አፕልኬሽኖች፣አነቃቂ ምስሎች ቀርቦላችኋል አውርደው ይጠቀሙ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 01 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Libros.

15 407
Suscriptores
+1524 horas
+1857 días
+77830 días
Archivo de publicaciones
የአዳራሽ ለውጥ ማሳወቂያ       ======== የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ “ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና ኪነጥበብ፤ ዕድሉ፣ ተግዳሮቱ እና መፍትሔው” በተሰኘ ርዕስ ያዘጋጀውን የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና ቢልት ኢንቫይሮመንት ኮሌጅ (5 ኪሎ ካምፓስ) አዳራሽ ለማካሄድ ቀደም ሲል ጥሪ ማስተላለፉ ይታወሳል። ሆኖም ግን፣ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና እየተሰጠ በመሆኑ የፓናል ውይይቱን እዚያው አቅራቢያ ከዩኒቨርስቲው ፊት ለፊት ወደሚገኘው #የኢትዮጵያ_ቅርስ_ባለሥልጣን _አዳራሽ (በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም 5 ኪሎ ግቢ) የተቀየረ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን። 🗓ቀን፦ ሐሙስ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ሰዓት፦ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት -12፡00 ሰዓት መድረኩ ለሁሉም ክፍትና ነፃ በመሆኑ፤ ጥሪ የተደረገላችሁ የመንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተወካዮች፣ የክብር እንግዶች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ተማሪዎች እና ፍላጎቱ ያላችሁ ዜጎች በሙሉ በተለወተለወጠው አዳራሽ በተጠቀሰው ሰዓት ተገኝታችሁ እንድትሳተፉ በአክብሮት እንጋብዛለን። በአካል መገኘት ለማትችሉ በዙም (Zoom) ወይም በፖስተሩ ላይ ያለውን QR code በመጠቀም መከታተል ትችላላችሁ። 🔗Zoom link: https://us06web.zoom.us/j/86023294307?pwd=p6iQ4yPvX5udQy5OAmbCER2NIYLO4J.1 👉Meeting ID: 860 2329 4307 👉Passcode: 798030

ሁላችሁም በአክብሮት በነጻ ተጋብዛችኋል!          ``````````````` የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የፓናል ውይይት መድረክ አካዳሚው በተለያዩ ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የኅብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግና ሳይንሳዊ አሠራሮችን ለማጎልበት ሕዝባዊ የገለጻና የፓናል ውይይት መድረኮችን ሲያካሂድ ቆይቷል። ይህንን ሂደት በማስቀጠል “ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና ኪነጥበብ፤ ዕድሉ፣ ተግዳሮቱ እና መፍትሔው” በሚል ርዕስ በዕውቀትና የመረጃው ዓለም ላይ ጉልህ ተጽዕኖ እየፈጠረ በሚገኘው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (#ArtificialIntelligence/ #AI) ላይ አካዳሚው ሊያከናውናቸው ካቀዳቸው ተከታታይ መድረኮች የመጀመሪያውን የፓናል ውይይት በዘርፉ ከፍተኛ ምሑራን አቅራቢነትና አወያይነት ያካሂዳል። አቅራቢዎች፡- 🟢ሰርጸ ፍሬ ስብሃት፡- ፖሊሲ፣ አርካይቭ እና የኪነጥበብ ሀብቶች ጥበቃ 🟢ወንድወሰን ሙሉጌታ (ዶ/ር): - ለሰውሠራሽ አስተውሎት ሀገራዊ የቋንቋ እና ሥነጥበብ     መረጃን ማሰልጠን (Data Feeding) እና ማላመድ ላይ ህጋዊና ሥነምግባራዊ መርሆዎች 🟢በአካል ግዛቸው (ዶ/ር): -የቴክኖሎጂውእድገትና ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ 🟢በሰናይት ጥበቡ (AI  እና ሥነጽሑፍ) እንዲሁም በመድኅን ተሰማ (AI እና የኢትዮጵያ      ሙዚቃ ዳሰሳ ጥናት) ተግባራዊ ልምድ እና ዳሰሳ  ይካሄዳል። 🟢የፓናል ውይይቱን  ብርሃኑ በሻህ (ዶ/ር) ይመሩታል። ስለሆነም የዘርፉ ባለሙያዎች፣ ጥሪ የተደረገላችሁ የክብር እንግዶች፣ ጋዜጠኞች፣ ተማሪዎች እና በፓናል ውይይቱ መሳተፍ የምትፈልጉ ዜጎች በሙሉ መድረኩ ለሁሉም ነጻና ክፍት ስለሆነ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በአካል በመገኘት እንድትሳተፉ በአክብሮት ተጋብዛችኋል። 🗓ቀን፦ ሐሙስ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ሰዓት፦ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት -12፡00 ሰዓት 📍ቦታ፦ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና ቢልት ኢንቫይሮመንት ኮሌጅ (አአዩ-5 ኪሎ ካምፓስ)              ኦዲተሪየም - አዳራሽ በአካል መገኘት ለማትችሉ በዙም (Zoom) ወይም በፖስተሩ              ላይ ያለውን QR code በመጠቀም መከታተል ትችላላችሁ። 🔗Zoom link: https://us06web.zoom.us/j/86023294307?                        pwd=p6iQ4yPvX5udQy5OAmbCER2NIYLO4J.1 👉Meeting ID: 860 2329 4307 👉Passcode: 798030

❝ሀገር የምትራመደው በአንድ ሳንቲ ሜትር ዕውቀት፤ መቶ ሳንቲ ሜትር ሥነ-ሥርዓት ነው።❞ ‎አንዳንድ ጊዜ ሰዎች መጽሐፍን ከመክፈታቸው በፊት ይመዝኑታል። ሐሳቡን ከመረዳት ይልቅ ገጾቹን መቁጠር ይቀላቸዋል። ምክንያቱም ቁጥር መቁጠር ቀላል ነው፤ ሐሳብን መሸከም ግን ከባድ ነው። ‎ ‎የወረቀት ብዛት ብዙዎችን ያስጨንቃል፤ የሐሳብ ብዛት ግን ጥቂቶችን ብቻ ያስደስታል። ወረቀት ለመግዛት ገንዘብ ያስፈልጋል፤ ሐሳብን ለመቀበል ግን ክፍት አእምሮ፣ ትዕግሥት እና ራስን ለመጠየቅ ድፍረት ያስፈልጋል። ‎ ‎ሰውን የሚያስፈራው ብዙ ጊዜ የመጽሐፉ ዋጋ አይደለም፤ የሚያስፈራው ከመጽሐፉ ጋር የሚጀምረው ውይይት ነው። ጥልቅ መጽሐፍ መረጃ አይጨምርልህም፤ የነበርክበትን አስተሳሰብ ይፈታተነዋል። አንዳንድ መጽሐፍት ሲዘጉ አያልቁም፤ ያኔ ነው በውስጥህ መነበብ የሚጀምሩት። ‎ ‎1,008 ገጽ ያለውን መጽሐፍ ሲያዩ በመጀመሪያ የሚያስቡት "ስንት ይሆን?" የሚለውን ነው። ነገር ግን 1,008 ሰዓት በስልካቸው ላይ ሲያሳልፉ የጠፋውን ጊዜ አይቆጥሩትም። ገንዘብ ሲወጣ ዓይናችን ያየዋል፤ ጊዜ ሲወጣ ግን ሕይወታችን ብቻ ያውቀዋል። ‎ ‎እውነታው ግን መጽሐፍ በገጹ አይመዘንም፤ በውስጡ በተቀመጠው ሕይወት ነው የሚመዘነው። 1,008 ገጾች 1,008 ወረቀቶች አይደሉም፤ 1,008 ሐሳቦች፣ 1,008 ጥያቄዎች፣ 1,008 ጉዞዎች፣ 1,008 ነፍሳት የተደበቁባቸው መስኮቶች ናቸው። ታላቅ መጽሐፍ ወረቀት አይሸጥም፤ አዲስ የማየት ዓይን ይሰጣል። ‎ይህን ስንረዳ ደግሞ መጽሐፉ የማን እንደሆነ ማወቅ ይገባናል። ‎ ‎"መዝሙረ ሄላም" የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሑፍ ውስጥ ልዩ አሻራ ያለው ደራሲ አዳም ረታ አዲስ ለኛ የሚሰጠን መጽሀፉ ነው። አዳም ረታን የሚያነብ ሰው በቀላሉ ታሪክ አያነብም፤ ቋንቋ ውስጥ ይጓዛል። ሐረጎቹን ብቻ አይከተልም፤ በእነሱ መካከል የተደበቁትን ዝምታዎችም ያዳምጣል። ‎ ‎ደራሲው "ማሕሌት"፣ "አለንጋና ምስር"፣ "እቴሜቴ ሎሚ ሽታ"፣ "ከሰማይ የወረደ ፍርፍር"፣ "ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ"፣ "ሕማማትና በገና" የተሰኙ የአጫጭር ልቦለዶችን፣ እንዲሁም "ግራጫ ቃጭሎች"፣ "የስንብት ቀለማት" እና "መረቅ" የተሰኙ ረጅም ልቦለዶችን ለአንባቢያን አበርክቷል። በአጻጻፍ ስልቱ ልዩነት፣ በቋንቋው ውበት እና በሐሳቡ ጥልቀት የሚጠቀስ ደራሲ ነው። ‎ ‎እናም 1,008 ገጽ ሲባል የሚቆጠረው የወረቀት ብዛት ብቻ አይደለም፤ የአንድ ደራሲ የዓመታት ጉዞ፣ የንባብ ትዕግሥት፣ የጥናት ልፋት፣ የልምድ ጭማቂ፣ የጥያቄ ሸክም እና የሕይወት ትርጉም ነው። የምንከፍለውም ለወረቀት ሳይሆን፣ ለዚያ የተጨመቀ ዘመን ነው። ‎ ‎የሐሳብ ዋጋ በብር ሊለካ ቢችል ኖሮ፣ የዓለም ታላላቅ መጽሐፍት በሀብታሞች መደርደሪያ ላይ ብቻ በተቀመጡ ነበር። ነገር ግን ታሪክ የሚያስተምረን ሌላ ነው፤ ዓለምን የለወጡት መጽሐፍት በወረቀታቸው ብዛት አይደለም፣ በያዙት ሐሳብ ጥልቀት ነው። ‎ ‎ስለዚህ መጽሐፍን በገጹ አትመዝነው። አንዳንድ ጊዜ በጣም ውድ የሆነው የገዛኸው መጽሐፍ አይደለም፤ በፍርሃትህ ምክንያት ሳታነበው የተውኸው መጽሐፍ ነው። ‎ ‎ምክንያቱም እውቀት ዋጋ አለው፤ ግን የእውቀት ዋጋ በብር አይለካም፤ በሕይወትህ ውስጥ በሚፈጥረው ለውጥ ነው እንጂ። ©የሶሪት ማስታወሻ ሁሌም ማንበብ!

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

እማማ አፀደ የሚባሉ ጎረቤት አሉን የእናቴ ጓደኛ ናቸው። እማማ አፀደ አመም አድርጓቸው ህመማቸው በባሰ ቁጥር እናቴን ጠሏት። ይሰድቧታል ሌባ ናት ይላሉ። መሰሪ ናት ይላሉ። ልትገለኝ ትፈልጋለች ይላሉ። መርዝ አበላቺኝ ይላሉ ። አትምጣብኝ ብለው ስሞታ ይናገራሉ ሌሊት እቤቴ ልትገባ ነበር ይላሉ ። ሰው እንዳትመስላችሁ ይላሉ ። እናቴ ቤታቸው መሄድ አቆመች ። ከቤት መውጣት እያቆሙ ግቢያቸው መዋል ጀመሩ .... እናቴ እሷ መሆኗን አትንገሩ ብላ ፤ ምግብ ትልክላቸዋለች ። በእህታቸውን  ልጅ ፤ ምን ጎደለ ጤናቸው እንዴት ነው እያለች ትሰልላቸዋለች... ንዴት ሊገድለኝ ይደርሳል ። እቆጣታለሁ << ስምሽን እያጠፉሽ እየሰደቡሽ እየጠሉሽ አትተያቸውም ወይ?>> እላታለሁ!! <<ጭንቅላታቸው እጢ ወጥቶባቸዋል እሱ ነው ትንሽ ቀየር ያደረጋቸው እንጂ ፤ እሳቸው እንኳን ሳልበድል ብበድላቸው እንኳን በክፉ አያነሱኝም>> ትለኛለች። ምግብ ትልክላቸዋለች ። በእህታቸው ልጅ በኩል የሚያስፈልጋቸውን  መድኃኒት መግዣ ከኛ ወስዳ ... ተበድራም ቢሆን  ትገዛላቸዋለች ። እሳቸው ያቺ ምናምንቴ ፣ ድግምታም ያቺ ነጠላ እያሉ ጮክ ብለው እናቴን ሲሰድቧት ይውላሉ  ። ጠላኋቸው !! አንድ ቀን ለምን ግን እንዲ ስምሽን እያጠፉ እየጠሉሽ እያልፈለጉሽ አልጠላሻቸውም? ብዬ እናቴን ጠየቅኋት። <<ጓደኛዬ ናቸው! እዚህ ሰፈር ስመጣ እሳቸው ናቸው ያለመዱኝ ። እድር ያስገቡኝ ፥ የሌለኝን እቃ ያዋሱኝ ፥ የተቆረቆሩልኝ ፥ የአረሱኝ ፣የመከሩኝ... እንዲህ አይባልም እያሉ መንገድ ያሳዩኝ እርሳቸው ናቸው ። ድንገት ታመው ነው የተቀየሩት ።ከሁሉም ጋር ነው መጣላት የጀመሩት እኔ ላይ ትንሽ ጠንከር አሉ እንጂ ... በክፉ ግዜ እንኳን ወዳጅ ላይ ጠላት ላይ አይጨከንም!! የጨዋ ሰው ልክ የሚታየው ሲጣሉት ነው ። በፍቅር ግዜ ሰው አይመዘንም ክፉ ግዜ ነው ሰው የሚያጠለው .... አፀዱ እንዴት አይነት ጥሩ ሰው መሰሉህ ዛሬ ህመም ተጣብቷቸው እን'ጂ ። ስንት ቀን መሰለህ እጦት በሳቸው ሳብያ ከቤታችን የተባረረው ። አፀደ ደግ 'ሩህሩህ ናቸው... እናንተ ሳትወለዱ ማንም ሳይኖረኝ ነው ከኔ ጋር የነበሩት...       የአፀደ ውለታ አለብኝ !>>   © Adhanom Mitiku ሁሌም ማንበብ!

photo content

🤌🏾

This text provides a fresh, alternative approach to school leadership by arguing that profound professional development must be built on a foundation of self-understanding and self-management 🏫🧠. While it is highly relevant for headteachers and school principals, its insights apply to educators and staff at all levels who want to enhance their effectiveness ✨. Key Themes & Structure 📚 The Individual & Personal Foundation: The first part of the book explores personality, identity, emotional intelligence, and brain-based learning 🧠💡. It introduces practical techniques—including Neuro-Linguistic Programming (NLP)—to help educators improve their communication skills, manage stress, and model professional excellence 🎯. Interpersonal & Team Dynamics: The middle chapters transition into collaborative skills, focusing on career management, effective decision-making, team learning, coaching, and mentoring strategies 🤝📈. School-Wide Leadership: The final sections address broader institutional health, explor

ኢትዮጵያዊ ሀገሩ የት ነው? "..እንደኔ እምነት ስለኢትዮጵያዊነት በአደባባይ ከመሰበካችን በፊት “የየምናባችንን ኢትዮጵያ” የጋራ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠንየ“ኢትዮጵያዊነት” ፍቺ ላይ በግልጽ መነጋገር መጀመር አለብን። ኢትዮጵያ🇪🇹 ስንል ማን ማንን ታካትታለች? ማን ሲወጣ ትፈርሳለች? ማን ሲያኮርፍ ትጎላለች? ማንስ ሲቀር ሙሉ ትሆናለች? የሚለው ሐሳብ ላይ እንግባባ። ከዚያ የእኔ ኢትዮጵያ፣ ከአንተ እና ከአንቺ ኢትዮጵያ ጋር በምን ትመሳሰላለች ? የምትለያየውስ በምንድነው? ብለን በግልጽ እንነጋገርበት። ይህን ማድረግ ስንችል ብሔራዊ መግባባት ላይ መድረስ የሚያቅተን አይመስለኝም። አንድነታቸውን እና ልዩነታቸው ላይ ስንስማማ “ኢትዮጵያ ትፈርሳለች አትፈርስም፣ አለች የለችም፣ ታሸንፋለች አታሸንፍም” በሚል ክርክር ጊዜ ማባከን የምናቆም ይመስለኛል። እኔ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ፍለጋ ወጥቻለሁ። ለጥያቄዬ መልስ ፍለጋ ስባዝን የገባኝ ነገር ግን፣ ፀቤ ከማስታወቂያው ጋር ሳይሆን ከጊዜ ወደ ጊዜ “በኢትዮጵያዊነቴ እኮራለሁ” የምትለው እሳቤ አድጋ ወደ ማን አህሎኝነት፣ ከዚያም አልፎ ‹እኔ ካንተ እበልጣለሁነት› ሲተካ በማየቴ እየረበሸኝ መምጣቱን ነው። ምናልባት ይሄን እንድል ያስገደደኝ በአደባባይ ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነትን ማቀንቀን ከሁሉም በላይ አደገኛ ነገር እየሆነ እንደመጣና "ኢትዮጵያ" በምትባል አጥር ውስጥ መደበቅ የአንዱን ብሔር ተወላጅ ለመስደብ ፈቃድ የሚያሰጥ መሆኑን ስለታዘብኩም ይሆናል። በበኩሌ እንዲህ ዓይነት ግራ መጋባት ውስጥ የገባሁት አንድ ከመሆናችን በፊት የተለያየን መሆናችንን ለመቀበል ‹ዲናያል› ላይ ስላለን ብሔርን ለየብቻ ስሙ ተጠርቶ ማየት የማይሹ እና ማንነቴ ኢትዮጵያዊነቴ ብቻ ነው ብለው ድርቅ የሚሉ አንዳንድ ሰዎችን ስለሚያስታውሰኝም ይሆናል።  ከኢትዮጵያዊ ሀገሩ የት ነው? ገፅ 364 ©እስከዳር ግርማይ ሁሌም ማንበብ!

ሰኔ 20/ 2018 ዓ.ም (ቅዳሜ ከ8:00 ጀምሮ) ሁላችሁም በነጻ ተጋብዛችኋል! ነገረ መጻሕፍት! ተጋባዥ እንግዳ:- እስከዳር ግርማይ የተመረጡት መጻሕፍት:- - የፈረንጅ ሚስት - ኢትዮጵያዊ ሀገሩ
ሰኔ 20/ 2018 ዓ.ም (ቅዳሜ ከ8:00 ጀምሮ) ሁላችሁም በነጻ ተጋብዛችኋል! ነገረ መጻሕፍት! ተጋባዥ እንግዳ:- እስከዳር ግርማይ የተመረጡት መጻሕፍት:-                 - የፈረንጅ ሚስት                 - ኢትዮጵያዊ ሀገሩ የት ነው?                                            አዘጋጅና አቅራቢ:- እንዳለጌታ ከበደ አሰናጅ:- ዛጎል የመጻሕፍት ባንክ የዝግጅት ቦታ:- FSS. አዳራሽ በዝግጅቶቻችን ላይ በአካል በመገኘት መሳተፍ ለምትፈልጉ አድራሻችን:- ቀበና፣ ካቶሊክ፣ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አቅራቢያ፣ ወደ ሳንፎርድ ትምህርት ቤት በሚወስደው መንገድ፣ ባማ አዲስ ሕንፃ አጠገብ፣ FSS አዳራሽ ሲሆን፣ የመገኛ ቦታው Google Map link:- https://maps.app.goo.gl/2n1myQXCCaTteCw69?g_st=ic ለበለጠ መረጃ:-    0976066720                                0900651010

˝አንከፍትልህም...ይህቺ ሚስኪን (ወደናቴ እየጠቆመ) ለስንቱ ሃብታም፣ ለስንቱ ባለ ሥልጣን የከረቸመችውን ልቧን ለኔ ከፈተች። ምን ተጠቀመች? ምንም !! እድሜ ልኳን ጡረታ የወጣ ወታደር ባሏ ሰክሮ ሲመጣ በር ከፋች ሆና ቀረች...˝(ስለሌላ ባል እንጂ ስለራሱ የሚያወራ አይመስልም።) ˝እሷን ተዋት...እቺ ሀገር ራሷ...እቺ እጇን ወደአንተ ትዘረጋለች የተባለችው...ሃሃሃ...እቺ ኢትዮጵያ... ጓደኞቼን ዋጥ ስልቅጥ ያደረገችው ሀገር ራሷ...ለንጉሥ ልቧን ስትከፍት፣ ለወታደር ልቧን ስትከፍት፣ ለወንበዴ ልቧን ስትከፍት፣ ለሶሻሊዝም፣ ለምናምኒዝም ልቧን ስትከፍት- ይሄው መከፈት መዘጋት  የሰለቸው በሯ ተገንጥሎ ክፍቷን ቀረች። እናስ ? ምናችን ጅል ነው የምከፍትልህ ?...አንከፍትም !! አንከፍትም !! በከፈትን ቁጥር እየገባ የታጨቀብንን ጣጣ ባስወጣህልን ይልቅ !...ላንተም አይመችህ...ውስጣችን ነድዷል፣ ከስሏል - የተቃጠለ ቤት ውስጥ ለመኖር ይሄን ያህል ስታንኳኳ መኖር...ኤዲያ” እናቴ እንባዋ ጠብ ሲል ይታየኛል። ጎምለል ጎምለል...˝አንከፍትም !! አናውቅም እንዴ...ወላ መስኮት ወላ በሩ በተዘጋ ቤት ሰተት ብለህ ገብተህ 'ሰላም ለእናንተ' ስትል? አሁን ምን ያዘህ?...ግባ...ይሄው በግድግዳው ግባ። መቼም ዓይናችን እያየ አንከፍትም...˝ እያጉተመተመ ልብሱን ያወላልቃል። ˝አይዞህ አንበሳዬ...ምነው ከኔ ከምትፈጠር በቀረብህ... የማይረባ አባት ለአንድ ልጁ እንኳን የማይሆን - ወይ አባት - አላየንም አባት - እንደማለዳ ውሻ ስምህን ተከትሎ ከሚጮህ ስሜ ሌላ ምን አወርስሃለው - ቤሳቤስቲን...˝ ድንገት፣ አለሜ...እራት በልታችኋል...˝ ይላታል እናቴን። ˝አዎ˝ ወይም ˝አልበላንም˝ አትልም። ሁልጊዜ መልሷ ይገርመኛል፣ ˝ቆንጆ ወጥ ሰርቻለሁ፤ ትንሽ ልስጥህ እስቲ...˝ ትለዋለች።  ˝አ...ይ...˝ይላል ስልል ባለ ድምፅ። አንዳንዴ ˝አይ...˝ ብሏትም ታቀርብለታች፣ ተነስቶ ይበላል፤ አንዳንዴ ˝አይ...˝ ካለ ትመለሳለች። አማርኛ አስተማሪያችን ˝ልጆች ቋንቋን ከቤተሰብ ከማህበረሰብ ይማራሉ˝ አሉኝ እንጂ ቋንቋን የምንማረው ከሕይወት፣ ለዛውም መተሳሰብ፣ መከባበር እና መፈቃቀር ካለበት የሕይወት ልምዳችን ብቻ ነው። አማርኛ አስተማሪያችን ራሳቸው፣ አባባ˝አይ˝ ቢል እራት ˝አቅርቢልኝ ማለት መሆኑን በጭራሽ አያውቁም። ከማህበረሰቡ ይሄን አልተማሩማ !! ስሜትና ሰዋሰው ለየቅል ናቸው !! ገፅ 47-48 አለቀ © ዶክተር አሸብር ሁሌም ማንበብ!

አባቴ በመጠኑ ሲሰክር( ሞቅ ሲለው) ፊት ለፊቱ ቆሞ "ሳተናው ደህና አመሸህ!" የሚላቸው የአፄ ቴዎድሮስ ሥዕል የሽጉጣቸውን አፈሙዝ አፋቸው ውስጥ አስገብተው መቅደላ ጫፍ ላይ ሬሳና ቁስለኛ ከስራቸው ተለሽልሾ የሚታይበት ሥዕል ፣ በቀኝ በኩል ከዕቃ መደርደሪያዋ በላይ ግድግዳው ላይ ተለጥፎ ይገኛል። (አባቴ ከዚህኛው ሥዕል ጋር የመረረ ጥል የለውም፣ አልፎ አልፎ ካልሆነ...።     አባቴ ስካሩ ከመደበኛው ስካር ከፍ ሲልና፣ ቀን ከገጠመው የሕይወት ስንክሳር ጌሾ ጋር ሲቀየጥ ደግሞ ከማይጋጩት ባላጋራ ጋር ይጋጫል፣ "...የጌታ እየሱስ ክርስቶስ" ምሥል ጋር!! እየሱስ ቀይ መጎናጸፊያ ለብሶ፣ ረጅም ምርኩዙን በብብቱ ስር ይዞ፣ በር እያንኳኳ...በግራ በኩል!! አባቴ ከዚህ ሥዕል ጋር ይጣላል (ድፍረቱ አይገርምም ?) ፂሙን እያሻሸ ለረጅም ደቂቃዎች በዝምታ ሥዕሉ ጋር አፍጥጦ ይቆይና ድንገት፣,,,"አንከፍትም!!" ብሎ ይጮሃል። እናቴ ሽምቅቅ ትላለች። "ለስንቱ እንክፈት፣ ሲያንኳኩ ስንከፍት፣ ገብተው እኛን ሲያስወጡን። በጣታቸው ሲያንኳኩ 'ቤት ለእንግዳ' ብለን ስንከፍት  በክንዳቸው ሲደቁሱን ከመክፈት ጋር ተጣልተናል ፤ አንከፍትም...!!" እናቴ ወደ ጣራው ዓይኗን ልካ በለሆሳስ ታነበንባለች። ለክርስቶስ "ቅድም ያልኩህን እንዳትረሳው አደራ!" የምትል ይመስለኛል። አባቴ ይንጎማለላል። ረጅም ነው ቁመቱ። ብን ተደርጎ የተበጠረ ጥቁር ከርዳዳ ፀጉሩ ላይ ወደ ፊት አካባቢ ትንሽ ሽበት ጣል ያደረገበት። የጨርቅ ሱሪው የተኩስ መስመር ቀጥ ማለት፣ "ሱሪውን ከለበሰው ጀምሮ ተቀምጦ አያውቅም እንዴ" የሚያስብል በሚገባ የተወለወለ አሮጌ የወታደር ቦት ጫማ። ይንጎማለላል... "አንከፍትም! እድሜ ልኬን በርህን ሳንኳኳ የከረቸምክብኝ፣ እንዴት ነው የኔን ልብ ዛሬ የምከፍትልህ። የገቡትንም ማስወጫ አጥተናል እንኳን አዲስ ለሚያንኳኳ ልንከፍት - አንከፍትም!!" ይንጎራደዳል። አንዳንዴ ፊቱ ላይ የሚንቀለቀለውን ቁጣ ሳይ፣ "በቃ ገንጥሎ ጣለው ክርስቶስዬ ጉዱ ፈላ" እላለሁ። ይሄ ሥዕል ከድሮ ጀምሮ ግድግዳችን ላይ ስለተለጠፈ ነው መሰለኝ ክርስቶስ ከእኛ ቤት ሌላ መሄጃ ያለው አይመስለኝም ነበር። እናቴና ክርስቶስ የአባቴን ባህሪ ችለው የኖሩት ሌላ መሄጃ ስለሌላቸው ይመስለኝ ነበር... ገፅ 46-47 ይቀጥላል... © ዶክተር አሸብር ሁሌም ማንበብ!

ትንሽ ወደግራ ዘምበል... " አባቴን ጥምድ አድርጎ የያዘው የግራ እግሩን በፈንጅ ያጣ ወታደር ጎረቤት አለን ፣ ለዚህች በየአምስት እርምጃው ለምትከሰት እንክሻው 'የአካል ጉዳተኛ' ተብሎ ጡረታ ይበላል። ይሄ ለጷግሜ ከመስከረም እኩል ደመወዝ ከመክፈል አይተናነስም - አይ እች ሀገር ! አይ ታሪክ !" እያለ ያሽሙረዋል - በክራንቹ መሬት እየቆረቆረ...!!        የአባቴን እግር የጨረፈችው ጥይት ለአባቴ ግንባር የተተኮሰች መሆኗን ዘንግቶ። የተጫረ እግር ከተቆረጠ እግር እያወዳደረ በጉድለት ቁና የታሪክ ገለባውን ሊሰፍር ይዳዳዋል። ጡረታን የጉዳት ዳረጎት አድርጎ የሚያስብ ከንቱ !! ሰው አንገቱን ተቆርጦ ጡረታ እየተቀበለ መኖር ቢችል ኖሮ፣ "ለሀገራቸው ክብር" አንገታቸውን የተቆረጡቱ "ግራ እግር ምን አላት" ብለው በተቆረጠው ግራ እግሩ በሳቁበት ነበር ፤ አንዱ ባንዱ ሲስቅ ጀምበሯ ጥልቅ" ( በጨለማ መሳቅ የለመደ ህዝብ ስለጀምበር መጥለቅ ምን ገዶት። ለምን እንጦሮጦስ አትወርድም። ኮኮቦችን ወላ ጨረቃዋን አስከትላ።)      ቀን ቀን ትሁት፣ የተከበረ፣ የተጣላ የሚያስታርቅ የመንደሩ ዋልታ ነው አባቴ። ማታ... አቤት! ቀንና ማታ በአባቴ ባህሪ ሲለኩ ያላቸው ልዩነት። ጧት የነበረው አባቴ ሌላ ክፍለ ዘመን፣ ማታ የሚከሰተው ደግሞ ሌላ ላይ የተፈጠረ፤ ሁለት አባት ያለኝ እስኪመስለኝ!!  አባቴ ማታ ማታ ከራሱና ከእነዛ ሁለት ሥዕሎች ጋር ይጣላል። " አባትህ ስራው ምንድነው ?" ብባል፣ "አባቴ ስራው ምን እንደሆነ አላውቅም" ነው መልሴ። ትምህርት ቤትም እንደዚሁ ብዬ መልሼ ሁሉም ሳቁብኝ። እኔ ግን ለምን እንደሳቁ አልገባኝም !! የተማሪቹ እሺ ይሁን - ምድረ ኩታራ። ቲቸር ምን አሳቀው ? ( ከሳቁ በፊት አንቱ ነበር የምለው።) የቲቸር ሳቅ ስላበሳጨኝ ሆነ ብዬ እንዲህ ስል ሳቁን ተረጎምኩት ፣ "አባትህ ቢያጣ ቢያጣ መምህር መሆን ያቅተዋል ?" ማለቱ ነው።" ባይሰማኝም አንጀቴ ራሰ። ይሄን አስቀያሚ መላጣ፣ ኮቱ የተዛነፈ ሂሳብ አስተማሪ ተውትና ስላባቴ ልንገራችሁ... (ሲጀመር ሂሳብ አስተማሪ ስለአባቴ ሥራ ምን አገባው - ደሞ ይስቃል እንዴ! ስለ አባቴ ሥራ እንዴት ልበላችሁ? አባቴ አሁን ሹፌር ነው ተብሎ አንድ ፌርማታ ሳያልፍ  ጸሐፊ ይሆናል ፣ "እሳቸው የሚጽፉት ማመልከቻ መሬት ጠብ አይልም" ተብሎ ባለጉዳይ ቤታችን ሲመጣ፣ አባቴ መጋዝና ሜርቴሎውን ይዞ ገና ድሮ አናፂ ሆኗል። እንግዲህ በክረምት ጣራችሁ አፍስሶ ወይ የእንጨት አጥራችሁ ወድቆ ትላንት ግንቦት ላይ አናፂ የነበረ አባቴን ሰኔ አንድ "ጠግንልን" ብላችሁ ብትመጡ አባቴ ከተከመረ የከሰል ጆንያ ኋላ ቆሞ 'የከሰል ነጋዴ' ሆኖ ታገኙታላችሁ ("ዱቤ ክልክል ነው" ከሚል ፅሁፍ ጋር)...እና አባቴ ሥራው ምንድነው ልበል? ብዙ ሥራ ያለውና ምንም ብር የሌለው አባት! ገፅ 44-45 ይቀጥላል... ©ዶክተር አሸብር  ሁሌም ማንበብ!