Jafer Books 📚
የንባብ ባህል እንዲዳብር እንተጋለን !! አድራሻችን ለገሃር ተወልደ ህንጻ ስር አብርሆት ቤተመጻሕፍት ግቢ ውስጥ ጥቁር አንበሳ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት ሜክሲኮ ደብረወርቅ ህንጻ ስር ሳሪስ አዲሱ ሰፈር ጀሞ ለቴሌግራም https://t.me/Jafbok ለፌስቡክ https://www.facebook.com/jaferbookshop?mibextid=ZbWKwL ለዌብሳይት www.jaferbooks.com
Mostrar más22 671
Suscriptores
+1624 horas
+2117 días
+62930 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
" ምሥጥሩን ማወቅ " ሰባተኛው ዕትም ገበያ ላይ ውሏዋል ።
ስለ ምሥጢሩን ማወቅ መጽሐፍ ከኒውስዊክ ጸሐፊ (ጄሪ አድለር) የተሰጠ አስተያየት . . .
በሕትመትን ዓለም የራስን ማሻሻያ(SELF-HELP) መጻሕፍት ደራሲያን በአንድ መጽሐፍ አይወሰኑም፡፡ አውስትራሊያዊቷ የቲቪ አዘጋጅ ርሆንዳ ባይርን በ2006 ዓ.ም ባወጣችውና ከፍተኛ የሽያጭ ደረጃ ባገኘላት “ ምሥጢሩ” (THE SECRET) መጽሐፏ “የመላውን ዩኒቨርስ መስተጋብር ፤ እያንዳንዱን የሕይወት ክስተትና ገጠመኝ” የሚወስን ሕግ ይፋ አደረገች፡፡ በቀጣይ ሁለት ዓመታት ደግሞ የምሥጢሩን የምሥጋና መጽሐፍና የምሥጢሩን ዕለታዊ አስተምህሮዎች በተከታታይ አስነበበች፡፡ አንባቢያን ' ምን ቀራት ' ሲሉ ጠየቁ . . .
በቀጣይ 'ኃያሉ ምሥጢር ' ( THE MAGIC) ለሕትመት በበቃ በአንደኛው ቀን የአማዞንን ከፍተኛ ደረጃ ተቀላቀለ፡፡ የዚህ የሽያጭ ደረጃ እንግዳ ነገር ደግሞ ደራሲዋ ባይርን ቃለ መጠየቅ አለመስጠቷና መጽሐፋንም አለማስተዋወቋ ነበር፡፡
ከ19 ሚሊዮን ቅጂ በላይ ታትሞ የተሸጠላትን “ ምሥጢሩ) /THE SECRET/ መጽሕፍ ታሳቢ ያደረገ አንባቢ ደራሲዋን በቀላሉ ሊመለከታት አይችልም፡፡
የርሆንዳ ባይርን ጠቃሚ (ምክራዊ) ቃላት
1፡ “ሕይወት አስደሳች መሆን አለባት፡፡ ስትደሰቱ በታላቅ ስሜት ውስጥ ስለምትሆኑ የተመኛችሁትን ዓይነት ሕይወት ስታጋኙ ፤ በመጨነቅ ደግሞ የሚያስጨንቅ ሕይወት ይኖራችኃል፡፡”
2፡“በልጅነታቹ ፤በጉርምስናቹም ሆነ በአዋቂ ዕድሜያችሁ የገጠማችሁና የማትወዷውን ነገሮች ይዛችሁ በሕይወት መስመር ተጔዙ፡፡”
3፡“እያንዷንዷ ሴኮንድ ሕይወታችሁን የምትቀይሩበት ዕድል ናት በየትኛውም ቅፅበት ሐሳባችሁን መቀየር ስለምትችሉ!”
4፡“የአእምሮአችሁ ሾፌር በመሆናችሁ ወደየት መሄድ እንዳለበት በማዘዝ ምሩት አእምሮችሁ በራሱ መሻት ከመስመር ውጪ ሲራመድ የሚችለው እናንት ምን ማድረግ እንዳለበት ካልነገራችሁት ብቻ ነው፡፡”
5፡“የምትናገሩት ታሪክ መጥፎም ይሁን ጥሩ የሕይወታችሁ ታሪክ ይሆናል፡፡ ስለ ሕይወታችሁ አስደናቂነት መናገር ስትጀምሩ የስበት ሕጉ የተናገራችሁትን አስደናቂ ሕይወት ትቀበሉ ዘንድ ያደርጋል፡፡”
6፡“የግዛታችሁ መሪ ናችሁና ያሰባችሁት ወይም የተሰማችሁ ስሜት ግዛታችሁ በሆነው ሰውነታችሁ ውስጥ ሕግ ይሆናል፡፡”
7፡“ማመስገን ፀጋን የምናበዘባት አንዱ ስሜት ነው፡፡ ስለዚህ በየዕለቱ ጤነኛ ስለሆናችሁ አመስግኑ፡፡”
8፡“ሕይወት በእናንተ ላይ የሚከሰት ነገር አይደለም፡፡ሕይወታችሁ የሐሳባችሁ አፀፌታ ምላሽ ናት፡፡”
👏 4👍 1👌 1
" ዮቶር ኮብላይ ካህን " በዓለማየሁ ደመቀ
አስራአራተኛው ዕትም ::
ጥቂት ቅጂዎች ይቀሩናል :: እና ገዝተው የግልዎ አድርገዋል ?
👌 6
የሕይወት ተፈራ ሁለት መጻሕፍት በድጋሚ ታትመው ለንባብ ገበያ ቀርበዋል ::
በቅርቡ " ማማ በሰማይ " ለገበያ ይበቃል ::
@jafbok
❤ 2👍 1
መዲና በየወሩ የምትወጣ ኪናዊ መጽሔት ናት። ዓላማዋ ስለሥነ ጽሑፍ እና ስለ ሌሎች የጥበብ ዘውጎች የምንወያይበትን አውድ ማስፋት፣ ወዲያውም ለአዳዲስ ፀሐፍት እና ለሥነ ጽሑፍ ነክ ውይይቶች መታያ ቦታ መፍጠር፤ ለተደራስያኑም አማራጭ ጣዕም መስጠት ነው።
መዲና ዲጂታል መጽሔት
መዲና ዲጂታል መጽሔት
ቅጽ 1 ቁጥር 2
https://t.me/Medinamagazine
❤ 6👍 1🔥 1
Repost from Esubalew Abera N.
⭕️ የመጻሕፍት ወግ | ከአድማስ ባሻገር
“የመጻሕፍት ወግ” ለበዓሉ ግርማ የመጀመሪያ ድርሰት በኾነው “ከአድማስ ባሻገር” ልብ ወለድ መጽሐፍ ዙሪያ ቆይታውን አድርጓል። እንድትመለከቱት እጋብዛለሁ።
📌 ሊንኩ ይኼው 👇
https://youtu.be/A5FwU-DhPyw?si=mc_XH9CE2v8bfM70
🔥 3
ፍቅር እስከ መቃብር
ሁለት ወጣት ኢትዮጵያውያን ከሃገራቸው ብዙ ርቀት እየሩሳሌም ላይ ተገናኙ። ወጣቱ ሃገራቸውን በዲፕሎማትነት ሊያገለግሉ በ1937 በእየሩሳሌም ከትመው ነበር። በግዜው እየሩሳሌም በእንግሊዝ ግዛት አስተዳደር ስር ነበረች። ወጣቱም በዛ የኢትዮጵያ ቆንሲል ሆኑ። በቆይታቸው አንዲት ውብ ኢትዮጵያዊት ተዋወቁ።
ኢትዮጵያዊቷ ኢትዮጵያ ውስጥ ተወልዳ በሁለት አመቷ ወደ እየሩሳሌም መጣች። አያቷ ለመመንኮስ ወደ እየሩሳሌም ሲመጡ ነበር ህፃኗን ይዘው የመጡት። ህፃኗ በእየሩሳሌም በአያቷ መልካም አስተዳደግ ውብ ወጣት ሆነች።
ሁለቱ ወጣቶች ወዲያውኑ ተጋቡ። ምንም እንኳን ፍሬ ለማየት ባይታደሉም ደስተኛ እና የሚያስቀኑ ጥንዶች ነበሩ።
ሁለቱ ባለትዳሮች በባልየው ስራ ምክንያት አውሮፓ እና አሜሪካ በሚዘዋወሩበት ወቅት እንኳን ተለያይተው አያውቁም። በ1954 ግን ኃያሉ ሞት ለያቸው። ወይዘሮዋ በህመም አረፉ። አርፈው አስከሬናቸው አያታቸው ወደ አሉበት ቅድስት እየሩሳሌም ባለቤታቸው ወስደው በጌቴሰማኒ የመጨረሻው እንዲሆን አደረጉ፡፡
ጎልማሳው ብርቱ ሃዘን ገባቸው። በአዲስአበባ የሚገኘውን መኖሪያ ቤታቸውን በባለቤታቸው ስም ለተሰየመ በአዲስአበባ ከተማ ምክር ቤት ለሚተዳደር የልጆች ማሳደጊያ በስጦታ ሰጡ።
ጎልማሳው ዳግመኛ አላገቡም። አርባ አመት በብቸኝነት ኖረው በ1995 አረፉ።
ባለታሪኮቹ ሃዲስ አለማየሁ እና ክበበ―ጸሐይ በላይ ነበሩ። ፍቅራቸውም እስከ መቃብር ነበር!
©በ Tewodros Shewangizaw
❤ 21👍 4