Jafer Books 📚
የንባብ ባህል እንዲዳብር እንተጋለን !! አድራሻችን ለገሃር ተወልደ ህንጻ አራት ኪሎ ብርሃና ሰላም ፊት ለፊት አብርሆት ቤተመጻሕፍት ግቢ ውስጥ ጥቁር አንበሳ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት ሳሪስ አዲሱ ሰፈር ጀሞ ለቴሌግራም https://t.me/Jafbok ለፌስቡክ https://www.facebook.com/jaferbookshop?mibextid=ZbWKwL ለዌብሳይት www.jaferbooks.com
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram Jafer Books 📚
El canal Jafer Books 📚 (@jafbok) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 32 595 suscriptores, ocupando la posición 899 en la categoría Libros y el puesto 1 035 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 32 595 suscriptores.
Según los últimos datos del 24 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 595, y en las últimas 24 horas de 48, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 10.50%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 6.64% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 424 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 164 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 13.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“የንባብ ባህል እንዲዳብር እንተጋለን !!
አድራሻችን
ለገሃር ተወልደ ህንጻ
አራት ኪሎ ብርሃና ሰላም ፊት ለፊት
አብርሆት ቤተመጻሕፍት ግቢ ውስጥ
ጥቁር አንበሳ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት
ሳሪስ አዲሱ ሰፈር
ጀሞ
ለቴሌግራም https://t.me/Jafbok
ለፌስቡክ https://www.facebook.com/jaferbookshop?mibextid=ZbWKwL
ለዌብሳይት www.jaferbook...”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 25 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Libros.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 24 junio | +48 | |||
| 23 junio | +34 | |||
| 22 junio | +32 | |||
| 21 junio | +28 | |||
| 20 junio | +40 | |||
| 19 junio | +17 | |||
| 18 junio | +10 | |||
| 17 junio | +25 | |||
| 16 junio | +31 | |||
| 15 junio | +19 | |||
| 14 junio | +26 | |||
| 13 junio | +8 | |||
| 12 junio | +2 | |||
| 11 junio | +32 | |||
| 10 junio | +21 | |||
| 09 junio | +26 | |||
| 08 junio | +25 | |||
| 07 junio | +16 | |||
| 06 junio | +39 | |||
| 05 junio | +38 | |||
| 04 junio | +16 | |||
| 03 junio | +16 | |||
| 02 junio | +12 | |||
| 01 junio | +43 |
| 2 | የያዕቆብ ትሪዮ
በዓለማየሁ ታዬ
ደራሲ ያዕቆብ ብርሃኑ በ TRIO /ሶስባንድ/ ተከስቷል። ባንድ ዥምበር ሶስት መጻሕፍትን አሳትሞ እነሆ ብሎናል።
“ሠለስቱ ጣዖታት”
“የመሻገር ሲቃ”
“ብርሃን ጨልጦ መስከር” ሰሞኑን በጃእፈር ደጃፍ ያለፉ የደራሲው በረከቶች ናቸው። እንደ ያዕቆብ ያለ ደራሲ ሶስባንድ ይዞ ሲመጣብን መጯጯህ ግድ ነው።
ብቁ ደራሲ ጊዜውን፡ ንባቡን፡ ምርምሩን፡ ፍልስፍናውን፡ ተብሰልስሎቱን፡ ምናቡን፡ ገንዘብ አድርጎ የደረሰውን በረከት እንዲሁ ባንድ ጀምበር ሲለቅብን፤ የመጽሐፍ መደርደሪያችንን ሲሞላብን እንደ አንባቢ ማጉረምረም ተገቢ ነው። አንዱን ድርሰት አጣጥሞ ወደሌላ ስራው ለመተላለፍ በቂ ጊዜ ይፈልጋልና!
ያዕቆብ ሉዓላዊ/ከፍ ያለ/ ኪነጥበብን ለመከወን የሚተጋ፡ ለማንበብ፡ ለመፃፍ፡ ለመመራመር፡ ለማብሰልሰልና ለመፈላሰፍ ጎዳና እስከመውጣት ዋጋ የከፈለ ደራሲ መሆኑን ሁላችን እናውቃለን። ታዲያ ደራሲው፡ ሃያሲው፡ ተርጓሚው፡ አብሰልሳዩ ሶስባንድ ይዞብን ሲመጣ አሁንም ልክ አይደለም ብለን ብንጯጯህ እውነት አይኖረንም?
ደግነቱ የታተሙት መጽሐፎች ሁለተኛ እትሞች ናቸው።
በቀዳሚ፤ “ሠለስቱ ጣዖታት” ሁለት መቶ ዓመታትን ወደ ኋላ ተስፈንጥሮ መቼቱን ያደላደለ ድንቅ መዝገብ ነው። መጽሐፍ ሳይሆን መዝገብ ያልኩት ደራሲው የኛን ነገር የዳኝበት አግባብ በግለሰብ፡ በቀዬ፡ በ ጎጥና በከባቢ ቅጥ ሳይሆን በአገር ደረጃ ስለሆነ ነው። እኛ ሃበሾች ከቀደመው ጊዜ አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ የሚከተሉንን ፡ የሚያሳድዱንን፤ የሚያሰግዱንን፡ ልቦና ወ ተምኔታችንን መቀመቅ አውርደው የሚያዝረከርኩንን ሠለስት ጣዖታት ያሳየበት ሠለስቱ ጣዖታት በፍቅር ታሪክ ተዋዝቶ በጠነከረ ትእዝብትና ሂስ የተሰናሰለ ልቦለድ ነው። “ፖፑላር ድርሰት” ጽፌ አንባቢን አልገዛም፤ ኪሴን አልሞላም፡ ኑሮዬን አላደረጅም፡ ይልቅዬ ለጥበብ ስለጥበብ ስለ ነፍሴ ኡኡታ ለፍፌ ጦሜን አድራለሁ! ከሚል ታማኝ ብእር የተወለደ ስራ ነው- ሠለስቱ ጣኦታት። ጥበብን ላለ አንባቢ “ሠለስቱ ጣዖታት” እንደገና ታትሟልና ፈረሱም ሜዳውም እነሆ!
ሲቀጥል “የመሻገር ሲቃ”ም ለደራሲው ሁለተኛ ዕትም ረጅም ልቦለድ ነው። ዝኒ ከማሁ "ዐብዮታዊ" የጥበብ በረከት ነው። "ዐበየ" እምቢ አለ እንዲል- ሲድኒ ሼልደንንና ሮበርት ሉድለምን ጨምሮ የዓለም ደራሲያን የመረጡትን አንባቢን በእግር ጥፍር አቁሞ ከገጽ ገጽ ልብ አንጠልጥሎ የመተረክ መላ ላይ ያዕቆብ ያመጸበት “እምቢኝ” ያለበት ሐዲስ ያሰናኘት ብልሃት የሞከረበት ስራ ነው።/አሰናኘት በዚህ አውደ ምንብብ የመቼት ምርጫ፤ የገፀባህሪያት አሳሳል፤ የአተራረክ ስልት፤ የመመስጠር የመቋጠርና የመፍታት ብልሃት፤ ዕብንን ወአልማዝነት የማለዘብ ጥበብ፤ ድቅድቅ ጨለማን በብርሃን ዘሃ የማወናበድ ሴራ ጠራራ ፀሐይን በጽልመት ለበቅ የመለምጠጥ ሸር የተገመደበት አሰነኛኘት እንደ ማለት/።
በመሻገር ሲቃ እልፍኝ ውስጥ አለልህ “ቃየን” ብሎ ገጸባህሪ፡ እውናዊ ሰው አትለው፡ ረቂቅ መንፈስ ፡ጅላጅል ጂኒ አትለው፡ ብልጣ ብልጥ ኤሊየን! ከየት? እንዴት? እንደመጣብህ ሳታውቀው እንደ አንዳች ቋጥኝ ቀልብና መንፈስህ ላይ ተጎብሮ ሲያበቃ ደግሞ እንደገና እንደ ሐጋይ ደመና ብንን ትንን ብሎ የሚጠፋ አዚመኛ የዘመን ወኪል!
"ቃየን አፈንጋጭ ገፀ ባህሪ ነው።" አይገልፀውም። ከአደፍርስ ቀጥሎ በረዥም ልቦለዶቻችን ውስጥ የተከሰተ ልዩ/እንግዳ/ ግራ የሚያጋባ ግለሰብ። ከመዝገብ ስሙ አንስቶ አጠቃላይ ስነምግባሩና ሐልዎቱ እንቆቅልሽ ነው። ያፈቀራትን እንስት የማማለሉን ክህሎት ተክኖበታል። በራሷ በተፈቃሪዋ አንደበት
“እና ያን ምሽት እንዲህ ያለኝ መሰለኝ...”
‹‹ፍቅሬ አበባዬ ሙሽራዬ ሆይ... ከዘለዓለም ጫፍ ጠራሁሽ፡፡ ከሞት መንጋጋ አስጣልሁሽ፡፡ የሕይወትንም ውኃ አጠጣሁሽ፡፡ ከሞት ጽኑ ቀንበር ነጻ አወጣሽኝ፡፡ በትንፋሽ አክናፍ እልመዓለምን አስቃኘሽኝ፡፡ በሕይወት መዝገብም አስጻፍሽኝ፡፡ ፍቅር እንደ ማህሌት ነው፡፡ እንደ ሱባዔ.. እንደ ጦም ጠሎት፡፡ ፍቅሬ አበባዬ የገነት ወፌ ሆይ... ነይ ፍቅርን እናፍቅረው፡፡ በዋሊያና በውርንጫ ዓይነት መዋደድ እንዋደድ... ፍቅሬ አበባዬ ሙሽራዬ ሆይ... አንቺ በመቅበዝበዜ መሀል የተጣልሽ ምጥን የፈገግታ ቅኔ ነሽ...››
እንዲህ ዐይነቱ ሥነ-ግጥማዊ ቃላት ሃረጋትና አናቅጽ ድርሳኑን ያቅለመለሙ የደራሲው አሻራዎች/ቀለማት ናቸው።
በእኔ አተያይ ባማርኛችን የስነፅሁፍ ታሪክ የቃየን እኩያ ገጸባህሪ አደፍርስ ነው። የዳኛቸው ወርቁ ድርሳን ከአደፍርስ ሞት በኋላ የዘለቀው ሶስት ከሩብ ገፆችን አይሞላም። የያዕቆብ ልቦለድ ግን ከቃየን ኅልፈት በኋላ ምን ያህል ገፅ እንደዘለቀ ያንባቢ የቤት ስራ ይሁንልኝ። ያዕቆብ ልብ የማንጠልጠሉን የዋና ገፀባህሪን ኅይወት እስከ መፅሐፉ ፍፃሜ ድረስ የማዝለቁን ቁምነገር ቸል ማለቱ “ I am not into popular literature. I am a man of my own literary philosophy!” እያለ መሆኑን አስረግጦ ያስረዳናል።
በቃዳሚ ብለን ሲቀጥልን አስከትለን ሲሰልስ ላይ የምናገኘው “ብርሃን ጨልጦ መስከርን” ነው።
ሲሰልስ፤ ደራሲው ብርሃን ጨልጦ የሰከረበት ዳጎስ ያለ ድርሳኑ ከዚህ ቀደም ያነበብናቸውን “ከባዶ ላይ መዝገን” እና “በፍም እሳት ማቃመስ”ን አጣምሮ በአንድ ቅፅ ያቀረበበት ስራው ነው። በፍም እሳት ማቃመስን ይቆዝምበት ዘንድ የዛሬ ዓመት አካባቢ ያዋስኩት አንድ ወዳጄ ያዕቆብን አጣጥሞ ካነበበ በኋላ “ በአገራችን የኅትመት በረከቶች ላይ ተስፋ ቆርጬ ነበር አለኝ” ለጠቅ አድርጎም "በዚህ ዘመን እንዲህ ዐይነት ምርጥ መጽሐፍ ይታተማል የሚል እምነት አለበረኝም። ንባብ ሁሉ አቁሜ ነበር" አለኝ ከልቡ እያመሰገነኝ። ብርሃን ጨልጦ መስከር ውስጥ ከሰከሩ ርዕሶች መካከል-
1 አነስታይ ጣዖታትን ፍለጋ
2 ከዲያብሎስ ጋር መደነስ
3 ከአልቦ ቅዝምዝም መባተት
4 ከዘለዓለም ስካር መንቃት
5 (ምነው የኔ ዝብዘባ አብቅቶ ያዕቆብን ላንባቢዎቹ ባስረከብኩ)
ነገር ቢበዛ ባህያ አይጫንምም አይዶል ሚሉት የቀድሞ ሰዎች?
እስኪ ሠለስቱን የያዕቆብ ድርሳናት ተደረሱና አግንኜ ከሆነ በጥበብ ችሎት ላይ አማናዊ ባልኾነ ምስክርነት ቆሜ ከኾነ 7alemayehu@gmail.com ላይ ሞግቱኝ። | 1 489 |
| 3 | እኛ ዘንድ ሲመጡ ሁሉንም አይነት መጸሐፍቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ ።
መጥተዉ ስለሚጎበኙን እናመሰግናለን🙏🙏🙏
በታማኝነት እናገለግሎታለን።
ጃዕፈር መጸሐፍት🎉🎉 | 2 251 |
| 4 | ጠይም ትዉስታዎች
“በሱ ባለዉ አበራ”
በቅናሽ ዋጋ እኛ ዘንድ መጥተዉ ይሸምቱ 🔥🔥
ጃዕፈር መጸሐፍት | 2 194 |
| 5 | New arrival books 🎉🎉
Call us 0911932088
0911125324 | 2 911 |
| 6 | “የፍርድ አፈጻጸም “
“በካሴ መልካም”
በመደብራችን ያገኙታል
ጃዕፈር መጸሐፍት | 3 728 |
| 7 | “የተከዜ ፖለቲካ “
ኃይል፣ ማንነት እና የኢትዮዽያ
ብሔራዊ ደኀንነት
“በቹቹ አለባቸዉ”
በመደብራችን ያገኙታል
ጃዕፈር መጸሐፍት | 5 143 |
| 8 | ሁሉም ቅርንጫፎቻችን በናንተ ዉድ ደንበኞቻችን እንዳሸበረቁ ነዉ ዉድ ደንበኞቻችን መጥታችሁ ስለምትጎበኙን እናመሰግናለን።🙏🙏🙏 | 5 244 |
| 9 | ሁሉም ቅርንጫፎቻችን በናንተ ዉድ ደንበኞቻችን እንዳሸበረቁ ነዉ ዉድ ደንበኞቻችን መጥታችሁ ስለምትጎበኙን እናመሰግናለን።🙏🙏🙏 | 1 |
| 10 | ሶምነስ በእርጥብ እጁ ፊቱን አባብሶና አፉን ተጉመጥምጦ ሲያበቃ ጀብሎውን ተጭኖ ወደ ውጪ አመራ። "ማነህ አንተ ልጅ?"ወይዘሮ አስካለ ተጣሩ።"ስምህ አልያዝ አለኝ እኮ! ነግሬህ የለ? ብታመሽ ከፍቶ የሚያስገባህ አታገኝም። ሰማኸኝ?" አሉት። በየቀኑ እንዲህ ይሉታል።"እሺ አላመሽም!" ይመልስላቸዋል።
የክረምት ጠዋት ለስላሳ ፀሐይ የሚያርፍበት ገላው ጮክ ብሎ ይናገራል። በብርድ ቆረፋፍዶ ያደረ ቆዳው መፍታታት ሲጀምር አቤት ማንኮሻኮሹ! በለግላጋ ሴት መዳፍ እንደታሰሰ ሁሉ እሰይታ ያፈልቃል።የተያያዘው መንገድ ወደ ካዛንቺስ ያደርሳል። ቀጥሎ ወደ ዑራኤል...።
ሶምነስ ሀያ ሁለት በሚወስደው መንገድ ላይ ቀኙን ይዞ ቁልቁል ሲራመድ የሆነችዋ ገጠመችው። ጸጉሯን አሳጥራ የተቆረጠጭ ቆንጆ ሴት። ዐይን ለዐይን ተገጣጠሙ። አለፋት። "የኾነ ቦታ አውቃታለሁ። የት ነው የማውቃት?..." ልቡ ምቷን ለማቆም ምንም አልቀራትም። ቀስ ብሎ ዞሮ አያት። ልጅት "ሃያ ሁለት" የሚጠራ ታክሲ በእጅ ምልክት አስቆመች።እሷም ከመሳፈሯ በፊት ዞራ አየችው። ደንገጥ ብሎ ፊቱን መለሰ። ታክሲው አልባሌ ነገር እንደጫነ ሁሉ ይዟት ወደ ሃያ ሁለት ተወረወረ። የለመደበት ባለጌ ታክሲ።.... | 4 786 |
| 11 | “ጠይም ትዉስታዎች “
በ እሱባለዉ አበራ ንጉሴ
አሁን በመደብራችን ያገኙታል። | 4 621 |
| 12 | የመጽሐፍ ዐውደ - ርዕይና ባዛር
ለገሃር ተወልደ ሕንጻ ስር በከፈትነው አዲሱ የመጽሐፍ መደብራችን ውስጥ ከሰኔ 29-ሐምሌ 5 ድረስ በሚገርም አቀራረብ ከብዙ አማራጭ መጻሕፍት ጋር ከታላቅ ቅናሽ ጋር አደራጅተን እንጠብቃቹሃለን !
ጃዕፈር መጻሕፍት !
የንባብ ባህል እንዲዳብር እንተጋለን ! | 4 459 |
| 13 | ከአጋዘን ቆዳ የተሰራ ምንጣፍ ላይ በእርጋታ ተቀምጧል። ዮጋ እንደሚሰራ ሰው እግሮቹን አቆላልፎ ዐይኑን ከድኗል። መላ ሰውነቱ መስራት ያቆመ ይመስል አንዳችም እንቅስቃሴ አይታይበትም። ለብዙ ዘመናት ጨለማ ውስጥ እንደኖረ የጥንት ዓለማት ሐውልት ሆኗል።
ጆሮዎቹ ግን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ስል ሆነዋል።ንፋሱ መልካም ዜና የሚነግረው ይመስል ክፍሉ ውስጥ በቀስታ ይገለባበጣል።
ከውጭ በኩል ወደ እሱ የሚቀርብ ለስላሳ የእግር ዳና እየተሰማው ነው። ብዙ ሳይቆይ ከጀርባ ያለው በር ተንኳኳ።
አለቃ...ከበሩ ባሻገር የቆመው ሰው ድምፁን ቀንሶ ተጣራ። አስቸኳይ የስልክ ጥሪ አለህ። ላሳውቅህ ብዬ ነው።
ዐይኑን ሳይገልጥ በረዥሙ ተነፈሰ። ምንም አይነት ጉዳይ ቢሆን እሱ እስካልጠራቸው ድረስ እንዳይመጡ ትእዛዝ ሰጥቷቸው ነበር።
አባ ሲና ናቸው አዲስ ነገር ተፈጥሯል ነው የሚሉት
ዐይኑን ገልጦ ወደ ኋላ ዞረ። ቤቱ ሙሉ በሙሉ በጽልመት ሊዋጥ ምንም አልቀረው። ከጥልቅ ዝምታ ጋር ተዋስጦ የሰፈነው ድንግዝግዝታ ከራስ በቀር የማያሳይ ቢሆንም እሱን ግን ምንም ነገር ከማየት አላገደውም።
ግባ አለ ፊቱን ወደነበረበት አቅጣጫ እየመለሰ።
በሩ በዝግታ ተከፍቶ ገመድ አልባ መነጋገሪያ የያዘ ሰው ተጠጋው።
አቤት አለ ስልኩን ወደ ጆሮው አስጠግቶ።
"ትልቅ ችግር ገጥሞናል መለኮት..." | 3 828 |
| 14 | አዲስ አበባ ልብ ካላት በዚያ ዘመን ልቧ ይመታ የነበረው ጨርቆስ 4ኛ ክፍለ ጦር ላይ ነበር። አብዛኛው የጨርቆስ ልጆች የምንማረው ፈለገ ዮርዳኖስ ትምህርት ቤት ነው። ፈለገ ዮርዳኖስ እንደዛሬው ሳይሆን ታላቅና ዝነኛ ትምህርት ቤት ነበር። የኢትዮጵያ መሪዎች የእነ ኮሎኔል አጥናፉ አባተ እና የጄኔራል ገብረየስ ወልደ ሃና ልጆች፣ የኮሎኔል ነጋሽ ዱባለ ልጆች ወዘተ በአንድ ላይ እየኖርን በአንድ ላይ እንማር ነበር። እንዲያውም የጄኔራል ገብረየስ ልጅ ዶክተር ጥበበ ገብረየስ ጓደኝነታችን እስከ አሁን ድረስ ዘልቆ እሱ ሲያገባ እኔ ሚዜው ለመሆን በቃሁ።
ፈለገ ዮርዳኖስ ትምህርት ቤት ፀጋዬ ደበላ የሚባል የስፖርት መምህር ነበር። በትምህርት ቤቱ ልማድ መሠረት ክፍል ውስጥ አንድ ተማሪ ከረበሸ የክፍሉን ተማሪ በሙሉ በመቅጣት የታወቀ ሰው ነበር። ተማሪዎች ይህንን ልምዱን ስለምናውቅ አሪፍ መዝሙር አዘጋጀንለት።
"ኢትዮጵያ ትቅደም፣
ትቅደም በስፖርት ጎደና
ፀጋዬ ደበላ አስተምሯልና!"
ይህንን ዝማሬ አዘጋጅተን እሱ ክፍሉን ሁሉ ሊገርፍ ሲመጣ እኛ በመስኮት ከሩቅ እናየውና ወዲያው እያጨበጨብን መዝሙሩን ጮክ ብለን እንዘምራለን። ፀጋዬ ደበላ ይህን መዝሙር ሲሰማ ፈገግ ብሎ ተመልሶ ይሄዳል።... | 4 150 |
| 15 | “የጃፓን መንገድ “
ቋሚ ጥቅም እንጂ ቋሚ ጠላት የለም
“በ አስፋ ማመጫ አረጋዉ”
በመደብራችን በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኙታል ።
ጃዕፈር መጸሐፍት
☎️0911932088
0911125324 | 4 784 |
| 16 | የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 13ቀን 2018 የመጽሐፍ ፊርማ ስነስርአት ይኖረናል !
ሁላችሁም ተጋብዛቹሀል።
ቦታ አዲሱ የጃዕፈር መጸሐፍት መደብር ለገሀር ኖክ ማደያዉ አጠገብ
ቅዳሜን ከተወዳጁ ደራሲ ቡርሐን አዲስጋር 🎉🎉 | 4 990 |
| 17 | ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ዐዉደ ርዕይ መልስ ለናተ ለዉድ ደንበኞቻችን የተቀረዉን መጸሐፍት በመደብራችንቦታ ቦታቸዉን በማስያዝ እናንተን ዉድ ደንበኞቻችንን እየጠበቅናቹ ነዉ።ኑ እንዲ ያማሩ የደመቁ መፀሀፍትን እኛ ዘንድ በተመጣጣኝ ዋጋ ይሸምቱ።
እዉነተኛ ቅናሽ
የንባብ ባህል እንዲዳብር እንተጋለን
ጃዕፈር መጸሐፍት | 6 451 |
| 18 | ዑስታዝ አብዱልፈታህ ሙስጠፋ ከወንድሞችህ ጋር በመሆን ለገሃር የከፈትነውን አዲሱንና ዘመናዊውን መጽሐፍ መደብራችንን ስለጎበኛችሁልን ከልብ እናመመግናለን :: ዱኣቹንም አላህ መቅቡል ያድርግልን !
🙏🙏🙏 | 5 456 |
| 19 | የታደለ ገድሌ ጸጋዬ የመጽሐፍ ፊርማ ስነስርአት ባደረግን ጊዜ ::
ፎቶ :- ገብሬላ ሸዋቀና ! | 4 174 |
| 20 | እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1965 ዓ.ም ላይ ነበር የንጉሥ ኃይለሥላሴን ፊውዳላዊ ሥርዓት የመቃወም ሀሳብ በአእምሮዬ ውስጥ ብልጭ ያለው። እናም ይህ ሀሳብ ብልጭ ካለብኝ በኃላ ለብዙ ጊዜ ከራሴ ጋር ግብ ግብ ገጠምኩ። በአንድ በኩል ፊት ለፊት ለመቃወም ይዳዳኛል። በሌላ በኩል ደግሞ የማይሆን ነገር ውስጥ ገብቼ እንዳልሳሳት ሰጋሁ። ፊት ለፊት ብቃወም በእኔ ላይ የሚመጣብኝን ወይም ሊደርስብኝ የሚችለውን ነገር መገመት አልተቻለኝም ነበር። አገር ቤት ሳለሁ ያለምንም ምክንያት የግለሰቦች ንብረት ሲቀማ አይቻለሁ። ብዙ ሰዎች ያለፍርድ ሲታሰሩ ተመልክቻለሁ። በዚህ መልኩ ያየኋቸው በደሎች ብዙ ናቸው።
በአንድ በኩል ፊት ለፊት ለመቃወም ሲዳዳኝ በሌላ በኩል ደግሞ የማይሆን ነገር ውስጥ ገብቼ እንዳልሳሳት በሚል የሀሳብ አጣብቂኝ ውስጥ ሳለሁ በአንድ ወቅት ግርማሜ ነዋይ "ብርሃኑ የሚደግፍህ ጠንካራ ድርጅት ሳይኖር ዝም ብለህ ብትጮህ ምን ታመጣለህ?" ሲል ጣል ያደረገብኝ ቁም ነገር ትዝ አለኝ።
ያም ሆኖ ለአገሬ ስል የምከፍለው ክብር መስዋዕትነት፣ በውጭ አገረ ከሚጠብቀኝ የማይታወቅ የሕይወት ዕጣ ፋንታና ፍርሃት፣ ያፈራሁትን ሀብት ከማጣት ስጋት፣ እንዲሁም ከወዳጅና ከዘመድ የመለየት ሁኔታ ጋር ሲነጻጸር ከፍ ያለ ቦታ ይኖረዋል ወደሚል ድምዳሜ አዘነበልኩ። | 3 909 |
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
