በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ
Ir al canal en Telegram
Every one comment us about the informations that we are uploading. you are also very wellcommed to give us nominations which helps us to improve our capability with regard to the concerns of the organization.
Mostrar más1 539
Suscriptores
+224 horas
+57 días
+4030 días
Archivo de publicaciones
#ነዋሪዎችን ከጤና መጓደልና ከአደጋ ስጋት የታደገው የወንዝ ዳርቻ ልማት…
በአዲስ አበባ ከተማ በተከናወነው የወንዝ ዳርቻ ልማት ለጤና ስጋት የነበሩ አከባቢዎችን ወደ ምቹ የመዝናኛ ቦታነት ተቀይረዋል፡፡
ከዚህ በፊት ለበርካታ ነዋሪዎች ንብረት እና ሕይወት መጥፋት ምክንያት የነበሩ ስፍራዎች አሁን ላይ በአረንጓዴ ልማት አጊጠዋል።
የወንዝ ዳርቻ ልማት ሳቢ፣ ማራኪ፣ ለከተማ ነዋሪ ምቹ በማድረግ እና በማስተዳደር በኩል ብዙ ሀገራት የተሻለ ልምድ እና ተሞክሮ እንዳላቸው ይነገራል፡፡
በኢትዮጵያ በለውጡ አመታት በትኩረት ከተሰራባቸውና ውጤት ከተገኘባቸው ስራዎች መካከል የወንዝ ዳርቻ ልማት ተጠቃሽ ነው፡፡
በዚህም በአዲስ አበባ ከቀበና ድልድይ እስከ እንጦጦ ተራራ ያለው የወንዞች ዳርቻ ልማት ለዚህ በጎ ተግባር በአብነት ተጠቃሽ ከሆኑት ፕሮጀክቶች መካከል ዋነኛው ነው፡፡
በከተማዋ የደረቅ እና የፍሳሽ ቆሻሻ መጣያ የነበሩት እነዚህ ወንዞች በዙሪያቸው ለሚኖሩ ዜጎች የአደጋ ስጋትና የጤና ጠንቅ ሆነው ቆይተዋል፡፡
ከተማዋ አስደናቂ ገጽታን እንድትላበስ ያስቻለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ከከተማ ውበት ባሻገር የዜጎችን አኗኗር የማሻሻል ላቅ ያለ ዓላማን ያነገበ ነው፡፡
በዚሁ የልማት ተነሳሽነት አማካኝነት ወንዞችን ንጹህ በማድረግ ውብ መናፈሻዎች የተገነቡ ሲሆን፥ ለወጣቱ የሥራ ዕድል የፈጠረና የይቻላል ሀሳብን የገነባ ልማት መሆኑ ይወሳል፡፡
እነዚህን የልማት ስራዎች ተከትሎ የንግድ ቦታዎች የተስፋፉ ሲሆን፥ ወንዞችን የሚያገናኙ በርካታ ድልድዮች በዚህ የወንዝ ዳርቻ ልማት መገንባታቸው የሚጠቀስ ጉዳይ ነው፡፡
ልማቱ ያመጣውን ትሩፋት በአግባቡ መጠቀም፣ በባለቤትነት ስሜት መጠበቅና ወደ ሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች እንዲስፋፋ ማድረግ ከኅብረተሰቡ የሚጠበቁ ኃላፊነቶች ናቸው፡፡
ለዚህ ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የልማቱን ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡
በጠቃላይ የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ብክለትን በመከላከል ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን ለነዋሪዎች እያስገኙ ሲሆን፥ ማህበረሰቡም ልማቱን በመጠበቅና በመንከባከብ ለቀጣዩ ትውልድ የማስተላለፍ የዜግነት ግዴታውን መወጣት ይጠበቅበታል፡፡
+6
የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች የቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራ ጎበኙ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች፣ ሰራተኞች፣ የክፍለ ከተማ የዘርፉ አመራሮች፣የጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል ተወካይ፤ የአረንጓዴ አምባሳደሮች እና የደብሊዩ አር አይ (WRI) ተወካዮች በተገኙበት በታላቁ የቀበና የወንዝ ዳርቻና ፏፏቴ ልማት ፕሮጀክት ላይ የመስክ ምልከታና ጉብኝት ተካሄደ።
በዚህ የመስክ ጉብኝት ላይ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር እንዳሻው ከተማ ለጉብኝቱ ታዳሚዎች ሰፊ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል።
ኢንጂነር እንዳሻው በማብራሪያቸው፤ አጠቃላይ የወንዝ ዳርቻ ልማቱ 12.5 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ እንዳለው የገለፁ ሲሆን፣ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየርና ከአየር ንብረት ለውጥ አንጻር የፕሮጀክቱ መሳካት ያለውን ከፍተኛ ፋይዳን አስገንዝበዋል።
ከጉብኝት መርሃ ግብሩ አስቀድሞ የቢሮው የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፣ በተደረገው የጋራ ውይይትም የበጀት ዓመቱ የሥራ አፈፃፀም እጅግ አበረታች የነበረ መሆኑ ተገልጿል።
+9
ቢሮዉ በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የስራ ክፍሎች እና የዘርፉ የክ/ከተማ ጽ/ቤቶች ዕዉቅና ሰጠ፡፡
የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ለነበራቸዉ የስራ ክፍሎች፤የዘርፉ የክ/ከተማ ጽ/ቤቶች እና በአረንጓዴ ልማት ዘርፍ ድጋፍ ላደረጉ ግብረ ሰናይ ድርጅት ደብሊዩ አር አይ (WRI) ዕዉቅና ሰጥቷል፡፡
ዕዉቅናዉ በዓመቱ የቢሮዉን ዕቅድ ወደ መሬት አዉርደዉ በመተግበር በኩል እንደ የስራ ክፍል እና ክ/ከተማ እንዲሁም እንደተቋም ባስመዘገቡት አበረታች የስራ አፈፃፀም የላቀ ዉጤት በማመዝገባቸዉ መሆኑን በዕዉቅና አሰጣጥ መድረኩ ተገልጿል፡፡
በዚሁ መሰረትም እንደ ክ/ከተማ ለሚ ኩራ፤አዲስ ከተማ እና ኮልፌ ክ/ከተሞች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ሲይዙ እንደ ማዕከል ደግሞ ዲ/ዝ/ት/ክ/ዳይሬክቶሬት፤የአረንጓዴ ልማት እንክብካቤ ዳይሬክቶሬት እና ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ከ1ኛ እስከ 3ኛ የአፈፃፀም ደረጃ ይዘዉ የበጀት ዓመቱን አጠናቀዋል፡፡
በዕዉቅና አሰጣጥ መድረኩ ላይ ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉን ጨምሮ ሌሎች የቢሮዉ ከፍተኛ አመራሮች፤የጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል ዳይሬክተር፤ የአረንጓዴ አምባሳደሮች፤የክ/ከተማ ጽ/ቤት ኃላፊዎች፤ የደብሊዩ አር አይ (WRI) ተወካይ እና የቢሮዉ ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡
የቢሮዉ ኃላፊ ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉ ዕዉቅናዉ የጀመርነዉን የልማት ስራ ከግብ ለማድረስ የተደረገዉን ጥረት ለማበረታታት መሆኑን ገልጸዉ ከተማችንን አረንጓዴ፤ ዉብና ለኑሮና ለስራ ጤናማና ምቹ ለማድረግ ጉዳዩ የሚመለከተዉ ሁሉ በቅንጅት መስራት እንዳለበት አፅንኦት ሰጥተዋል፡፡
+9
አዲስ ለተደራጁ ማህበራት በዕጣ የስራ ዕድል ተሰጠ፡፡
የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በስራና ክህሎት ቢሮ ተደራጅተዉ ከመጡ 40 ማህበራት የቢሮዉ የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ተወካይ በተገኙበት 22ቱን በዕጣ ለይቶ በአረንጓዴ ልማት ዘርፍ የስራ ዕድል ተሰጥቷቸዋል፡፡
በመድረኩ ተገኝተዉ ስራዉ ስለሚጠይቃቸዉ የድሲፕሊን መስፈርቶች ላይ ገለፃና ማብራሪያ የሰጡት የቢሮዉ ም/ኃላፊ ኢንጂነር እንዳሻዉ ከተማ የስራ ዕድል የተፈጠረላቸዉ ማህበራት ስራቸዉን በጥብቅ ድሲፕሊን መፈፀም እንዳለባቸዉ ያሳሰቡ ሲሆን የስራዉ ጥራትና ፍጥነት ለድርድር አይቀርብም ብለዋል፡፡
በአመራሩ ፤በባለሙያዉና በማህበራቱ መካከል የሚኖረዉ ግንኙነት የስራ ጥራትና ፍጥነትን ለማረጋገጥ መሆን አለበት ያሉት ኢንጂነር እንዳሻዉ ስራዉ ስታንዳርዱን ጠብቆ እንዲከናወን በጥብቅ ድሲፕሊንና ክትትል መተግበር ይገባል ያሉ ሲሆን፤ዛሬ ለማህበራቱ ተጠቃሚነት በፍትሃዊነት የተሰጠዉ ስራ የስራዉን ጥራትና ዉጤታማነትን ለማረጋገጥ ጭምር መሆኑንም አመላክተዋል፡፡
በሌላ በኩል የአረንጓዴና የላንድስኬፕ ስራን ስታንዳርዱን ጠብቆ ለመስራት ሙያዊ ብቃት የግድ መሆኑን ያስገነዘቡት ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ጌታሁን በበኩላቸዉ ዲዛይንን በትክክል በማንበብ ወደ መሬት አዉርዶ ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡
ስራዉ በየደረጃዉ ካሉ አመራሮችን ሰራተኞች ጋር በመቀናጀት የሚሰራ በመሆኑ ማህበራትም የሚሰጠዉን ትዕዛዝ ተቀብለዉ ከሁሉም ጋር ተቀናጅተዉ መስራት እንዳለባቸዉ ወ/ሮ ፀሐይ አሳስበዋል፡፡
ከማህበራቱም የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን የቢሮዉ ም/ኃላፊ ኢንጂነር እንዳሻዉ ከተማ ምላሽና ማብራሪያ እንዲሁም የስራ መመሪያና ስምሪት ሰጥተዋል፡፡
የአረንጓዴ መሰረተ ልማቶቻችንን ወቅቱን ባገናዘበ መልኩ እንንከባከብ!
የክረምት ወራት ለሀገራችን የላቀ በረከት ይዞ የሚመጣ፣ ምድሪቱ የምትለመልምበትና የፈሰሰው የለፋችሁበት የአረንጓዴ አሻራ ፍሬ የሚያፈራበት ልዩ ወቅት ነው።
ይሁን እንጂ ክረምት ለተክሎችና ለአረንጓዴ መሰረተ ልማቶች ምቹ ሁኔታን ብቻ ሳይሆን የራሱን ፈተናዎችም ይዞ ይመጣል። በመሆኑም የተከልናቸው ችግኞችና የለሙ አረንጓዴ ቦታዎችን በተገቢው መንገድ እንዲያድጉና ዘላቂ እንዲሆኑ በዚህ ወቅት ልዩ እንክብካቤና ጥበቃ ልናደርግላቸው ይገባል።
የእርጥበት መጠን መጨመር ለተክሎች ብቻ ሳይሆን ለአረሞችና ለተባዮችም መፈልፈያ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። አረሞች ከተከልናቸው ችግኞች ጋር በምግብና በፀሐይ ብርሃን ስለሚፎካከሩ፣ በየጊዜው የአረም መንቀል ስራ መስራት ያስፈልጋል።
ከዚህ በተጨማሪ የዕፅዋት በሽታዎችና ተባዮች እንዳይከሰቱ ቅድመ ጥበቃ ማድረግና ከተከሰቱም ባህላዊ ወይም ተፈጥሯዊ መከላከያዎችን በመጠቀም የችግኞቹን ጤንነት መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን በዘርፉ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ ምክር ይሰጣል።
በክረምት ወቅት ከሚከሰት ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ብርቱ ንፋሶች ገና በታዳጊነት ላይ ያሉ ለስላሳ ችግኞችን የመስበር ወይም የመንቀል አቅም አላቸው።
ይህንን ለመከላከል ደካማ ለሆኑ ችግኞች የድጋፍ እንጨቶችን ማሰርና በዙሪያቸው አፈር ማጥበቅ ጠቃሚ ነው። ጎርፍ ሊሸረሽራቸው በሚችሉ ተዳፋት ቦታዎች ላይ ደግሞ የተፈጥሮ ድንጋይ ወይም የእርከን ስራዎችን በመስራት አፈሩና ዕፅዋቱ ተጠርገዉ እንዳይጠፉ መጠበቅ እንደሚገባ የዘርፉ ባለሙያዎች ይመክራሉ።
የአረንጓዴ መሰረተ ልማት ጥበቃ የጥቂት አካላት ስራ ብቻ አይደለም፤ የማህበረሰባችን የጋራ ሀብት በመሆኑ የሁላችንንም ትብብር ይጠይቃል። በአካባቢያችን የሚገኙ መናፈሻዎችንና የተተከሉ ችግኞችን ከእንስሳት ንክኪና ከሰው ሰራሽ ጉዳቶች በጋራ ልንጠብቃቸው ይገባል።
እያንዳንዳችን በቤታችን፣ በሰፈራችንና በስራ ቦታችን ያሉትን አረንጓዴ ስፍራዎች በባለቤትነት ስሜት ስንከባከብ ለትውልድ የሚተርፍ የተፈጥሮ ፀጋን እናስተላልፋለን።
አረንጓዴ ልማታችን የነገው ውበታችንና የጤናችን መሰረት ነውና፣ በዚህ ክረምት የተከልነውን ሳናስረክብ፣ የተንከባከብነውን ሳናጠፋ አብረን እናሳድጋቸው!
የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ አቅም ያጎላው የአረንጓዴ አሻራ ስኬት
******
ለዘመናት በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ የድርቅና የምግብ እጥረት መገለጫ ተደርጋ ስትቆጠር የነበረችው ኢትዮጵያ፤ በቅርብ ዓመታት በራሷ አቅም አቅዳና አስተባብራ እውን እያደረገቻቸው የምትገኛቸው ታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ያንን የተሳሳተ እይታ በዘላቂነት በመቀየር የዓለምን ትኩረት በከፍተኛ ሁኔታ እየሳቡ ይገኛሉ።
ከእነዚህም መካከል ሀገሪቱ በጥቂት ዓመታት ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎቿን በማሳተፍ በየአመቱ የምታካሂደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አዲስ ገጽታዋን ለዓለም ያስተዋወቀ እና የዲፕሎማሲ አቅሟን ከፍ ያደረገ ተግባር ሆኗል።
በተለይም በ2018 ዓ.ም በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል የተከናወነው ታሪካዊ ዘመቻ በርካታ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስቧል።
የቻይናውያን ዥንዋና ኦል አፍሪካን ጨምሮ በኤዥያ በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ሚዲያዎች የኢትዮጵያ ህዝብ ያሳየውን ከፍተኛ ተነሳሽነት እና የህዝብ ተሳትፎ አድንቀዋል።
ዘገባዎቹ መርሃ ግብሩ የተራቆተ መሬትን መልሶ ለማቋቋም ደንን ለማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የግብርና ምርታማነትን በመጨመር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ አጉልተው አሳይተዋል።
ይህ አጠቃላይ ጥረት ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ነገን አሻግሮ በመመልከት እና የጋራ ጥቅምን ታሳቢ በማድረግ የተገነባ የመደመር ትውልድ አሻራ ከመሆኑም በላይ በዛፎች ሽፋን ምክንያት የአፈር መሸርሸርን በመከላከል የውሃ ምንጮች እንዳይደርቁ በማድረግ እና ቡናና የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞችን በማስፋፋት ለምግብ ሉአላዊነት ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
በተመሳሳይ በችግኝ ማዘጋጀት መንከባከብና መትከል ሂደት ለበርካታ ወጣቶችና ሴቶች የስራ እድል ፈጥሯል።
በተጨማሪም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ከከተማ ግብርና ከሌማት ቱሩፋት እንዲሁም አዲስ አበባን ውብ እና ለኑሮ ተስማሚ ከሚያደርጉ የኮሪደር ልማት እና የወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች ጋር ተቀናጅቶ እየተተገበረ ይገኛል።
መርሃ ግብሩ ከሀገር አልፎ ለጎረቤት ሀገራት እና ለአለም አቀፍ የአየር ንብረት መስተካከል የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ችግኝ የመትከል እና የመንከባከብ ባህልን አቀናጅቶ በማስቀጠል የማይበገር ስነ ምህዳር እና ኢኮኖሚ ለመገንባት የተጀመረው ሀገራዊ ርብርብ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
+2
የአረንጓዴ ልማት ስራ የቱሪዝም ዘርፍን በማነቃቃት ረገድ የጎላ ድርሻ አለው።
የአረንጓዴ ልማት የአንድን ከተማ ውበት ከመጨመር ባለፈ ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ያለው ፋይዳ እጅግ ከፍተኛ ነው። መዲናችንን በአረንጓዴ ተክሎች እና በፓርኮች ማሳመር የአየር ንብረቷን የተመጣጠነ ከማድረጉም በላይ፣ የከተማዋን አጠቃላይ ገፅታ በመቀየር ሳቢና ማራኪ ያደርጋታል። ይህ ውበት ደግሞ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ዘናጭ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ፣ ለአገር ገፅታ ግንባታ ትልቅ አዎንታዊ ሚና ይጫወታል።
ይህ የአረንጓዴ ልማት እንቅስቃሴ የቱሪዝም ዘርፍን በማነቃቃት ረገድ የጎላ ድርሻ አለው። ከተማዋ በፓርኮችና በአረንጓዴ ስፍራዎች ስታጌጥ የውጭና የሀገር ውስጥ ቱሪስቶችን ቀልብ መሳብ ትችላለች። ቱሪስቶች ወደ መዲናችን በብዛት ሲመጡ ደግሞ ከሆቴል፣ ከትራንስፖርት፣ ከምግብ እና ከሌሎች የቱሪስት መዳረሻ አገልግሎቶች የሚገኘው ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ያድጋል። ይህም ለከተማዋ አዲስ የገቢ ምንጭ በመሆን የኢኮኖሚ አቅሟን ያጠናክራል።
ሆኖም ይህንን ዘላቂ ጥቅም ማግኘት የሚቻለው እኛ ነዋሪዎች የበኩላችንን ኃላፊነት ስንወጣ ብቻ ነው። እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍል አካባቢውን የማሳመር፣ የተተከሉ አረንጓዴ ልማቶችን የመጠበቅ እና የመንከባከብ ግዴታ አለበት። የተሰሩትን ፓርኮችና የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች ከአውዳሚነት በመጠበቅና ተክሎችን በየቀኑ በመንከባከብ፣ መዲናችንን ለትውልድ የሚተርፍ የውበትና የገቢ ምንጭ ማድረግ ይጠበቅብናል።
#ተሰፍሮ የማያልቀዉ የአረንጓዴ መዝናኛ ቦታዎቸው እልፍ በረከቶች
በአሁኑ ወቅት በከተሞቻችን እየተስፋፉ ያሉ የለሙ የአረንጓዴ መሰረተ ልማቶች ለነዋሪዎች ምቾትንና ውበትን ከመስጠት ባለፈ፣ ለልጆች ሁለንተናዊ እድገትና ግንዛቤ ያላቸው አስተዋፅኦ እጅግ የጎላ ነው።
ልጆች ከቤተሰቦቻቸው ጋር አብረው ወደነዚህ ስፍራዎች ወጥተው ሲዝናኑ፣ ከቤተሰብ ጋር ያላቸውን ትስስር ከማጠናከራቸውም በላይ ከአካባቢያቸው ጋር በተሻለ ሁኔታ እንዲተዋወቁ ትልቅ ዕድል ይፈጥርላቸዋል። ይህ አይነቱ ግንኙነት በተለይ በማደግ ላይ ላሉ ህፃናት ስለ ተፈጥሮና ስለ ማህበረሰብ ያላቸውን እውቀት በብዙ መልኩ ያሰፋዋል።
እነዚህ አረንጓዴ ቦታዎች ቀደም ሲል የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ወይም የማይጠቅሙና የተረሱ ስፍራዎች የነበሩ መሆናቸውን ማወቃቸው ለልጆች ትልቅ የህይወት ትምህርት ይሰጣል። ትናንት የነበረውን አስከፊ ገፅታ ዛሬ ወደለመለመና ወደሚያምር የመዝናኛ ስፍራ ተቀይሮ በአይናቸው ሲያዩ፣ በአእምሯቸው ውስጥ ትልቅ የለውጥና የልማት አድናቆት ይፈጠራል። ይህም ማንኛውንም የማይጠቅም ነገር በትጋትና በስራ ወደ ጠቃሚ ነገር መለወጥ እንደሚቻል በተግባር የሚያዩበት አጋጣሚ ነው።
በተጨማሪም ልጆች የዚህን ለውጥ ታሪክና ውበት ሲረዱ፣ በተፈጥሮአቸው ያዩትንና የታዘቡትን መልካም ነገር ለጓደኞቻቸውና ለሌሎች ሰዎች የማስተዋወቅ ፍላጎት ያድግባቸዋል። በአካባቢያቸው ስላለው ልማት በኩራትና በደስታ መናገር ይጀምራሉ።
ይህ ተሳትፏቸው ደግሞ ገና በለጋ እድሜያቸው ለአካባቢያቸው እንክብካቤና ጥበቃ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉና የባለቤትነት ስሜት እንዲሰማቸው ያግዛቸዋል።
ይህ ሂደት ልጆች “የመልማትን ኃይል” በጥልቀት እንዲረዱ ያደርጋቸዋል። ልማት ማለት እይታን መቀየር ብቻ ሳይሆን የአኗኗር ዘይቤን፣ ጤናንና ደስታን የሚጨምር ታላቅ ጉልበት ያለዉ መሆኑን ይገነዘባሉ።
በጥፋት ምትክ ልማት ሲተካ ያለውን የመቀየር አቅም በአይናቸው አይተው ስለሚያድጉ፣ ወደፊት እነሱም ለራሳቸው ለአገራቸውና ለወገኖቻቸው አወንታዊ ለውጥን የሚያመጡ ንቁና transformative (ለዋጭ) ዜጎች እንዲሆኑ ትልቅ መሰረት ይጥልላቸዋል።
+7
የኮሪደር እና የወንዝ ዳር ልማቶች ገጽታን ከመቀየር ባለፈ በአእምሮ፣ በጤና እና በአካል የበለጸገ ትውልድን ለመገንባት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው
በአዲስ አበባ የተገነቡ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ገጽታን ከመቀየር ባለፈ በአእምሮ፣ በጤና እና በአካል የበለጸገ ትውልድን ለመገንባት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው ።
በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የከተማዋን መሠረተ ልማት ከዘመኑ ጋር በማስተሳሰር፣ የነዋሪዎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ደህንነት ማሻሻልና አረንጓዴ ቦታዎችን በማስፋፋት ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት ችለዋል።
ከተማዋን ለቱሪስቶች ማራኪ ከማድረጉም በላይ በወንዞች ዳርቻዎች ላይ የነበሩ የጎርፍ አደጋ ስጋቶችን በመቀነስ ህብረተሰቡ ንጽህናው የተጠበቀ የመኖሪያ እና መዝናኛ ስፍራዎችን እንዲያገኝ አድርጓል።
በዚህም ዘላቂ የከተማ ልማት እውን እንዲሆን በማስቻል የዜጎችን የኑሮ ጥራት ከፍ አድርጓል።
የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ሥራ ከፍተኛ የገጽታ ግንባታ ከመፍጠሩም በላይ ሁሉንም ተጠቃሚ ማድረግ የቻለ አካታች ልማት ነው።
በተጨማሪም የተከናወኑት ግዙፍ የልማት ሥራዎች ለንባብ፣ ለምርምር እና ለህፃናትና ወጣቶች መዝናኛ ያላቸው ፋይዳ ከፍተኛ ነው።
በተለይም የቱሪዝም ፍሰትን በማሳደግና የውጭ ምንዛሬ ገቢን በመጨመር ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
በመሆኑም ህብረተሰቡ የተገነቡት መሠረተ ልማቶች ያላቸውን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመገንዘብ በባለቤትነት ስሜት ሊንከባከባቸውና ሊጠብቃቸው ይገባል።
የወንዝ ዳርቻ፣ መጽዳት ቤቶችና ቆሻሻ አወጋገድ በመስተካከሉ መጥፎ ሽታዎችን በማስቀረት ለነዋሪዎች፣ ለህፃናት፣ ለሁሉም ህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም ለቱሪስቶችም ጭምር ዘመኑን የሚመጥን ከተማ ተፈጥሯል።
