ch
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

前往频道在 Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

显示更多

📈 Telegram 频道 Fresh መረጃ | FreshNews 的分析概览

频道 Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 57 308 名订阅者,在 教育 类别中位列第 2 949,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 550

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 57 308 名订阅者。

根据 10 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -1 536,过去 24 小时变化为 -33,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.91%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.93% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 241 次浏览,首日通常累积 1 681 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

凭借高频更新(最新数据采集于 11 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

57 308
订阅者
-3324 小时
-3497
-1 53630
帖子存档
አሜሪካ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአሜሪካ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ሕጋዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመ። በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደሕንነት መሥሪያ ቤት ሥር የሚገኘ
አሜሪካ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአሜሪካ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ሕጋዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመ።  በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደሕንነት መሥሪያ ቤት ሥር የሚገኘው የዜግነትና የፍልሰት አገልግሎት በአገሪቱ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተሰጠው ከለላ በመጪው ሐምሌ 10 ቀን 2018 እንደሚያበቃ ትላንት አርብ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለሶርያ፣ ሶማሊያ፣ የመን፣ ደቡብ ሱዳን እና ምያንማር ዜጎች የተሰጠው ጊዜያዊ ከለላ በተመሣሣይ ቀን ያበቃል።  ውሳኔው የሚመለከታቸው የሔቲ ዜጎች ከቀሪዎቹ አምስት አገራት አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ በአሜሪካ ለመቆየትና ለመሥራት የሚፈቅድላቸውን ከለላ ያጣሉ። ይህ ከለላ የተፈጥሮ አደጋ፣ የትጥቅ ግጭት ወይም ሌሎች ያልተለመዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ከገጠማቸው አገራት ወደ አሜሪካ የገቡ ሰዎች በአገሪቱ እንዲቆዩ እና በሕጋዊ መንገድ እንዲሠሩ የሚፈቅ ነው።  ከለላው የተሰጣቸው በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ቢመለሱ “በግል ደሕንነታቸው ብርቱ ሥጋት አይገጥማቸውም” በሚል አመክንዮ በአገሪቱ የመቆየትና የመሥራት ዕድላቸው እንዲያበቃ የተወሰነው ባለፈው ታኅሳስ 2018 ነበር።  @Yenetube @Fikerassefa

ኢራን ትራምፕን ለመግደል‼️ እስራኤል ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በእሱ ላይ የግድያ ሙከራ ለማድረግ እያቀደች እንደሆነ የሚጠቁም መረጃ እንዳላት አለምአቀፍ ሚዲያዎች ዘግበዋል። የአሜሪካ መንግ
ኢራን ትራምፕን ለመግደል‼️ እስራኤል ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በእሱ ላይ የግድያ ሙከራ ለማድረግ እያቀደች እንደሆነ የሚጠቁም መረጃ እንዳላት አለምአቀፍ ሚዲያዎች ዘግበዋል። የአሜሪካ መንግስት እና ኢራን በዚህ  ሪፖርት ላይ  ምላሽ አልሰጡም። ነገር ግን ዋሽንግተን ቀደም ሲል ኢራን ትራምፕን ለመግደል ያደረጓቸውን በርካታ ሙከራዎች እንዳከሸፈች ተናግራለች። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

በዓለም ዋንጫው ሀገሩን ወክሎ የተጫወተው ደቡብ አፍሪካዊው አማካይ ህይወቱ አለፈ ​በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ሀገሩን ወክሎ የተጫወተው ደቡብ አፍሪካዊ አማካይ ጄይደን አዳምስ በ25 ዓመቱ ህይወቱ
+2
በዓለም ዋንጫው ሀገሩን ወክሎ የተጫወተው ደቡብ አፍሪካዊው አማካይ ህይወቱ አለፈ  ​በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ሀገሩን ወክሎ የተጫወተው ደቡብ አፍሪካዊ አማካይ ጄይደን አዳምስ በ25 ዓመቱ ህይወቱ ያለፈው፤ ራሱን አጥፍቶ እንደሆነ መረጃዎች ጠቁመዋል።  ​የማሜሎዲ ሰንዳውንሱ ተጫዋች፣ ብሔራዊ ቡድኑ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫውን የጥሎ ማለፍ ዙር በመቀላቀል አዲስ ታሪክ በጻፈበት መድረክ ላይ በሦስቱም የምድብ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቶ ነበር።  ​አዳምስ በውድድሩ ወቅት አያቱ ከዚህ ዓለም በሞት በተለዩ ማግስት ከቼክ ሪፐብሊክ ጋር በተደረገው ጨዋታ ላይ በመሰለፍ አስደናቂ የሆነ የአዕምሮ ጥንካሬና ፅናት አሳይቷል።  ​ከተጫዋቹ ህልፈት በኋላ ከመላው የእግር ኳስ ቤተሰብ የተጫዋቹን ተሰጥኦ እና ለቡድኑ የነበረውን ታማኝነት የሚያወድሱ የሀዘን መግለጫዎች እየወጡ ይገኛሉ።  @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ከ11.5 በመቶ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ በላይ የሚጠይቁ አከራዮች እስከ ሦስት ወር የኪራይ ክፍያ ቅጣት ይጣልባቸዋል - የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለዘንድሮ
ከ11.5 በመቶ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ በላይ የሚጠይቁ አከራዮች እስከ ሦስት ወር የኪራይ ክፍያ ቅጣት ይጣልባቸዋል - የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለዘንድሮው በጀት ዓመት የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5 በመቶ እንዲሆን ወስኗል፡፡ ይህንን ሕግ በሚተላለፉ አከራዮች ላይ ከባድ የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣል ከኢቢሲ ዶት ስትሪም ጋር ቆይታ ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ ተናግረዋል:: ኃላፊዋ እንደገለጹት ይህ የጭማሪ ጣሪያ የተወሰነው የከተማዋን ነባራዊ ሁኔታ፣ የተከራዮችን የመክፈል አቅም፣ የኑሮ ውድነትን እና የዋጋ ግሽበትን ታሳቢ ያደረገ ጥልቅ ሳይንሳዊ ጥናት ተካሂዶበት ነው @Seledadotio @Seledadotio

#አሳዛኝ መረጃ የዴዚ እናት አረፈች 😭😭‼ ልጄን የማህበራዊ ሚዲያው እንዳይበላብኝ ነው የምታገለው! የተወዳጇን የዴዚን እናት ቲናን የተዋወኳት ከሁለት አመት በፊት ዴዚን ወደ 20-30 ፕሮግራማችን
#አሳዛኝ መረጃ የዴዚ እናት አረፈች 😭😭‼ ልጄን የማህበራዊ ሚዲያው እንዳይበላብኝ ነው የምታገለው! የተወዳጇን የዴዚን እናት ቲናን የተዋወኳት ከሁለት አመት በፊት ዴዚን ወደ 20-30 ፕሮግራማችን ልንጋብዛት ስናስብ ነበር። ማናጀሯ ነኝ አለችኝ። ቲና ልጇ ዴይዚን እንደሚፈርስ እንቁላል ነው የምታያት በቃለመጠይቁ ላይ የምትጠይቃትን ጥያቄ ፣ እንዴት እንደምታወራት ፣ ምን እንደምትላት ሁሉንም ማወቅ እፈልጋለሁ አለችኝ. ብንጨቃጨቅም የሞያውን ስነምግባርና አሰራር ሳንለቅ ተግባባን። በመጨረሻም ከአንድም ሁለት ጊዜ ያማረ ቃለመጠይቅ አደረግን. ከዛ በኋላ ነው እኔና ቲና ጥሩ ወዳጅ የሆንነው. አብዛኛው ጊዜ ወሬአችን ስለዴይዚ ነው አብዝተሽዋል እስከምላት ድረስ ስለልጇ ትጨነቃለች ብዙ ያየሁባት ስስቴ ናት ትለኛለች. የማህበራዊ ሚዲያው እንዳይበላብኝ ነው የምታገለው ትለኛለች. ብዙ ጊዜ ለምን ከዴይዚ ጋር ቃለመጠይቅ አላደርግላችሁም ብያት ነበር. ''እንኳን ወጥቼ ላወራ ፎቶዬም እንዲታይ አልፈልግም'' ትለኝ ነበር። እንዲህ ያለችው እናት ፤ ልጇ  ልትጎዳባት የመሰላት ጊዜ ግን በአደባባይ ወጥታ በብዙዎች እየተሰደበች ከብዙዎች ጋር ስለልጇ ተሟግታለች። በእርግጥ ትንሿ ዴይዚም እናቷ ምን ያህል እንደምትወዳት ታውቃለች! ዛሬ ቲና ማረፏን ሰማሁ! እጅግ በጣም አስደንጋጭና አሳዛኝ መርዶ ነው! ቲና በጣም ትሁት ፣ ሰው አክባሪ ፣ በልጆቿ የማትደራደር እውነተኛ እናት ነበረች! ፈጣሪ ነፍሷን በሰላም ያሳርፍልን. ለልጆቿ ለመላው ቤተሰቧና ወዳጇቿ መፅናናትን እመኛለሁ። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

በርንሃም ቀጣዩ የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ሊሾሙ ነው አንዲ በርንሃም የሌበር ፓርቲ አባላት አብዛኛዎቹ ሰር ኬይር ስታርመርን እንዲተኩ ከመረጡ በኋላ ቀጣዩ የሌበር ፓርቲ መሪ እና ጠቅላይ ሚኒ
በርንሃም ቀጣዩ የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ሊሾሙ ነው   አንዲ በርንሃም የሌበር ፓርቲ አባላት አብዛኛዎቹ ሰር ኬይር ስታርመርን እንዲተኩ ከመረጡ በኋላ ቀጣዩ የሌበር ፓርቲ መሪ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሆን ሌላ እርምጃ ወስዷል።የበርንሃም የሌበር ፓርቲ አመራር ጥያቄ ከ403 የሌበር ፓርቲ አባላት መካከል 322 ድጋፍ አግኝተዋል፡፡   ይህም ተቀናቃኞቻቸዉ በድምጽ ረገድ ከእርሳቸዉ ጋር ለመወዳደር የማይቻል ከመሆኑ በፊት ከሚያስፈልገው 323 አባላት ውስጥ አንድ ብቻ እንዲያንስ ያደርገዋል። አንዳንድ የፓርላማ አባላት ሐሙስ ዕለት ድምጽ መስጠት እንዳልቻሉ ነገር ግን ወደ ፓርላማ ከተመለሱ በኋላ በርንሃምን እንደሚደግፉ ይናገራሉ።   እንደሚጠበቀው ማንም ሰው ወደ ውድድሩ ካልገባ፣ በርንሃም በሚቀጥለው ሳምንት የሌበር ፓርቲ መሪ ተብለዉ ይሾማሉ፣ ከአስር ቀናት በኃላ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ስልጣን ይይዛሉ ተብሎ ይጠበቃል።ይህም የቀድሞው የታላቁ ማንቸስተር ከተማ ከንቲባ በሜከርፊልድ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በተደረገ የድጋሚ ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ወደ ስልጣን የመጡበት ያልተለመደ የስልጣን ሽግግርን ያሳያል።   በርንሃም በሰጡት መግለጫ፣ የፓርቲው መሪ እንድሆን ለሾሙኝ የሌበር ፓርቲ አባላት "በጥልቅ አመስጋኝ" መሆናቸውን ተናግረዋል።ድጋፉ የመጣው ከመላው ፓርቲ ሲሆን "ብሪታንያ ለፖለቲካ አዲስ አቀራረብ እንደሚያስፈልጋት የጋራ እምነት" እንደሚያንፀባርቅ ተናግረዋል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል

የዘውዲቱ ሆስፒታል በ90 ቀናት ውስጥ 17 ሺህ ለሚጠጉ ሰዎች ነጻ ህክምና ሊሰጥ ነው የዘውዲቱ ሆስፒታል የአስተኝቶ ህክምና ዲፓርትመንት ኃላፊ የሆኑት ዶክተር ወንደሰን በላችሁ ለብስራት ሬድዮ እንደገ
የዘውዲቱ ሆስፒታል በ90 ቀናት ውስጥ 17 ሺህ ለሚጠጉ ሰዎች ነጻ ህክምና ሊሰጥ ነው   የዘውዲቱ ሆስፒታል የአስተኝቶ ህክምና ዲፓርትመንት ኃላፊ የሆኑት ዶክተር ወንደሰን በላችሁ ለብስራት ሬድዮ እንደገለጹት ሆስፒታሉ በክረምት የበጎ አድራጎት መርሃ ግብር በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል። በተለያዩ ቦታዎች በመገኘትና ድንኳን በመትከል ነጻ የህክምና እና የዕይታ ልየታ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገልፀዋል።   በዚህም ክብር ለአረጋውያን የበጎ አድራጎት ድርጅት ማቆያ ውስጥ በመገኘት አራት ሀኪሞች፣ ስድስት ነርሶች፣ የአይን፣ የጥርስ እና የስነ-አእምሮ ባለሙያዎችን ባካተተ ቡድን ለዜጎች ህክምና ሰጥቷል። 200 ለሚሆኑ ሰዎች የዕይታ እና የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል። ከተጠቃሚዎቹ መካከል ከዚህ ቀደም የደም ግፊትና የስኳር ህመም የነበረባቸው ሰዎች የተገኙ ሲሆን እዛው ህክምናቸውን እንዲቀጥሉ ምክር ተሰጥቷቸዋል።   ዶክተር ወንደሰን አክለው እንደተናገሩት አራት ሰዎች በአይን ሞራ ግርዶሽ ፤ ሁለት ሰዎች በትራኮማ በሚመጣ የአይን ኢንፌክሽን ተጠቅተዋል። ሶስት ሰዎች ደግሞ የዕይታ ችግር ስላለባቸው መነጽር እንደሚያስፈልጋቸው ተለይተዋል።  ይህ የነጻ ህክምና መርሃ ግብር ለ90 ቀናት ሲቆይ በሁለት የአረጋውያን መርጃ ድርጅቶች በቀጣይ ተመሳሳይ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዷ ።17 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች በነጻ ህክምናዉ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ግብፅ እና ኢትዮጵያ ሳይስማሙ ቀሩ በኢትዮጵያ አዘጋጅነት ለአራት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 22ኛው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሚኒስትሮች ምክር ቤት እና 37ኛው የአስተባባሪ ኮሚቴ
ግብፅ እና ኢትዮጵያ ሳይስማሙ ቀሩ በኢትዮጵያ አዘጋጅነት ለአራት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 22ኛው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሚኒስትሮች ምክር ቤት እና 37ኛው የአስተባባሪ ኮሚቴ አስቸኳይ ልዩ ጉባዔ ዛሬ ተጠናቋል። ጉባዔው ያስፈለገው ግብፅና ሊቢያ ጨምሮ 13 አባል ሀገራት ያሉት ትስስሩ የመበታተን አደጋ የተጋረጠበት በመሆኑ ነው፡፡ አባል ሀገራቱን ከመበታተን ለመታደግ የህግ ማዕቀፎችን በማሻሻልና ማጠናከር ማስፈለጉን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ገልጸዋል። በጉባዔው አዲስ የሚመሰረተው የኤሌክትሪክ ኃይል የገበያ ማዕከል ዋና መቀመጫን ለመወሰን ውይይት ተደርጓል፡፡ በዚህ አጀንዳ ኢትዮጵያ ከድርጅቱ አባል ሀገራት ብቸኛ የኃይል አቅራቢ እንደመሆኗ ለአራት ቀናት በዘለቀው የትስስሩ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ከፍተኛ ሙግት ማካሄዱ ተገልጿል፡፡ በተለይም ከግብፅ ጋር  የገበያ ማዕከሉ ኢትዮጵያ መሆን አለበት በሚለው ሃሳብ ከፍተኛ ሙግት መደረጉን ኢንጂነር ሃብታሙ ገልፀዋል። በዚሁ ጉዳይ የግብፅ ተወካዮች ማዕከሉ ወደ ካይሮ ካልሆነ በሚል የያዙት አቋም ከኢትዮጵያ ጋር ከመግባባት ሳይደርሱበት ጉባዔው ተጠናቋል። @Addis_News @Addis_News

ጋምቤላ ከ7 ቶን በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ አስገባ! የጋምቤላ ክልል ማዕድን ኤጀንሲ በ2018 በጀት ዓመት ከ7 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ የወርቅ ምርት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉን አስታውቋ
ጋምቤላ ከ7 ቶን በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ አስገባ! የጋምቤላ ክልል ማዕድን ኤጀንሲ በ2018 በጀት ዓመት ከ7 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ የወርቅ ምርት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉን አስታውቋል። ኤጀንሲው ለፋና ዲጂታል እንደገለጸው፥ ይህ ታላቅ ስኬት የተመዘገበው በክልሉ ያለውን እምቅ የወርቅ ማዕድን ሀብት በሚገባ ለማልማትና ጥቅም ላይ ለማዋል በተደረገው ከፍተኛ ጥረት ነው። የወርቅ ምርቱ የተሰበሰበው በክልሉ በሚንቀሳቀሱ ባህላዊ፣ ልዩ አነስተኛ እና የወርቅ አምራች ኩባንያዎች አማካኝነት መሆኑም ተገልጿል። ይህንን ከፍተኛ የሀብት ክምችት ገቢ ለማድረግ የማዕድን ሀብት ልማት አሰራርን በማዘመን ዘርፉን ከብክነት ለመታደግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል። በተለይም በማዕድን ዘርፉ ውስጥ የሚስተዋለውን ሕገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ ለመከላከል የተከናወነው ቁጥጥርና ዘመቻ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ኤጀንሲው አመልክቷል። በቀጣይም በክልሉ ያለውን እምቅ የማዕድን ሀብት ይበልጥ በተገቢው መንገድ አልምቶ ለሀገር ልማት ለማዋል በትኩረት እንደሚሰራም ተጠቁሟል። @YeneTube @FikerAssefa

ፕሬዚዳንት ትራምፕ የተኩስ አቁም ስምምነቱ «መቋረጡን» ቢያውጁም #አሜሪካ አና #ኢራን ድርድሩን እንደሚቀጥሉ ገለጹ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ሳምንት በሁለቱ አገራት መካከል የተቀሰ
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የተኩስ አቁም ስምምነቱ «መቋረጡን» ቢያውጁም #አሜሪካ አና #ኢራን ድርድሩን እንደሚቀጥሉ ገለጹ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ሳምንት በሁለቱ አገራት መካከል የተቀሰቀሰውን አዲስ ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ የተኩስ አቁም ስምምነቱ «መቋረጡን» ቢያውጁም፥ ቴህራን የድርድር ጥያቄ በማቅረቧ ዩናይትድ ስቴትስ ከኢራን ጋር የምታደርገውን ንግግር ለመቀጠል መስማማቷን አስታወቁ። ፕሬዚዳንት ትራምፕ ባለፈው ዓርብ «ትሩዝ ሶሻል» በተሰኘው የማኅበራዊ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መግለጫ፥ «የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ንግግሩን እንድንቀጥል ጠይቃናለች፤ እኛም በዚህ ተስማምተናል፤ ነገር ግን ዩናይትድ ስቴትስ የተኩስ አቁም ስምምነቱ መቋረጡን በግልጽ አስታውቃቸዋለች» ብለዋል። ይህ የፕሬዚዳንቱ አስተያየት የወጣው በዚህ ሳምንት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተደረገውን ወታደራዊ ጥቃት ተከትሎ ነው። የቅርብ ጊዜው የሁለቱ አገራት ውጥረት ያገረሸው በባሕረ ሰላጤው በንግድ መርከቦች ላይ የተሰነዘረውን ጥቃት ተከትሎ አሜሪካ በኢራን ኢላማዎች ላይ የአየር ጥቃት በመሰንዘሯ ሲሆን፥ ቴህራንም በጎረቤት የባሕረ ሰላጤው አገራት በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋማት ላይ ጥቃት በመሰንዘር የአፀፋ ምላሽ ሰጥታለች። @Yenetube @Fikerassefa

የ3 ዓመትን ህፃን ልጅ በማባበል ጠልፋ የወሰደች ግለሰብ በእስራት ተቀጣች ተካሳሽ ወ/ሮ አገኘውሽ ታርኩ መጋቢት 24 ቀን 2018 ከጠዋቱ 2 ሰዓት አከባቢ በጂንካ ከተማ ጤናአዳም ቀበሌ የግል ተበዳይ
የ3 ዓመትን ህፃን ልጅ በማባበል ጠልፋ የወሰደች ግለሰብ በእስራት ተቀጣች   ተካሳሽ ወ/ሮ አገኘውሽ ታርኩ መጋቢት 24 ቀን 2018 ከጠዋቱ 2 ሰዓት አከባቢ በጂንካ ከተማ ጤናአዳም ቀበሌ የግል ተበዳይ የ3 ዓመት ህፃን መክሊት ተስፋለም የተባለችውን  መጫወቻ አሻንጉሊት ይዛ በማባብል ልፋ ወስዳለች፡፡ ህፃኗ ከልጆች ጋር እየተጫወተች ሳለ አጠገቧ በመቀመጥ በአሻንጉሊት አታላ በጀረባዋ በማዘል ይዛት እየሄደች ባለችበት በአከባቢው ማህበረሰብ ጥቁማ ተይዛለች፡፡   የጂንካ ከተማ ፍትህ ጽ/ቤት የሴቶች እና ህፃናት ስራ ሂደት ዐቃቤ ህግ መዝገቡ መርምሮ በአስችኳይ ክስ መስርቷል፡፡ በ1996 ዓ.ም በወጣው የኢፌዴሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 589(2) ሥር ለአካል መጠን ያልደረሰች ልጅን መጥለፍ ወንጀል ክስ በመመስረት እና ማሰረጃ በማሰማት ሲያከራክር ቆይቶ ሀምሌ 2 ቀን 2018 በጂንካ ከተማ መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋለው  ችሎት ተከሳሽን ያርማል ማህበረሰቡንም ያስተምራል በማለት በ7 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል።   ማህበረሰቡ መሰል የወንጀል ድርጊቶች እንዳይፈፀም ልጆቻቸውን እንዲጠብቁ እና  እንድከታተሉ  ሲል የጂንካ ከተማ ፍትህ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ህዝቅኤል አምባው  ያሳሰቡ ሲሆን  እንደዝህ አይነት ወንጀል ሲፈፀም ለህግ አካል ጥቆማ እንዲያደርሱ መልዕክት ማስተላለፋቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል፡፡   በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል

በአዲስ አበባ ከተማ በሆቴሎች እና ተመሳሳይ ተቋማት የመኝታ አገልግሎት ላይ የ5 በመቶ ማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ ተጣለ። ⚫️ በአዲሱ ደንብ ድንጋጌ መሰረት ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም የመኝታ ክፍሎቹን ብዛትና የእያንዳንዱን ክፍል የቀን የዋጋ ዝርዝር በገቢዎች ቢሮ በአካል ቀርቦ በልዩ ቅጽ መሙላትና ማሳወቅ ይኖርበታል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሆቴሎች፣ በሪዞርቶች፣ በሞቴሎች እና በሌሎች መሰል የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ አዲስ የማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ የሚጥል ደንብ አወጣ። "የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የመኝታ አገልግሎት ማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ ደንብ ቁጥር 204/2018" በሚል የወጣው ይህ ደንብ፣ የከተማዋን የገቢ አቅም ለማሳደግና መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በደንቡ አንቀጽ 6 መሠረት፣ ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ተጠቃሚ ለክፍል አገልግሎት ከሚከፍለው ዋጋ ላይ 5 በመቶ (5%) የማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ እንዲከፍል ይደረጋል። ይህ የታክስ ተመን የሚሰላው የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ሳይታከልበት ባለው መደበኛ የክፍል ዋጋ ላይ ተመስርቶ መሆኑ ተደንግጓል። ይህ አዲስ የታክስ ሕግ በከተማዋ አስተዳደር ወሰን ውስጥ የሚገኙ ሁሉንም የመኝታ አገልግሎት ሰጪዎችን የሚያካትት ሲሆን፣ እነዚህም፦ • ከ1 እስከ 7 ኮከብ ደረጃ ያላቸው ሆቴሎች እና ኮከብ የሌላቸው ሆቴሎች፣ • ሪዞርቶች፣ ሎጆች እና ሞቴሎች፣ • የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች (Guest Houses) እና ፔንሲዮኖችን ያጠቃልላል። አገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ በየወሩ ወይም በየሦስት ወሩ (እንደ ግብር ከፋይ ደረጃቸው) የሰበሰቡትን ታክስ ለከተማው ገቢዎች ቢሮ ሪፖርት የማድረግና ገቢ የማድረግ ግዴታ ተጥሎባቸዋል። ደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች  በየወሩ ሪፖርት አድርገው ገቢ የሚያደርጉ ሲሆን ደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች ደግሞ በየሦስት ወሩ ሪፖርት አድርገው ገቢ ያደርጋሉ። ደንቡን በማይተገብሩ፣ ሪፖርት በሚያዘገዩ ወይም የገቢ መረጃ በሚደብቁ ተቋማት ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና ቅጣት እንደሚጣል ተመልክቷል። ለማሳያም ሪፖርት ያዘገየ ተቋም ካለበት ዕዳ ላይ እስከ 50 በመቶ የሚደርስ ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችልና የታክስ መረጃ መደበቅ ደግሞ በወንጀል እንደሚያስጠይቅ ተደንግጓል። እንደ ደንቡ ድንጋጌ፣ ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በገቢዎች ቢሮ በአካል ቀርቦ የመመዝገብ ግዴታ ያለበት ሲሆን፣ በሚመዘገብበት ወቅትም የተቋሙን የክፍሎች ብዛትና የእያንዳንዱን ክፍል የቀን የዋጋ ዝርዝር በልዩ ቅጽ መሙላትና ማሳወቅ ይኖርበታል። ይህ የታክስ አከፋፈል ሂደት ከተቋማቱ የንግድ ፈቃድ እድሳት ጋርም በቀጥታ የተያያዘ ነው። የከተማዋ የቱሪዝም ኮሚሽን የሆቴሎችን የሙያ ብቃት ፈቃድ የሚያድሰው ተቋማቱ ታክሱን በአግባቡ መክፈላቸውን የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ከገቢዎች ቢሮ ሲያቀርቡ ብቻ መሆኑ በደንቡ ላይ በግልጽ ተቀምጧል። የታክስ አሰባሰቡን ግልጽነት ለማረጋገጥም፣ ተቋማቱ በሚሰጡት የሽያጭ ደረሰኝ ላይ "የማዘጋጃ ቤታዊ መኝታ አገልግሎት ታክስ" የሚለው ሐረግ በግልጽ እንዲሰፍር ታዟል። የሒሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ የሌለባቸው ግብር የሚከፍሉ ተቋማት ደግሞ ከሚሰጡት አገልግሎት 70 በመቶው ላይ የ5 በመቶ ታክስ ታስቦ እንዲከፍሉ ይደረጋል። በተጨማሪም ተቋማቱ የሰበሰቡትን የታክስ ገቢ በየወሩ ጠቅልለው ሪፖርት ከማድረጋቸው ባለፈ፣ ሰብስበው ባጠናቀቁ በ30 ቀናት ውስጥ ለዚሁ ተብሎ ወደተከፈተ የባንክ ሒሳብ ገቢ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም በታክስ አሰባሰብና በአሠራር ሂደት ላይ ቅሬታ ካላቸው በየደረጃው ለሚገኝ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ የማቅረብ መብት አላቸው። ኮሚቴው ቅሬታውን ተቀብሎ በ15 የሥራ ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት ያለበት ሲሆን፣ በውሳኔው ቅር የተሰኘ ወገን ውሳኔው በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ለከተማ አስተዳደሩ የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን አቤቱታውን ማቅረብ ይችላል። ማንኛውም የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋም ከመኝታ አገልግሎት የተገኘን ገቢ ወቅቱን ጠብቆ ሪፖርት አለማሳወቅ ለዘገየበት በየወሩ 5 ከመቶ ከክፍያው ከ50 ከመቶ ያልበለጠ ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል። በተጨማሪም የታክስ ገቢውን በወቅቱ ገቢ ያላደረገ ተቋም በወቅታዊ የባንክ ብድር ወለድ ተመን መሠረት ወለድና በወለዱ ላይ ተጨማሪ 15 በመቶ ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል። አዲስ አበባ የቱሪስት መዳረሻነቷ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ፣ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለከተማዋ የልማት ስራዎች ለማዋል ታስቦ የወጣ መሆኑን የመግቢያው ክፍል ያስረዳል። ይህም የከተማዋን የገቢ መሠረት በማስፋት የንግድ እንቅስቃሴው ለከተማዋ እድገት የሚኖረውን ድርሻ ከፍ ያደርጋል ተብሏል። ይህ ደንብ በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተፈርሞ የወጣ ሲሆን፣ ከሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የጸና ሆኗል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ሰራቆ ቀበሌ በግ ሰር'ቆ ሲያ'ርድ በህብረተሰቡና በፀጥታ ሀይሎች ትብብር በቁጥጥር ስር የዋለው ሌባ መቀጣጫ ሆነ። ሰ'ርቆ በመግፈፍ ላይ የነበረውን በግ ተሸክ
+1
በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ሰራቆ ቀበሌ በግ ሰር'ቆ ሲያ'ርድ በህብረተሰቡና በፀጥታ ሀይሎች ትብብር በቁጥጥር ስር የዋለው ሌባ መቀጣጫ ሆነ። ሰ'ርቆ በመግፈፍ ላይ የነበረውን በግ ተሸክ'ሞ ከተማውን እንዲዞር ተደርጓል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

ለሶስት የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ ተሰጠ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለሶስት አዳዲስ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ ፕራይዝዎርዝ ኢንቨስትመንት ባንክ አ.
ለሶስት የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ ተሰጠ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለሶስት አዳዲስ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ ፕራይዝዎርዝ ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ በኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ ፈቃድ ከተሰጣቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ በተጨማሪም ብሉፊን ካፒታል አድቫይዘሪ ኃ.የተ.የግ.ማ እና ሉሚና ካፒታል ኃ.የተ.የግ.ማ በሰነደ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት ማማከር ዘርፍ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል፡፡ ይህን ተከትሎም በባለስልጣኑ ፈቃድ የተሰጣቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎችን ጠቅላላ ቁጥር 21 ደርሷል፡፡ ባለስልጣኑ አገልግሎት ሰጪዎቹ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ሁሉን ባለሃብቶች ባማከለ መልኩ በዕውቀት፣ በታማኝነት እንዲሁም በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስቧል፡፡ በሌላ በኩል የሶስቱ አዳዲስ አገልግሎት ሰጪዎች 10 ተሿሚ እንደራሴዎች እንዲሁም የ15 ቦርድ አባላት ሹመት ፈቃድ መጽደቁን የባለስልጣኑ መረጃ አመልክቷል፡፡ @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

በፊሊፒንስ H5N1 የተባለ የወፍ በሽታ መቀስቀሱን የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት አስታወቀ። ኦሬንታል ሚንዶሮ በተባለው ግዛት በ 39 የደሮ እርባታ ጣቢያዎች በሽታው መከሰቱን የገለጸው ድርጅቱ ወደ
በፊሊፒንስ H5N1 የተባለ የወፍ በሽታ መቀስቀሱን የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት አስታወቀ። ኦሬንታል ሚንዶሮ በተባለው ግዛት በ 39 የደሮ እርባታ ጣቢያዎች በሽታው መከሰቱን የገለጸው ድርጅቱ ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይሰራጭ ስጋቱን ገልጿል።  ይህ በሽታ ከዚህ ቀደምም በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች የተከሰተ ሲሆን የዶሮ ገበያውን ክፉኛ አናግቶት ነበር።   የሰዎች ከቦታ ወደ ቦታ የመዘዋወርም በተወሰነ መልኩ አስተጓጉሎ እንደነበርም ዘገባው ጠቅሷል። በፍሊፒንስ የወፍ በሽታው የታየባቸው የደሮ እርባታ ጣቢያዎች ውስጥ የነበሩ ደሮዎች በሙሉ እንዲቃጠሉ መደረጉን ሮይተርስ ዘግቧል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ጀርመን በኢራቅ ያላትን ወታደራዊ ካምፕ ዘግታ እንደምትወጣ አስታወቀች። የጀርመን የመከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በቴሌግራም ገጻቸው እንዳሉት ወታደሮቹ እስከ መጪው መስከረም ባለው ጊዜ ሙሉ በሙሉ ይ
ጀርመን በኢራቅ ያላትን ወታደራዊ ካምፕ ዘግታ እንደምትወጣ አስታወቀች።  የጀርመን የመከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በቴሌግራም ገጻቸው እንዳሉት ወታደሮቹ እስከ መጪው መስከረም ባለው ጊዜ ሙሉ በሙሉ ይወጣሉ። በኢራን የእስላማዊ መንግስት የተባለው ታጣቂ ቡዱን  የሚያደርሰውን ጥቃት ለመከላከልና የኢራቅ ወታደሮችን ለማሰልጠን በሚል የተለያዩ ሐገራት ወታደሮቻቸውን በኢራቅ ማሰማራታቸውን ይታወቃል።  ጀርመን የዚሁ ፕሮጀክት አካል በመሆን በኤርቢል ከተማ 30 የሚሆኑ ወታደሮቿን በማሰማራት ለኢራቅ ወታደሮች የስልጠና ድጋፍ ሲሰጡ እንደነበር ዘገባዎች ያመላክታሉ። አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት ተከትሎ ለወታደሮቹ ደህንነት በመስጋት ጀርመን እስከ መጪው መስከረም ሙሉ በሙሉ ካምፑን ዘግታ እንደምትወጣ ሮይተርስ ዘግቧል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ዜና፡ ብርቅዬው የ #ዋልያ_አይቤክስ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነሱ ምክንያት «ለመጥፋት አደጋ በእጅጉ የተጋለጠ» በሚል መደብ ውስጥ ተካተተ ዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ሕብረት (IUCN) በቅርቡ ባ
ዜና፡ ብርቅዬው የ #ዋልያ_አይቤክስ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነሱ ምክንያት «ለመጥፋት አደጋ በእጅጉ የተጋለጠ» በሚል መደብ ውስጥ ተካተተ ዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ሕብረት (IUCN) በቅርቡ ባደረገው ግምገማ በ #ኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘው የዋልያ አይቤክስ ዝርያ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን ተከትሎ፤ «ለመጥፋት አደጋ በእጅጉ የተጋለጠ» በሚል መደቡ ውስጥ መካተቱን አስታወቀ። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ፖል ሾልት ሾልት እንደገለጹት የተደረጉ ተጨማሪ ጥናቶች በኢትዮጵያ #ስሜን_ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ብቻ የሚገኘው ዋሊያ አይቤክስ ቁጥር አሁንም እያሽቆለቆለ መሆኑን ያሳያሉ። በታህሳስ 2017 በተካሄደ ጥናት 271 ዋልያዎች ብቻ ተገኝተዋል ብለዋል። ይህም በአንድ ዓመት ውስጥ ከፍተኛ የቁጥር ማነስ መኖሩን አመላክቷል ብለዋል። ለዝርያው መመናመን፤ ለሥጋና ለባህላዊ መድኃኒትነት የሚደረገው ሕገ-ወጥ አደን፣ የተፈጥሮ መኖሪያ መራቆት እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የሰዎች ድንበር መተላለፍ ቀዳሚ ምክንያቶች መሆናቸው በጥናት ተረጋግጧል ተብሏል። https://addisstandard.com/Amharic/?p=13273

#ኢትዮጵያውያን ላኪዎች #የእንግሊዝን ከቀረጥ ነፃ የንግድ መርሃ-ግብር እንዲጠቀሙ ተጠየቀ የኢትዮጵያውያ ላኪዎች ብቁ የሆኑ ምርቶችን በቅናሽ ወይም ያለምንም ቀረጥ ወደ እንግሊዝ ገበያ ለማስገባት የሚ
+1
#ኢትዮጵያውያን ላኪዎች #የእንግሊዝን ከቀረጥ ነፃ የንግድ መርሃ-ግብር እንዲጠቀሙ ተጠየቀ የኢትዮጵያውያ ላኪዎች ብቁ የሆኑ ምርቶችን በቅናሽ ወይም ያለምንም ቀረጥ ወደ እንግሊዝ ገበያ ለማስገባት የሚያስችለውን የእንግሊዝ ታዳጊ አገራት የንግድ መርሃ-ግብር (DCTS) ይበልጥ እንዲጠቀሙበት ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደ የሥልጠና አውደ-ጥናት ላይ ጥሪ ቀረበ። አውደ-ጥናቱ በለንደን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የእንግሊዝ የንግድና ቢዝነስ መሥሪያ ቤት፣ በአዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ እንዲሁም የኢትዮጵያ የንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን፤ ከኢትዮጵያና ከእንግሊዝ የተውጣጡ ወደ 100 የሚጠጉ ተሳታፊዎችን በአካልና በበይነ-መረብ ተሳትፈዋል። https://www.facebook.com/share/p/193cHnCPi9/

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በመምሰል የማታለል (በተለምዶ ሿሿ) ተብሎ የሚጠራውን ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ሰኔ 28
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በመምሰል የማታለል (በተለምዶ ሿሿ) ተብሎ የሚጠራውን ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 1:40 በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ሪቼ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው። የግል ተበዳይ ከአጎና ወደ እስታዲየም ለመሄድ በማሰብ ኮድ 3-83620 ኦሮ ነጭ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በማስቆም ትገባለች። ተጠርጣሪዎችም የግለሰቧን ወደ ተሽከርካሪው መግባት ተከትለው በማዋከብ እና ትኩረቷን በማሳጣት ይዛው ከነበረው ቦርሳ ውስጥ 32 ሺ ብር ግምት ያለው ሳምሰንግ ስልክ ሰርቀው ጥለዋት ይሄዳሉ። ይህን የተመለከቱ የትራፊክ ፖሊሶች ተሽከርካሪውን በማስቆም እና ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ ሰርተዋል። ተጠርጣሪዎቹ ከተያዙ በኋላ በተሽከርካሪው ውስጥ በተደረገ ፍተሻ 7 ስልኮች መገኘታቸውን የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አስታውቋል። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል ነፍሰ ጡር መኖሯ የተገለጸ ሲሆን የቀን ውሎ አበል በመክፈል እና ተሽከርካሪ በመከራየት ወንጀሉን የሚፈፅሙ ግለሰቦች እንዳሉ ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ትራንስፖርት ሲጠቀም ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

በደቡባዊ ስፔን በተቀሰቀሰ ሰደድ እሳት ቢያንስ የ12 ሰዎች ህይወት አለፈ በስፔን ደቡባዊ አንዳሉሲያ ክልል ውስጥ በፍጥነት እየተዛመተ በመጣ ሰደድ እሳት ቢያንስ 12 ሰዎችን ገድሏል።የክልሉ ባለስልጣ
በደቡባዊ ስፔን በተቀሰቀሰ ሰደድ እሳት ቢያንስ የ12 ሰዎች ህይወት አለፈ   በስፔን ደቡባዊ አንዳሉሲያ ክልል ውስጥ በፍጥነት እየተዛመተ በመጣ ሰደድ እሳት ቢያንስ 12 ሰዎችን ገድሏል።የክልሉ ባለስልጣናት አርብ ዕለት በክልሉ ውስጥ የተመዘገበው እጅግ ገዳይ የእሳት ቃጠሎ መሆኑን አስታዉቀዋል፣ በርካታ ተጨማሪ ሰዎች እስካሁን እንዳልተገኙም ይፋ ተደርጓል። ባለስልጣናት የእሳቱን መንስኤ እስካሁን አላረጋገጡም፣ ይህ ሰደድ እሳት አገሪቱ ያጋጠመዉ ከፍተኛ የሙቀት መጠን እያሳለፈች ባለችበት ወቅት ነው።   እሳቱ ሐሙስ ከሰዓት በኋላ በአልሜሪያ ግዛት በሎስ ጋላርዶስ ማዘጋጃ ቤት በሚገኘው ኤን-340 አውራ ጎዳና አቅራቢያ ተቀስቅሷል። ኃይለኛ ነፋስ እሳቱን በፍጥነት ወደ አጎራባች ቤዳር ማዘጋጃ ቤት አቀጣጥሎታል።የአካባቢው ባለስልጣናት እንደዘገቡት የአደጋ ጊዜ አገልግሎቶች በርካታ ተጎጂዎችን ከአንድ የገጠር መንደር ለመሸሽ ሲሞክሩ በተሽከርካሪዎች ውስጥ ተይዘው ተገኝተዋል።   ባለስልጣናት የነፍስ አድን ፍለጋ ስራቸውን ቀጥለዋል። የአንዳሉሲያ የክልል መሪ ጁዋንማ ሞሬኖ አርብ ዕለት ለካዴና ሰር ሬዲዮ እንደተናገሩት አስራ ዘጠኝ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ሲል ማለታቸዉን የሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።ሌሎች አራት ሰዎች ደግሞ በትናንሽ ቃጠሎዎችና በመተንፈሻ አካላት ችግር ምክንያት በቦታው ህክምና ተደርጎላቸዋል። ወደ 50 የሚጠጉ የተፈናቀሉ ነዋሪዎች በአካባቢው በሚገኝ የባህል ማዕከል ተጠልለው እንደሚገኙ ባለስልጣናቱ አክለዋል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል