ch
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

前往频道在 Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

显示更多

📈 Telegram 频道 Fresh መረጃ | FreshNews 的分析概览

频道 Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 55 839 名订阅者,在 教育 类别中位列第 3 023,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 579

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 55 839 名订阅者。

根据 26 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -738,过去 24 小时变化为 -30,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.60%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.93% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 011 次浏览,首日通常累积 1 635 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

凭借高频更新(最新数据采集于 27 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

55 839
订阅者
-3024 小时
+1347
-73830
帖子存档
በኢሮብ ወረዳ 35 ሺህ ህዝብ ለከባድ ድርቅ ተጋልጧል። በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የሚገኘው ኢሮብ ወረዳ ከባድ ድርቅ እየተጋፈጠ ሲሆን፤ በአካባቢው የሚኖሩ 35 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ለድርቅ አደጋ መ
+2
በኢሮብ ወረዳ 35 ሺህ ህዝብ ለከባድ ድርቅ ተጋልጧል። በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የሚገኘው ኢሮብ ወረዳ ከባድ ድርቅ እየተጋፈጠ ሲሆን፤ በአካባቢው የሚኖሩ 35 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ለድርቅ አደጋ መጋለጣቸው ተገልጿል። በወረዳው የክረምት ዝናብ በበቂ ሁኔታ ባለመዝነቡ የውሃ ጉድጓዶች መድረቃቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በውሃ እጥረቱም የቤት እንስሳት መሞት መጀመራቸውን አስረድተዋል። በወረዳው የሚገኙ ስምንት ቀበሌዎች በከፍተኛ ተራራና ተዳፋት አካባቢዎች መሆናቸው የተጀመረውን የእርዳታ ማዳረስ ስራ ፈታኝ እንዳደረገው ተጠቁሟል። የአካባቢው አርሶ አደሮች እንደሚሉት፣ ከዚህ በፊት እንደ ዘንድሮ ያለ ከባድ ድርቅ አጋጥሟቸው አያውቅም። የዝናብ እጥረቱ በማሳ ላይ የተዘራው እህል እንዲደርቅ ከማድረጉም በላይ በክረምት ዝናብ ይሞሉ የነበሩ የውሃ ጉድጓዶች እንዲደርቁ አድርጓል። የኢሮብ አካባቢ የኢሮብ ብሄረሰብ የሚኖርበት ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወረዳዎች አንዱ ነው።  አካባቢው በ2013 ዓ.ም በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ ጥቃት የደረሰበት ሲሆን እስካሁንም አንዳንድ የቀበሌ ገበሬ ማህበራት በኤርትራ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ይገኛሉ። Via_tikvah @Addis_News @Addis_News

በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በቴሌ ብር መተግበሪያ የ4 ነጥብ 19 ትሪሊየን ብር የዲጅታል ግብይት መፈጸሙን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ። ኢንቨስትመንት ሆልዲንግሱ ይሄንን ያለ
በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በቴሌ ብር መተግበሪያ የ4 ነጥብ 19 ትሪሊየን ብር የዲጅታል ግብይት መፈጸሙን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ። ኢንቨስትመንት ሆልዲንግሱ ይሄንን ያለው በስሩ የሚገኙ ተቋማት አመታዊ አፈጻጸም ግምገማ ለ3ኛ ቀን መቀጠሉን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ላይ ነው። የቴሌ ብር ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ60 ሚሊዮን በላይ መድረሱን ያነሳው ተቋሙ ቴሌ ብር በ2018 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 83 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱንም ገልጿል። በተጨማሪም በበጀት አመቱ የኢትዮ ቴሌኮም ገቢ በ33 ነጥብ 2 በመቶ ማደጉም ነው የተጠቀሰው። @Addis_News @Addis_News

የዓለም ጤና ድርጅት ኡጋንዳ ከኢቦላ ነፃ መሆኗን አረጋገጠ ኡጋንዳ የመጨረሻው የተረጋገጠ ታካሚ ከሆስፒታል በወጣ በ42ኛው ቀን፣ ባለፈው ወር ቫይረሱ በይፋ መጥፋቱን ገልጻ ነበር። የዓለም ጤና ድርጅት
የዓለም ጤና ድርጅት ኡጋንዳ ከኢቦላ ነፃ መሆኗን አረጋገጠ ኡጋንዳ የመጨረሻው የተረጋገጠ ታካሚ ከሆስፒታል በወጣ በ42ኛው ቀን፣ ባለፈው ወር ቫይረሱ በይፋ መጥፋቱን ገልጻ ነበር። የዓለም ጤና ድርጅትም ምንም አይነት የቀረ የቫይረስ ስርጭት ሰንሰለት አለመኖሩን ለማረጋገጥ ሁኔታውን ሲከታተል ቆይቷል። ጎረቤት ኮንጎ ቫይረሱ መከሰቱን ካወጀችበት ከግንቦት 7 ጀምሮ ኡጋንዳ በአጠቃላይ 20 የቫይረሱ ተጠቂዎችን አረጋግጣ ነበር። በምስራቅ ኮንጎ ያለው ሁኔታ በጣም የተለየ ነው፤ ቫይረሱ የጤና ባለሙያዎችን በከፍተኛ ሁኔታ በሚያሰጋ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል። በስድስት ግዛቶች ውስጥ ከ2 ሺህ በላይ ሞቶችን ጨምሮ ከ4 ሺህ 5መቶ በላይ የቫይረሱ ተጠቂዎች ተመዝግበዋል። ባለፈው ሳምንት የዓለም ጤና ድርጅት ለጎረቤት ሀገራት፣ በተለይም ከኮንጎ ጋር የየብስ ድንበር ለሚጋሩት፣ ስጋቱ አሁንም ከፍተኛ መሆኑን ገልጾ አዳዲስ ጊዜያዊ ምክረ ሃሳቦችን አቅርቧል። እስከዳር ግርማ @Ethionews433 @Ethionews433

ከ70 በላይ ለሚሆኑ ደን ጠባቂ ሬንጀሮች የዕዉቅና ስጦታ ተበረከተ ቴምር ፕሮፐርቲስ 75 ለሚጠጉ የደን ጠባቂ ሬንጀሮችና "Plogging Ethiopia" የተባለውን ተቋም በመመስረት ላለፉት 6 ዓመታት
+2
ከ70 በላይ ለሚሆኑ ደን ጠባቂ ሬንጀሮች የዕዉቅና ስጦታ ተበረከተ ቴምር ፕሮፐርቲስ 75 ለሚጠጉ የደን ጠባቂ ሬንጀሮችና "Plogging Ethiopia" የተባለውን ተቋም በመመስረት ላለፉት 6 ዓመታት በበጎ ፈቃደኝነት የወዳደቁ ፕላስቲኮችንና ቆሻሻዎችን በመሰብሰብ ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ለፕሮፌሰር ፍሬው ከፍያለው ልዩ ዕውቅናና ስጦታ ሰጥቷል። ቴምር ፕሮፐርቲስ ለአካባቢ ጥበቃ የማይተካ አስተዋፅኦ ለሚያበረክቱ የጉለሌ እፅዋት ማዕከል ሬንጀሮች ዕውቅናና ስጦታ ሰጥቷል። የጉለሌ እዕዋት ማዕከል እዕዋትን በመሰብሰብ፤ በማሰራጨትና ወደ ተፈጥሯዊ መኖሪያቸው እንዲመለሱ በሚደረጉ የምርምርና የጥበቃ ሥራዎች ወሳኝ ሚና እንደሚሰጥ ተነግሯል። በማዕከሉ ሥር የሚገኙ ሬንጀሮችም የደን ሀብትን፣ ብዝሃ ሕይወትን የሥነ-ምህዳር ሚዛንን ለመጠበቅ በየዕለቱ ከፍተኛ ኃላፊነት እንደሚወጡ ተገልጿል፡፡ ዕውቅናዉ ለአቶ ፍሬው የተሰጠ ግለሰባዊ ሽልማት ብቻ ሳይሆን፤ ለተፈጥሮና ለአካባቢ ጥቢቃ በተግባር ለሚተጉ ሁሉ የሚሰጥ አድናቆት፤ ማበረታቻና የአካባቢ ጥቢቃ ተሳትፎን ለማጠናከር የታለመ መልዕከት ነው ተብሏል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

አሜሪካ በአውሮፓ ያላትን ወታደራዊ ኃይል ልትቀንስ እንደምትችል ተገለፀ ፔንታጎን በአውሮፓ የተሰማሩትን ወደ 80 ሺህ የሚጠጉ የአሜሪካ ወታደሮች ቁጥርና አቀማመጥ እየገመገመ ሲሆን፣ ለመከላከያ ሚኒስት
አሜሪካ በአውሮፓ ያላትን ወታደራዊ ኃይል ልትቀንስ እንደምትችል ተገለፀ ፔንታጎን በአውሮፓ የተሰማሩትን ወደ 80 ሺህ የሚጠጉ የአሜሪካ ወታደሮች ቁጥርና አቀማመጥ እየገመገመ ሲሆን፣ ለመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴት ቢያንስ አራት የተለያዩ የጦር ኃይል አማራጮችን ለማቅረብ እየሠራ ይገኛል፡፡ እነዚህ አማራጮች የወታደሮች ቁጥር፣ የሚቀመጡበት ቦታ፣ የመዛወሪያ ፍጥነትና የሚያስከፍለውን ወጪ ያካትታሉ። አማራጮቹም እስከ ኖቬምበር 6 ድረስ ለሄግሴት እንዲቀርቡ ታቅዷል። የኔቶ አጋሮች ግን ግምገማው በአውሮፓ ያለውን የአሜሪካ ወታደራዊ ተሳትፎ በእጅጉ ሊቀንስ ይችላል በሚል ስጋት ላይ ይገኛሉ፡፡ የትራምፕ አስተዳደርም በበኩሉ አውሮፓውያን የኔቶ አባላት ለራሳቸው ደህንነት የበለጠ ኃላፊነት እንዲወስዱ እየጠየቀ ነው። በተለይም በኢራን ጦርነት ወቅት አንዳንድ የኔቶ አገራት ለአሜሪካ የጦር ማረፊያና የአየር ክልል መጠቀሚያ ፈቃድ በበቂ ፍጥነት አልሰጡም በሚል ትራምፕ ቅሬታ አቅርበዋል። ፔንታጎን የጀመረው ግምገማ በዲሴምበር እንዲጠናቀቅ ቢጠበቅም፣ ዋናው ጥያቄ አሜሪካ በአውሮፓ ያላትን ወታደራዊ ኃይል በምን ያህል ትቀንሳለች፣ እና የኔቶ አጋሮቿስ የሚፈጠረውን ክፍተት እንዴት ይሞላሉ? የሚለው ሆኗል። በቤዛዊት አራጌ #ዳጉ_ጆርናል

ሜታ በማህበራዊ ሚዲያ በወጣቶች ላይ ከደረሰዉ ጉዳት ጋር ተያይዞ ከአሜሪካ ክፍለ ሀገራት ጋር የ17 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሰ ሜታ ፕላትፎርምስ ፌስቡክን እና ኢንስታግራምን ሆን ብሎ ወጣቶች ለምርቶቹ ሱስ እንዲያዙ በሚያደርግ መልኩ በመቅረፅ እና ህዝቡን በማታለል በ47 የአሜሪካ ክፍለ ሀገራት የቀረበበትን ክስ ለመጨረስ የ17 ቢሊዮን ዶላር ክፍያ ለመፈፀም መስማማቱን የክፍለ ሀገራቱ አቃቢያነ ህግ አስታውቀዋል። ኩባንያው ከስምምነቱ አካል አድርጎ የህፃናትን ደህንነት የሚጠብቁ እርምጃዎችን በስራ ላይ ለማዋል ተስማምቷል። ሜታ በወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያ ሱስ ዙሪያ የተመሰረተበትን ታሪካዊ ክስ ለማቆም እና በ47 ክፍለ ሀገራት የቀረቡበትን አቤቱታዎች ለመጨረስ 17 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል በፌስቡክ እና ኢንስታግራም ገጾቹ ላይ የህፃናት ደህንነት ማረጋገጫዎችን ለማካተት መስማማቱ ተገልጿል። ካሊፎርኒያ፣ ኮሎራዶ፣ ኬንታኪ እና ኒው ጀርሲ እ.ኤ.አ. በ2023 በቴክኖሎጂ ኩባንያው ላይ ክስ ካቀረቡት 29 ክፍለ ሀገራት መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን፣ አዲሱ ስምምነት የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ማርክ ዙከርበርግ በካሊፎርኒያ ፌደራል ፍርድ ቤት በዳኞች ፊት ቀርበው ምስክርነት ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቅ የነበረውን የፍርድ ሂደት አሳጥሮታል። የቨርጂንያ ጠቅላይ አቃቢ ህግ ጄይ ጆንስ ባወጡት መግለጫ፣ ስምምነቱ በቨርጂንያ ብቻ 353 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ሲሆን፣ በክፍለ ሀገሪቱ የደንበኞች መብት ጥበቃ ታሪክ ውስጥ ከሁሉም የበለጠው እንደሆነ ገልፀዋል። ለዓመታት ሜታ በወጣቶች የአእምሮ ጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱ ሱስ አጋላጭ እና ጎጂ የሆኑ የንድፍ ባህሪያትን አስመልክቶ ህዝቡን ሆን ብሎ ሲያታልል ቆይቷል ብለዋል ጆንስ። ይህ ስምምነት እነዚህን አደገኛ አሰራሮች የሚያስቆም እና ህፃናትን ከኦንላይን ጉዳት የሚጠብቅ ትርጉም ያለው እፎይታን የሚያስገኝ ነው ሲሉ አክለዋል። ሜታ ለተጠየቀው አስተያየት ወዲያውኑ ምላሽ አልሰጠም። ይህ የ17 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት፣ ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2025 ካስመዘገበው የ201 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ድርሻ ያለው ነው። ክሱ ሜታ፣ ህፃናትን ለገጾቹ ሱስ የሚያስይዙ ባህሪያትን ሆን ብሎ በመቅረፅ እና እነዚህን ከህዝብ በመሸሸግ ለወጣቶች የአእምሮ ጤና ቀውስ አስተዋጽኦ አድርጓል በማለት ይከሳል። በተጨማሪም ሜታ ያለወላጆች ፈቃድ ከ13 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትን መረጃ ዘወትር በመሰብሰብ የፌደራል ህጎችን ጥሷል የሚል ክስም ቀርቦበታል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

በኔፓል በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከ8መቶ በላይ ሰዎች የደረሱበት እንዳልታወቀ ተገለጸ፡፡ በኔፓል እና ቲቤት ድንበር አካባቢ በተከሰተው በዚህ አደጋ፣ ከፍተኛ የሆነ የጭቃ እና የውሃ ማዕበል መኖሪያ ቤቶ
+2
በኔፓል በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከ8መቶ በላይ ሰዎች  የደረሱበት እንዳልታወቀ ተገለጸ፡፡ በኔፓል እና ቲቤት ድንበር አካባቢ በተከሰተው በዚህ አደጋ፣ ከፍተኛ የሆነ የጭቃ እና የውሃ ማዕበል መኖሪያ ቤቶችን ደምስሷል፤ መንገዶችን እና ድልድዮችንም ጠራርጎ ወስዷል። በአሁኑ ወቅት የህይወት አድን ቡድኖች የተረፉ ሰዎችን ለማፈላለግ ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ እስከ አሁን ባለው መረጃ በኔፓል ከ8መቶ  በላይ ሰዎች የገቡበት ያልታወቀ ሲሆን፤ የ1መቶ77 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል። ሆኖም በአካባቢው ላይ እየዘነበ ባለው ሀይለኛ ዝናብ እና የአካባቢው አስቸጋሪ መልክአ-ምድር ምክንያት  የፍለጋ ስራው ፈታኝ  ሆኗል። በቲቤት በኩል ደግሞ የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን፤ የ5መቶ58 ሰዎች ደብዛ ጠፍቷል። እስካሁን ድረስ በሁለቱም ድንበሮች በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎች ያሉበት አልታወቀም። የኔፓል ባለስልጣናት እንዳሳወቁት ከሆነ ከጠፉት መካከል 1መቶ78 የህንድ፣ 1መቶ27 የኔፓል፣ 65 የአሜሪካ፣ 35 የአውስትራሊያ እና 33 የብሪታንያ ቱሪስቶች ይገኙበታል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር ቅጣት ሊጥል ነዉ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር ቅጣት ሊጥል ነዉ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር ቅጣት ሊጥል ነዉ የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ከጣቢያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት እየተስተዋለ ያለውን ያልተገባ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪና የመስመር ማሳጠር ችግሮችን ለመቅረፍ የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን አስታውቋል። ቢሮው የህዝብ ትራንስፖርት ታሪፍን በማጥናትና በማስወሰን ረገድ ትልቅ ሃላፊነት እንዳለበት የገለጹት የቢሮው የስራ ሃላፊ፣ የታሪፍ ተግባራዊነቱንም በቅርበት እየተቆጣጠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። @Seledadotio @Seledadotio

ሕንድ የጦር መሳሪያ ምስጢሯን ለግል ኩባንያዎች አሳልፋ ሰጠች ‼ ሕንድ የሀገር ውስጥ የጦር መከላከያ ምርቷንና የቴክኖሎጂ አቅሟን ሙሉ በሙሉ በራስ ለማስቻል ያለመ ታሪካዊ ፖሊሲ ይፋ አድርጋለች። የመ
+3
ሕንድ የጦር መሳሪያ ምስጢሯን ለግል ኩባንያዎች አሳልፋ ሰጠች ‼   ሕንድ የሀገር ውስጥ የጦር መከላከያ ምርቷንና የቴክኖሎጂ አቅሟን ሙሉ በሙሉ በራስ ለማስቻል ያለመ ታሪካዊ ፖሊሲ ይፋ አድርጋለች።  የመከላከያ ሚኒስትሩ ራጅናት ሲንግ የሀገሪቱ የጦር ምርምር ተቋም (DRDO) ያበለጸጋቸውን የላቁ ባህላዊ የሚሳይል ቴክኖሎጂዎች፣ የሴንሰር አሰራሮችና ማምረቻ ምስጢራት ለሀገር ውስጥ የግል ኩባንያዎች እንዲተላለፉ በይፋ ፈቅደዋል።  ይህ አዲስ የቴክኖሎጂ ሽግግር ቀደም ሲል በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉ ተቋማት ብቻ ተወሰኖ የነበረውን የሚሳይል ማምረት ሂደት ሙሉ በሙሉ በመቀየር የግል ዘርፉን በዋናነት የሚያሳትፍበትን መንገድ ከፍቷል።   በዚህ መርሃ ግብር መሰረት እንደ አካሽ (Akash)፣ አስትራ (Astra)፣ ሩድራም (Rudram) እና ናግ (Nag) ያሉ የአየር ላይ፣ የመሬት ላይ እና የፀረ-ታንክ የሚሳይል ስርአቶች በግል ኩባንያዎች በከፍተኛ መጠን እንዲመረቱ ይደረጋል።  ሆኖም የሀገሪቱ የኑክሌር ስትራቴጂካዊ ሚሳይሎች በዚህ ስምምነት ውስጥ አልተካተቱም።   ውሳኔው ሕንድ ከውጭ ሀገራት በቢሊዮን ዶላሮች የሚገዙ የጦር መሳሪያዎችን ፍላጎት በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት፣ የጦር ኃይሏን ፍላጎት በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማሟላትና የትናንሽና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን የቴክኖሎጂ አቅም ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ውድ ስልክ በህዝብ በጀት ገዝተዋል የተባሉ 3 ከፍተኛ አመራሮች ከኃላፊነት ታገዱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ በእናቶችና ሕፃናት ጤና ፕሮግራም በጀት ውድ ስልክ ተገዝቷል በሚል በ
ውድ ስልክ በህዝብ በጀት ገዝተዋል የተባሉ 3 ከፍተኛ አመራሮች ከኃላፊነት ታገዱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ በእናቶችና ሕፃናት ጤና ፕሮግራም በጀት ውድ ስልክ ተገዝቷል በሚል በማህበራዊ ሚዲያና በመገናኛ ብዙሃን በተሰራጨው መረጃ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥቷል።  መንግስት የህዝብን ሀብት በአግባቡ እና ለታለመለት ዓላማ ብቻ መዋሉን ለማረጋገጥ ባደረገው ማጣራት፣ ጉዳዩን በጥልቀት የሚያጣሩ የፍትህ፣ የኦዲት እና የፀረ-ሙስና አካላትን አደራጅቶ ወደ ምርመራ ስራ መግባቱን አስታውቋል። በጉዳዩ የተጠረጠሩ ሦስት አመራሮችም ከዛሬ ጀምሮ ከኃላፊነታቸው እንዲታገዱ ተደርጓል።  የክልሉ መንግስት ማጣራቱ እንደተጠናቀቀ የህዝብን ሀብት ባባከኑ አካላት ላይ የማያዳግም ህጋዊ፣ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጾ፣ ህዝቡ የብልሹ አሰራር ጥቆማዎችን በመስጠትና ከጎኑ በመቆም ያደረገውን @Freshmerejaet @Freshmerejaet

ይህ ታሪክ የደግነት፣ የፍቅርናየሰብአዊነት ታላቅ ምሳሌ ነው አንድ ሚና የተባለ ግብፃዊ ክርስቲያን ወጣት በቁርአን ጥያቄና መልስ ውድድር አሸንፎ ያገኘውን የዑምራ (የሐጅ) ጉዞ ሽልማት ለሙስሊም ጎረቤ
ይህ ታሪክ የደግነት፣ የፍቅርናየሰብአዊነት ታላቅ ምሳሌ ነው አንድ ሚና የተባለ ግብፃዊ ክርስቲያን ወጣት በቁርአን ጥያቄና መልስ ውድድር አሸንፎ ያገኘውን የዑምራ (የሐጅ) ጉዞ ሽልማት ለሙስሊም ጎረቤቱ ለእማ አሊ በመስጠት የብዙዎችን ልብ ነክቷል። እማ አሊ ወደ ቅድስት ሀገር መካ ሄደው ለመጎብኘት ለብዙ ዓመታት ይመኙ ነበር፤ ጉዞውን ለማሸነፍም ተደጋጋሚ ሙከራዎችን አድርገዋል። ይህ ህልማቸው ምን ያህል ትልቅ እንደሆነ የተረዳው ሚና፣ ለእርሳቸው ሲል በውድድሩ ላይ ተሳትፎ  አሸነፈ። ሽልማቱን ባገኘ ጊዜም የእማ አሊን የረጅም ጊዜ ህልም እውን ለማድረግ ሽልማቱን አበረከተላቸው። ከ20 ዓመታት በላይ በጎረቤትነት አብረው የኖሩት ሚና፣ እማ አሊን እንደራሱ ታላቅ እህት አድርጎ እንደሚያያቸው ይናገራል። ይህ አነቃቂ ድርጊት ደግነትና ሰብአዊነት ከሃይማኖት ልዩነት በላይ ሰዎችን እርስ በእርስ ማቀራረብ እንደሚችሉ የሚያሳይ ውብ ማስታወሻ ነው። @Seledadotio @Seledadotio

ዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ የሰላም ጥሪ አቀረበ‼ በፌዴራል መንግሥት እና በህወሓት አመራሮች መካከል እየባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ፣ በአፍሪካ ኅብረት መሪነት እየተደረገ ያለውን የማሸማገል ጥረት የአ
ዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ የሰላም ጥሪ አቀረበ‼ በፌዴራል መንግሥት እና በህወሓት አመራሮች መካከል እየባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ፣ በአፍሪካ ኅብረት መሪነት እየተደረገ ያለውን የማሸማገል ጥረት የአውሮፓ ኅብረት አባል የሆኑ 22 አገራት፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ኖርዌይ፣ ካናዳ እና አሜሪካ በአንድ ድምፅ ደገፉ።  በድሮን ጥቃቶችና በወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ሳቢያ በድርቅ ለተጎዳው የትግራይ ሕዝብ ዳግም ጦርነት መቀስቀስ "አስከፊ" እንደሚሆን አገራቱ አፅንኦት ሰጥተው አስጠንቅቀዋል። ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አደራዳሪዎች አንዱ የሆኑት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ አዲስ አበባና መቀለ በመገኘት ዳግም ምክክሮችን ማስጀመራቸው አብዛኛዎቹ አካላት የተቀበሉት ሲሆን፤ በሌላ በኩል ህወሓት የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲነሳ፣ ወታደራዊ ከበባ እንዲቆም እና የትግራይ ሉዓላዊ ግዛት ወደነበረበት እንዲመለስ ቅድመ ሁኔታዎችን ማስቀመጡ ተነግሯል።  በሁለቱ ወገኖች መካከል የሚስተዋለው አለመግባባት ሕዝቡን በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ከቷል። @Addis_News @Addis_News

በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ተማሪዎች በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ተማሪ ሰምሃል መሃሪ
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ተማሪዎች በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ተማሪ ሰምሃል መሃሪ የትምህርት ቤቱን ከፍተኛ ውጤት 550.76 ማስመዝገቧ ተገልጿል፡፡ atc_news @Addis_News @Addis_News

#ታርጋቸውን አሳውቁ‼️ በ9417 ላይ እየደወላችሁ የታርጋ ቁጥራቸውን ጥቀሱ! 👉ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ እስከ 200 አሽከርካሪዎች በየቀኑ እርምጃ እየተወሰደባቸው ነው የአዲስ አበባ ትራንስፖርት
#ታርጋቸውን አሳውቁ‼️ በ9417 ላይ እየደወላችሁ የታርጋ ቁጥራቸውን ጥቀሱ! 👉ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ እስከ 200 አሽከርካሪዎች በየቀኑ እርምጃ እየተወሰደባቸው ነው የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አላግባብ ታሪፍ በሚጨምሩና መስመር በሚያሳጥሩ አሽከርካሪዎች ላይ የ5 ሺህ ብር ቅጣት ሊጥል ነው። ከ15 ሺህ በላይ የህዝብ ትራንስፖርቶች ቢኖሩም፣ ጥቂት የማይባሉ ግን ህዝቡን እያማረሩ ይገኛሉ። መንግሥት ጥብቅ እርምጃ ለመውሰድ ተዘጋጅቷል። 9417 ደውሉ፣ የታርጋ ቁጥራቸውን አሳውቁ!" @Addis_Reporter @Addis_Reporter

የአፍሪካ ህብረትና ኢጋድ ለቀጣናው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሞሐመድ አሊ ዩሱፍ ከኢጋድ ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጋር ተወ
የአፍሪካ ህብረትና ኢጋድ ለቀጣናው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሞሐመድ አሊ ዩሱፍ ከኢጋድ ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ሁለቱ ወገኖች የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናን ሰላም እና ደህነት ማረጋገጥ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት ÷ በሱዳን ሰላም ለማስፈን ጥረት ከሚያደርገው የሱዳን የሰላም ተልዕኮ ጋር የነበራቸውን ቆይታ አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል፡፡ በውይይቱ በሱዳን ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ኢጋድ እና የአፍሪካ ህብረት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የህብረቱ መረጃ ያመላክታል፡፡ @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ ደረሰ የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ
የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ ደረሰ የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ ተሾመ ገልፀዋል። 201 ሜትር ርዝመት ያለው የግድብ ግንባታው 6 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የአፈር ቁፋሮ በማካሄድ አጠቃላይ ግድቡ ከሚፈልገው 7 ነጥብ 72 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት ውስጥ 81 ነጥብ 2 በመቶው ማለትም 6 ነጥብ 27 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት (RCC) ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል። የኃይል ማመንጫ ቤቱ የቁፋሮ ሥራ እንዲሁም የሲቪል ሥራው የመጀመሪያ ደረጃ የኮንክሪት ሙሌት ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንም ተናግረዋል። የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራውን በታቀደው ጊዜ ለማጠናቀቅ ዕቃዎች በበርካታ ፋብሪካዎች እንዲመረቱ መደረጉንም ገልጸዋል። የፋይናንስ አቅርቦት በተለይም የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና ተያያዥ ችግሮች በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ፈጥሮ መቆየቱን ያስታወሱት ኢንጂነር መብራቱ፣ አሁን ላይ ተቋሙ ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልገውን ፋይናንስ በራሱ በመሸፈኑ ግንባታው እየተፋጠነ ይገኛል ብለዋል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ኢዜማ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የተዋቀረውን ኮሚቴን ውድቅ ማድረጉን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ ረቡዕ በሰጠው መግለጫ፤ በአዲስ አበባ ጉዳይ
ኢዜማ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የተዋቀረውን ኮሚቴን ውድቅ ማድረጉን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ ረቡዕ በሰጠው መግለጫ፤ በአዲስ አበባ ጉዳይ ምክረ ሃሳብ እንዲያዘጋጅ የተሰየመው አስማሚ ኮሚቴ አሰራር የኮሚሽኑን ሕጋዊ ማዕቀፍ የጠበቀ አይደለም ብሏል። የፓርቲው መሪ አቶ እዮብ መስፍን እንደገለጹት፤ የኮሚቴው አወቃቀርና አካሄድ የኮሚሽኑን ሕግ ያልተከተለ በመሆኑ ፓርቲው አጠቃላይ ሂደቱን ውድቅ በማድረግ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ቅሬታ አቅርቧል። ኢዜማአክሎም በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ካለው ተቃውሞ በተጨማሪ፤ በምክክሩ ወቅት የቀረቡ 400 ያህል ምክረ ሃሳቦችና የውይይት ቃለ ጉባኤዎች ለሕዝብ ግልጽ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል።" @Seledadotio @Seledadotio

የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ! በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ብቻ ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢ
የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን  የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ! በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ብቻ ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ።አገልግሎቱ ባወጣው የወርሃዊ የዋጋ ንረት መረጃ፣ በሐምሌ ወር የተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ከባለፈው አመት ጋር ከነበረው 13.7 በመቶ  ጋር ሲነጻጸር ጭማሪ አድርጓል።  ሰኔ ወር ላይ የነበረው 14.8 በመቶ ነበር። በዚህ ወር የምግብ ዋጋ ንረት 15.7 በመቶ ሲሆን፣ የምግብ ያልሆኑ ዕቃዎችና አገልግሎቶች የዋጋ ንረት ደግሞ 14.8 በመቶ ደርሷል ሲል አገልግሎቱ ገልጿል።የዋጋ ንረቱ በ2018 ዓ.ም. መጀመሪያ ወራት ላይ በመቀነስ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ ዳግም እየጨመረ የመጣ ሲሆን በመጋቢት ወር የነበረው የዋጋ ንረት ከወራት ዝቅተኛ ደረጃዎች አንዱ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ ወራት ግን ጭማሪ ታይቷል። በተለይም የምግብ ዋጋ ጭማሪ ለአጠቃላይ የዋጋ ንረቱ መጨመር ዋነኛ አስተዋጽዖ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል ሲሆን የምግብ ዋጋ ንረት 15.7 በመቶ መድረሱ የዋጋ ጭማሪው በቤተሰቦች የዕለት ተዕለት ወጪ ላይ ጫና መፍጠሩን ያሳያል። ባለፈው አመት ከነበረው የዋጋ ግሽበት ከ13.7 በመቶ ጀምሮ በዓመቱ መካከል እስከ 9 በመቶ አካባቢ ዝቅ ብሎ ነበር።ይሁን እንጂ ነገር ዳግም በመጨመር በሰኔ 14.8 በመቶ እና በሐምሌ 15.3 በመቶ ደርሷል። በመሆኑም የቅርብ ወራት የዋጋ ንረት አዝማሚያ በኢትዮጵያ የእቃና የአገልግሎት ዋጋ ጭማሪው እንደገና እየተፋጠነ መምጣቱን ያሳያል ሲል የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ገልጿል። @YeneTube @FikerAssefa

በኢራን አዲስ የ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ተገኘ በደቡባዊ የፋርስ (Fars) ግዛት ውስጥ ከ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚገመተው አዲስ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መገኘቱን የ
+2
በኢራን አዲስ የ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ተገኘ በደቡባዊ የፋርስ (Fars) ግዛት ውስጥ ከ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚገመተው አዲስ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መገኘቱን የኢራን የፔትሮሊየም ሚኒስትር ሞህሴን ፓክኔጃድ ይፋ አደረጉ። ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከተገኘው አጠቃላይ ክምችት ውስጥ ከ160 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚሆነው የተፈጥሮ ጋዝ በቀላሉ ወጥቶ ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል ነው። አዲሱ የተፈጥሮ ጋዝ በጥራት ደረጃው «ጣፋጭ» (sweet gas) የሚባል ሲሆን፣ መርዛማ የሆነውን የሃይድሮጅን ሳልፋይድ (hydrogen sulphide) ጋዝ ይዘት አነስተኛ በመሆኑ ማውጣትና ማልማት የሚጠይቀውን ወጪ በእጅጉ ይቀንሰዋል። ብሉምበርግ (Bloomberg) የዘርፉን ባለሙያዎች ጠቅሶ እንደዘገበው፣ አዲሱ ክምችት ተለምቶ ሙሉ በሙሉ ወደ ምርት ለመግባት እና ለገበያ ለመቅረብ በርካታ ዓመታትን ሊወስድ ይችላል። ይህ አዲስ ጥራት ያለው የጋዝ ግኝት ይፋ የተደረገው፣ በቅርቡ ከተቀሰቀሰው የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በኋላ በአሜሪካ እና በእስራኤል በጋራ በተሰነዘሩ ጥቃቶች ምክንያት የኢራን የጋዝ ማውጫ ተቋማት፣ የነዳጅ ማከማቻዎች እና የትራንስፖርት መሠረተ-ልማቶች ከፍተኛ ውድመት በደረሰባቸው ወቅት ነው። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

በቀን በአማካይ ከ 20 እስከ 35 እናቶች በጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ይወልዳሉ። 2018 ላይ አንድም እናት በወሊድ ምክንያት ያልሞተበት መሆኑን ሆስፒታሉ አስታውቋል። በአዲስ አበባ ከተማ አ
በቀን በአማካይ ከ 20 እስከ 35  እናቶች በጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ይወልዳሉ። 2018 ላይ አንድም እናት በወሊድ ምክንያት ያልሞተበት መሆኑን ሆስፒታሉ አስታውቋል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደሩ ጤና ቢሮ ስር ከሚገኙ ሆስፒታሎች አዱ የሆነው ​ጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ ያለ ትልቅ ሆስፒታል ሲሆን  በቀን በአማካይ ከ20 እስከ35 እናቶች እንደሚወልዱ  የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት  ዶክተር  እሸቱ ታደለ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል። ሆስፒታሉ በወር ውስጥ ከ650 እስከ 700 እናቶች የወሊድ አገልግሎት የሚያገኙበት ትልቅ ተቋም መሆኑ ሀላፊው የተናገሩ ሲሆን ያለምንም ክፍያ በነፃ የወሊድ አገልግሎት እየሰጠ እንደሆነም ተገልጿል። በሆስፒታሉ ህፃናት እና እናቶች ተገቢውን የህክምና አገልግሎት እንዲገኙ የፅንሰ-የነፍስ ጡር እናቶች እና የህፃናት ስፔሻሊስቶች በትስስር እየሰሩ እንደሚገኙ ያታወቀ ሲሆን በ2018 ዓመትም አንዲትም እና ከወሊድ ጋር በተያያዛ ህይወቷ ያላለፈበት መሆኑ ተነግራል፡፡     በትግስት ላቀው #ዳጉ_ጆርናል