uk
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

Відкрити в Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Fresh መረጃ | FreshNews

Канал Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 55 750 підписників, посідаючи 3 019 місце в категорії Освіта та 580 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 55 750 підписників.

За останніми даними від 28 серпня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -674, а за останні 24 години на -21, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 3.63%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 3.01% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 2 026 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 682 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 9.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 29 серпня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Освіта.

55 750
Підписники
-2124 години
+1837 днів
-67430 день
Архів дописів
የ 46 አመቱ የአንበሳ ባንክ ጥበቃ የ 12 ክፍል ፈተናን 320.25 ዉጤት አመጡ 👉🏼ባንኩ በዉጤቱ ተደስቶ የተለያዩ ስጦታዎችንም አበርክቶላቸዋል የአንበሳ ባንክ የጥበቃ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ሰይፈ
የ 46 አመቱ የአንበሳ ባንክ ጥበቃ የ 12 ክፍል ፈተናን 320.25 ዉጤት አመጡ 👉🏼ባንኩ በዉጤቱ ተደስቶ የተለያዩ ስጦታዎችንም አበርክቶላቸዋል የአንበሳ ባንክ የጥበቃ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ሰይፈ ተስፋዬ ካሕሳይ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማለፊያ ነጥብ ማግኘታቸዉን ዳጉ ጆርናል ከባንኩ ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል። በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን ሰለዋ ወረዳ ደላ ከተማ በሚገኘው የአንበሳ ባንክ ቅርንጫፍ ላለፉት ሰባት አመታት በጥበቃ ስራ እየሰሩ የሚገኙ አቶ ሰይፈ በ46 አመታቸው የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቅያ ፈተና ተፈትነው 320.25 ነጥብ በማምጣት ወደ ዩንቨርስቲ ማለፋቸውን ባንኩ ማሳወቁን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል። በዚህም የባንኩ የዳይሬክቶሮች ቦርድ አባላት ፣ ማኔጅመንት እና ሰራተኞች በሙሉ የተሰማቸዉን ደስታ ገልጸዋል። በዚሁ መሰረት ለአቶ ሰይፈ ተስፋዬ ባንኩ ማበረታቻዎች ለመስጠት ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን አቶ ሰይፈ ተስፋይ ካሕሳይ ወደ ዩንቨርስቲ ለመግባት እና ለመማር የሚያስፈልጋቸው ማንኛውም ወጪ የዩንቨርስቲ ቆይታቸው እስከሚያጠናቅቁ ድረስ ሙሉ ወጪያቸውን ባንኩ እሸፍንላቸዋለሁ ብሏል። በተጨማሪም አቶ ሰይፈ ወደ ዩንቨርስቲ ከገቡበት ወር ጀምሮ አሁን የሚከፈላቸ ወርሃዊ ደመወዝ ሙሉ በሙሉ በየወሩ ለቤተሰቦቻቸው እንዲከፈል እንደሚደረግም ዳጉ ጆርናል ሰምቷል። በሌላ በኩል አቶ ሰይፈ ተስፋይ ካሕሳይ የዩንቨርስቲ ትምህርታቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባንኩ በተገቢው የስራ ዘርፍ በመመደብ በቋሚነት ቀጥሮ የሚያሰራቸው ይሆናል ተብሏል። @Seledadotio @Seledadotio

የኢራን ተመራማሪዎች በብርሃን አማካኝነት የካንሰር ሕዋሳትን የሚያጠፋና 80% ውጤታማ የሆነ ስማርት "ጄል" ሰሩ ይህ "ስማርት ሃይድሮጄል" (ፈሳሽ ቅባት) የጡት ካንሰር ዕጢዎችን በጥንቃቄ ኢላማ በማ
የኢራን ተመራማሪዎች በብርሃን አማካኝነት የካንሰር ሕዋሳትን የሚያጠፋና 80% ውጤታማ የሆነ ስማርት "ጄል" ሰሩ ይህ "ስማርት ሃይድሮጄል" (ፈሳሽ ቅባት) የጡት ካንሰር ዕጢዎችን በጥንቃቄ ኢላማ በማድረግ ለማከም የኬሞቴራፒ እና በብርሃን ላይ የተመሠረተ ሕክምናን ያጣመረ ነው። ጄሉ ከተፈጥሯዊና ከሰውነት ጋር ተስማሚ ከሆነ "ካይቶሳን" ከተባለ ንጥረ ነገር የተሠራ ነው፡፡ ስፑትኒክ እንደዘገበው መድኃኒቱን በተቆጣጠረ ሁኔታ የሚለቅ ሲሆን፣ የሌዘር ብርሃን ሲያርፍበት ይነቃቃል፡፡ በተለየ ሁኔታ የካንሰር ሕዋሳትን የሚጎዱ የኦክሲጅን ውህዶችን ያመነጫል፡፡ የተደረጉት ሙከራዎች እንደሚያሳዩት፣ ጄሉ ጤናማ ሕዋሳትን ሳይነካ ከ80% በላይ የሚሆኑትን የጡት ካንሰር ሕዋሳት ማጥፋት ችሏል፡፡ ይህ አቀራረብ ከተለመዱት የጡት ካንሰር ሕክምናዎች በተሻለ፣ አነስተኛ ጉዳት የሚያስከትል እና ቀጥተኛ ዒላማውን ብቻ የሚያጠቃ አማራጭ ሊሆን ይችላል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

"እግዚአብሔር ይመስገን አለሁ" ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ራቅ ማለታቸውን ተከትሎ የተለያዩ የሐሰት ዜናዎች ሲሰራጭ ሰንብቷል። በዛሬው እ
"እግዚአብሔር ይመስገን አለሁ" ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ራቅ ማለታቸውን ተከትሎ የተለያዩ የሐሰት ዜናዎች ሲሰራጭ ሰንብቷል። በዛሬው እለት ብልጽግና ፓርቲ በይፋዊ የቲክቶክ ገጹ ለሰሞንኛው አጀንዳ መልስ የሚመስል ቪዲዮ ለቋል። በቪዲው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ! "አለሁ እግዚአብሔር ይመስገን" በማለት ሲናገሩ ተሰምተዋል። via_አንድ አፍታ @Addis_News @Addis_News

የኢራን ጦርነት በአውሮፓ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት እያሟጠጠው ነው - ዘገባ ዎል ስትሪት ጆርናል የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ፣ የኢራን ግጭት በአውሮፓ የሚገኘ
የኢራን ጦርነት በአውሮፓ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት እያሟጠጠው ነው - ዘገባ ዎል ስትሪት ጆርናል የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ፣ የኢራን ግጭት በአውሮፓ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት እጅግ እየጎዳው ይገኛል፤ በተለይም የ ፓክ-3 ፓትሪዮት ሚሳኤል መከላከያዎች እና የረዥም ርቀት ሚሳኤሎች ክምችት "ከአስጊ ደረጃ በላይ" ዝቅ ማለቱ ተገልጿል። በግጭቱ ወቅት 1,700 የፓትሪዮት ሚሳኤል መከላከያዎች አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ 200 የታድ መከላከያዎች እና 150 የባህር ኃይል ስታንዳርድ ሚሳኤሎች ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ዘገባው አክሎ እንደገለጸው በርካታ የታድ ስርዓቶች እና ድሮን ተከላካይ መሣሪያዎች ከአውሮፓ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ተዛውረዋል። የመሣሪያዎቹ እጥረት አሁን በጦርነት እቅድ ዝግጅት ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ የአሜሪካ አውሮፓ እዝ የተግባር እቅዶቹን አስተካክሏል። ሆኖም ነጩ ቤተ መንግስት እና ፔንታጎን "እጥረት" መኖሩን የሚገልፀውን ገለጻ በመቃወም፣ ያለው ክምችት ለስትራቴጂካዊ አላማዎች በቂ እንደሆነ አስምረው ተናግረዋል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

#ትኩረት ያሸዋል ተባለ "አዲስ አበባ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ታወር ፊት ለፊት፣ ከቡናና ሻይ አጠገብ ባለው ዋና መንገድ ላይ የሚገኝ ይህ 'ፖል' የብዙዎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥሏል ነው የተባለው ። 😱
#ትኩረት ያሸዋል ተባለ "አዲስ አበባ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ታወር ፊት ለፊት፣ ከቡናና ሻይ አጠገብ ባለው ዋና መንገድ ላይ የሚገኝ ይህ 'ፖል' የብዙዎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥሏል ነው የተባለው ። 😱 በተለይ በምሽት እይታው ስለሚቀንስ፣ አሽከርካሪዎችም ሆኑ እግረኞች ለማይፈለግ አደጋ እየተጋለጡ ይገኛሉ። ይህ ፖል ከመንገዱ ተነስቶ ሌላ ምቹ ቦታ ላይ ካልተተከለ የከፋ አደጋ ሊያደርስ ይችላል። የሚመለከተው አካል አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ እና የአካባቢው ነዋሪዎችም ሆኑ አሽከርካሪዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እናሳስባለን። ⚠️⚠️ ይህ መረጃ ለሚመለከተው አካል እስኪደርስ ሼር በማድረግ ተባበሩ!" @Seledadotio @Seledadotio

በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማራቹ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተጠንቀቁ ። በ3 የሻይ ሲኒ ደረሰኝ ምክንያት 300 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል። በአዲሱ የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ደረሰኝ አ
+2
በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማራቹ  ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተጠንቀቁ ። በ3 የሻይ ሲኒ  ደረሰኝ  ምክንያት 300 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል። በአዲሱ የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ደረሰኝ አለመስጠት ንብረትዎን ሊያሳጣዎት ይችላል! አንድ ሰራተኛዎ ቸልተኛ ሆና 100 ብር ለሚያወጣ 'ሻይ' ደረሰኝ ባትቆርጥ... ቅጣቱ 100 ብር ሳይሆን 100 ሺህ ብር ነው ተብሏል። ይባስ ብሎ ደግሞ... ሰራተኛዋ ለ3 ደንበኞች ደረሰኝ ካልሰጠች፣ ለድርጅቱ ባለቤት የ300 ሺህ ብር መብረቅ የመሰለ ቅጣት ይወርድበታል። ይህ ቅጣት ደግሞ በአዋጁ አንቀጽ 125 ንኡስ ቁጥር 2 መሰረት በባለስልጣኑ ሊነሳ ወይም 'ይቅር' ሊባል አይችልም! መፍትሄው መክፈል ብቻ ነው! ነጋዴዎች ተጠንቀቁ፣ ሰራተኞቻችሁን አስተምሩ። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ዩኤፋ በፊፋ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ሊያነሳ ነው የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (ዩኤፋ)፣ የአለም እግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) የዓለም ዋንጫን ለግል ባለሀብቶች ለማስተላለፍ አቅዶት የነበረውን ውድቅ የተደረገ ፕሮጀክት እንደገና ላለማንሳት ዋስትና ማግኘቱን ተከተሎ፣ በፊፋ ውድድሮች ላይ ጥሎት የነበረውን የማዕቀብ ዛቻ በይፋ ለማንሳት መዘጋጀቱ ተገልጿል። በዩኤፋ እና በፊፋ መካከል በተፈጠረው የዓለም ዋንጫን በግል ፋይናንስ የማንቀሳቀስ ውዝግብ ጥላ አርፎበት የቆየ ቢሆንም፣ የአውሮፓ እግር ኳስ የበላይ አካል ግን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ጥሎት የነበረውን የማዕቀብ ዛቻ ያነሳል ተብሏል። የዓለም እግር ኳስ ኢኮኖሚን በክለቦች እና በብሔራዊ ቡድኖች የሚቆጣጠረው ዩኤፋ፣ በጂያኒ ኢንፋንቲኖ የሚመራው ፊፋ እንደ ዓለም ዋንጫ እና የክለቦች ዓለም ዋንጫ ያሉ ትልልቅ ውድድሮችን የሚያስተዳድር የግል የንግድ ተቋም ለማቋቋም ማቀዱ ባለፈው ሐምሌ ወር አጋማሽ ላይ ይፋ ሲሆን ከፍተኛ ቁጣውን ገልጻ ነበር። ይህ እቅድ የግል ኢንቨስተሮች በ ፊፋ ፎርዋርድ ኢንተርፕራይዝ (FFE) በተሰኘው አዲስ አሰራር ስር ድርሻ እንዲገዙ የሚፈቅድ ነበር። በፕሬዚዳንት አሌክሳንደር ሴፈሪን የሚመራው ዩኤፋ፣ እቅዱን ደብዛዛ እና ግልጽነት የጎደለው የጓሮ በር ድራማ ሲል በፅኑ ኮንኖታል። በወቅቱ የአውሮፓ እግር ኳስ የበላይ አካል ባወጣው ጠንካራ መግለጫ እነዚህ እቅዶች እስካሉ ድረስ ማንኛውም የዩኤፋ ብሔራዊ ቡድን በምንም ዓይነት የፊፋ ውድድር ላይ አይሳተፍም ብሎ የነበረ ሲሆን፣ ይህ እቅድ በፍጥነት እንዲሰረዝ ዋና ምክንያት እንደነበር ይነገራል። ነገር ግን የዩኤፋ ስራ አስፈፃሚዎች እና የአውሮፓ አባል ሀገራት ማህበራት በሞናኮ ስብሰባ ከማድረጋቸው አስቀድሞ፣ በፊፋ ውድድሮች ላይ የተጣለው የማዕቀብ ዛቻ በከፍተኛ ሁኔታ ሊነሳ እንደሚችል የኤኤፍፒ ምንጮች ዘግበዋል። ዩኤፋ እቅዱ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ ከመጠየቁም በላይ እግር ኳስን በዚህ መልኩ ለማበላሸት የሚደረጉ መሰል ሙከራዎች ዳግም እንደማይደገሙ ጠንካራ ዋስትና እንዲሰጠው መጠየቁ ይታወቃል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

photo content

ለስድስት ወራት ታግዶ የቆየውን የሮይተርስ ዘጋቢዎች ፈቃድ ታደሰ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከዓለም አቀፉ የዜና ተቋም ሮይተርስ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ከተወያየ በኋላ፣ ላለፉት ስድስት ወራት
ለስድስት ወራት ታግዶ የቆየውን የሮይተርስ ዘጋቢዎች ፈቃድ ታደሰ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከዓለም አቀፉ የዜና ተቋም ሮይተርስ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ከተወያየ በኋላ፣ ላለፉት ስድስት ወራት ታግዶ የቆየውን የሦስት ቋሚ የዜና ወኪሎቹን የዘገባ ፈቃድ ማደሱን አስታውቋል። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ ከሮይተርስ ኤክስክዩቲቭ ኤዲተር ኒክ ታተር እና የአፍሪካ ኤዲተር ሲልቪያ አሎይሲ ጋር ባካሄዱት ውይይት፤ ተቋሙ ባለፉት ሰባት ወራት ካሰራጫቸው ዘገባዎች መካከል የተወሰኑት የኢትዮጵያን ሕግ፣ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን እና ብሔራዊ ጥቅም የሚጻረሩ እንዲሁም የጋዜጠኝነት ሙያዊ ሥነ-ምግባርን ያልተከተሉ እንደነበሩ የሚዲያ ሞኒተሪንግ ውጤቶችን በማስደገፍ ማስረዳታቸውን የባለስልጣኑ መረጃ ያመላክታል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ሮይተርስ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያሰራጫቸው አንዳንዶቹ ዘገባዎች በሚዛናዊነት፣ በትክክለኝነት እና በተአማኒነት በኩል ክፍተት የነበረባቸውና ወደ አንድ ወገን ያደሉ እንደነበሩ ገልጸው፣ ለተስተዋሉት የሕግና የሙያ ሥነ-ምግባር ጥሰቶች አስፈላጊው እርማት ሊደረግላቸው እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። በውይይቱ ላይ የሮይተርስ ኃላፊዎች በበኩላቸው፣ የዜና ወኪሉ ገለልተኛ ሚዲያ መሆኑን ገልጸው ዘገባዎችን ሚዛናዊ፣ በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሠረቱ እና ከአድልዎ የጸዱ ለማድረግ ጥብቅ የኤዲቶሪያል መመሪያዎችን እንደሚከተሉ አስረድተዋል።  ባለሥልጣኑ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የሮይተርስ ቋሚ የዜና ወኪሎች ፈቃድ መታደሱን አውቀው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉላቸው ጥሪ አቅርቧል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የደም ግፊት መጠን መጨመር (Hypertension) ሲያጋጥም መደረግ እና መደረግ የሌለባቸው ወሳኝ የህክምና ጥንቃቄዎች ይፋ ሆኑ   ደም በደም መላሾች ውስጥ በከፍተኛ ኃይል ሲፈስ የሚከሰተው እና ብዙ ጊዜ ምንም አይነት ግልጽ ምልክት ሳይያሳይ የልብ እና የኩላሊት ህመሞችን የሚያስከትለው የደም ግፊት መጨመር፣ በብዙዎች ዘንድ "ጸጥተኛው ገዳይ" በመባል እንደሚታወቅ የህክምና ባለሙያዎች ይገልጻሉ።   የህመሙን ስጋት ለመቀነስ እና የደም ግፊትን በጤናማ ደረጃ ውስጥ ለማቆየት ህመምተኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ አበይት መመሪያዎች ተዘርዝረዋል።   የደም ግፊትን በዘላቂነት ለመቆጣጠር በፖታሺየም የበለፀጉ ምግቦችን፣ አትክልትና ፍራፍሬዎችን አብዝቶ መመገብ እና በየቀኑ ቢያንስ ለ30 ደቂቃ ያህል ቀልጣፋ የእግር ጉዞ ወይም ቀላል እንቅስቃሴዎችን ማድረግ የደም መላሾችን በማስፋት ግፊቱን ይቀንሳል።   ከዚህ በተጨማሪ በቂ እንቅልፍ ማግኘት፣ ጭንቀትን የሚቀንሱ የአእምሮ እረፍቶችን መውሰድ እና የደም ግፊት መጠንን በቤት ውስጥ በየጊዜው በመለካት መመዝገብ የህክምና ክትትሉን ውጤታማ ያደርገዋል ተብሏል።   በሌላ በኩል ጨው እና ከፍተኛ የሶዲየም መጠን ያላቸውን የታሸጉ ምግቦች አብዝቶ መመገብ የሰውነት ፈሳሽ እንዲከማች በማድረግ ግፊቱን በከፍተኛ ሁኔታ ስለሚጨምር ሊወገድ ይገባል ነው የተባለው።   ያለ ሐኪም ትዕዛዝ የሚወሰዱ የህመም ማስታገሻዎች (እንደ Ibuprofen እና Diclofenac ያሉ) የደም ግፊትን ይበልጥ ስለሚቀሰቅሱና የኩላሊት ስራን ስለሚጎዱ ያለ አግባብ መጠቀም አይገባም።   በተጨማሪም ሲጋራ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣት እና ከመጠን በላይ ቡና ማብዛት የደም መላሾችን በማጥበብ ግፊቱ እንዲያቅበዘብዝ ስለሚያደርጉ መተው አስፈላጊ መሆኑ ተመላክቷል።   ከታዘዘ የደም ግፊት መድኃኒት ውጭ የባህላዊ ህክምናዎችን ብቻ አምኖ የመድኃኒት መጠን መቀነስ ወይም ማቋረጥ ለድንገተኛ የልብ ድካም እና የአእምሮ ደም መፈሰስ (Stroke) ያጋልጣል።   ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ የሚያስፈልገው መቼ ነው? የደም ግፊት መጠኑ ድንገት ከፍ ብሎ ከጽኑ የራስ ምታት፣ የደረት ህመም፣ የእይታ መደብዘዝ ወይም የመተንፈስ ችግር ጋር ከተያያዘ በአፋጣኝ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።  @Freshmerejaet @Freshmerejaet

የ ቁማር አስከፊነት 💔💔💔😭😭😭 ይህቺ ልጅ እንዲህ የምታለቅሰው የሴዶ መሸነፍ አበሳጭቷት ብቻ አይደለም። እርሱ ያሸንፋል ብላ ለስራ መስሪያ ከባንክ የተበደረቺውን ብር ሳይቀር አሲዛ በቁማር ተበልታ ነው።💔💔💔(via seid social) https://t.me/+s9JcxTA5tA1hYTRk https://t.me/+s9JcxTA5tA1hYTRk

በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ‼️ በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ አስከፊ ሆኗል። ከላይ የሚታየው ምስል ዛሬ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም የተወሰደ ሲሆን የተዘራው ሰብል ሙሉ ለሙሉ እየደረቀ ነው። ከብቶ
+3
በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ‼️ በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ አስከፊ ሆኗል። ከላይ የሚታየው ምስል ዛሬ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም የተወሰደ ሲሆን የተዘራው ሰብል ሙሉ ለሙሉ እየደረቀ ነው። ከብቶች በመኖ እጥረት እየሞቱ ይገኛሉ። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

የማርሻል አርት አሰልጣኙ ማስተር ሀሰን ሞሚን ከጆኒ ጋር ለመፋለም ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ በሀገር ውስጥ የኤምኤምኤ (MMA) ስፖርት ዘርፍ አዲስ ውጥረት የሚያነሳስ መረጃ ወጥቷል። የአፋር ክልል ተወ
የማርሻል አርት አሰልጣኙ ማስተር ሀሰን ሞሚን ከጆኒ ጋር ለመፋለም ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ በሀገር ውስጥ የኤምኤምኤ (MMA) ስፖርት ዘርፍ አዲስ ውጥረት የሚያነሳስ መረጃ ወጥቷል። የአፋር ክልል ተወላጅ እና የዳካይቶ ሪዩ (Dakayto Ryu) ማርሻል አርት አሰልጣኝ ማስተር ሀሰን ሞሚን፡ በቅርቡ ትልቅ ትኩረት ከሳበው ተፎካካሪ ጆኒ (Johnny) ጋር በሪንግ ውስጥ ለመጋጠም ጥሪ ማቅረባቸው ተሰምቷል። ማስተር ሀሰን የሀገር በቀል የትግል ስፖርት እና የባህል ማርሻል አርት ጥንካሬን በኦክታጎን ውስጥ ለማሳየት ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የገለፁ ሲሆን፡ አሁን ላይ የግጥሚያው መካሄድ በETFC አዘጋጆች እና በሚመለከታቸው አካላት ውሳኔ ላይ የተመሰረተ ሆኗል። የሁለቱ ተወዳዳሪዎች የክህሎት ልዩነትና የተለያየ የስፖርት መነሻ የብዙዎችን ትኩረትስቧል። የስፖርት ቤተሰቡ ግምት፦ • የዳካይቶ ሪዩ አሰልጣኙ ማስተር ሀሰን ሞሚን ያሸንፋሉ? • ወይንስ የጆኒ የኤምኤምኤ ቴክኒክ የበላይነቱን ይይዛል? እርስዎ የትኛውን ተወዳዳሪ ይደግፋሉ? @Seledadotio @Seledadotio

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕገ ወጥ የሐዋላ እና ፈቃድ የሌላቸውን የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ይፋ አደረገ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ ህብረተሰቡ፣ የዳያስፖራ አባላት እና ደንበኞች ፈቃ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕገ ወጥ የሐዋላ እና ፈቃድ የሌላቸውን የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ይፋ አደረገ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ ህብረተሰቡ፣ የዳያስፖራ አባላት እና ደንበኞች ፈቃድ የሌላቸውን የገንዘብ አስተላላፊ ወኪሎች እና ሕገ ወጥ የሐዋላ መረቦችን ከመጠቀም እንዲቆጠቡ አሳስቧል። እነዚህ ሕገ ወጥ ተግባራት በኢትዮጵያ ሕግ በጥብቅ የተከለከሉ መሆናቸውን በመግለጽ፣ በእነዚህ መንገዶች ገንዘብ መላክም ሆነ መቀበል ደንበኞችን ለከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ፣ ለክፍያ መዘግየት፣ ለባንክ ሒሳብ ዕገዳ፣ እንዲሁም ለሕግ ተጠያቂነት እንደሚያጋልጥ አስጠንቅቋል። ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባው የገንዘብ ዝውውር እያደገ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ፣ ዜጎች ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸውን የገንዘብ ማስተላለፊያ መንገዶችን ብቻ መጠቀም እንዳለባቸው አመልክቷል፡፡ ሕገ ወጥ መንገዶችን መጠቀም ላኪዎችንም ሆነ ተቀባይ ቤተሰቦችን አግባብነት ባላቸው ሕጎች መሠረት ለአስተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃዎች ሊያጋልጥ እንደሚችል ነው የገለጸው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ የገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት እንዲሰጡ ፈቃድ ያልተሰጣቸውን 17 ሕገ ወጥ አስተላላፊ ድርጅቶችን ይፋ አድርጓል። በዚህም አዱሊስ መኒ ትራንስፈር፣ አማል ኤክስፕረስ፣ አማል ዩኤስኤ፣ አማና ኤክስፕረስ፣ አቫንቲ፣ አዋሽ ዳይሬክት፣ ባካል መኒ ትራንስፈር፣ ጁባ ኤክስፕረስ፣ ራስሚ ፔይ፣ ረማድ ፔይ (ወይም ረማዳ ፔይ ካህ)፣ ሽጌይ መኒ ትራንስፈር፣ ታጅ ፋይናንሻል ሰርቪስ፣ ታሳ ፔይ፣ ተወከል መኒ ሰርቪሰስ፣ ዩኤስዋየር፣ ወርልድ ዳይሬክት ሊንክ እና ዞላ የተሰኙ ድርጅቶች ሕጋዊ ፈቃድ የሌላቸው መሆናቸው ገልጿል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የዉሃ መስመር በመሰበሩ በአንዳንድ አከባቢዎች ላይ የዉሃ አቅርቦት ተቋረጠ በአዲስ አበባ ከተማ በባለ 800 ሚሊ ሜትር ዲያሜትር ስፋት ያለዉ የዉሃ ግፊት መስጫ መስመር ላይ ስብራት ማጋጠሙን የአዲስ
የዉሃ መስመር በመሰበሩ በአንዳንድ አከባቢዎች ላይ የዉሃ አቅርቦት ተቋረጠ በአዲስ አበባ ከተማ በባለ 800 ሚሊ ሜትር ዲያሜትር ስፋት ያለዉ የዉሃ ግፊት መስጫ መስመር ላይ ስብራት ማጋጠሙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ዉሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታውቋል ። የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ሰርካለም ጌታቸዉ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸዉ ቆይታ እንደገለፁት ከገላን የጋራ መኖሪያ ቤት አከባቢ የሚገኝ እና በተለምዶ አቃቂ ክፍለ ከተማ 3ሀ ተብሎ ከሚጠራዉ የግፊት መስጫ ጣቢያ ወደ ሀና ማሪያም የግፊት መስጫ ጣቢያ የሚወስደው ባለ 800 ሚሊ ሜትር ከባድ የግፊት መስጫ መስመር ግንባታ በሚገነቡ ባለሀብቶች ምክንያት ተሰብሯል ። በዚህም የተነሳ ሀና ሰፈራ፣ሀና ማሪያም፣ አዲስ አበባ እና ኦሮሚያ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ ሀና ፉሪ፣ ላፍቶ፣ ጀሞ አንድ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እና አካባቢው እንዲሁም ቫርኔሮ እና ለቡ ሙዚቃ ቤት አካባቢ ውሃ ማሰራጨት እንዳልተቻለ ተገልጿል ። ባለስልጣኑ መስመሩን ለመጠገን ሙሉ የከባድ መስመር ባለሙያዎችን ማሰማራቱን ገልጿል ። መስመሩን ተጠግኖ ወደ መደበኛ ስርጭት እስኪመለስ ድረስ ደንበኞች በትእግስት እንዲጠባበቁ መልዕክቱን አስተላልፏል ። Via:- ዳጉ ጆርናል @Yenetube @Fikerassefa

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕገ ወጥ የሐዋላ እና ፈቃድ የሌላቸውን የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ይፋ አደረገ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ ህብረተሰቡ፣ የዳያስፖራ አባላት እና ደንበኞች ፈቃ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕገ ወጥ የሐዋላ እና ፈቃድ የሌላቸውን የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ይፋ አደረገ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ ህብረተሰቡ፣ የዳያስፖራ አባላት እና ደንበኞች ፈቃድ የሌላቸውን የገንዘብ አስተላላፊ ወኪሎች እና ሕገ ወጥ የሐዋላ መረቦችን ከመጠቀም እንዲቆጠቡ አሳስቧል። እነዚህ ሕገ ወጥ ተግባራት በኢትዮጵያ ሕግ በጥብቅ የተከለከሉ መሆናቸውን በመግለጽ፣ በእነዚህ መንገዶች ገንዘብ መላክም ሆነ መቀበል ደንበኞችን ለከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ፣ ለክፍያ መዘግየት፣ ለባንክ ሒሳብ ዕገዳ፣ እንዲሁም ለሕግ ተጠያቂነት እንደሚያጋልጥ አስጠንቅቋል። ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባው የገንዘብ ዝውውር እያደገ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ፣ ዜጎች ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸውን የገንዘብ ማስተላለፊያ መንገዶችን ብቻ መጠቀም እንዳለባቸው አመልክቷል፡፡ ሕገ ወጥ መንገዶችን መጠቀም ላኪዎችንም ሆነ ተቀባይ ቤተሰቦችን አግባብነት ባላቸው ሕጎች መሠረት ለአስተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃዎች ሊያጋልጥ እንደሚችል ነው የገለጸው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ የገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት እንዲሰጡ ፈቃድ ያልተሰጣቸውን 17 ሕገ ወጥ አስተላላፊ ድርጅቶችን ይፋ አድርጓል። በዚህም አዱሊስ መኒ ትራንስፈር፣ አማል ኤክስፕረስ፣ አማል ዩኤስኤ፣ አማና ኤክስፕረስ፣ አቫንቲ፣ አዋሽ ዳይሬክት፣ ባካል መኒ ትራንስፈር፣ ጁባ ኤክስፕረስ፣ ራስሚ ፔይ፣ ረማድ ፔይ (ወይም ረማዳ ፔይ ካህ)፣ ሽጌይ መኒ ትራንስፈር፣ ታጅ ፋይናንሻል ሰርቪስ፣ ታሳ ፔይ፣ ተወከል መኒ ሰርቪሰስ፣ ዩኤስዋየር፣ ወርልድ ዳይሬክት ሊንክ እና ዞላ የተሰኙ ድርጅቶች ሕጋዊ ፈቃድ የሌላቸው መሆናቸው ገልጿል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የሟቾች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል በኔፓልና በቻይና ቲቤት በተከሰተ ከባድ ጎርፍ ከ390 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ሲቀጠፍ፥ ከ1ሺ 500 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ሲሉ የአካባቢው ባለሥል
+2
የሟቾች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል በኔፓልና በቻይና ቲቤት በተከሰተ ከባድ ጎርፍ ከ390 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ሲቀጠፍ፥ ከ1ሺ 500 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ሲሉ የአካባቢው ባለሥልጣናት ገልጸዋል። አደጋው በሂማሊያ አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ውስጥ ከፍተኛ የጭቃና የድንጋይ ናዳ በመውደቁ የተነሳ ሲሆን፣ በአካባቢው ከተሞችና ሸለቆዎች ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ አስከትሏል። የነፍስ አድን ሰራተኞች ሰዎችን በህይወት ለማትረፍ መረባረባቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል ተብሏል። የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ቺያንግ በቲቤት የደረሰውን አደጋ በቦታው ተገኝተው ተመልክተዋል። የኔፓል ቱሪዝም መምሪያ ትላንት ባወጣው መረጃ፣ ከ34 አገራት የመጡ 668 ቱሪስቶች ከረቡዕ ጠዋት ጀምሮ የደረሱበት እንዳልታወቀ ገልጿል። ከእነዚህም መካከል ቢያንስ 177 ከህንድ፣ 90 ከአሜሪካ፣ 34 ከአውስትራሊያ፣ 33 ከብሪታንያ እና 25 ከካናዳ የመጡ ናቸው ብሏል። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም በኔፓል ከጠፉት መካከል 100 የቻይና ዜጎች እንደሚገኙበት እወቁልኝ ብሏል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

በትምህርት ዘርፋ ተፅእኖን አሳድረዋል በተባሉ ርእሰ መምህራኖች ላይ እርምጃ ተወሰደ የስልጤ ዞን ትምህርት መምሪያ የተማሪዎችን ዉጤት ለማሻሻል እና የማለፍ ምጣኔን ለማሳደግ ለዘርፉ ማናቆ በሆኑ ጉዳዮ
በትምህርት ዘርፋ ተፅእኖን አሳድረዋል በተባሉ ርእሰ መምህራኖች ላይ እርምጃ ተወሰደ የስልጤ ዞን ትምህርት መምሪያ የተማሪዎችን ዉጤት ለማሻሻል እና የማለፍ ምጣኔን ለማሳደግ ለዘርፉ ማናቆ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ጥናት አድርጎ የመፍትሄ እርምጃዎችን ተግባራዊ ማድረጉን አስታውቋል ። መምሪያዉ ባደረገዉ ጥናት መሠረት የመምህራን የአቅም ማነስ ፣የተነሳሽነት ችግር ፣የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ድክመት እና ሙሉ ጊዜን በትምህርት ቤት አለማዋል ለምሳሌም በግብርና ፣ንግድና ሌሎች ተጨማሪ ሰራዎች ላይ ማዋላቸዉ ለዘርፉ ችግር ሆኖ መቆየቱን የስልጤ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሹክራላ አወል ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ። በዚህም የተነሳ ለትምህርት መስጠት የነበረባቸውን አስፈላጊ ሰዓት በሌሎች ስራዎች ላይ በማሳለፍ በትምህርት ላይ ተፅዕኖ የፈጠሩ 27 ርዕሰ መምህራኖችን ከስራ ማሰናበትን ጨምሮ ሌሎችንም የማስተካከያ እርምጃዎች መዉሰድ ተችሏል ። በተጨማሪም በወላጆች እና በተማሪዎች  በኩል የተስተዋሉ ክፍተቶችን በመለየት መቅረፍ መቻሉም ተገልጿል ። በዚህም የተነሳ የተማሪዎች የ12 ክፍል የብሄራዊ ፈተናን የማለፍ ምጣኔ ከፍ ማድረግ መቻሉ ተጠቁሟል ። በዞኑ በ2016 ዓመት የተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ 3.9 እንደነበር የሚያስታውሱት ኃላፊዉ በ2017 ወደ 5.9 በመቶ እንዲሁም በ2018 ዓ.ም ደግሞ ወደ 11 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ። በመባ ወርቅነህ #ዳጉ_ጆርናል

የታሪኩ ጋንጋሲ አነጋጋሪ መልእክት ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ (ታሪኩ ጋንጋሲ) በአዲስ አበባ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ታፕ ፋይት
የታሪኩ ጋንጋሲ አነጋጋሪ መልእክት ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ (ታሪኩ ጋንጋሲ) በአዲስ አበባ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ታፕ ፋይት ቻምፒዮና (ETFC 002፤ Adwa Fight Night) ዋና ፍልሚያ ጆኒ ጁጁትሱ ሰዶን ማሸነፉን ተከተሎ፣ ታዋቂው ድምፃዊ ታሪቁ ጋንክሲ በማህበራዊ ሚዲያው ያስተላለፈው የትችት መልእክት ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። በሺዎች የሚቆጠሩ ተመልካቾችን በሳበው በዚህ ውድድር ዙሪያ ድምፃዊው «ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ፣ እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ» የሚል ግጥማዊ ቅሬታ ያቀረበ ሲሆን፣ ይኸውም በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ውስጥ እየተስፋፋ ያለውን የፍትህ ማጣት፣ የጦርነት ስቃይ፣ ተቋማዊ የሌብነትና የዘረፋ ወንጀል እንዲሁም የከፋ የኢኮኖሚ ውደቀት ችላ በማለት ህዝቡ ጥልቅ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ውስጥ እያለ በእንደዚህ አይነት የትግል ትዕይንቶች ላይ ትኩረት ማድረጉን ለመኮነን እንደሆነ ተገልጿል። ድምፃዊው ይህን ማህበራዊ ተቃርኖ በማንሳት የሰጠው አስተያየት በበርካቶች ዘንድ ድጋፍና የተለያየ ትችት በማስተናገድ በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ ሰፊ አከራካሪ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመጀመሪያ ጊዜ 39.5 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ ተቋሙ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 96.5 ቢሊዮን ብር ማትረፉን የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመጀመሪያ ጊዜ 39.5 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ ተቋሙ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 96.5 ቢሊዮን ብር ማትረፉን የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። የዘንድሮው ትርፍ ካለፉት ዓመታት አንጻር የ23 በመቶ ልዩነት እንዳለውም ተገልጿል። ተቋሙ አሁን ላይ በጥቅሉ እስከ 9,730 ሜጋ ዋት ያህል የማመንጨት አቅም እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፣ አጠቃላይ የተቋሙ አፈጻጸም 92 በመቶ መድረሱንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል። አሁን ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 585 ቢሊዮን ብር ሀብት እንዳለውና መንግሥት አለኝ ከሚላቸው ተቋማት ግንባር ቀደሙ እንደሆነም ተናግረዋል። በያዝነው ዓመት ያልተሳኩትን ጨምሮ አዳዲስ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በቀጣይ 2019 ዓ.ም እንደሚያከናውንም አገልግሎቱ አስታውቋል። በዚህም 121 ቢሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ 9,770 ሜጋ ዋት ለማመንጨት መታቀዱንም ኢንጂነር አሸብር ተናግረዋል። @Seledadotio @Seledadotio