uz
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

Kanalga Telegram’da o‘tish

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Fresh መረጃ | FreshNews analitikasi

Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 55 472 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 3 059-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 593-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 55 472 obunachiga ega bo‘ldi.

02 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -816 ga, so‘nggi 24 soatda esa -67 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 3.94% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 3.16% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 185 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 753 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

55 472
Obunachilar
-6724 soatlar
-3367 kun
-81630 kun
Postlar arxiv
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚዎች ውስጥ 62 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ማለፋቸው ተነገረ። የ12 ክፍል ማለፊያ ነጥብ ካመጡት ውስጥ 7ቱ ሴት ታራሚዎች ይገኙበታልም ተብላል፡፡   በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃና በሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል እና በዘዋይ ማረሚያ ማእከላት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱት ተፈታኞች 63 ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 62 ማለፋቸውን ማረመያ ቤቱ አስታውቋል፡፡   በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ፣ በሴቶች ማረሚያ ማዕከላት በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ እና ለፈተና የተቀመጡት 31 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፤ከነዚህም ውስጥ 7ቱ ሴቶች መሆናቸው ታውቋል፡፡   በተመሳሳይ የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው 23 የህግ ተማሪዎች  መካከል 22ቱን ማሳለፍ መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን በአጠቃላይ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚስች 62 ማለፋችው ተነግራል፡፡የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ካስፈተናቸው በሁለቱ ማዕከላት አጠቃላይ ተፈታኝ ተማሪዎች መቶ በመቶ ወደ ዩኒቨርስቲ መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት ማስመዘገብ ተችሏል፡፡ የሕግ ታራሚ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ተከትሎ የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የመጀመሪያ ደረጃና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ሳምሶን ወንድሜነህ እንደተናገሩት ማረሚያ ቤቱ ለታራሚዎች የፈጠረው ምቹ የትምህርት ከባቢ እና የታሪሚዎች ጠንካራ ተነሳሽነት ለዚህ አስደናቂ 100 ከመቶ ውጤት ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። በማዕከላቱ የሚገኙት ትምህርት ቤቶች እንደማንኛውም የህዝብ ት/ቤት ደረጃውን የጠበቀና የተሟላ መምህራን የተመደቡለት መሆኑን የገለፁት አቶ ሳምሶን የህግ ታራሚ ተማሪዎችም በህግ ጥላ ስር ቢሆኑም ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውንና ለውጤት እንደበቁም አመላክተዋል፡፡ አቶ ሳምሶን አክለውም በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ታራሚዎች ተስፋና መነሳሳትን የፈጠረ ሲሆን ማረሚያ ቤት የህይወት ማብቂያ ሳይሆን አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ መሆኑን በተግባር ያሳየ ነው፤ ብለዋል። የህግ ታራሚ ተማሪዎች  ያመጡት ውጤት መታረምና መታነፃቸውን ማሳያ በመሆኑን ገልፀው መንግስት በይቅርታና ምህረት መልቀቅ የሚችልበትን መንገድ አሊያም የትምህርት ሚኒስቴር የሕግ ታራሚ መሆናቸውን በመረዳት ትምህርታቸውን በርቀት እንዲከታተሉ ዩኒቨርሲቲዎችን እንዲያመቻችላቸው ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡   @Freshmerejaet @Freshmerejaet

«የሆርሙዝን ስም ወደ "ትራምፕ ስትሬት" ብንቀይረውሳ?» — ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በራሳቸው የሶሻል ሚዲያ መድረክ Truth Social ባሰፈሩት አነጋጋሪ መልእክት፣
«የሆርሙዝን ስም ወደ "ትራምፕ ስትሬት" ብንቀይረውሳ?» — ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በራሳቸው የሶሻል ሚዲያ መድረክ Truth Social ባሰፈሩት አነጋጋሪ መልእክት፣ ስትራቴጂካዊውን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ  ስም ለመቀየር ሀሳብ አቅርበዋል። ትራምፕ ባሰፈሩት መልእክት «አሁን አካባቢውን በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ቁጥጥር ስር ስላደረግነው፣ የሆርሙዝን ስም ወደ "ትራምፕ ስትሬት" ብንቀይረውሳ?» ሲሉ ጠይቀዋል አክለውም እንደ አሜሪካ ሀገር ሁሉ ቦታው «ከመቼውም ጊዜ በላይ ሳቢና ተፈላጊ  ይሆናል!» ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ይህ የትራምፕ አስተያየት የመጣው በአሜሪካ እና በኢራን መካከል በሆርሙዝ የባህር መስመር እና በላራክ ደሴት አካባቢ ከፍተኛ የሚሳኤል እና የባህር ኃይል ፍጥጫ እና ጥቃት በተካሄደበት ወቅት ነው። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

በሀሰተኛ ሰነድ ማጭበርበር ወንጀል ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የነበሩት ቀሲስ በላይ መኮንን ከእስር መፈታታቸው ተገለጸ። ​ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ ጠዋት ከእስር ተፈተው በአሁ
በሀሰተኛ ሰነድ ማጭበርበር ወንጀል ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የነበሩት ቀሲስ በላይ መኮንን ከእስር መፈታታቸው ተገለጸ። ​ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ ጠዋት ከእስር ተፈተው በአሁኑ ሰዓት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል። ​ግለሰቡ በሐሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት 6 ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማውጣት በመሞከራቸው፣ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የአምስት ዓመት እስራት እና የ10 ሺህ ብር ቅጣት ተፈርዶባቸው የነበረ መሆኑ ይታወሳል። ​ከእሳቸው ጋር አብረው ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ሌሎች ሁለት ተከሳሾች ደግሞ እያንዳንዳቸው የአራት ዓመት እስራት እና የ3 ሺህ ብር ቅጣት ተወስኖባቸው እንደነበር አይዘነጋም። ተከሳሾቹ የወንጀል ሕጉን እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ተላልፈዋል በሚል ጥፋተኛ ተብለው ከተፈረደባቸው በኋላ፣ ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ በይፋ ከእስር ተለቀዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

በባህርዳር ከተማ የቀን ሰራተኛው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ዕድለኛ ሆነ 👉 ሽልማቱ ከወሎ ወደ ባህር ዳር ደርሷል የባህር ዳር ነዋሪው ወጣት ኃይሌ እስከዚያው መኮንን በቆረጠው ቶምቦላ ሎተሪ በ4ኛ ዕጣ
+1
በባህርዳር ከተማ የቀን ሰራተኛው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ዕድለኛ ሆነ 👉 ሽልማቱ ከወሎ ወደ ባህር ዳር ደርሷል የባህር ዳር ነዋሪው ወጣት ኃይሌ እስከዚያው መኮንን በቆረጠው ቶምቦላ ሎተሪ በ4ኛ ዕጣ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ዕድለኛ ሆኗል፡፡ ወጣት ኃይሌ በቀን ስራ የተሰማራ ሲሆን አልፎ አልፎ ህይወቱን ለመቀየር ብዙ ሥራዎችን ይሞክር እንደነበር ገልጾ፤ ከነዚህም አንዱ እና ዋነኛው ሎተሪን መቁረጥ እንደነበር የገለጸ ሲሆን እድልና አጋጣሚ ገጥሞ እድለኛ አድርጎኛል በማለት ሽልማቱን ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በተረከበበት ወቅት በደስታ ስሜት ውስጥ ሆኖ ገልጾልናል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio

የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ወደሚዋሠነው ብሉ ናይል ግዛት በርካታ ተዋጊዎችን በማንቀሳቀስ ላይ መኾኑን አስታወቀ። ወደ ብሉ ናይል ግዛት ደማዚን ከተማ አካባቢ የተንቀሳቀሱት ተዋጊዎች የፈጥኖ ደራሹን ኃይል ለመውጋት ከሱዳን ጦር ሠራዊት ጋር የወገኑ ኃይሎች እንደሆኑ የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከተያዘው ሳምንት መጀመሪያ ጀምሮ በግዛቲቱ በርካታ አካባቢዎች በመንግሥት ወታደሮችና በፈጥኖ ደራሹ ኃይል መካከል ውጊያ በመካሄድ ላይ መሆኑን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ ስትራቴጂካዊቷን ኩርሙክ ከተማ ከአንድ ሳምንት በፊት ከሱዳን ጦር ሠራዊት መንጠቁ ይታወሳል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

በቻይና ጎዳናዎች ላይ ስራ የጀመረው የሮቦት ትራፊክ ፖሊስ የወደፊቱ የትራፊክ ቁጥጥር አዲሱ ምዕራፍ በምስራቅ ቻይና ዢጂያንግ ግዛት በምትገኘው ዮንግካንግ ከተማ፣ የትራፊክ ፍሰትን የመቆጣጠር እና የማ
በቻይና ጎዳናዎች ላይ ስራ የጀመረው የሮቦት ትራፊክ ፖሊስ የወደፊቱ የትራፊክ ቁጥጥር አዲሱ ምዕራፍ በምስራቅ ቻይና ዢጂያንግ ግዛት በምትገኘው ዮንግካንግ ከተማ፣ የትራፊክ ፍሰትን የመቆጣጠር እና የማስተካከል ስራ የሚያግዝ የሮቦት ትራፊክ ፖሊስ የመጀመሪያ የሙከራ ስራውን በይፋ ጀምሯል። ይህ የቴክኖሎጂ ድንቅ ውጤት የሆነው ሮቦት ለ30 ደቂቃ ብቻ በመብራት ከተሞላ በኋላ ለአራት ሰዓታት ያህል ያለምንም እረፍት በተከታታይ መስራት የሚችል ነው። የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው የመንገድ መገናኛዎች ላይ የሚከናወኑ መደበኛና ተደጋጋሚ ተግባራትን በብቃት ለማከናወን ተቀርጾ የተሰራ ነው። ሮቦቱ በተለይም አሽከርካሪዎችንና እግረኞችን በስርዓት የመምራት፣ የመንገድ ላይ ደህንነት ማሳሰቢያዎችን የመስጠትና በትራፊክ መጨናነቅ ወቅት የትራፊክ ፖሊሶችን ስራ በከፍተኛ ደረጃ የማቃለል ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል። ይህ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ ውጤት የከተሞችን የመንገድ ደህንነትና የትራፊክ አስተዳደር ወደ አዲስ የዘመናዊነት ደረጃ የሚያሸጋግር ድንቅ እርምጃ ተደርጎ ተወስዷል። @Addis_News @Addis_News

የሆንግ ኮንግ አክቲቪስት ጆሹዋ ዎንግ በብሔራዊ ደህንነት ሕግ ጥፋተኛነቱን አመነ ታዋቂው የሆንግ ኮንግ የዴሞክራሲ መብት ተሟጋች ጆሹዋ ዎንግ፣ ከውጭ ኃይሎች ጋር አብሮ በመስራት እና ማዕቀብ እንዲጣል
የሆንግ ኮንግ አክቲቪስት ጆሹዋ ዎንግ በብሔራዊ ደህንነት ሕግ ጥፋተኛነቱን አመነ ታዋቂው የሆንግ ኮንግ የዴሞክራሲ መብት ተሟጋች ጆሹዋ ዎንግ፣ ከውጭ ኃይሎች ጋር አብሮ በመስራት እና ማዕቀብ እንዲጣል በመጠየቅ በብሔራዊ ደህንነት ሕግ የቀረበበትን ክስ ፍርድ ቤት ቀርቦ አምኗል። የ29 ዓመቱ አክቲቪስት እ.ኤ.አ በ2020 በቻይና እና በሆንግ ኮንግ ላይ ማዕቀብ ወይም ማገጃ እንዲጣስ የውጭ ሀገራትን ጠይቋል በሚል በከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሷል።ወንጀሉ ከ3 እስከ 10 ዓመታት የሚደርስ እስራት የሚያስቀጣ ሲሆን፣ ድርጊቱ ከባድ አደጋ አደረሰ ተብሎ ከታመነ እስከ ዕድሜ ልክ እስራት ሊደርስበት ይችላል። ዎንግ በአሁኑ ወቅት በመንግስት ላይ በማመፅ ወንጀል የተበየነበትን የአምስት ዓመት ገደማ ቅጣት በመፈጸም ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት ከእስር ይፈታል ተብሎ ይጠበቅ ነበር። ዓቃቤ ሕግ እንዳስታወቀው፣ ዎንግ ዓለም አቀፍ ማዕቀብ እንዲጣል ለመጠየቅ መጣጥፎችን የጻፈና የቀድሞዋ የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲን ጨምሮ ከበርካታ የውጭ ሀገር ፖለቲከኞች ጋር ተገናኝቷል። ክሶቹ ሲነበቡለት በታላቅ ድምፅ ጥፋተኛ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን፣ የምዕራባውያን ዲፕሎማቶችም በችሎቱ ላይ ተገኝተዋል። የቅጣት ውሳኔው የሚሰጥበት ቀን በቀጣይ የሚገለጽ ይሆናል።   ሰላማዊ ነጋሲ @Ethionews433 @Ethionews433

የብራዚል የንግድና ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከፈተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በብራዚል ጉብኝታቸው ወቅት ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ጋር ያደረጉትን ውይይት መ
+2
የብራዚል የንግድና ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከፈተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በብራዚል ጉብኝታቸው ወቅት ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ጋር ያደረጉትን ውይይት መነሻ በማድረግ ቢሮው መከፈቱን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና አሜሪካ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር መለስ ዓለም ገልጸዋል። ተቋሙ ቢሮውን በአዲስ አበባ መክፈቱ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብርን በማላቅ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተመላክቷል። ሀገራቱ የብሪክስ አባል እንደመሆናቸው ትብብራቸውን ወደ ተጨባጭ የንግድ ዕድሎች ለመቀየር እገዛ እንደሚያደርግም ነው የተገለጸው፡፡ በተጨማሪም የብራዚል ባለሀብቶች በኢትዮጵያና በምስራቅ አፍሪካ ገበያ ያሉ የንግድ እድሎችን ለመመልከት የሚያስችል ነው፡፡ በተመሳሳይ በኢትዮጵያ የሚገኙ ባለሀብቶች በብራዚል ያለውን ዕድል ለመመልከት እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡ @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የደቡብ ኮሪያ ጠንቋዮች AI ገቢያችንን ክፋኛ ቀንሶብናል ብለው አማረሩ በቴክኖሎጂ ምጥቀት ቀዳሚ ከሆኑት የዓለማችን አገራት መካከል አንዷ በሆነችው ደቡብ ኮሪያ፣ የቅርብ ጊዜው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዕድገት የዘመናት ታሪክ ባለው የባህላዊ ዕድል ትንበያ (ጥንቆላ) ኢንደስትሪ ላይ ከፍተኛ አደጋ እየደቀነ መሆኑ ተሰማ። በአገሪቱ የሚገኙ ታዋቂ ዕድል ተንባዮችና ጠንቋዮች ወደ እነርሱ ይመጡ የነበሩ ደንበኞቻቸው ፊታቸውን ወደ AI ቴክኖሎጂ በማዞራቸው ምክንያት ሥራቸው ክፉኛ እንደ ተቀዛቀዘባቸው በምሬት በመግለጽ ላይ ናቸው። በዋና ከተማዋ ሴኡል ዳርቻ በሚገኘውና በባህላዊ ዕድል ተንባዮች (ጠንቋዮች) መንደርነቱ በሚታወቀው ‘ሚያ መንደር’ ውስጥ አሁን ላይ የደንበኞች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ቀንሷል። ቀደም ባሉ ዓመታት የደቡብ ኮሪያ ነዋሪዎች ስለ ጤናቸው፣ ትዳር፣ ፍቅር፣ ገንዘብ እና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸው ለመጠየቅ ወደዚህ መንደር በብዛት ይጎርፉ ነበር። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ አብዛኞቹ ዜጎች በአካል ወደ መንደሩ ከመሄድ ይልቅ በኢንተርኔት አማካኝነት እንደ ChatGPT እና Gemini ያሉ የ-AI መተግበሪያዎችን በመጠቀም ዕድላቸውን መተንበይ መምረጣቸው ተገልጿል። በዚሁ መንደር ውስጥ ከቀሩት ጥቂት ዕድል ተንባዮች መካከል አንዷ የሆኑት የ86 ዓመቷ አዛውንት ሶንግ ኦ-ሱን ሁኔታውን ሲያስረዱ፣ እሳቸው አሁንም ከዘመናዊው የኢንተርኔት ዓለም ርቀው እንደሚኖሩና ዕድልን ለመተንበይ “አራቱ የዕጣ ፈንታ ምሰሶዎች” (Saju) የሚባለውን የኮሪያ ጥንታዊ ኮከብ ቆጠራ ዘዴ በብሬይል መጽሐፍ እያነበቡ እንደሚጠነቁሉ ገልጸዋል። አዛውንቷ ባለፉት 40 ዓመታት ያካበቱት ይህ የሰዎች ስነ-ልቦና የመረዳትና የማማከር ልምድ AI በቀላሉ ሊተካው የማይችለው የላቀ ሰብአዊ ችሎታ መሆኑን በጽኑ ያምናሉ። “በሕይወት የመኖር ተስፋ ቆርጠው ለመሞት እንኳ ወደ እኔ የመጡ ሰዎችን አሳምኜና አጽናንቼ ሕይወታቸውን እንዲቀጥሉ አድርጌያለሁ” ሲሉም የሥራቸውን ማኅበራዊ ፋይዳ ያስረዳሉ። ይሁን እንጂ የኢኮኖሚው እውነታ ሌላ ሆኗል። ቀደም ሲል በአካባቢው ከ 70 እስከ 80 የሚደርሱ ጠንቋዮች በሥራ ላይ የነበሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ቁጥራቸው ከ20 በታች ዝቅ ብሏል። እንደ ‘ኢንኖፎሬስት’ (Innoforest) የተባለው የደቡብ ኮሪያ የጀማሪ ኩባንያዎች ትንተና ድርጅት መረጃ መሠረት፣ በአገሪቱ ያለው የዕድል ትንበያ ገበያ እጅግ ግዙፍና በ 2024 ብቻ በግምት 986 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የደረሰ ቢሆንም፣ አብዛኛው የገበያ ድርሻ ግን ወደ ዘመናዊ መተግበሪያዎች እየተዛወረ ነው። ለዚህ ሽግግር ዋነኛው ምክንያት የዋጋና የቅልጥፍና ጉዳይ መሆኑ ይነገራል። የ-AI መተግበሪያዎች አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ በነጻ ወይም በጣም በዝቅተኛ ክፍያ በሰከንዶች ውስጥ የሚሰጡ ሲሆን፣ በአንጻሩ እንደ ወይዘሮ ሶንግ ያሉ ባህላዊ ባለሙያዎች ለአንድ የዕድል ትንበያ ክፍለ-ጊዜ እስከ 35 ዶላር ገደማ ያስከፍላሉ። ይህ የዋጋ ልዩነትና የቴክኖሎጂው ተደራሽነት፣ ወጣቱ የኮሪያ ትውልድ ከባህላዊው መንደር ይልቅ ስማርት ፎኑን እንዲመርጥ ማድረጉን የዘርፉ ታዛቢዎች ገልጸዋል። 45% - 55% የሚጠጉ ደቡብ ኮርያውያን በህይወት ዘመናቸው ቢያንስ አንድ ጊዜ የህይወት እጣ ፋንታቸው እንዲተነበይላቸው በመፈለግ ወደ ዕድል ተንባዮች (ጠንቋዮች) ቤት ያመራሉ። Via መዝናኛ ሚዲያ ዳጉ_ጆርናል @Freshmerejaet @Freshmerejaet

✨ ብዙ ሰዎች እድልን ይጠብቃሉ፤ ጥቂቶች ግን ይሞክራሉ። እርስዎስ ከየትኞቹ ውስጥ ነዎት? ✨ 🎉 Bella Bingo የደስታ፣ የመዝናኛ እና የአሸናፊነት ቦታ ነው! 🎁 አስደሳች ቦነሶች 💰 የማሸነ
✨  ብዙ ሰዎች እድልን ይጠብቃሉ፤ ጥቂቶች ግን ይሞክራሉ። እርስዎስ ከየትኞቹ ውስጥ ነዎት? ✨ 🎉 Bella Bingo የደስታ፣ የመዝናኛ እና የአሸናፊነት ቦታ ነው! 🎁 አስደሳች ቦነሶች 💰 የማሸነፍ እድሎች ⚡ ቀላል እና ፈጣን ተሳትፎ 🎊 በየቀኑ አዲስ ደስታ 🏆 አሸናፊ የመሆን እድል 📍ባሉበት ሁነው በ ስልክዎ የሚዝናኑበት ጨዋታ 🌟 ዕድል ለሚሞክሩት በሩን ትከፍታለች! 🌟 ድል ለሚደፍሩት ትመጣለች! 🔥 ዛሬ ይቀላቀሉ! 🔥 ይጫወቱ! 🔥 ይዝናኑ! 🔥 ዕድልዎን ይሞክሩ @BellaBingo1bot ለማንኛውም እገዛ --09 72 75 73 19 ይደውሉ 💙 Bella Bingo – የደስታ፣ የዕድል እና የአሸናፊዎች ምርጫ!

የአስመራ ነዋሪዎች በንጹህ ውሃ አጥረት ምክንያት ቀይ ባህርን ለመጠጣት ተገደዋል ተባለ‼️ በኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የሚኖሩ ዜጎች በከባድ የውሃ እጥረት ምክንያት የዕለት ተዕለት ህይወታቸው መስተጓጎሉንና ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል። የከተማዋ ነዋሪዎች ልብስ ማጠብ እና የንጽህና መጠበቂያ የሚሆኑ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለመጠበቅ ሲሉ የውሃ አጠቃቀማቸውን እጅግ ለመቀነስና አማራጭ የውሃ ምንጮችን በፍለጋ ለመንከራተት መገደዳቸውን ገልጸዋል። ​የችግሩ አሳሳቢነት የከፋባቸው አያሌ የከተማዋ ነዋሪዎች እንደሚናገሩት መደበኛ የቧንቧ ውሃ ማግኘት ካቆመ ቆይቷል፤ በዚህም ምክንያት የውሃ ቦቴዎችን በመጠበቅ በውድ ዋጋ ውሃ ለመግዛት ተገደዋል። ሁኔታው ይበልጥ አሳዛኝ የሚሆነው ደግሞ አቅም በሌላቸው ዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ሲሆን አንዳንዶቹ የዝናብ ውሃ ለመሰብሰብ ሲጠባበቁ ሌሎች ደግሞ ከቀይ ባህር የሚጓጓዘውን የጨው ውሃ ለተለያዩ ፍጆታዎች ለማዋል እስከመገደድ ደርሰዋል። ​ባለፈው ሐምሌ ወር የወጣ አንድ ጥናት እንዳመለከተው በኤርትራ እየተባባሰ ለመጣው የውሃ አቅርቦት ችግር በምክንያትነት የተጠቀሱት የአየር ንብረት ለውጥ፣ የቆዩና የወደሙ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም ደካማ የውሃ አስተዳደር ስርዓት ናቸው። ጥናቱ አክሎም በአሁኑ ወቅት የሚገኘው የውሃ አቅርቦት መደበኛ ያልሆነና ለጤና አስተማማኝ እንዳልሆነ በማስገንዘብ ሊከሰት የሚችለውን የጤና አደጋ ጠቁሟል። ​ይህ ደረቅ ወቅቶች በመጡ ቁጥር ተደጋገሞ የሚከሰተው የውሃ እጥረት በነዋሪዎች የኢኮኖሚ አቅም ላይም የከፋ ጫና እያሳደረ ይገኛል። የውሃ ግዥ ወጪ እየጨመረ መምጣቱ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦች ያላቸውን ትንሽ ገቢ ለውሃ እንዲያወጡ በማስገደድ ተጨማሪ የኑሮ ውድነት ፈጥሮባቸዋል። አሁን ላይ በአስመራ እየታየ ያለው ይህ ቀውስ በከተማዋ ያለውን የዘለቀ የመሰረተ ልማት ውድቀትና የመሰረታዊ አገልግሎቶች ማጣት አጉልቶ የሚያሳይ አሳሳቢ ክስተት ሆኗል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፥ የተገባደደው ዓመት የኢትዮጵያ
መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፥ የተገባደደው ዓመት የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ ጅማሮ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገበበት ነው ብለዋል፡፡ በዚህም ምክንያት መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ስያሜዎች እንደሚከበሩ አመልክተዋል፡፡ ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን - ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ እድገት ተላቅቃ ወደ ፈጣንና እመርታዊ የእድገት ምህዋር መግባቷን የምናሳይበት ቀን ነው ብለዋል፡፡ ይህ ዕለት በሁሉም ዘርፍ የተሰሩ ሥራዎችን እመርታዊ ለውጥ የምናስገነዝብበት ይሆናል ነው ያሉት፡፡ ጳጉሜን 2 - የማንሰራራት ቀን - 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ እድገት ወደ ሁለንተናዊ ከፍታ መሸጋገር የጀመረችበት ቀን በመሆኑ ዕለቱ የማንሰራራት ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ጳጉሜን 3 - የጽናት ቀን በሚል ስያሜ ይከበራል፤ ኢትዮጵያ ለዘመናት በጽናት ጠብቃው የኖረችውን ነጻነትና ሉዓላዊነት ማስቀጠል የዛሬው ትውልድ ኃላፊነት መሆኑን ለማስገንዘብ ዕለቱ የጽናት ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል ብለዋል፡፡ ጳጉሜን 4 - የኅብር ቀን - ኢትዮጵያ የብዝሃ ማንነቶች ሀገር እንደመሆኗ ብዝሃነት ጌጣችንና ኅብረታችን ነው፤ ኅብረታችን ደግሞ የአንድነትና የጥንካሬያችን ምንጭ መሆኑን በማውሳት፤ ዕለቱ የኅብር ቀን መባሉን አስረድተዋል፡፡ ጳጉሜን 5 - የነገ ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ዓላማውም ኢትዮጵያ ነገዋን ዛሬ እየሰራች እንደምትገኝ ማስገንዘብ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ @Addis_News @Addis_News

አሜሪካ በፈፀመችው የቦምብ ጥቃት በሰርግ ቦታ ላይ የነበሩ ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውንየኢራን ቀይ መስቀል ማህበር ገለፀ ። የኢራን ቀይ መስቀል ማህበር እንዳስታወቀው፣ በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ
አሜሪካ በፈፀመችው የቦምብ ጥቃት በሰርግ ቦታ ላይ የነበሩ  ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውንየኢራን ቀይ መስቀል ማህበር ገለፀ ። የኢራን ቀይ መስቀል ማህበር እንዳስታወቀው፣ በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ የሰርግ ስነ-ሰርዓት ላይ በአሜሪካ ጥቃት ምክንያተት አራት ሰዎች (አንድ ህጻን ጨምሮ) ህይወታቸው አልፏል፤ ከ50 በላይ ሰዎችም ቆስለዋል። ቀይ መስቀል በማህበራዊ ትስስር ገጹ  ባጋራው  ጽሁፍ፤ "በአሜሪካ የሚሳኤል ጥቃት የቦምብ ፍንጣሪ በሆርሞዝጋን ግዛት በሲሪክ ወረዳ ኩሄስታክ ከተማ የሰርግ ዝግጅት እየተካሄደበት በነበረ የመኖሪያ ቤት ላይ አርፎ የሰዎችን ህይወት አጥፍቱዋል" ብሏል። ማህበሩ አክሎም "ከ50 በላይ ሰዎች ቆስለዋል፤ አንድን ህጻን ጨምሮ አራት ሰዎችም ሰማዕትነት ተቀብለዋል" ሲል ገልጿል። የኢራን የመንግስት ይፋ ያደረገው ቪዲዮ፣ በሲሪክ በሚገኘው የሰርግ ስፍራ ላይ የደረሰውን ሰፊ ፍርስራሽ እና ጉዳት የሚያሳይ ሲሆን፣ በስተጀርባም የሰዎችን ድምጽና ጩኸት ማድመጥም ተችሏል። የአሜሪካ ባለስልጣናት እስካሁን ድረስ ስለተባለው ድርጊት መረጋገጥ የሰጡት አስተያየት የለም፤ነገር ግን ኢራን ለደረሰው ጥቃት አፀፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ ዝታለች፡፡ በደቡባዊቷ ሲሪክ ወረዳ የምትገኘው ስፍራ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ባለው የሆርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ ትገኛለች።   ሀና ሰይፉ   @Ethionews433 @Ethionews433

"መንግሥት ከተጠያቂነት ሊያመልጥ አይችልም!" - አብን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በንፁሀን ላይ የተፈጸሙትን ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ የእምነት ተ
"መንግሥት ከተጠያቂነት ሊያመልጥ አይችልም!" - አብን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በንፁሀን ላይ የተፈጸሙትን ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ የእምነት ተቋማት ውድመትና እገታዎችን በጽኑ ኮንኗል። ንቅናቄው ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅ ኃላፊነቱን አልተወጣም ሲል ከሷል። ጥቃቱን በታጣቂዎች ላይ ብቻ በማሳበብ መንግሥት ከተጠያቂነት ነፃ ሊሆን እንደማይችል የገለጸው አብን፤ በጸጥታ መዋቅሩ ላይ ላለው ውድቀት የባለሥልጣናት ተጠያቂነት ሊረጋገጥ እንደሚገባ አሳስቧል። አብን አክሎም የዜጎች የመኖር መብት ባልተከበረበት ሁኔታ ስለ አገራዊ ብልፅግና ማውራት እውነታውን መካድ ነው ብሏል። ችግሩን ዘላቂ በሆነ መንገድ ለመፍታት የፌደራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት የተቀናጀ እርምጃ እንዲወስዱ፣ ገለልተኛ አካላት የሚሳተፉበት የምርመራ ሥርዓት እንዲዘረጋና ተፈናቃዮች በአስቸኳይ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

በህንድ የቲክቶክ እይታ ለማግኘት ወደ አንበሳ ማቆያ የዘለለው ግለሰብ መነጋገሪያ ሆኗል በህንድ ላሆር መካነ አራዊት ውስጥ አንድ የቲክቶክ ተጠቃሚ ለማህበራዊ ሚዲያ የሚሆን ቪዲዮ ለመቅረጽ ወደ አንበሶ
በህንድ የቲክቶክ እይታ ለማግኘት ወደ አንበሳ ማቆያ የዘለለው ግለሰብ መነጋገሪያ ሆኗል በህንድ ላሆር መካነ አራዊት ውስጥ አንድ የቲክቶክ ተጠቃሚ ለማህበራዊ ሚዲያ የሚሆን ቪዲዮ ለመቅረጽ ወደ አንበሶች ማቆያ ስፍራ ዘሎ ሲገባ በመታየቱ፣ ከፍተኛ የደህንነት ጉድለት ተከስቷል። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት የተሰራጨው ይህ ቪዲዮ፣ በስፍራው ስላለው የደህንነት አጠባበቅ ሁኔታ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል። አንድ የቲክቶክ ተጠቃሚ የአንበሶች ማቆያ አቅራቢያ ወደሚገኘው የተከለከለ ቦታ እና ወደ አንበሳ ማቆያው ውስጥ በተደጋጋሚ የገባ ሲሆን፣ በስፍራው የነበሩት የደህንነት ሰራተኞችም እርምጃውን ማስቆም አልቻሉም። ይህ ክስተት በስፍራው ስለሚተገበሩት የደህንነት አሰራሮች እና የደህንነት ሰራተኞች አፈጻጸም ላይ ጥያቄዎችን አስነስቷል። የአራዊት መናፈሻው አስተዳደር፣ የደህንነት አሰራሮችን ለማጠናከር እንዲሁም የጎብኚዎችን እና የእንስሳትን ደህንነት ለማረጋገጥ አዲስ የደህንነት ኩባንያ እየተቀጠረ መሆኑን ገልጿል። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተወዳጅነትን ለማትረፍ (ቫይራል ለመሆን) ሲባል አንድ ግለሰብ ህይወቱን ለአደጋ ሲያጋልጥ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም። ከዚህ ቀደም በክይበር ፓክቱንክዋ ግዛት ስዋት ወረዳ፣ አንድ ወጣት የቲክቶክ ተጠቃሚ ቪዲዮ እየቀረጸ ሳለ ሽጉጡን በድንገት በመተኮሱ ሕይወቱ አልፏል። ለማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም ለቲክቶክ) አዳዲስ እና ልዩ በሆኑ መንገዶች ቪዲዮ የመቅረጽ አዝማሚያ የሚያስከትለውን የሞት አደጋ መቀነስ አልተቻለም፤ ልዩ በሆነ መልኩ ቪዲዮ የመቅረጽ ከፍተኛ ፍላጎትም ሕይወት ቀጥፏል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የኮሊደር ልማት ይቀጥላል‼️ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በቀጣዩ ዓመት በከተማዋ የኮሪደር ልማት የሚካሄድባቸው አካባቢዎች እንደተለዩ በከተማዋ አስተዳደር የ2019 በጀት ዓመትና የቀጣ
የኮሊደር ልማት ይቀጥላል‼️ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በቀጣዩ ዓመት በከተማዋ የኮሪደር ልማት የሚካሄድባቸው አካባቢዎች እንደተለዩ በከተማዋ አስተዳደር የ2019 በጀት ዓመትና የቀጣይ አምስት ዓመታት ዕቅድ የግምገማ መድረክ ላይ ተናገሩ። አዳነች የኮሪደር ልማት በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል። የወንዞችን ዳርቻ ማደስና "የወደቁ" ሠፈሮችን የማንሳት ሥራ በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውስጥ በቁጥር ተለይቶ መቀመጡን አዳነች ገልጠዋል። አዳነች አያይዘውም፣ ያረጁ ሠፈሮችን የማደስ ሥራ ነዋሪዎችን በንጽህና እንዲኖሩ ከመደገፉ ባሻገር፤ በተደጋጋሚ የሚከሠቱ ተላላፊ በሽታዎችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በቀጣዩ የኮሊደር ልማት የትኞቹ ሰፈሮች እንደሚነሱ በግልፅ አልታወቀም። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

አባይ ቴሌቪዥን ማስጠንቀቂያ ተሰጠው! "የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በአባይ ቴሌቪዥን ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ባለስልጣኑ ባለፉት ሦስት ወራት ባደረገው ክትትል፣ ጣቢያው በዜናዎቹ
+2
አባይ ቴሌቪዥን ማስጠንቀቂያ ተሰጠው! "የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በአባይ ቴሌቪዥን ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ባለስልጣኑ ባለፉት ሦስት ወራት ባደረገው ክትትል፣ ጣቢያው በዜናዎቹና በፕሮግራሞቹ ላይ ከባድ የሕግና የሙያ ስነ-ምግባር ጥሰቶችን ፈጽሟል ብሏል። ከጥሰቶቹ መካከል፦ከባህላችን ያፈነገጡ ፀያፍ ንግግሮችን ማሰራጨት፣የሴቶችን ክብር የሚነኩ ይዘቶች፣እና ያልተረጋገጡ የዜና ምንጮችን መጠቀም ይጠቀሳሉ። የጣቢያው ኃላፊዎች ጥፋቱን አምነው ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን፣ በአፋጣኝ እርምጃ እንደሚወስዱም ቃል ገብተዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

በላይቭ (Live) ግድያ የፈፀሙት በቁጥጥር ስር ዋሉ። "100 ተጠርጣሪዎች ታፈሱ! የሳውዲው ግድያ መረጃ... "በሳውዲ አረቢያ ድንበር ላይ በኢትዮጵያውያን መካከል የተፈፀመው አስደንጋጭ ግድያ አዲስ
በላይቭ (Live) ግድያ የፈፀሙት በቁጥጥር ስር ዋሉ። "100 ተጠርጣሪዎች ታፈሱ! የሳውዲው ግድያ መረጃ... "በሳውዲ አረቢያ ድንበር ላይ በኢትዮጵያውያን መካከል የተፈፀመው አስደንጋጭ ግድያ አዲስ መረጃ ወጥቷል። • ግድያውን የፈፀመው ግለሰብና 5 ግብረ አበሮቹ ተይዘዋል። • በሶሻል ሚዲያ ጉዳዩን በማራገብ ተጠርጣሪ የሆኑ ከ100 በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል። • የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከሳውዲ የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ወንጀለኞችን የማደን ስራውን አጠናክሯል። የኢትዮጵያዊነትን ባህል ያረከሰው ይሄ ድርጊት የህግ የበላይነት ሊረጋገጥበት ይገባል። ድምፅ ለሆናችሁና መረጃ ለሰጣችሁ ሁሉ ኤምባሲው ምስጋና አቅርቧል። @Addis_News @Addis_News

በካፌ ውስጥ ተቀጥሮ የሚሰራው ግለሰብ የመኪና ዕድለኛ ሆነ ​በደቡብ ወሎ ኩታበር ወረዳ ነዋሪ የሆነው ወጣት ሰለሞን ብርሃን በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የቶምቦላ ሎተሪ 3ኛ ዕጣ አሸናፊ በመሆን የዘመ
+1
በካፌ ውስጥ ተቀጥሮ የሚሰራው ግለሰብ የመኪና ዕድለኛ ሆነ ​በደቡብ ወሎ ኩታበር ወረዳ ነዋሪ የሆነው ወጣት ሰለሞን ብርሃን በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የቶምቦላ ሎተሪ 3ኛ ዕጣ አሸናፊ በመሆን የዘመናዊ ኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ባለቤት ሆኗል። በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዋና መሥሪያ ቤት በተካሄደው በርክከብ ሥነ-ሥርዓት ላይ ወጣት ሰለሞን የመኪናውን ቁልፍ እና ህጋዊ ሊብሬ ተረክቧል። ​በግል ካፌ ውስጥ ተቀጥሮ የሚሠራው ወጣት ሰለሞን ብርሃን ከዕለት ተዕለት ሥራው በተጓዳኝ አዘውትሮ ሎተሪ የመግዛት የቆየ ልማድ እንደነበረው ገልጿል። ላለፉት በርካታ ዓመታት ተስፋ ሳይቆርጥ ዕድሉን ሲሞክር የቆየው ወጣቱ፣ አሁን ላይ የ3ኛ ዕጣ አሸናፊ በመሆኑ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማውና የዘመናት ትልቅ ሕልሙ እንደተሳካለት ተናግሯል። ​ይህ በዕድል የደረሰውን ዘመናዊ ኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ለግል አገልግሎት ከመጠቀም ይልቅ ቀጣይ ሕይወቱን ለማሻሻል በሚያስችለው መልኩ የትራንስፖርት አገልግሎት ለማሰማራት ማቀዱን ገልጿል። @Seledadotio @Seledadotio

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን 1.25 ሚሊዮን ቶን ማዕድን የማቀናበር አቅም ያለው ፋብሪካ ሊገነባ ነው ✍️ የፋብሪካው አስገንቢ ሚድሮክ ጎልድ፤ የግንባታ መሣሪያዎች እንዲያቀርብለት ከኦስትሪያ
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን 1.25 ሚሊዮን ቶን ማዕድን የማቀናበር አቅም ያለው ፋብሪካ ሊገነባ ነው   ✍️ የፋብሪካው አስገንቢ ሚድሮክ ጎልድ፤ የግንባታ መሣሪያዎች እንዲያቀርብለት ከኦስትሪያው የሲሚንቶ እና ማዕድን ኩባንያ ሴምቴክ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል።   ❤️ ሴምቴክ፤ በስምምነቱ መሠረት በዓመት 1 ሚሊዮን 250 ሺህ ቶን ወርቅ አዘል ድንጋይ ማቀነባበር የሚችል የወርቅ ፋብሪካ ማሽነሪ የማምረትና የመገንባት ተግባር እንደሚያከናውን ሚድሮክ ጎልድ አስታውቋል።   🔙 ሚድሮክ በመተከል ዞን 33,000 ኪሎ ግራም የሚገመት ትልቅ የወርቅ ክምችት ማግኘቱን በነሐሴ 2006 ዓ.ም አስታውቆ እንደነበር የሀገር ውስጥ ሚዲያ በዘገባው አስታውሷል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet