ar
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

الذهاب إلى القناة على Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Fresh መረጃ | FreshNews

تُعد قناة Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 55 818 مشتركاً، محتلاً المرتبة 3 017 في فئة التعليم والمرتبة 580 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 55 818 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -716، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -15، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 3.62‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 2.98‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 019 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 663 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

55 818
المشتركون
-1524 ساعات
+1677 أيام
-71630 أيام
أرشيف المشاركات
የሟቾች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል በኔፓልና በቻይና ቲቤት በተከሰተ ከባድ ጎርፍ ከ390 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ሲቀጠፍ፥ ከ1ሺ 500 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ሲሉ የአካባቢው ባለሥል
+2
የሟቾች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል በኔፓልና በቻይና ቲቤት በተከሰተ ከባድ ጎርፍ ከ390 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ሲቀጠፍ፥ ከ1ሺ 500 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ሲሉ የአካባቢው ባለሥልጣናት ገልጸዋል። አደጋው በሂማሊያ አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ውስጥ ከፍተኛ የጭቃና የድንጋይ ናዳ በመውደቁ የተነሳ ሲሆን፣ በአካባቢው ከተሞችና ሸለቆዎች ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ አስከትሏል። የነፍስ አድን ሰራተኞች ሰዎችን በህይወት ለማትረፍ መረባረባቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል ተብሏል። የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ቺያንግ በቲቤት የደረሰውን አደጋ በቦታው ተገኝተው ተመልክተዋል። የኔፓል ቱሪዝም መምሪያ ትላንት ባወጣው መረጃ፣ ከ34 አገራት የመጡ 668 ቱሪስቶች ከረቡዕ ጠዋት ጀምሮ የደረሱበት እንዳልታወቀ ገልጿል። ከእነዚህም መካከል ቢያንስ 177 ከህንድ፣ 90 ከአሜሪካ፣ 34 ከአውስትራሊያ፣ 33 ከብሪታንያ እና 25 ከካናዳ የመጡ ናቸው ብሏል። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም በኔፓል ከጠፉት መካከል 100 የቻይና ዜጎች እንደሚገኙበት እወቁልኝ ብሏል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

በትምህርት ዘርፋ ተፅእኖን አሳድረዋል በተባሉ ርእሰ መምህራኖች ላይ እርምጃ ተወሰደ የስልጤ ዞን ትምህርት መምሪያ የተማሪዎችን ዉጤት ለማሻሻል እና የማለፍ ምጣኔን ለማሳደግ ለዘርፉ ማናቆ በሆኑ ጉዳዮ
በትምህርት ዘርፋ ተፅእኖን አሳድረዋል በተባሉ ርእሰ መምህራኖች ላይ እርምጃ ተወሰደ የስልጤ ዞን ትምህርት መምሪያ የተማሪዎችን ዉጤት ለማሻሻል እና የማለፍ ምጣኔን ለማሳደግ ለዘርፉ ማናቆ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ጥናት አድርጎ የመፍትሄ እርምጃዎችን ተግባራዊ ማድረጉን አስታውቋል ። መምሪያዉ ባደረገዉ ጥናት መሠረት የመምህራን የአቅም ማነስ ፣የተነሳሽነት ችግር ፣የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ድክመት እና ሙሉ ጊዜን በትምህርት ቤት አለማዋል ለምሳሌም በግብርና ፣ንግድና ሌሎች ተጨማሪ ሰራዎች ላይ ማዋላቸዉ ለዘርፉ ችግር ሆኖ መቆየቱን የስልጤ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሹክራላ አወል ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ። በዚህም የተነሳ ለትምህርት መስጠት የነበረባቸውን አስፈላጊ ሰዓት በሌሎች ስራዎች ላይ በማሳለፍ በትምህርት ላይ ተፅዕኖ የፈጠሩ 27 ርዕሰ መምህራኖችን ከስራ ማሰናበትን ጨምሮ ሌሎችንም የማስተካከያ እርምጃዎች መዉሰድ ተችሏል ። በተጨማሪም በወላጆች እና በተማሪዎች  በኩል የተስተዋሉ ክፍተቶችን በመለየት መቅረፍ መቻሉም ተገልጿል ። በዚህም የተነሳ የተማሪዎች የ12 ክፍል የብሄራዊ ፈተናን የማለፍ ምጣኔ ከፍ ማድረግ መቻሉ ተጠቁሟል ። በዞኑ በ2016 ዓመት የተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ 3.9 እንደነበር የሚያስታውሱት ኃላፊዉ በ2017 ወደ 5.9 በመቶ እንዲሁም በ2018 ዓ.ም ደግሞ ወደ 11 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ። በመባ ወርቅነህ #ዳጉ_ጆርናል

የታሪኩ ጋንጋሲ አነጋጋሪ መልእክት ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ (ታሪኩ ጋንጋሲ) በአዲስ አበባ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ታፕ ፋይት
የታሪኩ ጋንጋሲ አነጋጋሪ መልእክት ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ (ታሪኩ ጋንጋሲ) በአዲስ አበባ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ታፕ ፋይት ቻምፒዮና (ETFC 002፤ Adwa Fight Night) ዋና ፍልሚያ ጆኒ ጁጁትሱ ሰዶን ማሸነፉን ተከተሎ፣ ታዋቂው ድምፃዊ ታሪቁ ጋንክሲ በማህበራዊ ሚዲያው ያስተላለፈው የትችት መልእክት ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። በሺዎች የሚቆጠሩ ተመልካቾችን በሳበው በዚህ ውድድር ዙሪያ ድምፃዊው «ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ፣ እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ» የሚል ግጥማዊ ቅሬታ ያቀረበ ሲሆን፣ ይኸውም በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ውስጥ እየተስፋፋ ያለውን የፍትህ ማጣት፣ የጦርነት ስቃይ፣ ተቋማዊ የሌብነትና የዘረፋ ወንጀል እንዲሁም የከፋ የኢኮኖሚ ውደቀት ችላ በማለት ህዝቡ ጥልቅ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ውስጥ እያለ በእንደዚህ አይነት የትግል ትዕይንቶች ላይ ትኩረት ማድረጉን ለመኮነን እንደሆነ ተገልጿል። ድምፃዊው ይህን ማህበራዊ ተቃርኖ በማንሳት የሰጠው አስተያየት በበርካቶች ዘንድ ድጋፍና የተለያየ ትችት በማስተናገድ በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ ሰፊ አከራካሪ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመጀመሪያ ጊዜ 39.5 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ ተቋሙ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 96.5 ቢሊዮን ብር ማትረፉን የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመጀመሪያ ጊዜ 39.5 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ ተቋሙ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 96.5 ቢሊዮን ብር ማትረፉን የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። የዘንድሮው ትርፍ ካለፉት ዓመታት አንጻር የ23 በመቶ ልዩነት እንዳለውም ተገልጿል። ተቋሙ አሁን ላይ በጥቅሉ እስከ 9,730 ሜጋ ዋት ያህል የማመንጨት አቅም እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፣ አጠቃላይ የተቋሙ አፈጻጸም 92 በመቶ መድረሱንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል። አሁን ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 585 ቢሊዮን ብር ሀብት እንዳለውና መንግሥት አለኝ ከሚላቸው ተቋማት ግንባር ቀደሙ እንደሆነም ተናግረዋል። በያዝነው ዓመት ያልተሳኩትን ጨምሮ አዳዲስ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በቀጣይ 2019 ዓ.ም እንደሚያከናውንም አገልግሎቱ አስታውቋል። በዚህም 121 ቢሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ 9,770 ሜጋ ዋት ለማመንጨት መታቀዱንም ኢንጂነር አሸብር ተናግረዋል። @Seledadotio @Seledadotio

በኢንዶኔዥያ የተቀሰቀሰውን መንግስታዊ ተቃውሞና ሁከት ተከትሎ በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት ተስተጎጎለ በኢንዶኔዥያ ዋና ከተማ ጃካርታ ተካሂዶ የነበረው ተቃውሞ ወደ ሁከት መቀየሩን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ የትራንስፖርት ባለስልጣናት በዛሬው ዕለት አንዳንድ የባቡር እና የአውቶቡስ መስመሮች አገልግሎታቸውን እንዲያቋርጡ ወይም መስመር እንዲቀይሩ ማድረጋቸውን አስታወቁ። በተለያዩ ቡድኖች አስተባባሪነት ትናንት ሐሙስ ጠዋት በፓርላማ ሕንጻ አቅራቢያ የተካሄደው ተቃውሞ፣ ባለፈው ዓመት ለሁለት ሳምንታት ዘልቆ የነበረውንና ለፕሬዝዳንት ፕራቦዎ ሱቢያንቶ አስተዳደር የመጀመሪያው ፈተና የሆነውን ከባድ ጸረ-መንግሥት ተቃውሞ ዓመት ታሳቢ ያደረገ እንደነበር ተገልጿል። ሰልፈኞቹ በመንግሥት ፖሊሲዎች ላይ ያላቸውን ቅሬታ የገለጹ ሲሆን፣ በሙስና በተጠረጠሩ ባለስልጣናት ላይም ጠንካራ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። ሰልፉ በዕለቱ ምሽቱን መበተኑ ቢገለጽም፣ ጥቁር ሸሚዝ የለበሱ ግለሰቦች ከሰልፉ በኋላ በጎዳናዎች ላይ በመቆየት የፖሊስ ጣቢያና ሁለት ሞተር ሳይክሎችን በእሳት ማቃጠላቸውን፣ መንገድ መዝጋታቸውን እንዲሁም በፖሊስ ላይ ድንጋይና ዱላ መወርወራቸውን የአካባቢው ሚዲያዎች ዘግበዋል። ፖሊስ በበኩሉ ሁከቱን ለመበተን በአስለቃሽ ጭስ እና በከፍተኛ ጉልበት በሚረጭ ውሃ ምላሽ ሰጥቷል። በአመጹ አካባቢ በርካታ የፍንዳታ ድምፆች የተሰሙ ሲሆን፣ የጃካርታ ፖሊስ እስካሁን በይፋ መግለጫ ባያወጣም የፖሊስ ቃል አቀባይ ቡዲ ሄርማንቶ ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን በሰጡት አስተያየት የሁከት ድርጊቶች መከሰታቸውን አረጋግጠዋል። ፖሊስ ሁከት ለማስነሳት ሞክረዋል ያላቸውን 65 ሰዎችን ያሰረ ሲሆን፣ ከአስሪዎቹም ጋር የአየር ሽጉጦች፣ የመገናኛ መሣሪያዎች እና ሞሎቶቭ ኮክቴል ለመሥራት የሚያስችሉ ቁሳቁሶችን መያዙን አስታውቋል። የተቃውሞው መቀስቀስ እ.አ.አ. በ2024 በከፍተኛ ድምፅ ተመርጠው ወደ ሥልጣን የመጡት የቀድሞው ጄኔራል ፕሬዝዳንት ፕራቦዎ ሱቢያንቶ፣ በሕዝብና በባለሃብቶች ዘንድ እየተሸረሸረ የመጣውን እምነት ለመመለስ እየታገሉ ባሉበት አስቸጋሪ ወቅት ላይ የተከሰተ ነው። ቴምፖ በተሰኘው የምርመራ የዜና ድርጅት በቅርቡ በተካሄደ ጥናት የፕራቦዎ የሕዝብ ድጋፍ መጠን ወደ 38 በመቶ ዝቅ ማለቱ ታውቋል። በሁከቱ ምክንያት በዛሬው ዕለት በጃካርታ የመንገደኞች ባቡር እና አውቶቡስ መስመሮች ላይ መስተጓጎል ያጋጠመ ሲሆን፣ በፓርላማው አቅራቢያ ያሉ በርካታ ዋና ዋና ጎዳናዎች መዘጋታቸውን የትራፊክ አስተዳደሩ መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ @Freshmerejaet @Freshmerejaet

በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት መማር ያልቻሉ ወጣቶች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ስልጠና እንዲያገኙ ተደረገ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አጋር የሆነው ፋዌ (FAWE) ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን የሁለተ
+1
በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት መማር ያልቻሉ ወጣቶች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ስልጠና እንዲያገኙ ተደረገ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አጋር የሆነው ፋዌ (FAWE) ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን የሁለተኛ ዙር የትምህርትና ስልጠና ፕሮግራም ተጠቃሚዎችን የተመለከተ ዓመታዊ ጉባኤ አካሂዷል። ጉባኤው ትምህርት ፈልገው አቅም ላጡ ወጣቶች፣ ለሴቶች፣ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለተፈናቃዮች እና ለስደተኞች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ገብተው ስልጠና እንዲያገኙ ማስቻልን ዓላማ ያደረገ ነው፡፡ በዚሁ መሠረት በፕሮግራሙ ከታቀፉት 396 ተማሪዎች መካከል 326ቱ ሴቶች፣ 60ቹ በተለያዩ ምክንያቶች የተፈናቀሉ ሲሆኑ 40 የሚሆኑት ደግሞ የተለያዩ የአካል ጉዳት ያጋጠማቸው ተማሪዎች መሆናቸው ተገልጿል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥልጠናና የተቋማት አቅም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሁዲን አባሞጋ  ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከአለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር በመሆን  እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል FAWE አንዱ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ተማሪዎቹ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ስልጠና አግኝተው የተሻለ የሥራ  ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል  ከፌዴራል እስከ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮዎች የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመው በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ መናገራቸውን ብስራት ሬድዮ ሰምቷል። ተማሪዎቹ   ሥራ ፈጣሪ፣ ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ  ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርግም ጠቁመዋል፡፡ በቅድስት ደጀኔ #ዳጉ_ጆርናል

የጎረቤቷን የ5 ዓመት ልጅ 10 ሜትር ጉድጓድ ውስጥ የጣለችው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን ዋቻ ከተማ ቀበሌ02 ሆስፒታል ሰፈር አካባቢ ነሐሴ 20 ቀን
+1
የጎረቤቷን የ5 ዓመት ልጅ 10 ሜትር ጉድጓድ ውስጥ የጣለችው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን ዋቻ ከተማ ቀበሌ02 ሆስፒታል ሰፈር አካባቢ ነሐሴ 20 ቀን 2018ዓ.ም.ከምሽቱ 2ሰዓት ከ30 አካባቢ የ5 ዓመት ታዳጊን 10 ሜትር የሚረዝም የውሃ ጉድጓድ ውስጥ የጣለችው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሏን ፖሊስ አስታወቀ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ታዳጊዋ ከግለሰቧ ልጆች ጋር እየተጫወተች በነበረበት ወቅት ከወላጆቿ ጋር በነበራት ጥል ምክንያት ከሌሎቹ ልጆች ነጥላ በመውሰድ  10 ሜትር ጥልቀት ወዳለው የውሃ ጉድጓድ ውስጥ ከጣለቻት በኋላ ወደ ቤቷ መግባቷ ተገልጿል። ታዳጊዋ መጥፋቷን የተመለከቱ ወላጆቿና የአካባቢው ነዋሪዎች ፍለጋ ሲያደርጉም  ከጉድጓዱ ውስጥ የታዳጊዋን የለቅሶ ድምፅ በመስማት ማግኘታቸው የተገለጸ ሲሆን ፖሊስም ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር ታዳጊዋን ከ10 ሜትር ጉድጓዱ ውስጥ አውጥተው ወደ ዋቻ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በመውሰድ ህክምና እንድታገኝ አድርገዋል። የ5 ዓመቷን ታዳጊም ከሁለት ሰዓታት የጉድጋድ ቆይታ በኋላ በሕይወት መገኘቷንና እና ከተገኘች በኃላም ህክምና አግኘታ  ከቤተሰቦቿን ጋር መቀላቀሏን ፖሊስ አመልክቷል። ታዳጊዋን በጉድጓድ ውስጥ በመጣል የተጠረጠረችው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተካሄደባት እንደሚገኝ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል

የገቢዎች ሚኒስቴር የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች የ2018 በጀት ዓመት የሂሳብ ሪፖርት ሲያቀርቡ፣ ለእያንዳንዱ የንግድ ስራ መስክ በተናጠል እና ሁሉንም የንግድ መስኮች ያካተተ የተጠቃለለ ሪፖርት ማቅረ
የገቢዎች ሚኒስቴር የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች የ2018 በጀት ዓመት የሂሳብ ሪፖርት ሲያቀርቡ፣ ለእያንዳንዱ የንግድ ስራ መስክ በተናጠል እና ሁሉንም የንግድ መስኮች ያካተተ የተጠቃለለ ሪፖርት ማቅረብ እንዳለባቸው አውቀው ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳሰበ። የገቢዎች ሚኒስቴር፣ ከአንድ በላይ የንግድ መስክ ላይ ለተሰማሩ የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች ለእያንዳንዱ የንግድ ዘርፍ የተለየ የሂሳብ መዝገብ መያዝ እንዳለባቸው አውቀው ዝግጅት እንዲያደርጉ ጠይቋል። ይህ አሰራር ተግባራዊ የሚደረገው በገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 አንቀጽ 86 እና በሠንጠረዥ "ሐ" በተቀመጠው ድንጋጌ መሠረት ነው። @Addis_News @Addis_News

"ከቡርኪና ፋሶ ውጡ ካልሆ ትሞታላችሁ‼️ የቡርኪና ፋሶው መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ከሽብርተኞች ጋር ድርድር አላደርግም አሉ። የቡርኪና ፋሶ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ አገራቸውን እያተራመሱ ካ
"ከቡርኪና ፋሶ ውጡ ካልሆ ትሞታላችሁ‼️ የቡርኪና ፋሶው መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ከሽብርተኞች ጋር ድርድር አላደርግም አሉ። የቡርኪና ፋሶ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ አገራቸውን እያተራመሱ ካሉ ታጣቂ እና አሸባሪ ቡድኖች ጋር ምንም ዓይነት ድርድር አናደርግም ብለዋል። ከቡድኖቹ ጋር ምንም ዓይነት ድርድር የማድረግ ፍላጎት እንደሌላቸውና የማያወላውል ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ይፋ አድርገዋል። ካፒቴን ትራውሬ ለታጣቂ ቡድኖቹ ግልጽና ወሳኝ የሆነ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ከቡርኪና ፋሶ ውጡ ካልሆነ ትሞታላችሁ ብለዋል። መንግስት የአገሪቱን አንድ ስንዝር መሬት እንኳ ለሽብርተኞች አሳልፎ እንደማይሰጥና ሀገሪቷ ሉአላዊነቷ እስኪረጋገጥ ድረስ ውጊያው እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የሀገሪቱ ሰላም የሚረጋገጠው በድርድር ሳይሆን በመከላከያ ሰራዊት ጥንካሬ ነው ሲሉ ጠንካራ አቋማቸውን ገልጸዋል። @Addis_News @Addis_News

በኢሮብ ወረዳ 35 ሺህ ህዝብ ለከባድ ድርቅ ተጋልጧል። በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የሚገኘው ኢሮብ ወረዳ ከባድ ድርቅ እየተጋፈጠ ሲሆን፤ በአካባቢው የሚኖሩ 35 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ለድርቅ አደጋ መ
+2
በኢሮብ ወረዳ 35 ሺህ ህዝብ ለከባድ ድርቅ ተጋልጧል። በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የሚገኘው ኢሮብ ወረዳ ከባድ ድርቅ እየተጋፈጠ ሲሆን፤ በአካባቢው የሚኖሩ 35 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ለድርቅ አደጋ መጋለጣቸው ተገልጿል። በወረዳው የክረምት ዝናብ በበቂ ሁኔታ ባለመዝነቡ የውሃ ጉድጓዶች መድረቃቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በውሃ እጥረቱም የቤት እንስሳት መሞት መጀመራቸውን አስረድተዋል። በወረዳው የሚገኙ ስምንት ቀበሌዎች በከፍተኛ ተራራና ተዳፋት አካባቢዎች መሆናቸው የተጀመረውን የእርዳታ ማዳረስ ስራ ፈታኝ እንዳደረገው ተጠቁሟል። የአካባቢው አርሶ አደሮች እንደሚሉት፣ ከዚህ በፊት እንደ ዘንድሮ ያለ ከባድ ድርቅ አጋጥሟቸው አያውቅም። የዝናብ እጥረቱ በማሳ ላይ የተዘራው እህል እንዲደርቅ ከማድረጉም በላይ በክረምት ዝናብ ይሞሉ የነበሩ የውሃ ጉድጓዶች እንዲደርቁ አድርጓል። የኢሮብ አካባቢ የኢሮብ ብሄረሰብ የሚኖርበት ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወረዳዎች አንዱ ነው።  አካባቢው በ2013 ዓ.ም በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ ጥቃት የደረሰበት ሲሆን እስካሁንም አንዳንድ የቀበሌ ገበሬ ማህበራት በኤርትራ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ይገኛሉ። Via_tikvah @Addis_News @Addis_News

በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በቴሌ ብር መተግበሪያ የ4 ነጥብ 19 ትሪሊየን ብር የዲጅታል ግብይት መፈጸሙን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ። ኢንቨስትመንት ሆልዲንግሱ ይሄንን ያለ
በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በቴሌ ብር መተግበሪያ የ4 ነጥብ 19 ትሪሊየን ብር የዲጅታል ግብይት መፈጸሙን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ። ኢንቨስትመንት ሆልዲንግሱ ይሄንን ያለው በስሩ የሚገኙ ተቋማት አመታዊ አፈጻጸም ግምገማ ለ3ኛ ቀን መቀጠሉን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ላይ ነው። የቴሌ ብር ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ60 ሚሊዮን በላይ መድረሱን ያነሳው ተቋሙ ቴሌ ብር በ2018 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 83 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱንም ገልጿል። በተጨማሪም በበጀት አመቱ የኢትዮ ቴሌኮም ገቢ በ33 ነጥብ 2 በመቶ ማደጉም ነው የተጠቀሰው። @Addis_News @Addis_News

የዓለም ጤና ድርጅት ኡጋንዳ ከኢቦላ ነፃ መሆኗን አረጋገጠ ኡጋንዳ የመጨረሻው የተረጋገጠ ታካሚ ከሆስፒታል በወጣ በ42ኛው ቀን፣ ባለፈው ወር ቫይረሱ በይፋ መጥፋቱን ገልጻ ነበር። የዓለም ጤና ድርጅት
የዓለም ጤና ድርጅት ኡጋንዳ ከኢቦላ ነፃ መሆኗን አረጋገጠ ኡጋንዳ የመጨረሻው የተረጋገጠ ታካሚ ከሆስፒታል በወጣ በ42ኛው ቀን፣ ባለፈው ወር ቫይረሱ በይፋ መጥፋቱን ገልጻ ነበር። የዓለም ጤና ድርጅትም ምንም አይነት የቀረ የቫይረስ ስርጭት ሰንሰለት አለመኖሩን ለማረጋገጥ ሁኔታውን ሲከታተል ቆይቷል። ጎረቤት ኮንጎ ቫይረሱ መከሰቱን ካወጀችበት ከግንቦት 7 ጀምሮ ኡጋንዳ በአጠቃላይ 20 የቫይረሱ ተጠቂዎችን አረጋግጣ ነበር። በምስራቅ ኮንጎ ያለው ሁኔታ በጣም የተለየ ነው፤ ቫይረሱ የጤና ባለሙያዎችን በከፍተኛ ሁኔታ በሚያሰጋ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል። በስድስት ግዛቶች ውስጥ ከ2 ሺህ በላይ ሞቶችን ጨምሮ ከ4 ሺህ 5መቶ በላይ የቫይረሱ ተጠቂዎች ተመዝግበዋል። ባለፈው ሳምንት የዓለም ጤና ድርጅት ለጎረቤት ሀገራት፣ በተለይም ከኮንጎ ጋር የየብስ ድንበር ለሚጋሩት፣ ስጋቱ አሁንም ከፍተኛ መሆኑን ገልጾ አዳዲስ ጊዜያዊ ምክረ ሃሳቦችን አቅርቧል። እስከዳር ግርማ @Ethionews433 @Ethionews433

ከ70 በላይ ለሚሆኑ ደን ጠባቂ ሬንጀሮች የዕዉቅና ስጦታ ተበረከተ ቴምር ፕሮፐርቲስ 75 ለሚጠጉ የደን ጠባቂ ሬንጀሮችና "Plogging Ethiopia" የተባለውን ተቋም በመመስረት ላለፉት 6 ዓመታት
+2
ከ70 በላይ ለሚሆኑ ደን ጠባቂ ሬንጀሮች የዕዉቅና ስጦታ ተበረከተ ቴምር ፕሮፐርቲስ 75 ለሚጠጉ የደን ጠባቂ ሬንጀሮችና "Plogging Ethiopia" የተባለውን ተቋም በመመስረት ላለፉት 6 ዓመታት በበጎ ፈቃደኝነት የወዳደቁ ፕላስቲኮችንና ቆሻሻዎችን በመሰብሰብ ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ለፕሮፌሰር ፍሬው ከፍያለው ልዩ ዕውቅናና ስጦታ ሰጥቷል። ቴምር ፕሮፐርቲስ ለአካባቢ ጥበቃ የማይተካ አስተዋፅኦ ለሚያበረክቱ የጉለሌ እፅዋት ማዕከል ሬንጀሮች ዕውቅናና ስጦታ ሰጥቷል። የጉለሌ እዕዋት ማዕከል እዕዋትን በመሰብሰብ፤ በማሰራጨትና ወደ ተፈጥሯዊ መኖሪያቸው እንዲመለሱ በሚደረጉ የምርምርና የጥበቃ ሥራዎች ወሳኝ ሚና እንደሚሰጥ ተነግሯል። በማዕከሉ ሥር የሚገኙ ሬንጀሮችም የደን ሀብትን፣ ብዝሃ ሕይወትን የሥነ-ምህዳር ሚዛንን ለመጠበቅ በየዕለቱ ከፍተኛ ኃላፊነት እንደሚወጡ ተገልጿል፡፡ ዕውቅናዉ ለአቶ ፍሬው የተሰጠ ግለሰባዊ ሽልማት ብቻ ሳይሆን፤ ለተፈጥሮና ለአካባቢ ጥቢቃ በተግባር ለሚተጉ ሁሉ የሚሰጥ አድናቆት፤ ማበረታቻና የአካባቢ ጥቢቃ ተሳትፎን ለማጠናከር የታለመ መልዕከት ነው ተብሏል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

አሜሪካ በአውሮፓ ያላትን ወታደራዊ ኃይል ልትቀንስ እንደምትችል ተገለፀ ፔንታጎን በአውሮፓ የተሰማሩትን ወደ 80 ሺህ የሚጠጉ የአሜሪካ ወታደሮች ቁጥርና አቀማመጥ እየገመገመ ሲሆን፣ ለመከላከያ ሚኒስት
አሜሪካ በአውሮፓ ያላትን ወታደራዊ ኃይል ልትቀንስ እንደምትችል ተገለፀ ፔንታጎን በአውሮፓ የተሰማሩትን ወደ 80 ሺህ የሚጠጉ የአሜሪካ ወታደሮች ቁጥርና አቀማመጥ እየገመገመ ሲሆን፣ ለመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴት ቢያንስ አራት የተለያዩ የጦር ኃይል አማራጮችን ለማቅረብ እየሠራ ይገኛል፡፡ እነዚህ አማራጮች የወታደሮች ቁጥር፣ የሚቀመጡበት ቦታ፣ የመዛወሪያ ፍጥነትና የሚያስከፍለውን ወጪ ያካትታሉ። አማራጮቹም እስከ ኖቬምበር 6 ድረስ ለሄግሴት እንዲቀርቡ ታቅዷል። የኔቶ አጋሮች ግን ግምገማው በአውሮፓ ያለውን የአሜሪካ ወታደራዊ ተሳትፎ በእጅጉ ሊቀንስ ይችላል በሚል ስጋት ላይ ይገኛሉ፡፡ የትራምፕ አስተዳደርም በበኩሉ አውሮፓውያን የኔቶ አባላት ለራሳቸው ደህንነት የበለጠ ኃላፊነት እንዲወስዱ እየጠየቀ ነው። በተለይም በኢራን ጦርነት ወቅት አንዳንድ የኔቶ አገራት ለአሜሪካ የጦር ማረፊያና የአየር ክልል መጠቀሚያ ፈቃድ በበቂ ፍጥነት አልሰጡም በሚል ትራምፕ ቅሬታ አቅርበዋል። ፔንታጎን የጀመረው ግምገማ በዲሴምበር እንዲጠናቀቅ ቢጠበቅም፣ ዋናው ጥያቄ አሜሪካ በአውሮፓ ያላትን ወታደራዊ ኃይል በምን ያህል ትቀንሳለች፣ እና የኔቶ አጋሮቿስ የሚፈጠረውን ክፍተት እንዴት ይሞላሉ? የሚለው ሆኗል። በቤዛዊት አራጌ #ዳጉ_ጆርናል

ሜታ በማህበራዊ ሚዲያ በወጣቶች ላይ ከደረሰዉ ጉዳት ጋር ተያይዞ ከአሜሪካ ክፍለ ሀገራት ጋር የ17 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሰ ሜታ ፕላትፎርምስ ፌስቡክን እና ኢንስታግራምን ሆን ብሎ ወጣቶች ለምርቶቹ ሱስ እንዲያዙ በሚያደርግ መልኩ በመቅረፅ እና ህዝቡን በማታለል በ47 የአሜሪካ ክፍለ ሀገራት የቀረበበትን ክስ ለመጨረስ የ17 ቢሊዮን ዶላር ክፍያ ለመፈፀም መስማማቱን የክፍለ ሀገራቱ አቃቢያነ ህግ አስታውቀዋል። ኩባንያው ከስምምነቱ አካል አድርጎ የህፃናትን ደህንነት የሚጠብቁ እርምጃዎችን በስራ ላይ ለማዋል ተስማምቷል። ሜታ በወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያ ሱስ ዙሪያ የተመሰረተበትን ታሪካዊ ክስ ለማቆም እና በ47 ክፍለ ሀገራት የቀረቡበትን አቤቱታዎች ለመጨረስ 17 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል በፌስቡክ እና ኢንስታግራም ገጾቹ ላይ የህፃናት ደህንነት ማረጋገጫዎችን ለማካተት መስማማቱ ተገልጿል። ካሊፎርኒያ፣ ኮሎራዶ፣ ኬንታኪ እና ኒው ጀርሲ እ.ኤ.አ. በ2023 በቴክኖሎጂ ኩባንያው ላይ ክስ ካቀረቡት 29 ክፍለ ሀገራት መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን፣ አዲሱ ስምምነት የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ማርክ ዙከርበርግ በካሊፎርኒያ ፌደራል ፍርድ ቤት በዳኞች ፊት ቀርበው ምስክርነት ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቅ የነበረውን የፍርድ ሂደት አሳጥሮታል። የቨርጂንያ ጠቅላይ አቃቢ ህግ ጄይ ጆንስ ባወጡት መግለጫ፣ ስምምነቱ በቨርጂንያ ብቻ 353 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ሲሆን፣ በክፍለ ሀገሪቱ የደንበኞች መብት ጥበቃ ታሪክ ውስጥ ከሁሉም የበለጠው እንደሆነ ገልፀዋል። ለዓመታት ሜታ በወጣቶች የአእምሮ ጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱ ሱስ አጋላጭ እና ጎጂ የሆኑ የንድፍ ባህሪያትን አስመልክቶ ህዝቡን ሆን ብሎ ሲያታልል ቆይቷል ብለዋል ጆንስ። ይህ ስምምነት እነዚህን አደገኛ አሰራሮች የሚያስቆም እና ህፃናትን ከኦንላይን ጉዳት የሚጠብቅ ትርጉም ያለው እፎይታን የሚያስገኝ ነው ሲሉ አክለዋል። ሜታ ለተጠየቀው አስተያየት ወዲያውኑ ምላሽ አልሰጠም። ይህ የ17 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት፣ ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2025 ካስመዘገበው የ201 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ድርሻ ያለው ነው። ክሱ ሜታ፣ ህፃናትን ለገጾቹ ሱስ የሚያስይዙ ባህሪያትን ሆን ብሎ በመቅረፅ እና እነዚህን ከህዝብ በመሸሸግ ለወጣቶች የአእምሮ ጤና ቀውስ አስተዋጽኦ አድርጓል በማለት ይከሳል። በተጨማሪም ሜታ ያለወላጆች ፈቃድ ከ13 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትን መረጃ ዘወትር በመሰብሰብ የፌደራል ህጎችን ጥሷል የሚል ክስም ቀርቦበታል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

በኔፓል በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከ8መቶ በላይ ሰዎች የደረሱበት እንዳልታወቀ ተገለጸ፡፡ በኔፓል እና ቲቤት ድንበር አካባቢ በተከሰተው በዚህ አደጋ፣ ከፍተኛ የሆነ የጭቃ እና የውሃ ማዕበል መኖሪያ ቤቶ
+2
በኔፓል በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከ8መቶ በላይ ሰዎች  የደረሱበት እንዳልታወቀ ተገለጸ፡፡ በኔፓል እና ቲቤት ድንበር አካባቢ በተከሰተው በዚህ አደጋ፣ ከፍተኛ የሆነ የጭቃ እና የውሃ ማዕበል መኖሪያ ቤቶችን ደምስሷል፤ መንገዶችን እና ድልድዮችንም ጠራርጎ ወስዷል። በአሁኑ ወቅት የህይወት አድን ቡድኖች የተረፉ ሰዎችን ለማፈላለግ ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ እስከ አሁን ባለው መረጃ በኔፓል ከ8መቶ  በላይ ሰዎች የገቡበት ያልታወቀ ሲሆን፤ የ1መቶ77 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል። ሆኖም በአካባቢው ላይ እየዘነበ ባለው ሀይለኛ ዝናብ እና የአካባቢው አስቸጋሪ መልክአ-ምድር ምክንያት  የፍለጋ ስራው ፈታኝ  ሆኗል። በቲቤት በኩል ደግሞ የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን፤ የ5መቶ58 ሰዎች ደብዛ ጠፍቷል። እስካሁን ድረስ በሁለቱም ድንበሮች በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎች ያሉበት አልታወቀም። የኔፓል ባለስልጣናት እንዳሳወቁት ከሆነ ከጠፉት መካከል 1መቶ78 የህንድ፣ 1መቶ27 የኔፓል፣ 65 የአሜሪካ፣ 35 የአውስትራሊያ እና 33 የብሪታንያ ቱሪስቶች ይገኙበታል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር ቅጣት ሊጥል ነዉ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር ቅጣት ሊጥል ነዉ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር ቅጣት ሊጥል ነዉ የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ከጣቢያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት እየተስተዋለ ያለውን ያልተገባ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪና የመስመር ማሳጠር ችግሮችን ለመቅረፍ የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን አስታውቋል። ቢሮው የህዝብ ትራንስፖርት ታሪፍን በማጥናትና በማስወሰን ረገድ ትልቅ ሃላፊነት እንዳለበት የገለጹት የቢሮው የስራ ሃላፊ፣ የታሪፍ ተግባራዊነቱንም በቅርበት እየተቆጣጠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። @Seledadotio @Seledadotio

ሕንድ የጦር መሳሪያ ምስጢሯን ለግል ኩባንያዎች አሳልፋ ሰጠች ‼ ሕንድ የሀገር ውስጥ የጦር መከላከያ ምርቷንና የቴክኖሎጂ አቅሟን ሙሉ በሙሉ በራስ ለማስቻል ያለመ ታሪካዊ ፖሊሲ ይፋ አድርጋለች። የመ
+3
ሕንድ የጦር መሳሪያ ምስጢሯን ለግል ኩባንያዎች አሳልፋ ሰጠች ‼   ሕንድ የሀገር ውስጥ የጦር መከላከያ ምርቷንና የቴክኖሎጂ አቅሟን ሙሉ በሙሉ በራስ ለማስቻል ያለመ ታሪካዊ ፖሊሲ ይፋ አድርጋለች።  የመከላከያ ሚኒስትሩ ራጅናት ሲንግ የሀገሪቱ የጦር ምርምር ተቋም (DRDO) ያበለጸጋቸውን የላቁ ባህላዊ የሚሳይል ቴክኖሎጂዎች፣ የሴንሰር አሰራሮችና ማምረቻ ምስጢራት ለሀገር ውስጥ የግል ኩባንያዎች እንዲተላለፉ በይፋ ፈቅደዋል።  ይህ አዲስ የቴክኖሎጂ ሽግግር ቀደም ሲል በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉ ተቋማት ብቻ ተወሰኖ የነበረውን የሚሳይል ማምረት ሂደት ሙሉ በሙሉ በመቀየር የግል ዘርፉን በዋናነት የሚያሳትፍበትን መንገድ ከፍቷል።   በዚህ መርሃ ግብር መሰረት እንደ አካሽ (Akash)፣ አስትራ (Astra)፣ ሩድራም (Rudram) እና ናግ (Nag) ያሉ የአየር ላይ፣ የመሬት ላይ እና የፀረ-ታንክ የሚሳይል ስርአቶች በግል ኩባንያዎች በከፍተኛ መጠን እንዲመረቱ ይደረጋል።  ሆኖም የሀገሪቱ የኑክሌር ስትራቴጂካዊ ሚሳይሎች በዚህ ስምምነት ውስጥ አልተካተቱም።   ውሳኔው ሕንድ ከውጭ ሀገራት በቢሊዮን ዶላሮች የሚገዙ የጦር መሳሪያዎችን ፍላጎት በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት፣ የጦር ኃይሏን ፍላጎት በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማሟላትና የትናንሽና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን የቴክኖሎጂ አቅም ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ውድ ስልክ በህዝብ በጀት ገዝተዋል የተባሉ 3 ከፍተኛ አመራሮች ከኃላፊነት ታገዱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ በእናቶችና ሕፃናት ጤና ፕሮግራም በጀት ውድ ስልክ ተገዝቷል በሚል በ
ውድ ስልክ በህዝብ በጀት ገዝተዋል የተባሉ 3 ከፍተኛ አመራሮች ከኃላፊነት ታገዱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ በእናቶችና ሕፃናት ጤና ፕሮግራም በጀት ውድ ስልክ ተገዝቷል በሚል በማህበራዊ ሚዲያና በመገናኛ ብዙሃን በተሰራጨው መረጃ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥቷል።  መንግስት የህዝብን ሀብት በአግባቡ እና ለታለመለት ዓላማ ብቻ መዋሉን ለማረጋገጥ ባደረገው ማጣራት፣ ጉዳዩን በጥልቀት የሚያጣሩ የፍትህ፣ የኦዲት እና የፀረ-ሙስና አካላትን አደራጅቶ ወደ ምርመራ ስራ መግባቱን አስታውቋል። በጉዳዩ የተጠረጠሩ ሦስት አመራሮችም ከዛሬ ጀምሮ ከኃላፊነታቸው እንዲታገዱ ተደርጓል።  የክልሉ መንግስት ማጣራቱ እንደተጠናቀቀ የህዝብን ሀብት ባባከኑ አካላት ላይ የማያዳግም ህጋዊ፣ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጾ፣ ህዝቡ የብልሹ አሰራር ጥቆማዎችን በመስጠትና ከጎኑ በመቆም ያደረገውን @Freshmerejaet @Freshmerejaet

ይህ ታሪክ የደግነት፣ የፍቅርናየሰብአዊነት ታላቅ ምሳሌ ነው አንድ ሚና የተባለ ግብፃዊ ክርስቲያን ወጣት በቁርአን ጥያቄና መልስ ውድድር አሸንፎ ያገኘውን የዑምራ (የሐጅ) ጉዞ ሽልማት ለሙስሊም ጎረቤ
ይህ ታሪክ የደግነት፣ የፍቅርናየሰብአዊነት ታላቅ ምሳሌ ነው አንድ ሚና የተባለ ግብፃዊ ክርስቲያን ወጣት በቁርአን ጥያቄና መልስ ውድድር አሸንፎ ያገኘውን የዑምራ (የሐጅ) ጉዞ ሽልማት ለሙስሊም ጎረቤቱ ለእማ አሊ በመስጠት የብዙዎችን ልብ ነክቷል። እማ አሊ ወደ ቅድስት ሀገር መካ ሄደው ለመጎብኘት ለብዙ ዓመታት ይመኙ ነበር፤ ጉዞውን ለማሸነፍም ተደጋጋሚ ሙከራዎችን አድርገዋል። ይህ ህልማቸው ምን ያህል ትልቅ እንደሆነ የተረዳው ሚና፣ ለእርሳቸው ሲል በውድድሩ ላይ ተሳትፎ  አሸነፈ። ሽልማቱን ባገኘ ጊዜም የእማ አሊን የረጅም ጊዜ ህልም እውን ለማድረግ ሽልማቱን አበረከተላቸው። ከ20 ዓመታት በላይ በጎረቤትነት አብረው የኖሩት ሚና፣ እማ አሊን እንደራሱ ታላቅ እህት አድርጎ እንደሚያያቸው ይናገራል። ይህ አነቃቂ ድርጊት ደግነትና ሰብአዊነት ከሃይማኖት ልዩነት በላይ ሰዎችን እርስ በእርስ ማቀራረብ እንደሚችሉ የሚያሳይ ውብ ማስታወሻ ነው። @Seledadotio @Seledadotio