ru
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

Открыть в Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Fresh መረጃ | FreshNews

Канал Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 55 693 подписчиков, занимая 3 021 место в категории Образование и 580 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 55 693 подписчиков.

Согласно последним данным от 30 августа, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -697, а за последние 24 часа — -57, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 3.70%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 3.06% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 2 063 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 705 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 31 августа, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.

55 693
Подписчики
-5724 часа
+967 дней
-69730 день
Архив постов
በሰሜን ሸዋ ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ሥር የሚገኘው ተሐድሶ አምባ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ታራሚ ተፈታኞች መካከል 91% ታራሚዎችን አሳልፏል። 👏👏
በሰሜን ሸዋ ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ሥር የሚገኘው ተሐድሶ አምባ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ታራሚ ተፈታኞች መካከል 91% ታራሚዎችን አሳልፏል። 👏👏 ትምህርት ቤቱ ላለፉት አራት ዓመታት አንድም ተማሪ ማሳለፍ ያልቻለ ቢሆንም፣ ዘንድሮ 91 በመቶ ታራሚ ተፈታኞቹን ማሳለፍ መቻሉ ተገልጿል። ታራሚ ተፈታኞቹ ጥሩ ውጤት እንዲያመጡ የማጠናከሪያ ትምህርት ይሰጣቸው እንደነበር የሰሜን ሸዋ ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር የቻለሰው አሰፋ ለአሚኮ ተናግረዋል። @Seledadotio @Seledadotio

ቼልሲ ሁለተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ በ2ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ስታምፎርድ ብሪጅ ላይ ብራይተንን ያስተናገደው ቼልሲ 4 ለ 3 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ሮሚዮ ላቪያ ለቼልሲ የመጀመሪያው
+2
ቼልሲ ሁለተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ በ2ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ስታምፎርድ ብሪጅ ላይ ብራይተንን ያስተናገደው ቼልሲ 4 ለ 3 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ሮሚዮ ላቪያ ለቼልሲ የመጀመሪያውን ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ፣ ፔድሮ ኔቶ እና ጆዋዎ ፔድሮ ተጨማሪ ግብ አስቆጥረው ቼልሲ 3 ለ 0 እንዲመራ አስችለው ነበር። ሆኖም ማሊክ ጁኒየር ለብራይተን አስቆጥሮ የመጀመሪያው አጋማሽ በቼልሲ 3 ለ 1 መሪነት ተጠናቅቋል። በሁለተኛው አጋማሽ ጆዋዎ ፔድሯ በራሱ መረብ ላይ ያስቆጠራት ግብ ውጤቱን ወደ 3 ለ 2 ብታጠብም፣ ኮል ፓልመር ተጨማሪ ግብ አስቆጥሮ ቼልሲን 4 ለ 2 መሪ አድርጓል።  በጭማሪ ሰዓት ፓስካል ግሮስ ያስቆጠራት ግብም ብራይተንን ከሽንፈት አልታደገችም።  ቼልሲ በ3ኛው ሳምንት የሊጉ መርሐ-ግብር በቀጣይ ሳምንት እሁድ ሻምፒዮኑን አርሰናል በኢሚሬትስ ይገጥማል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የውጭ ሀገር መንጃ ፈቃድ ወደ ሀገር ውስጥ ለመቀየር የሚያሥፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች ምንድን ናቸው? ሙሉ መረጃው ከላይ ተያይዟል። @Seledadotio @Seledadotio
+1
የውጭ ሀገር መንጃ ፈቃድ ወደ ሀገር ውስጥ ለመቀየር የሚያሥፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች ምንድን ናቸው? ሙሉ መረጃው ከላይ ተያይዟል። @Seledadotio @Seledadotio

ሴዶ ቀጣይ በ ሩጫ ጠብቁኝ እያለ ይገኛል 😂😂😂 🚀 Downloaded with @VidDownloaderProBot https://t.me/+s9JcxTA5tA1hYTRk https://t.me/+s9JcxTA5tA1hYTRk

ከ48.1 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን የካፒታል በጀት የተገነባው ድልድይ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ። በደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ ለዘመናት የነበረውን የትራንስፖርት እንግልት የሚቀርፍና በርካታ ቀበሌዎ
ከ48.1 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን የካፒታል በጀት የተገነባው ድልድይ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ። በደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ ለዘመናት የነበረውን የትራንስፖርት እንግልት የሚቀርፍና በርካታ ቀበሌዎችን እርስ በእርስ የሚያስተሳስር የ48 ሜትር ርዝመት ያለው የሳልሜኔ ወንዝ የኮንክሬት ድልድይ ግንባታ በሙሉ ጥራትና በፍጥነት መጠናቀቁ ተበሰረ። የአማራ ክልል መንግስት በመደበው ከ48.1 ሚሊዮን ብር በላይ የካፒታል በጀት የተገነባው ይህ መሰረተ ልማት፣ አልብኮ ከተማን ከደጋጋ እና ነጢ ቀጠናዎች ጋር በማገናኘት የ9 ቀበሌዎች ነዋሪዎችን የቀን ተቀን እንቅስቃሴ የሚያቃልል ሆኗል። የድልድዩ መጠናቀቅ ለአካባቢው ያመጣቸውን ዋና ዋና ጥቅሞች በጥቅሉ ሲቃኙ፦ • በአካባቢው የሚመረቱ የግብርና ምርቶች ወደ ገበያ የሚቀርቡበትን መንገድ ከማስፋቱ በላይ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ያጠናክራል። • በየዓመቱ ታላቁ የመውሊድ በዓል በድምቀት የሚከበርበትን ታሪካዊውን የጀማል ንጉስ መስጅድ ለመጎብኘት ለሚመጡ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር እንግዶች ምቹ የትራንስፖርት አማራጭ ይፈጥራል። • የወረዳው መዲና ለሆነችው አልብኮ ከተማ ተጨማሪ ውበት በመስጠት የኢንቨስትመንትና የከተማዋን ፈጣን እድገት ያፋጥናል። ለዚህ ፕሮጀክት ስኬታማነት የዞኑና የወረዳው አስተዳደር አካላት ላደረጉት የቅርብ ክትትል፣ ስራውን በጥራት ላጠናቀቀው የወጣት ምሩቃን ኢንተርፕራይዝ ስራ ተቋራጭ እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ ላሳየው ያልተቋረጠ ትብብር ከፍተኛ ምስጋና ተቸርቷል። ©️ደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ @Seledadotio @Seledadotio

የኢሕአፓ አመራርና አባል ተጨማሪ ምስክር እንዲያቀርቡ ለቀጣይ ሳምንት ሐሙስ ቀጠሮ ተሰጣቸው ተጠርጣሪዎቹ ተጨማሪ ምስክር እንዲያቀርቡ በማለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለነሐሴ  28 ቀጠሮ መስጠቱን ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ተናገሩ። በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩት፤ የኢሕአፓ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው  ይስሐቅ ወልዳይ፣ የፓርቲው አባል አበበ አካሉ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ በዛሬው ዕለት  በከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው እንደነበር ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። የከፍተኛ  ፍርድ ቤት ዛሬ ባስቻለው ችሎት ተከሳሾቹ  የፌደራል ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን ማጠናቀቁን እና የቴክኒክና የፎረንሲክ መረጃዎች በቂ ስለሆኑ የፌደራል ፖሊስም መረጃዎችን ወደ ማጠናቀቁ  እንደደረሠ አሰረድቷል። ነገር ግን ተከሳሾቹ ያቀረቧቸው ምስክሮች በቁጥር ሁለት ብቻ  በመሆናቸው ፍርድ ቤቱ ለመጨረሻ ጊዜ በሚል ለቀጣይ ሳምንት ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ እንደተሠጣቸው ጠበቃ ሰለሞን አስረድተዋል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

የሱዳን ጦር ሠራዊት በምዕራብ ኢትዮጵያ የድንበር ጥቃት እየፈፀመ ነው - ጌታቸው ረዳ የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ጌታቸው ረዳ፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት በምዕራብ ኢትዮጵያ
የሱዳን ጦር ሠራዊት በምዕራብ ኢትዮጵያ የድንበር ጥቃት እየፈፀመ ነው - ጌታቸው ረዳ የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ጌታቸው ረዳ፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት በምዕራብ ኢትዮጵያ የድንበር አካባቢዎችንና መንደሮችን በከባድ መሳሪያ በመደብደብ ጉዳት እያደረሠ ይገኛል በማለት ለአልጀዚራ በሠጡት ቃል ከሰሱ። ጌታቸው፣ የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች ይረዳል በማለት ጭምር መወንጀላቸውን ዜና አውታሩ ማምሻውን ዘግቧል። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ከኢትዮጵያ ግዛት እየተነሳ በሱዳን ጦር ሠራዊት ላይ ጥቃት ይፈጽማል የሚለውን የሱዳን ባለሥልጣናት ውንጀላ ያስተባበሉት ጌታቸው፣ ኢትዮጵያ የሱዳንን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት እንደምታከብር ተናግረዋል ተብሏል። ሱዳን ጦሯን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጋር ወደሚዋሠነው ብሉናይል ግዛት ደማዚን ከተማ አካባቢ በብዛት እያንቀሳቀሰች መኾኗንም ዘገባው የሱዳን ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

“የድካሜን ፍሬና ውጤት በማስመዝገቤ ደስተኛ ነኝ”- ተማሪ ሮቤል ጌታቸው | ተማሪ ሮቤል ጌታቸው ይባላል። በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስ 590.08 ውጤት አምጥቷል። ሆ
+1
“የድካሜን ፍሬና ውጤት በማስመዝገቤ ደስተኛ ነኝ”- ተማሪ ሮቤል ጌታቸው | ተማሪ ሮቤል ጌታቸው ይባላል። በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስ 590.08 ውጤት አምጥቷል። ሆሳዕና ከተማ ሊች ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት ትምህርቱን ተከታትሏል። 2ኛውን ከፍተኛ ውጤትም አሰመዝግቧል። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ሀድያ ዞን፣ ሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የሊች ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ሮቤል ጌታቸው ለጋዜጣ ፕላስ በሰጠው አስተያየት፤ የድካሜን ፍሬና ውጤት በማስመዝገቤ ደስተኛ ነኝ ብሏል፡፡ ከትምህርት ዝግጅቱና ከጥናት ስልቱ ጋር በተያያዘ በሰጠው አስተያየት፣ በጭንቀትና በረጅም ሰዓታት ጥናት ከመወጠር ይልቅ ነፃ በሆነ አእምሮ በትኩረት ማጥናት ውጤታማ እንደሚያደርግ ተናግሯል። በቀን ውስጥ 4 ሰዓት ትኩረቱን ሰጥቶ እንደሚያነብም ገልጿል። በተለይ ለፈተና ብዙ ጊዜ መጨናነቅ ይታያል፤ በጭንቀት በጣም ብዙ ሰዓት ከማንበብ ይልቅ በተረጋጋ ሁኔታ የተመጠነ ሰዓት ወስዶ ማንበብ አዋጪ መሆኑን ይመሰክራል፡፡ ከአንደኛ ደረጃ ጀምሬ ሳነብ ማስታወሻ የመያዝ ልምድ ነበረኝ የሚለው ተማሪ ሮቤል፤ ቤተ መጻሕፍትም ሆነ፣ በግሌ በማነብበት ጊዜ ማስታወሻ እይዛለሁ፣ ጥያቄዎችንም እመዘግባለሁ፣ እያነበብኩ ጥያቄ እየሰራሁ የተሳሳትኩትን እየመዘገብኩ ጉድለቶችን እየሞላሁ የማጥናት ልምዴድ አለኝ ብሏል፡፡ ሮቤል እንደ ባዮሎጂ ያሉ ትምህርቶችን ለመረዳት የቪዲዮ አኒሜሽኖችን በመጠቀም ምስላዊ ትምህርቶችን መከታተሉ ከፍተኛ እገዛ እንዳደረገለት የገለፀው ተማሪ ሮቤል በባለፉት ዓመታት የወጡ የፈተና ጥያቄዎችን በማጥትና ተግባራዊ ልምምድ በማድረጉና በዚህ ልክ መዘጋጀቱም የላቀ ውጤት እንዲያስመዘግብ እንደረዳው ገልጿል። ከሁሉም በላይ ህልም ሊኖረን ይገባል የሚለው ሮቤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሁለተኛ ውጤት ይመጣል ብዬ ባልጠብቅም፣ ጥሩ ውጤት እንደሚመጣ እርግጠኛ ነበርኩኝ ይላል። ለዚህ ስኬት መምህራን ከሚሰጡት የመማር ማስተማር ስራ በላፈ፤ "The Secret" የተሰኘው የኦንላይን ማስተማሪያ ተቋም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጎለታል። “ከፍተኛውን ውጤት ካለማችሁ፣ መካከለኛውን ታገኛላችሁ፤ መካከለኛውን ካለማችሁ ደግሞ ዝቅተኛውን፤ ዝቅተኛውን ካለማችሁ ደግሞ ምንም አታገኙም” የሚለው የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ምክር ለዚህ ውጤት መመዝገብ አስተዋጽኦ ጉልህ መሆኑን አንስቷል። ለቴክኖሎጂና ፊዚክስ በጣም ልዩ ፍቅር እንዳለው የሚናገረው ሮቤል፤ አብራሪ የመሆን የልጅነት ሕልሙን ለማሳካት እንደሚሰራ ገልጿል። በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ኢንጅነሪንግና መሰል የቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይም በመሰማራት ለሀገሩ አንድ ነገር አበርክቶ የማለፍ ህልም እንዳለው ተናግሯል። ለየትኛውም ትምህርት ቤት ጥሩ ውጤት ማምጣት ትልቁ ሚና የመምህር ነው የሚለው ሮቤል፤ መምህራኑ በብሔራዊ ፈተናው ውጤታማ እንዲሆን ለነበራቸው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርቧል። በክብረአብ በላቸው @Ethionews433 @Ethionews433

የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ጌታቸው ረዳ፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት በምዕራብ ኢትዮጵያ የድንበር አካባቢዎችንና መንደሮችን በከባድ መሳሪያ በመደብደብ ጉዳት እያደረሠ ይገኛል በማለት ለአልጀዚራ በሠጡት ቃል ከሰሱ። ጌታቸው፣ የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች ይረዳል በማለት ጭምር መወንጀላቸውን ዜና አውታሩ ማምሻውን ዘግቧል። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ከኢትዮጵያ ግዛት እየተነሳ በሱዳን ጦር ሠራዊት ላይ ጥቃት ይፈጽማል የሚለውን የሱዳን ባለሥልጣናት ውንጀላ ያስተባበሉት ጌታቸው፣ ኢትዮጵያ የሱዳንን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት እንደምታከብር ተናግረዋል ተብሏል። ሱዳን ጦሯን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጋር ወደሚዋሠነው ብሉናይል ግዛት ደማዚን ከተማ አካባቢ በብዛት እያንቀሳቀሰች መኾኗንም ዘገባው የሱዳን ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት በአሳሳቢ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ‹‹ዎል ስትሪት ጆርናል›› የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘገበ። በመካከለኛው ምስራቅ ከኢራን ጋር ያለው ግጭት በአውሮፓ የሚገኘውን
የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት በአሳሳቢ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ‹‹ዎል ስትሪት ጆርናል›› የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘገበ። በመካከለኛው ምስራቅ ከኢራን ጋር ያለው ግጭት በአውሮፓ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት ክፉኛ እየጎዳው መሆኑ ተገልጿል። በተለይም የ‹ፓክ-3 ፓትሪዮት› ሚሳኤል መከላከያዎች እና የረዥም ርቀት ሚሳኤሎች ክምችት ከወትሮው በበለጠ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተመላክቷል። በዚህም ግጭት እስካሁን፦ 1 ሺህ 7 መቶ የፓትሪዮት ሚሳኤል መከላከያዎች፣ 2 መቶ የታድ መከላከያዎች፣ እና 150 የባህር ኃይል ስታንዳርድ ሚሳኤሎች አገልግሎት ላይ ውለዋል። ይህንኑ እጥረት ለማቃለል ሲባልም፤ በርካታ የታድ ስርዓቶች እና ድሮን ተከላካይ መሣሪያዎች ከአውሮፓ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ተዛውረዋል። ይህ የመሣሪያዎች እጥረት አሁን በጦርነት እቅድ ዝግጅት ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ፣ የአሜሪካ አውሮፓ እዝ የተግባር እቅዶቹን ማስተካከሉ ተሰምቷል። ነጩ ቤተ መንግስት እና ፔንታጎን ግን “እጥረት አለ” የሚለውን ዘገባ በመቃወም፣ ያለው ክምችት ለስትራቴጂካዊ አላማዎች በቂ እንደሆነ አስምረው ተናግረዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

የድሮን አሰሳ እና ጥቃት‼️ በራያ አካባቢ በህወሓት ወታደራዊ ቦታዎች ላይ የሚፈፀመው የድሮን ጥቃት እና አሰሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዛሬው ዕለት በአካባቢው ከፍተኛ የተባለ የድሮን አሰሳ ሲደረግ መዋሉን የአካባቢው ምንጮች ከምስል ጋር ገልፀውልናል። ህወሃት የትራንስ ኢትዮጵያ ተሽከርካሪዎችን በድርቅ ሰበብ ለወታደራዊ አገልግሎት እያዋላቸው መሆኑን፣የአዲግራት እና የአክሱም ዩኒቨርስቲ ሆስፒታሎችን ወታደራዊ የህክምና መስጫ ለማድረግ እንቅስቃሴ ጀምሯል። Via : አዩዘሀበሻ @Addis_Reporter @Addis_Reporter

የ 46 አመቱ የአንበሳ ባንክ ጥበቃ የ 12 ክፍል ፈተናን 320.25 ዉጤት አመጡ 👉🏼ባንኩ በዉጤቱ ተደስቶ የተለያዩ ስጦታዎችንም አበርክቶላቸዋል የአንበሳ ባንክ የጥበቃ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ሰይፈ
የ 46 አመቱ የአንበሳ ባንክ ጥበቃ የ 12 ክፍል ፈተናን 320.25 ዉጤት አመጡ 👉🏼ባንኩ በዉጤቱ ተደስቶ የተለያዩ ስጦታዎችንም አበርክቶላቸዋል የአንበሳ ባንክ የጥበቃ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ሰይፈ ተስፋዬ ካሕሳይ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማለፊያ ነጥብ ማግኘታቸዉን ዳጉ ጆርናል ከባንኩ ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል። በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን ሰለዋ ወረዳ ደላ ከተማ በሚገኘው የአንበሳ ባንክ ቅርንጫፍ ላለፉት ሰባት አመታት በጥበቃ ስራ እየሰሩ የሚገኙ አቶ ሰይፈ በ46 አመታቸው የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቅያ ፈተና ተፈትነው 320.25 ነጥብ በማምጣት ወደ ዩንቨርስቲ ማለፋቸውን ባንኩ ማሳወቁን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል። በዚህም የባንኩ የዳይሬክቶሮች ቦርድ አባላት ፣ ማኔጅመንት እና ሰራተኞች በሙሉ የተሰማቸዉን ደስታ ገልጸዋል። በዚሁ መሰረት ለአቶ ሰይፈ ተስፋዬ ባንኩ ማበረታቻዎች ለመስጠት ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን አቶ ሰይፈ ተስፋይ ካሕሳይ ወደ ዩንቨርስቲ ለመግባት እና ለመማር የሚያስፈልጋቸው ማንኛውም ወጪ የዩንቨርስቲ ቆይታቸው እስከሚያጠናቅቁ ድረስ ሙሉ ወጪያቸውን ባንኩ እሸፍንላቸዋለሁ ብሏል። በተጨማሪም አቶ ሰይፈ ወደ ዩንቨርስቲ ከገቡበት ወር ጀምሮ አሁን የሚከፈላቸ ወርሃዊ ደመወዝ ሙሉ በሙሉ በየወሩ ለቤተሰቦቻቸው እንዲከፈል እንደሚደረግም ዳጉ ጆርናል ሰምቷል። በሌላ በኩል አቶ ሰይፈ ተስፋይ ካሕሳይ የዩንቨርስቲ ትምህርታቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባንኩ በተገቢው የስራ ዘርፍ በመመደብ በቋሚነት ቀጥሮ የሚያሰራቸው ይሆናል ተብሏል። @Seledadotio @Seledadotio

የኢራን ተመራማሪዎች በብርሃን አማካኝነት የካንሰር ሕዋሳትን የሚያጠፋና 80% ውጤታማ የሆነ ስማርት "ጄል" ሰሩ ይህ "ስማርት ሃይድሮጄል" (ፈሳሽ ቅባት) የጡት ካንሰር ዕጢዎችን በጥንቃቄ ኢላማ በማ
የኢራን ተመራማሪዎች በብርሃን አማካኝነት የካንሰር ሕዋሳትን የሚያጠፋና 80% ውጤታማ የሆነ ስማርት "ጄል" ሰሩ ይህ "ስማርት ሃይድሮጄል" (ፈሳሽ ቅባት) የጡት ካንሰር ዕጢዎችን በጥንቃቄ ኢላማ በማድረግ ለማከም የኬሞቴራፒ እና በብርሃን ላይ የተመሠረተ ሕክምናን ያጣመረ ነው። ጄሉ ከተፈጥሯዊና ከሰውነት ጋር ተስማሚ ከሆነ "ካይቶሳን" ከተባለ ንጥረ ነገር የተሠራ ነው፡፡ ስፑትኒክ እንደዘገበው መድኃኒቱን በተቆጣጠረ ሁኔታ የሚለቅ ሲሆን፣ የሌዘር ብርሃን ሲያርፍበት ይነቃቃል፡፡ በተለየ ሁኔታ የካንሰር ሕዋሳትን የሚጎዱ የኦክሲጅን ውህዶችን ያመነጫል፡፡ የተደረጉት ሙከራዎች እንደሚያሳዩት፣ ጄሉ ጤናማ ሕዋሳትን ሳይነካ ከ80% በላይ የሚሆኑትን የጡት ካንሰር ሕዋሳት ማጥፋት ችሏል፡፡ ይህ አቀራረብ ከተለመዱት የጡት ካንሰር ሕክምናዎች በተሻለ፣ አነስተኛ ጉዳት የሚያስከትል እና ቀጥተኛ ዒላማውን ብቻ የሚያጠቃ አማራጭ ሊሆን ይችላል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

"እግዚአብሔር ይመስገን አለሁ" ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ራቅ ማለታቸውን ተከትሎ የተለያዩ የሐሰት ዜናዎች ሲሰራጭ ሰንብቷል። በዛሬው እ
"እግዚአብሔር ይመስገን አለሁ" ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ራቅ ማለታቸውን ተከትሎ የተለያዩ የሐሰት ዜናዎች ሲሰራጭ ሰንብቷል። በዛሬው እለት ብልጽግና ፓርቲ በይፋዊ የቲክቶክ ገጹ ለሰሞንኛው አጀንዳ መልስ የሚመስል ቪዲዮ ለቋል። በቪዲው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ! "አለሁ እግዚአብሔር ይመስገን" በማለት ሲናገሩ ተሰምተዋል። via_አንድ አፍታ @Addis_News @Addis_News

የኢራን ጦርነት በአውሮፓ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት እያሟጠጠው ነው - ዘገባ ዎል ስትሪት ጆርናል የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ፣ የኢራን ግጭት በአውሮፓ የሚገኘ
የኢራን ጦርነት በአውሮፓ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት እያሟጠጠው ነው - ዘገባ ዎል ስትሪት ጆርናል የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ፣ የኢራን ግጭት በአውሮፓ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት እጅግ እየጎዳው ይገኛል፤ በተለይም የ ፓክ-3 ፓትሪዮት ሚሳኤል መከላከያዎች እና የረዥም ርቀት ሚሳኤሎች ክምችት "ከአስጊ ደረጃ በላይ" ዝቅ ማለቱ ተገልጿል። በግጭቱ ወቅት 1,700 የፓትሪዮት ሚሳኤል መከላከያዎች አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ 200 የታድ መከላከያዎች እና 150 የባህር ኃይል ስታንዳርድ ሚሳኤሎች ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ዘገባው አክሎ እንደገለጸው በርካታ የታድ ስርዓቶች እና ድሮን ተከላካይ መሣሪያዎች ከአውሮፓ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ተዛውረዋል። የመሣሪያዎቹ እጥረት አሁን በጦርነት እቅድ ዝግጅት ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ የአሜሪካ አውሮፓ እዝ የተግባር እቅዶቹን አስተካክሏል። ሆኖም ነጩ ቤተ መንግስት እና ፔንታጎን "እጥረት" መኖሩን የሚገልፀውን ገለጻ በመቃወም፣ ያለው ክምችት ለስትራቴጂካዊ አላማዎች በቂ እንደሆነ አስምረው ተናግረዋል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

#ትኩረት ያሸዋል ተባለ "አዲስ አበባ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ታወር ፊት ለፊት፣ ከቡናና ሻይ አጠገብ ባለው ዋና መንገድ ላይ የሚገኝ ይህ 'ፖል' የብዙዎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥሏል ነው የተባለው ። 😱
#ትኩረት ያሸዋል ተባለ "አዲስ አበባ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ታወር ፊት ለፊት፣ ከቡናና ሻይ አጠገብ ባለው ዋና መንገድ ላይ የሚገኝ ይህ 'ፖል' የብዙዎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥሏል ነው የተባለው ። 😱 በተለይ በምሽት እይታው ስለሚቀንስ፣ አሽከርካሪዎችም ሆኑ እግረኞች ለማይፈለግ አደጋ እየተጋለጡ ይገኛሉ። ይህ ፖል ከመንገዱ ተነስቶ ሌላ ምቹ ቦታ ላይ ካልተተከለ የከፋ አደጋ ሊያደርስ ይችላል። የሚመለከተው አካል አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ እና የአካባቢው ነዋሪዎችም ሆኑ አሽከርካሪዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እናሳስባለን። ⚠️⚠️ ይህ መረጃ ለሚመለከተው አካል እስኪደርስ ሼር በማድረግ ተባበሩ!" @Seledadotio @Seledadotio

በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማራቹ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተጠንቀቁ ። በ3 የሻይ ሲኒ ደረሰኝ ምክንያት 300 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል። በአዲሱ የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ደረሰኝ አ
+2
በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማራቹ  ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተጠንቀቁ ። በ3 የሻይ ሲኒ  ደረሰኝ  ምክንያት 300 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል። በአዲሱ የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ደረሰኝ አለመስጠት ንብረትዎን ሊያሳጣዎት ይችላል! አንድ ሰራተኛዎ ቸልተኛ ሆና 100 ብር ለሚያወጣ 'ሻይ' ደረሰኝ ባትቆርጥ... ቅጣቱ 100 ብር ሳይሆን 100 ሺህ ብር ነው ተብሏል። ይባስ ብሎ ደግሞ... ሰራተኛዋ ለ3 ደንበኞች ደረሰኝ ካልሰጠች፣ ለድርጅቱ ባለቤት የ300 ሺህ ብር መብረቅ የመሰለ ቅጣት ይወርድበታል። ይህ ቅጣት ደግሞ በአዋጁ አንቀጽ 125 ንኡስ ቁጥር 2 መሰረት በባለስልጣኑ ሊነሳ ወይም 'ይቅር' ሊባል አይችልም! መፍትሄው መክፈል ብቻ ነው! ነጋዴዎች ተጠንቀቁ፣ ሰራተኞቻችሁን አስተምሩ። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ዩኤፋ በፊፋ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ሊያነሳ ነው የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (ዩኤፋ)፣ የአለም እግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) የዓለም ዋንጫን ለግል ባለሀብቶች ለማስተላለፍ አቅዶት የነበረውን ውድቅ የተደረገ ፕሮጀክት እንደገና ላለማንሳት ዋስትና ማግኘቱን ተከተሎ፣ በፊፋ ውድድሮች ላይ ጥሎት የነበረውን የማዕቀብ ዛቻ በይፋ ለማንሳት መዘጋጀቱ ተገልጿል። በዩኤፋ እና በፊፋ መካከል በተፈጠረው የዓለም ዋንጫን በግል ፋይናንስ የማንቀሳቀስ ውዝግብ ጥላ አርፎበት የቆየ ቢሆንም፣ የአውሮፓ እግር ኳስ የበላይ አካል ግን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ጥሎት የነበረውን የማዕቀብ ዛቻ ያነሳል ተብሏል። የዓለም እግር ኳስ ኢኮኖሚን በክለቦች እና በብሔራዊ ቡድኖች የሚቆጣጠረው ዩኤፋ፣ በጂያኒ ኢንፋንቲኖ የሚመራው ፊፋ እንደ ዓለም ዋንጫ እና የክለቦች ዓለም ዋንጫ ያሉ ትልልቅ ውድድሮችን የሚያስተዳድር የግል የንግድ ተቋም ለማቋቋም ማቀዱ ባለፈው ሐምሌ ወር አጋማሽ ላይ ይፋ ሲሆን ከፍተኛ ቁጣውን ገልጻ ነበር። ይህ እቅድ የግል ኢንቨስተሮች በ ፊፋ ፎርዋርድ ኢንተርፕራይዝ (FFE) በተሰኘው አዲስ አሰራር ስር ድርሻ እንዲገዙ የሚፈቅድ ነበር። በፕሬዚዳንት አሌክሳንደር ሴፈሪን የሚመራው ዩኤፋ፣ እቅዱን ደብዛዛ እና ግልጽነት የጎደለው የጓሮ በር ድራማ ሲል በፅኑ ኮንኖታል። በወቅቱ የአውሮፓ እግር ኳስ የበላይ አካል ባወጣው ጠንካራ መግለጫ እነዚህ እቅዶች እስካሉ ድረስ ማንኛውም የዩኤፋ ብሔራዊ ቡድን በምንም ዓይነት የፊፋ ውድድር ላይ አይሳተፍም ብሎ የነበረ ሲሆን፣ ይህ እቅድ በፍጥነት እንዲሰረዝ ዋና ምክንያት እንደነበር ይነገራል። ነገር ግን የዩኤፋ ስራ አስፈፃሚዎች እና የአውሮፓ አባል ሀገራት ማህበራት በሞናኮ ስብሰባ ከማድረጋቸው አስቀድሞ፣ በፊፋ ውድድሮች ላይ የተጣለው የማዕቀብ ዛቻ በከፍተኛ ሁኔታ ሊነሳ እንደሚችል የኤኤፍፒ ምንጮች ዘግበዋል። ዩኤፋ እቅዱ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ ከመጠየቁም በላይ እግር ኳስን በዚህ መልኩ ለማበላሸት የሚደረጉ መሰል ሙከራዎች ዳግም እንደማይደገሙ ጠንካራ ዋስትና እንዲሰጠው መጠየቁ ይታወቃል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

photo content

ለስድስት ወራት ታግዶ የቆየውን የሮይተርስ ዘጋቢዎች ፈቃድ ታደሰ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከዓለም አቀፉ የዜና ተቋም ሮይተርስ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ከተወያየ በኋላ፣ ላለፉት ስድስት ወራት
ለስድስት ወራት ታግዶ የቆየውን የሮይተርስ ዘጋቢዎች ፈቃድ ታደሰ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከዓለም አቀፉ የዜና ተቋም ሮይተርስ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ከተወያየ በኋላ፣ ላለፉት ስድስት ወራት ታግዶ የቆየውን የሦስት ቋሚ የዜና ወኪሎቹን የዘገባ ፈቃድ ማደሱን አስታውቋል። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ ከሮይተርስ ኤክስክዩቲቭ ኤዲተር ኒክ ታተር እና የአፍሪካ ኤዲተር ሲልቪያ አሎይሲ ጋር ባካሄዱት ውይይት፤ ተቋሙ ባለፉት ሰባት ወራት ካሰራጫቸው ዘገባዎች መካከል የተወሰኑት የኢትዮጵያን ሕግ፣ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን እና ብሔራዊ ጥቅም የሚጻረሩ እንዲሁም የጋዜጠኝነት ሙያዊ ሥነ-ምግባርን ያልተከተሉ እንደነበሩ የሚዲያ ሞኒተሪንግ ውጤቶችን በማስደገፍ ማስረዳታቸውን የባለስልጣኑ መረጃ ያመላክታል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ሮይተርስ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያሰራጫቸው አንዳንዶቹ ዘገባዎች በሚዛናዊነት፣ በትክክለኝነት እና በተአማኒነት በኩል ክፍተት የነበረባቸውና ወደ አንድ ወገን ያደሉ እንደነበሩ ገልጸው፣ ለተስተዋሉት የሕግና የሙያ ሥነ-ምግባር ጥሰቶች አስፈላጊው እርማት ሊደረግላቸው እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። በውይይቱ ላይ የሮይተርስ ኃላፊዎች በበኩላቸው፣ የዜና ወኪሉ ገለልተኛ ሚዲያ መሆኑን ገልጸው ዘገባዎችን ሚዛናዊ፣ በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሠረቱ እና ከአድልዎ የጸዱ ለማድረግ ጥብቅ የኤዲቶሪያል መመሪያዎችን እንደሚከተሉ አስረድተዋል።  ባለሥልጣኑ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የሮይተርስ ቋሚ የዜና ወኪሎች ፈቃድ መታደሱን አውቀው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉላቸው ጥሪ አቅርቧል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH