ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 475 subscribers, ranking 1 732 in the Transport category and 2 491 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 475 subscribers.
According to the latest data from 29 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 209 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 36.12%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.66% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 4 868 views. Within the first day, a publication typically gains 2 111 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 30 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 30 June | +13 | |||
| 29 June | +5 | |||
| 28 June | +18 | |||
| 27 June | +15 | |||
| 26 June | +19 | |||
| 25 June | +25 | |||
| 24 June | +10 | |||
| 23 June | +6 | |||
| 22 June | +7 | |||
| 21 June | +4 | |||
| 20 June | +8 | |||
| 19 June | +19 | |||
| 18 June | +11 | |||
| 17 June | +18 | |||
| 16 June | +8 | |||
| 15 June | +2 | |||
| 14 June | +3 | |||
| 13 June | +6 | |||
| 12 June | +3 | |||
| 11 June | +5 | |||
| 10 June | +3 | |||
| 09 June | +16 | |||
| 08 June | +13 | |||
| 07 June | +9 | |||
| 06 June | +1 | |||
| 05 June | 0 | |||
| 04 June | +2 | |||
| 03 June | +1 | |||
| 02 June | 0 | |||
| 01 June | +2 |
| 2 | የአንኮበር - ዱለቻ የአስፋልት ኮንክሪት የግንባታ ፕሮጀክት 98 ነጥብ16 በመቶ ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23/2018 (ኢ መ አ):- የአማራ እና የአፋር ክልልን በመንገድ መሰረተ ልማት የሚያስተሳስረው የአንኮበር - አዋሽ አርባ፡ ኮንትራት አንድ፡ የአንኮበር - ዱላቻ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት 98 ነጥብ16 በመቶ ተጠናቀቀ።
አጠቃላይ የግንባታ ስራው 39 ነጥብ 27 ኪሎ ሜትር የተጠናቀቀ ሲሆን በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑ የሚገኙት ቀሪ የማጠናቀቂያ ስራዎች የአነስተኛ የውሃ ማፋሰሻዎችን ማስተካከል፣ የመንገድ ዳር ምልክቶችን መትከል፣ የመንገድ ቀለም መቀባት እና ሌሎች ውስን የመንገዱ ቀሪ ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛል።
40 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ጅማሮውን ከአንኮበር ከተማ መውጫ ላይ አድርጎ እስከ ዱለቻ ከተማ ድረስ የሚዘልቅ ይሆናል።
ግንባታውን በ 1,010,575,130.84 (አንድ ቢሊዮን አስር ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባ አምስት ሺህ አንድ መቶ ሠላሳ ብር ከሠማንያ አራት ሳንቲም) ወጪ በፌደራል መንግስት ሙሉ በሙሉ ተሸፍኗል።
ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.ግ.ማኅበር ግንባታውን እያካሄደ ሲሆን የግንባታውን ጥራት የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እያከናወነው ይገኛል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በአማራ ክልል አንኮበር ወረዳ፣ አልዩ አምባ ቀበሌን እንዲሁም በአፋር ክልል የዱለቻ ወረዳ የጋቸኒ ቀበሌ እና ዱለቻ ከተማን በአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በማገናኘት ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ የደብረ ብርሀን አንኮበር ዱለቻ አዋሽ አርባ መገንጠያ የኢኮኖሚ ኮሪደር አካል በመሆኑ የሰሜን ሸዋ፣ የጎጃም እና ጎንደር የሚሄዱ የገቢ ወጪ እቃዎቹን ለማጓጓዝ አዲስ አበባ ሳይገባ በአቋራጭ ለማስተላለፍ ያግዛል።
በተጨማሪም መንገዱ በመገንባቱ ከዚህ በፊት ይወስድ የነበረውን የ 3 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 40 ደቂቃ ያሳጥራል።
የፕሮጀክቱ የጎን ስፋት በቀበሌ መቀመጫ 12ሜትር ሲሆን በገጠር 8-10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፣ የዚህ የኢኮኖሚ ኮሪደር አካል የሆነውና 42.18 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው የደብረ ብርሃን - አንኮበር መንገድ ፕሮጀክት ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለትራፊክ እንቅስቃሴ ክፍት መደረጉ ይታወሳል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 1 941 |
| 3 | No text... | 4 393 |
| 4 | የዲንኬ - ሳውላ - ሸፍቴ እና የቱርጋ ያላ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ 33 ነጥብ 51 በመቶ ደረሰ
ሳውላ (ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ፤ ኢመአ) — የጋሞ እና የጎፋ ዞኖችን እንዲሁም አራት ወረዳዎችን በዋናነት የሚያገናኘው የሎት 3 ዲንኬ -ሳዉላ - ሸፍቴ እና ቱርጋ ያላ ተለዋጭ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈጻጸም 33 ነጥብ 51 በመቶ ላይ ደርሷል።
ግንባታውን የቻይናው ው ዪ ኃ.የተ.የግ.ማ የተባለ የሥራ ተቋራጭ እያከናወነው የሚገኝ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥሩን ተግባር ኬ እና ጄ ፕሮጀክት አማካሪ ከማሪስዌ አማካሪ ጋር በጥምረት እንዲሁም ክሎቨር አማካሪ ኃ.የተ.የግ.ማ በንዑስ አማካሪነት በጋራ እየሰሩ ይገኛሉ።
ከ 3 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ የሚገኛው ይህ መንገድ 85 ነጥብ 68 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ አለው።
የመንገዱ ግንባታ ወጪ በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኢትዮጵያ መንግስት በጋራ የተሸፈነ ነው።
በእስካሁኑ የቀድሞው የሥራ ተቋራጭ ያከናወነውን ጨምሮ 40.5 ኪሎ ሜትር የሚሆን የአሥፋልት ንጣፍ ተከናውኗል።
በአዲሱ የሥራ ተቋራጭ ደግሞ የ25.6 ኪ.ሜ የአፈር ጠረጋ፣ የ23.7 ኪ.ሜ የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የ22.19 ኪ.ሜ የካፒንግ፣ የ19.5 ኪ.ሜ የሰብ ቤዝ፣ የ6.2 ኪ.ሜ የቤዝ ኮርስ እንዲሁም የ5.1 ኪ.ሜ አስፋልት ንጣፍ ስራ ሊጠናቀቅ ችሏል።
ከዚህ በተጨማሪ 3 ድልድዮች፣ 15 ቦክስ ካልቨርቶች፣ 1 ስላብ ካልቨርት እና 44 አነስተኛ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦዎች ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል።
በግንባታው ሂደት ላይ ወቅቱን ያልጠበቀ ከፍተኛ ዝናብ፣ የተቋራጩ የአፈጻጸም ማነስ፣ የወሰን ማስከበር ችግሮች እንዲሁም የግብዓት እጥረት አጋጥመዋል።
እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ከተቋራጩና ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በቅርብ እየተሰራ ይገኛል። ከአስፓልት ንጣፍ ስራዎች ጎን ለጎን ለዝናብ ወራት የሚስማሙ ስራዎችን መርጦ በመተግበር የግንባታውን ፍጥነት ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ከዲንኬ ቀበሌ ተነስቶ ሳውላ ከተማን አቋርጦ የኦይዳ ወረዳ ዋና መቀመጫ በሆነችው ሸፊቴ ከተማ ላይ ያበቃል።
የመንገዱ ግንባታ የአካባቢው የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ የማህበረሰቡን የእርስ በእርስ ግንኙነት ያጠናክራል።
ግንባታው ሲጠናቀቅ የወላይታ፣ ጋሞ እና ጎፋ ዞኖችን በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፍ በማስተሳሰር፤ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን እንደ ቡና፣ ለውዝ፣ በቆሎ፣ ስንዴ፣ ጤፍ እና ቅቤ ያሉ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ መሃል ገበያ ለማቅረብ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚህም በተጨማሪ መንገዱ የማዜ ብሔራዊ ፓርክን አቋርጦ የሚያልፍ በመሆኑ ለአካባቢው ብሎም ለሀገሪቱ የቱሪዝም መዳረሻ ዕድገት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ይታመናል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 3 583 |
| 5 | No text... | 6 788 |
| 6 | ደባርቅ - ቧሂት አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ለማፋጠን እየተሰራ ነው።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11/2018 (ኢ መ አ):- በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የደባርቅ እና ጃናሞራ ወረዳዎችን ከበየዳ ወረዳ የሚያገናኝው የደባርቅ - ቧሂት አስፋልት መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል።
አጠቃላይ የግንባታ ስራው 63 ነጥብ 21 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን በስካሁኑ የስራ እንቅስቃሴ የአስፓልት ማንጠፍ፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የድሪኒጅ ፣ የሰብ ቤዝ ፣ የቤዝኮርስ ፣ የቤዝ ቦርስ መፍጨት፣ የአስፓልትና ኮንክሪት ጠጠር መፍጨት፣ ፓይፐ ማምረት እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎች በመሰራት ላይ ይገኛል፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቱ ጅማሮውን ደባርቅ ከተማ ላይ አድርጎ ቧሂት ከተማ ድረስ የሚዘልቅ ነው፡፡
ግንባታው በ4,174,470,239.57 (አራት ቢሊዮን አንድ መቶ ሰባ አራት ሚሊዮን አራት መቶ ሰባ ሺህ ሁለት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ብር ከሃምሳ ሰባት ሳንቲም) በሆነ ወጪ በፌደራል መንግስት ነው የሚሸፈነው።
መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ግንባታውን እያካሄደ ሲሆን የግንባታውን ጥራት የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ ደግሞ አይ.ዲ.ኮን ኢንፍራስትራክቸር ደቬሎፕመንት ኮንሰልታንትስ ኃ.የተ.የግ ማህበር እያከናወነው ይገኛል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል።
አርሶ አደሮች ምርታቸውን ካለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማውጣት አምራችና እና ሸማቾችን በቀላሉ በማገናኘት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል።
የሰሜን ብሔራዊ ፓርክን ለውጭ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ምቹ እንዲሆን ከማስቻሉም ባለፈ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
በተጨማሪም በተሽከርካሪ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የ4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ያሳጥረዋል።
ፕሮጀክቱ በከተማ 19 ሜትር፣ በወረዳ 20.5 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጉ እየተገነባ ይገኛል ።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 4 729 |
| 7 | No text... | 4 962 |
| 8 | የጋምቤላ-አቦቦ -ፒኝውዶ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 09/2018 (ኢ መ አ):- በጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ እየተገነባ የሚገኘዉ የጋምቤላ - አቦቦ - ጎግ - ዲማ : ኮንትራት 1፡ የጋምቤላ - አቦቦ - ፒኝውዶ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
103 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይህ መንገድ አሁን ላይ አጠቃላይ አፈጻጸሙ 94 ነጥብ 2 በመቶ ላይ ደርሷል ፡፡
በእስካሁኑ የመንገዱ ግንባታ እንቅስቃሴ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ፣ የስትራክቸር ፣ የድልድይና የግንብ ፣ የሰብ ቤዝ ፣ ቤዝ ኮርስ ፣ የመንገድ ቀለም ቅብ፣ የመንገድ ዳር ደህንነት ሥራዎች እና የ85 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተከናውኗል።
ግንባታውን ቻይና ሬልዌይ 21 ግሩፕ ከጂያንግዢ እና ሃይድሮ - ፓወር ኮንስትራክሽን ጋር በጥምረት እያከናወኑት ይገኛሉ ። ፕሮሚናንት ኢንጂነሪንግ ሶሉሽን ኃ/የተ/የግ/ማ የማማከርና የቁጥጥር ተግባሩን በማካሄድ ላይ ነው ፡፡
መንገዱን ለመገንባት የሚውለው 1,354,114,598 (አንድ ቢሊዮን ሶስት መቶ ሀምሳ አራት ሚሊዮን አንድ መቶ አስራ አራት ሺ አምስት መቶ ዘጠና ስምንት) ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ።
መንገዱ በገጠር 11 በወረዳና በዞን 21.5 እንዲሁም በጋምቤላ ከተማ ላይ 36.5 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ነው ። ይህም ከዚህ ቀደም ይስተዋል የነበረውን የትራንስፖርት ችግር እንዲቀረፍ ያስችላል፡፡
የመንገዱ ግንባታ ከዚህ ቀደም ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ ከ4 ሰዓት ወደ 1 ሰዓት ከ 30 ደቂቃ ያሳጥረዋል።
የጋምቤላ - አቦቦ - ፒኝውዶ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የጋምቤላ ከተማን ከአኝዋክ ዞን ፣ ከአቦል ፣ አቦቦ እና ጎግ ወረዳዎች እንዲሁም ከአቦድ ፣ ከፑልጃይ ፣ ከኡኬዲ እና አጋንጋ ቀበሌዎች ጋር ያስተሳስራል ፡፡
ከዚህም ባሻገር በአካባቢው በስፋት የሚመረተውን የወርቅ ፣ የአሣ ፣ የቅባትና ሌሎች የግብርና ምርቶች በቀላሉ ለማዕከላዊ እና ለክልሉ የገበያ ማዕከላት ለማቅረብ ያስችላል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 3 973 |
| 9 | https://youtu.be/nqtsidxXtnU | 4 007 |
| 10 | No text... | 5 854 |
| 11 | ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ባለፉት 11 ወራት ውስጥ 1 ሺህ 756 ኪሎሜትር የሚሸፍኑ የመንገድ ጥገናዎችን አከናወነ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 05/2018 (ኢ መ አ):- የዓለምገና መንገድ አውታር አሥተዳደር ቅርጫፍ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት 11 ወራት ውስጥ 1 ሺህ 756 ኪሎሜትር የሚሸፍኑ የተለያዩ የመንገድ ጥገናዎችን አከናውኗል።
በዚህም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ የያዘውን ዕቅድ ማሳካት ችሏል።
የመንገድ ጥገናዎቹ የተከናወኑት 95 በመቶው በተቋሙ ራስ-ኅይል ሲኾን፥ ቀሪው በመንግሥት እና በግል የሥራ ተቋራጮች አማካኝነት ተከናውኗል።
ጥገናዎቹ የመንገዶቹን የጉዳት መጠን እና ዓይነት መሠረት በማድረግ በወቅታዊ፣ መደበኛ እና የከባድ የጥገና ዓይነቶች የተከናወኑ ናቸው።
ጥገና ከተከናወነባቸው መካከል:-
👉ቡታጅራ - ውልባረግ - ሆሳዕና
👉አዲስ አበባ - አምቦ - ጌዶ
👉አዲስ አበባ - ደብረብርሃን - አጣዩ
👉ወልቂጤ ማዞሪያ - ሆሳዕና
👉አዲስ አበባ - ጫንጮ - ፍቼ
👉ሞጆ - ዝዋይ
👉አዳማ - አዋሽ፣ አዲስ አበባ - ወሊሶ እንዲሁም የሞጆ - አዳማ መንገዶች በዋናነት ይጠቀሳሉ።
እነዚህ አውራ መንገዶች ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት የሚያስተናግዱ እና የወጪ-ገቢ ንግድ የሚተላለፍባቸው ወሳኝ ኮሪደሮች ከመሆናቸውም በተጨማሪ፣ ክልሎችን ከዞኖች ጋር የሚያስተሳስሩ ናቸው።
የመንገዶቹ መጠገን የትራንስፖርት ጊዜ እና ወጪ እንዲቀንስ አስችሏል። የተሻለ የመንገድ ደኅንነት እና ምቾት ፈጥራል። ከዚህ በተጨማሪም የወጪ እና ገቢ ንግዱ ፈጣን እና ቀልጣፋ እንዲሆን የጎላ አስተዋጽዖ አብርክቷል።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከጥገናው ጎን ለጎን የመሬት መንሸራተት መከላከል፣ የድንገተኛ አደጋ ምላሽ እንዲሁም የክብደት እና መጠን ቁጥጥር ጨምሮ መጠነ-ሰፊ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 4 524 |
| 12 | https://youtu.be/nqtsidxXtnU | 4 362 |
| 13 | No text... | 5 187 |
| 14 | የዳዬ-ግርጃ - መልካደስታ እና መለያ -መጆ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኢመአ)፦ የሲዳማ እና የኦሮሚያ ክልሎችን በመንገድ የሚያስተሳስረው እና 65 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የዳዬ-ግርጃ - መልካደስታ እና መለያ -መጆ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል።
ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 63 ነጥብ 4% በመቶው የተጠናቀቀ ሲሆን የአስፋልት ንጣፍ ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ስራዎች ፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ውስጥ ከሚገኘው ዳዬ ከተማ አድርጎ እስከ ግርጃ/መልካ ደስታ እና መጆ ከተማ ድረስ የሚዘልቅ ነው ።
ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,555,708,167.88 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አምስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ሰባት ብር ከሰማንያ ስምንት ሳንቲም) በኢትዮጵያ መንግስት ነው የሚሸፈነው ።
ግንባታውን ቻይና ቲሲጁ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የተባለ የሥራ ተቋራጭ በማካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራውን ደግሞ ስታዲያ ኢንጂነሪንግ ወርክስ ኮንሰልታንት በማከናወን ላይ ይገኛል።
የዚህ መንገድ ፕሮጀክት ደረጃውን በጠበቀ አስፋልት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል።
ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚመረቱ እንደ ቡና፣ እንሰት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዓድናትን ወደ ገበያ ለማቅርብ ምቹ ሁነታ ይፈጥራል።
በተጨማሪም በተሽከርካሪ ለመጓጓዝ ይወስድ የነበረውን የ 4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ከማሳጠሩም ባለፈ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎችን አላስፈላጊ እንግልት ያቃልላል።
በመስመሩ ላይ ያሉ ከተሞችን ከማስተሳሰሩም ባለፈ የከተሞችን እድገት ያፋጥናል።
የመንገድ ግንባታው በከተማ 21 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 4 731 |
| 15 | No text... | 6 947 |
| 16 | የጅማ-ጭዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተሻለ አፈፃፀም ላይ ይገኛል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኢመአ)፦በኦሮሚያና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያሳድገው የጅማ - ጭዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተሻለ አፈፃፀም ላይ ይገኛል ።
80 ኪሎሜትር በሚረዝመው የመንገዱ ግንባታ አፈፃፀም የአፈር ጠረጋ ፣ የውሃ ማስወገጃ ፉካዎችና የስትራክቸር ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን የፕሮጀክቱ 27.12 ኪሎ ሜትር የሚሆነው መንገድም በአስፋልት ንጣፍ ተሸፍኗል። ይህም አጠቃላይ አፈፃፀሙን 49.31 በመቶ አድርሶታል።
ከ2.4 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበለት የመንገዱ ግንባታ በቻይናው ቲሲጁ ሲቪል ኢንጅነሪንግ ግሩፕ አማካኝነት በመከናወን ላይ ነው።
የፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥሩን ሥራ ደግሞ ኪዮንግዶንግ ኢንጅነሪንግ ፣ ኦረንትያል ኮንሰልቲንግ ግሎባል እንዲሁም ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ በጋራ በመሆን እያከናወኑ ይገኛሉ።
የግንባታው ሙሉ ወጪ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ከጃፓን ዓለም አቀፍ ተራድዖ ድርጅት (JICA) በተገኘ ድጋፍ የተሸፈነ ነው።
የወሰን ማስከበር ችግሮች፣ የግንባታ ግብዓት አቅርቦት እጥረት ፣ የሥራ ተቋራጩ የአፈፃፀም ውስንነት እና የነዳጅ እጥረት በግንባታው ሂደት ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሮ ቆይቷል፡፡ አሁን ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሮችን ለመቅረፍ እና ግንባታውን ለማፋጠን በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
የጅማ ጭዳ መንገድ ሲጠናቀቅ እንደ ቡና ፣ ሰሊጥና የተለያዩ ፍራፍሬዎች እንዲሁም የግብርና ምርቶችን ወደ ገበያ ማዕከላት ለማድረስ የሚያስችል ነው።
እንዲሁም ወደ ኮይሻ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሚደረገውን የተሽከርካሪ ጉዞ ለማቀላጠፍና በአካባቢው የሚመረተውን የድንጋይ ከሰል በቀላሉ ለማጓጓዝ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ይታመናል፡፡
በተጨማሪም ለጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክና ለሃላላ ኬላ የቱሪስት መስህቦች አማራጭ መሄጃ በመሆኑ የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንደሚያሳድግ ይጠበቃል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 4 675 |
| 17 | ኢድ ሙባረክ | 6 131 |
| 18 | No text... | 6 193 |
| 19 | የአምቦ ወሊሶ የመንገድ ግንባታ የአስፋልት ሥራ ተጠናቋል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኢመአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው እና 63 ኪሎሜትር የሚረዝመው የአምቦ ወሊሶ የመንገድ ግንባታ የአስፋልት ሥራው ተጠናቋል ፡፡
በመንገዱ የግንባታ ሂደት የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የሰብ ቤዝ እና የቤዝ ኮርስ፣የ 5 ድልድይ ግንባታ እንዲሁም 63 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ለማከናወን ተችሏል።
የመንገዱን ቀሪ የማጠናቀቂያ ስራዎች የስላብ ከልቨርትና የድሬኔጅ ስራዎች ፣ የመንገድ ምልክቶች እንዲሁም በአምቦ እና ወሊሶ ከተሞች የእግረኛ መሄጃ መንገዶች ስራን በዚሁ በጀት አመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ።
የመንገዱን ግንባታ ያከናወነው መንግስታዊ የልማት ድርጅት የሆነው መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥሩን ሥራ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን የትራንፖርት ዘርፍ ሰርቶታል ፡፡
የግንባታ ወጪው 3,857,936,611 (ሶስት ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃምሳ ሰባት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ አስራ አንድ) ብር የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነዉ፡፡
ቀደም ሲል የነበረዉ መንገድ ለትራንስፖርት አስቸጋሪ እና ጠባብ የነበረ በመሆኑ አሁን ላይ በገጠር እና በቀበሌ 7 ሜትር ፣ በዞን እና በወረዳ 14 ሜትር ፣ በከተማ ደግሞ 21 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ተገንብቷል፡፡
ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ በ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘዉ አምቦ ከተማ ተነስቶ ወሊሶ ከተማ ላይ የሚያበቃ ነው፡፡
የመንገዱ መጠናቀቅ የምዕራብ ሸዋ(አምቦ) እና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ(ወሊሶ) ከተሞችን እንዲሁም የጭቱ ወረዳን፣የዳርያን እና አልቱፋ ቀበሌዎችን በቅርበት በማስተሳሰር ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜን ያሳጥራል፡፡
የአምቦ ወሊሶ መንገድ የህብረተሰቡን የትራንስፖርት ችግር ከመቅረፍ ባሻገር በአካባቢዉ የሚመረቱ እንደ ጤፍ ፣ እንሰት ፣ ገብስ እና በቆሎ ምርቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲወጣ በማድረግ አምራችና ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
በተጨማሪም የቱሪዝም መዳረሻ የሆነው ‘’የወንጪ ሃይቅ’’ መንገዱ በሚያልፍበት በኩል የሚገኝ በመሆኑ ለቱሪዝም ዘርፉ እድገት ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 4 026 |
| 20 | No text... | 5 984 |
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
