ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 475 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 732 في فئة النقل والمرتبة 2 491 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 475 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 29 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 209، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 5، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 36.12‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.66‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 868 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 111 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 11.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 475
المشتركون
+524 ساعات
+987 أيام
+20930 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يونيو '26
يونيو '26
+252
في 0 قنوات
مايو '26
+254
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+212
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+172
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+179
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+154
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+167
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+252
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+299
في 1 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+61
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+299
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+675
في 1 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+130
في 1 قنوات
Get PRO
مايو '25
+198
في 3 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+100
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+211
في 2 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+355
في 1 قنوات
Get PRO
يناير '25
+313
في 1 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+409
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+210
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+455
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+188
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+105
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+398
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+274
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+419
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+144
في 1 قنوات
Get PRO
مارس '24
+419
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+201
في 1 قنوات
Get PRO
يناير '24
+241
في 1 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+238
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+140
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+199
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+153
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+63
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+201
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+263
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+135
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+110
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+152
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+130
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+144
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+217
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+121
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+107
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+398
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+504
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+61
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+69
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+44
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+77
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+80
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+42
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+49
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+39
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+32
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+61
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+34
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+77
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+66
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+67
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+39
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+53
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+55
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+113
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+52
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+5 120
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
30 يونيو+13
29 يونيو+5
28 يونيو+18
27 يونيو+15
26 يونيو+19
25 يونيو+25
24 يونيو+10
23 يونيو+6
22 يونيو+7
21 يونيو+4
20 يونيو+8
19 يونيو+19
18 يونيو+11
17 يونيو+18
16 يونيو+8
15 يونيو+2
14 يونيو+3
13 يونيو+6
12 يونيو+3
11 يونيو+5
10 يونيو+3
09 يونيو+16
08 يونيو+13
07 يونيو+9
06 يونيو+1
05 يونيو0
04 يونيو+2
03 يونيو+1
02 يونيو0
01 يونيو+2
منشورات القناة
2
የአንኮበር - ዱለቻ የአስፋልት ኮንክሪት የግንባታ ፕሮጀክት 98 ነጥብ16 በመቶ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23/2018 (ኢ መ አ):- የአማራ እና የአፋር ክልልን በመንገድ መሰረተ ልማት የሚያስተሳስረው የአንኮበር - አዋሽ አርባ፡ ኮንትራት አንድ፡ የአንኮበር - ዱላቻ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ  ፕሮጀክት 98 ነጥብ16 በመቶ ተጠናቀቀ። አጠቃላይ የግንባታ ስራው 39 ነጥብ 27 ኪሎ ሜትር የተጠናቀቀ ሲሆን   በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑ የሚገኙት ቀሪ የማጠናቀቂያ ስራዎች የአነስተኛ የውሃ ማፋሰሻዎችን ማስተካከል፣ የመንገድ ዳር ምልክቶችን መትከል፣ የመንገድ ቀለም መቀባት እና ሌሎች ውስን የመንገዱ ቀሪ ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛል። 40 ኪሎ ሜትር  ርዝመትን የሚሸፍነው ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ጅማሮውን ከአንኮበር ከተማ መውጫ ላይ  አድርጎ እስከ ዱለቻ ከተማ ድረስ የሚዘልቅ ይሆናል። ግንባታውን በ 1,010,575,130.84  (አንድ ቢሊዮን አስር ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባ አምስት ሺህ አንድ መቶ ሠላሳ ብር ከሠማንያ አራት ሳንቲም) ወጪ በፌደራል መንግስት ሙሉ በሙሉ ተሸፍኗል። ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.ግ.ማኅበር ግንባታውን እያካሄደ ሲሆን የግንባታውን ጥራት የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ  ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እያከናወነው ይገኛል።   የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ  በአማራ ክልል አንኮበር ወረዳ፣ አልዩ አምባ ቀበሌን እንዲሁም በአፋር ክልል የዱለቻ ወረዳ የጋቸኒ ቀበሌ እና ዱለቻ ከተማን በአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በማገናኘት ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል። የመንገድ ፕሮጀክቱ የደብረ ብርሀን አንኮበር ዱለቻ አዋሽ አርባ መገንጠያ የኢኮኖሚ ኮሪደር አካል በመሆኑ የሰሜን ሸዋ፣ የጎጃም እና ጎንደር የሚሄዱ የገቢ ወጪ እቃዎቹን ለማጓጓዝ አዲስ አበባ ሳይገባ በአቋራጭ ለማስተላለፍ ያግዛል። በተጨማሪም መንገዱ በመገንባቱ ከዚህ በፊት ይወስድ የነበረውን የ 3 ሰዓት የጉዞ ጊዜ  ወደ 40 ደቂቃ ያሳጥራል። የፕሮጀክቱ የጎን ስፋት በቀበሌ መቀመጫ  12ሜትር ሲሆን  በገጠር 8-10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፣ የዚህ የኢኮኖሚ ኮሪደር አካል የሆነውና 42.18 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው የደብረ ብርሃን - አንኮበር መንገድ ፕሮጀክት ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለትራፊክ እንቅስቃሴ ክፍት መደረጉ ይታወሳል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
1 941
3
+6
لا يوجد نص...
4 393
4
የዲንኬ - ሳውላ - ሸፍቴ እና የቱርጋ ያላ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ 33 ነጥብ 51 በመቶ ደረሰ   ሳውላ (ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ፤ ኢመአ) — የጋሞ እና የጎፋ ዞኖችን እንዲሁም አራት ወረዳዎችን በዋናነት የሚያገናኘው የሎት 3 ዲንኬ -ሳዉላ - ሸፍቴ እና ቱርጋ ያላ ተለዋጭ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈጻጸም 33 ነጥብ 51 በመቶ ላይ ደርሷል። ግንባታውን የቻይናው ው ዪ ኃ.የተ.የግ.ማ የተባለ የሥራ ተቋራጭ እያከናወነው የሚገኝ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥሩን ተግባር ኬ እና ጄ ፕሮጀክት አማካሪ ከማሪስዌ አማካሪ ጋር በጥምረት እንዲሁም ክሎቨር አማካሪ ኃ.የተ.የግ.ማ በንዑስ አማካሪነት በጋራ እየሰሩ ይገኛሉ።   ከ 3 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ የሚገኛው ይህ መንገድ 85 ነጥብ 68 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ አለው። የመንገዱ ግንባታ ወጪ በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኢትዮጵያ መንግስት በጋራ የተሸፈነ ነው። በእስካሁኑ የቀድሞው የሥራ ተቋራጭ ያከናወነውን ጨምሮ 40.5 ኪሎ ሜትር የሚሆን የአሥፋልት ንጣፍ ተከናውኗል። በአዲሱ የሥራ ተቋራጭ ደግሞ የ25.6 ኪ.ሜ የአፈር ጠረጋ፣ የ23.7 ኪ.ሜ የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የ22.19 ኪ.ሜ የካፒንግ፣ የ19.5 ኪ.ሜ የሰብ ቤዝ፣ የ6.2 ኪ.ሜ የቤዝ ኮርስ እንዲሁም የ5.1 ኪ.ሜ አስፋልት ንጣፍ ስራ ሊጠናቀቅ ችሏል። ከዚህ በተጨማሪ 3 ድልድዮች፣ 15 ቦክስ ካልቨርቶች፣ 1 ስላብ ካልቨርት እና 44 አነስተኛ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦዎች ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል። በግንባታው ሂደት ላይ ወቅቱን ያልጠበቀ ከፍተኛ ዝናብ፣ የተቋራጩ የአፈጻጸም ማነስ፣ የወሰን ማስከበር ችግሮች እንዲሁም የግብዓት እጥረት አጋጥመዋል። እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ከተቋራጩና ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በቅርብ እየተሰራ ይገኛል። ከአስፓልት ንጣፍ ስራዎች ጎን ለጎን ለዝናብ ወራት የሚስማሙ ስራዎችን መርጦ በመተግበር የግንባታውን ፍጥነት ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ከዲንኬ ቀበሌ ተነስቶ ሳውላ ከተማን አቋርጦ የኦይዳ ወረዳ ዋና መቀመጫ በሆነችው ሸፊቴ ከተማ ላይ ያበቃል። የመንገዱ ግንባታ የአካባቢው የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ የማህበረሰቡን የእርስ በእርስ ግንኙነት ያጠናክራል።   ግንባታው ሲጠናቀቅ የወላይታ፣ ጋሞ እና ጎፋ ዞኖችን በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፍ በማስተሳሰር፤ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን እንደ ቡና፣ ለውዝ፣ በቆሎ፣ ስንዴ፣ ጤፍ እና ቅቤ ያሉ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ መሃል ገበያ ለማቅረብ የጎላ ሚና ይጫወታል። ከዚህም በተጨማሪ መንገዱ የማዜ ብሔራዊ ፓርክን አቋርጦ የሚያልፍ በመሆኑ ለአካባቢው ብሎም ለሀገሪቱ የቱሪዝም መዳረሻ ዕድገት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ይታመናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
3 583
5
+8
لا يوجد نص...
6 788
6
ደባርቅ - ቧሂት አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ለማፋጠን እየተሰራ ነው።   አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11/2018 (ኢ መ አ):- በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የደባርቅ እና ጃናሞራ ወረዳዎችን ከበየዳ ወረዳ የሚያገናኝው የደባርቅ - ቧሂት አስፋልት መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል።   አጠቃላይ የግንባታ ስራው 63 ነጥብ 21 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን በስካሁኑ የስራ እንቅስቃሴ የአስፓልት ማንጠፍ፣   የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የድሪኒጅ  ፣ የሰብ ቤዝ ፣ የቤዝኮርስ ፣ የቤዝ ቦርስ መፍጨት፣ የአስፓልትና ኮንክሪት ጠጠር መፍጨት፣   ፓይፐ ማምረት   እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎች በመሰራት ላይ ይገኛል፡፡   የመንገድ ፕሮጀክቱ ጅማሮውን ደባርቅ ከተማ ላይ አድርጎ  ቧሂት ከተማ ድረስ የሚዘልቅ ነው፡፡   ግንባታው በ4,174,470,239.57 (አራት ቢሊዮን አንድ መቶ ሰባ አራት ሚሊዮን አራት መቶ ሰባ ሺህ ሁለት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ብር ከሃምሳ ሰባት ሳንቲም) በሆነ ወጪ በፌደራል መንግስት ነው የሚሸፈነው። መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ግንባታውን እያካሄደ ሲሆን የግንባታውን ጥራት የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ  ደግሞ አይ.ዲ.ኮን ኢንፍራስትራክቸር ደቬሎፕመንት ኮንሰልታንትስ ኃ.የተ.የግ ማህበር እያከናወነው ይገኛል።    የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች  ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል። አርሶ አደሮች ምርታቸውን ካለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማውጣት  አምራችና እና ሸማቾችን በቀላሉ በማገናኘት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል።   የሰሜን ብሔራዊ ፓርክን ለውጭ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ምቹ እንዲሆን ከማስቻሉም ባለፈ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።  በተጨማሪም በተሽከርካሪ  ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የ4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ያሳጥረዋል። ፕሮጀክቱ በከተማ 19 ሜትር፣ በወረዳ  20.5 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጉ እየተገነባ ይገኛል ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
4 729
7
+3
لا يوجد نص...
4 962
8
የጋምቤላ-አቦቦ -ፒኝውዶ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ሰኔ 09/2018 (ኢ መ አ):- በጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ እየተገነባ የሚገኘዉ የጋምቤላ - አቦቦ - ጎግ - ዲማ : ኮንትራት 1፡ የጋምቤላ - አቦቦ - ፒኝውዶ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። 103 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይህ መንገድ አሁን ላይ አጠቃላይ አፈጻጸሙ 94 ነጥብ 2 በመቶ ላይ ደርሷል ፡፡ በእስካሁኑ የመንገዱ ግንባታ እንቅስቃሴ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ፣ የስትራክቸር ፣ የድልድይና የግንብ ፣ የሰብ ቤዝ ፣ ቤዝ ኮርስ ፣ የመንገድ ቀለም ቅብ፣ የመንገድ ዳር ደህንነት ሥራዎች እና የ85 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተከናውኗል። ግንባታውን ቻይና ሬልዌይ 21 ግሩፕ ከጂያንግዢ እና ሃይድሮ - ፓወር ኮንስትራክሽን ጋር በጥምረት እያከናወኑት ይገኛሉ ። ፕሮሚናንት ኢንጂነሪንግ ሶሉሽን ኃ/የተ/የግ/ማ የማማከርና የቁጥጥር ተግባሩን በማካሄድ ላይ ነው ፡፡ መንገዱን ለመገንባት የሚውለው 1,354,114,598 (አንድ ቢሊዮን ሶስት መቶ ሀምሳ አራት ሚሊዮን አንድ መቶ አስራ አራት ሺ አምስት መቶ ዘጠና ስምንት) ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ። መንገዱ በገጠር 11 በወረዳና በዞን 21.5 እንዲሁም በጋምቤላ ከተማ ላይ 36.5 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ነው ። ይህም ከዚህ ቀደም ይስተዋል የነበረውን የትራንስፖርት ችግር እንዲቀረፍ ያስችላል፡፡ የመንገዱ ግንባታ ከዚህ ቀደም ይወስድ  የነበረውን የጉዞ ጊዜ ከ4 ሰዓት ወደ 1 ሰዓት ከ 30 ደቂቃ ያሳጥረዋል። የጋምቤላ - አቦቦ - ፒኝውዶ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የጋምቤላ ከተማን ከአኝዋክ ዞን ፣ ከአቦል ፣ አቦቦ እና ጎግ ወረዳዎች እንዲሁም ከአቦድ ፣ ከፑልጃይ ፣ ከኡኬዲ እና አጋንጋ ቀበሌዎች ጋር ያስተሳስራል ፡፡ ከዚህም ባሻገር በአካባቢው በስፋት የሚመረተውን የወርቅ ፣ የአሣ ፣ የቅባትና ሌሎች የግብርና ምርቶች በቀላሉ ለማዕከላዊ እና ለክልሉ የገበያ ማዕከላት ለማቅረብ ያስችላል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
3 973
9
https://youtu.be/nqtsidxXtnU
4 007
10
+9
لا يوجد نص...
5 854
11
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ባለፉት 11 ወራት ውስጥ 1 ሺህ 756 ኪሎሜትር የሚሸፍኑ የመንገድ ጥገናዎችን አከናወነ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 05/2018 (ኢ መ አ):- የዓለምገና መንገድ አውታር አሥተዳደር ቅርጫፍ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት 11 ወራት ውስጥ 1 ሺህ 756 ኪሎሜትር የሚሸፍኑ የተለያዩ የመንገድ ጥገናዎችን አከናውኗል። በዚህም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ የያዘውን ዕቅድ ማሳካት ችሏል። የመንገድ ጥገናዎቹ የተከናወኑት 95 በመቶው በተቋሙ ራስ-ኅይል ሲኾን፥ ቀሪው በመንግሥት እና በግል የሥራ ተቋራጮች አማካኝነት ተከናውኗል። ጥገናዎቹ የመንገዶቹን የጉዳት መጠን እና ዓይነት መሠረት በማድረግ በወቅታዊ፣ መደበኛ እና የከባድ የጥገና ዓይነቶች የተከናወኑ ናቸው። ጥገና ከተከናወነባቸው መካከል:- 👉ቡታጅራ - ውልባረግ - ሆሳዕና 👉አዲስ አበባ - አምቦ - ጌዶ 👉አዲስ አበባ - ደብረብርሃን - አጣዩ 👉ወልቂጤ ማዞሪያ - ሆሳዕና 👉አዲስ አበባ - ጫንጮ - ፍቼ 👉ሞጆ - ዝዋይ 👉አዳማ - አዋሽ፣ አዲስ አበባ - ወሊሶ እንዲሁም የሞጆ - አዳማ መንገዶች በዋናነት ይጠቀሳሉ። እነዚህ አውራ መንገዶች ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት የሚያስተናግዱ እና የወጪ-ገቢ ንግድ የሚተላለፍባቸው ወሳኝ ኮሪደሮች ከመሆናቸውም በተጨማሪ፣ ክልሎችን ከዞኖች ጋር የሚያስተሳስሩ ናቸው። የመንገዶቹ መጠገን የትራንስፖርት ጊዜ እና ወጪ እንዲቀንስ አስችሏል። የተሻለ የመንገድ ደኅንነት እና ምቾት ፈጥራል። ከዚህ በተጨማሪም የወጪ እና ገቢ ንግዱ ፈጣን እና ቀልጣፋ እንዲሆን የጎላ አስተዋጽዖ አብርክቷል። ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከጥገናው ጎን ለጎን የመሬት መንሸራተት መከላከል፣ የድንገተኛ አደጋ ምላሽ እንዲሁም የክብደት እና መጠን ቁጥጥር ጨምሮ መጠነ-ሰፊ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
4 524
12
https://youtu.be/nqtsidxXtnU
4 362
13
+2
لا يوجد نص...
5 187
14
የዳዬ-ግርጃ - መልካደስታ   እና  መለያ -መጆ   የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኢመአ)፦ የሲዳማ  እና የኦሮሚያ ክልሎችን በመንገድ የሚያስተሳስረው  እና 65 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው  የዳዬ-ግርጃ - መልካደስታ   እና    መለያ -መጆ   የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል።   ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 63 ነጥብ 4% በመቶው የተጠናቀቀ ሲሆን የአስፋልት ንጣፍ ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ስራዎች ፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን  በምስራቃዊ  ሲዳማ   ዞን   ውስጥ   ከሚገኘው ዳዬ  ከተማ   አድርጎ እስከ ግርጃ/መልካ ደስታ እና መጆ  ከተማ  ድረስ የሚዘልቅ ነው ። ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,555,708,167.88 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አምስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ሰባት ብር ከሰማንያ ስምንት ሳንቲም)  በኢትዮጵያ መንግስት ነው የሚሸፈነው ። ግንባታውን  ቻይና  ቲሲጁ  ሲቪል  ኢንጂነሪንግ   ግሩፕ  የተባለ  የሥራ  ተቋራጭ  በማካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ የማማከሩንና  የቁጥጥሩን  ሥራውን  ደግሞ   ስታዲያ ኢንጂነሪንግ ወርክስ ኮንሰልታንት በማከናወን ላይ  ይገኛል። የዚህ መንገድ ፕሮጀክት ደረጃውን በጠበቀ አስፋልት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚመረቱ እንደ ቡና፣ እንሰት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዓድናትን ወደ ገበያ ለማቅርብ ምቹ ሁነታ ይፈጥራል።   በተጨማሪም በተሽከርካሪ ለመጓጓዝ ይወስድ የነበረውን የ 4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ከማሳጠሩም ባለፈ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎችን አላስፈላጊ እንግልት ያቃልላል። በመስመሩ ላይ ያሉ ከተሞችን ከማስተሳሰሩም ባለፈ የከተሞችን እድገት ያፋጥናል።   የመንገድ ግንባታው በከተማ 21  ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
4 731
15
+9
لا يوجد نص...
6 947
16
የጅማ-ጭዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተሻለ አፈፃፀም ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኢመአ)፦በኦሮሚያና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትስስር  ይበልጥ የሚያሳድገው   የጅማ - ጭዳ  የመንገድ  ግንባታ ፕሮጀክት በተሻለ አፈፃፀም ላይ ይገኛል ። 80 ኪሎሜትር በሚረዝመው የመንገዱ ግንባታ  አፈፃፀም የአፈር ጠረጋ ፣ የውሃ ማስወገጃ ፉካዎችና የስትራክቸር ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን  የፕሮጀክቱ 27.12 ኪሎ ሜትር የሚሆነው መንገድም በአስፋልት ንጣፍ ተሸፍኗል።  ይህም አጠቃላይ አፈፃፀሙን 49.31 በመቶ አድርሶታል። ከ2.4 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበለት የመንገዱ ግንባታ በቻይናው ቲሲጁ ሲቪል ኢንጅነሪንግ ግሩፕ አማካኝነት በመከናወን ላይ ነው። የፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥሩን ሥራ  ደግሞ ኪዮንግዶንግ ኢንጅነሪንግ ፣ ኦረንትያል ኮንሰልቲንግ ግሎባል እንዲሁም ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ በጋራ በመሆን እያከናወኑ ይገኛሉ። የግንባታው  ሙሉ ወጪ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ከጃፓን ዓለም አቀፍ ተራድዖ ድርጅት (JICA) በተገኘ ድጋፍ የተሸፈነ  ነው። የወሰን ማስከበር ችግሮች፣ የግንባታ ግብዓት አቅርቦት እጥረት ፣ የሥራ ተቋራጩ የአፈፃፀም ውስንነት እና የነዳጅ  እጥረት በግንባታው ሂደት ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሮ ቆይቷል፡፡ አሁን ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሮችን ለመቅረፍ እና  ግንባታውን ለማፋጠን በትኩረት እየሰራ ይገኛል። የጅማ ጭዳ መንገድ  ሲጠናቀቅ እንደ ቡና ፣ ሰሊጥና የተለያዩ ፍራፍሬዎች እንዲሁም የግብርና ምርቶችን ወደ ገበያ ማዕከላት ለማድረስ የሚያስችል ነው። እንዲሁም ወደ ኮይሻ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሚደረገውን የተሽከርካሪ ጉዞ ለማቀላጠፍና በአካባቢው የሚመረተውን የድንጋይ ከሰል በቀላሉ ለማጓጓዝ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ይታመናል፡፡ በተጨማሪም ለጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክና ለሃላላ ኬላ የቱሪስት መስህቦች አማራጭ መሄጃ በመሆኑ የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንደሚያሳድግ ይጠበቃል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
4 675
17
ኢድ ሙባረክ
ኢድ ሙባረክ
6 131
18
+8
لا يوجد نص...
6 193
19
የአምቦ ወሊሶ የመንገድ ግንባታ የአስፋልት ሥራ ተጠናቋል አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኢመአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው እና 63 ኪሎሜትር የሚረዝመው የአምቦ ወሊሶ የመንገድ ግንባታ የአስፋልት ሥራው ተጠናቋል ፡፡ በመንገዱ የግንባታ ሂደት የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የሰብ ቤዝ እና የቤዝ ኮርስ፣የ 5 ድልድይ ግንባታ እንዲሁም 63 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ለማከናወን ተችሏል። የመንገዱን ቀሪ የማጠናቀቂያ ስራዎች የስላብ ከልቨርትና የድሬኔጅ ስራዎች ፣ የመንገድ ምልክቶች እንዲሁም በአምቦ እና ወሊሶ ከተሞች የእግረኛ መሄጃ መንገዶች ስራን በዚሁ በጀት አመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ። የመንገዱን ግንባታ ያከናወነው መንግስታዊ የልማት ድርጅት የሆነው መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥሩን ሥራ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን የትራንፖርት ዘርፍ ሰርቶታል ፡፡ የግንባታ ወጪው 3,857,936,611 (ሶስት ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃምሳ ሰባት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ አስራ አንድ) ብር የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነዉ፡፡ ቀደም ሲል የነበረዉ መንገድ ለትራንስፖርት አስቸጋሪ እና ጠባብ የነበረ በመሆኑ አሁን ላይ በገጠር እና በቀበሌ 7 ሜትር ፣ በዞን እና በወረዳ 14 ሜትር ፣ በከተማ ደግሞ 21 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ተገንብቷል፡፡ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ በ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘዉ አምቦ ከተማ ተነስቶ ወሊሶ ከተማ ላይ የሚያበቃ ነው፡፡ የመንገዱ መጠናቀቅ የምዕራብ ሸዋ(አምቦ) እና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ(ወሊሶ) ከተሞችን እንዲሁም የጭቱ ወረዳን፣የዳርያን እና አልቱፋ ቀበሌዎችን በቅርበት በማስተሳሰር ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜን ያሳጥራል፡፡ የአምቦ ወሊሶ መንገድ የህብረተሰቡን የትራንስፖርት ችግር ከመቅረፍ ባሻገር በአካባቢዉ የሚመረቱ እንደ ጤፍ ፣ እንሰት ፣ ገብስ እና በቆሎ ምርቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲወጣ በማድረግ አምራችና ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ በተጨማሪም የቱሪዝም መዳረሻ የሆነው ‘’የወንጪ ሃይቅ’’ መንገዱ በሚያልፍበት በኩል የሚገኝ በመሆኑ ለቱሪዝም ዘርፉ እድገት ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
4 026
20
+8
لا يوجد نص...
5 984