ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 290 مشترک است و جایگاه 1 761 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 559 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 290 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 09 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 135 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 16 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 26.75% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.16% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 3 555 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 2 148 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 12 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 10 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 10 ژوئن | +3 | |||
| 09 ژوئن | +16 | |||
| 08 ژوئن | +13 | |||
| 07 ژوئن | +9 | |||
| 06 ژوئن | +1 | |||
| 05 ژوئن | 0 | |||
| 04 ژوئن | +2 | |||
| 03 ژوئن | +1 | |||
| 02 ژوئن | 0 | |||
| 01 ژوئن | +2 |
| 2 | የዳዬ-ግርጃ - መልካደስታ እና መለያ -መጆ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኢመአ)፦ የሲዳማ እና የኦሮሚያ ክልሎችን በመንገድ የሚያስተሳስረው እና 65 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የዳዬ-ግርጃ - መልካደስታ እና መለያ -መጆ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል።
ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 63 ነጥብ 4% በመቶው የተጠናቀቀ ሲሆን የአስፋልት ንጣፍ ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ስራዎች ፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ውስጥ ከሚገኘው ዳዬ ከተማ አድርጎ እስከ ግርጃ/መልካ ደስታ እና መጆ ከተማ ድረስ የሚዘልቅ ነው ።
ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,555,708,167.88 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አምስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ሰባት ብር ከሰማንያ ስምንት ሳንቲም) በኢትዮጵያ መንግስት ነው የሚሸፈነው ።
ግንባታውን ቻይና ቲሲጁ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የተባለ የሥራ ተቋራጭ በማካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራውን ደግሞ ስታዲያ ኢንጂነሪንግ ወርክስ ኮንሰልታንት በማከናወን ላይ ይገኛል።
የዚህ መንገድ ፕሮጀክት ደረጃውን በጠበቀ አስፋልት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል።
ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚመረቱ እንደ ቡና፣ እንሰት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዓድናትን ወደ ገበያ ለማቅርብ ምቹ ሁነታ ይፈጥራል።
በተጨማሪም በተሽከርካሪ ለመጓጓዝ ይወስድ የነበረውን የ 4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ከማሳጠሩም ባለፈ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎችን አላስፈላጊ እንግልት ያቃልላል።
በመስመሩ ላይ ያሉ ከተሞችን ከማስተሳሰሩም ባለፈ የከተሞችን እድገት ያፋጥናል።
የመንገድ ግንባታው በከተማ 21 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 2 333 |
| 3 | بدون متن... | 4 568 |
| 4 | የጅማ-ጭዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተሻለ አፈፃፀም ላይ ይገኛል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኢመአ)፦በኦሮሚያና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያሳድገው የጅማ - ጭዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተሻለ አፈፃፀም ላይ ይገኛል ።
80 ኪሎሜትር በሚረዝመው የመንገዱ ግንባታ አፈፃፀም የአፈር ጠረጋ ፣ የውሃ ማስወገጃ ፉካዎችና የስትራክቸር ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን የፕሮጀክቱ 27.12 ኪሎ ሜትር የሚሆነው መንገድም በአስፋልት ንጣፍ ተሸፍኗል። ይህም አጠቃላይ አፈፃፀሙን 49.31 በመቶ አድርሶታል።
ከ2.4 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበለት የመንገዱ ግንባታ በቻይናው ቲሲጁ ሲቪል ኢንጅነሪንግ ግሩፕ አማካኝነት በመከናወን ላይ ነው።
የፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥሩን ሥራ ደግሞ ኪዮንግዶንግ ኢንጅነሪንግ ፣ ኦረንትያል ኮንሰልቲንግ ግሎባል እንዲሁም ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ በጋራ በመሆን እያከናወኑ ይገኛሉ።
የግንባታው ሙሉ ወጪ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ከጃፓን ዓለም አቀፍ ተራድዖ ድርጅት (JICA) በተገኘ ድጋፍ የተሸፈነ ነው።
የወሰን ማስከበር ችግሮች፣ የግንባታ ግብዓት አቅርቦት እጥረት ፣ የሥራ ተቋራጩ የአፈፃፀም ውስንነት እና የነዳጅ እጥረት በግንባታው ሂደት ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሮ ቆይቷል፡፡ አሁን ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሮችን ለመቅረፍ እና ግንባታውን ለማፋጠን በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
የጅማ ጭዳ መንገድ ሲጠናቀቅ እንደ ቡና ፣ ሰሊጥና የተለያዩ ፍራፍሬዎች እንዲሁም የግብርና ምርቶችን ወደ ገበያ ማዕከላት ለማድረስ የሚያስችል ነው።
እንዲሁም ወደ ኮይሻ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሚደረገውን የተሽከርካሪ ጉዞ ለማቀላጠፍና በአካባቢው የሚመረተውን የድንጋይ ከሰል በቀላሉ ለማጓጓዝ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ይታመናል፡፡
በተጨማሪም ለጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክና ለሃላላ ኬላ የቱሪስት መስህቦች አማራጭ መሄጃ በመሆኑ የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንደሚያሳድግ ይጠበቃል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 3 667 |
| 5 | ኢድ ሙባረክ | 5 842 |
| 6 | بدون متن... | 5 938 |
| 7 | የአምቦ ወሊሶ የመንገድ ግንባታ የአስፋልት ሥራ ተጠናቋል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኢመአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው እና 63 ኪሎሜትር የሚረዝመው የአምቦ ወሊሶ የመንገድ ግንባታ የአስፋልት ሥራው ተጠናቋል ፡፡
በመንገዱ የግንባታ ሂደት የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የሰብ ቤዝ እና የቤዝ ኮርስ፣የ 5 ድልድይ ግንባታ እንዲሁም 63 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ለማከናወን ተችሏል።
የመንገዱን ቀሪ የማጠናቀቂያ ስራዎች የስላብ ከልቨርትና የድሬኔጅ ስራዎች ፣ የመንገድ ምልክቶች እንዲሁም በአምቦ እና ወሊሶ ከተሞች የእግረኛ መሄጃ መንገዶች ስራን በዚሁ በጀት አመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ።
የመንገዱን ግንባታ ያከናወነው መንግስታዊ የልማት ድርጅት የሆነው መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥሩን ሥራ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን የትራንፖርት ዘርፍ ሰርቶታል ፡፡
የግንባታ ወጪው 3,857,936,611 (ሶስት ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃምሳ ሰባት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ አስራ አንድ) ብር የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነዉ፡፡
ቀደም ሲል የነበረዉ መንገድ ለትራንስፖርት አስቸጋሪ እና ጠባብ የነበረ በመሆኑ አሁን ላይ በገጠር እና በቀበሌ 7 ሜትር ፣ በዞን እና በወረዳ 14 ሜትር ፣ በከተማ ደግሞ 21 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ተገንብቷል፡፡
ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ በ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘዉ አምቦ ከተማ ተነስቶ ወሊሶ ከተማ ላይ የሚያበቃ ነው፡፡
የመንገዱ መጠናቀቅ የምዕራብ ሸዋ(አምቦ) እና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ(ወሊሶ) ከተሞችን እንዲሁም የጭቱ ወረዳን፣የዳርያን እና አልቱፋ ቀበሌዎችን በቅርበት በማስተሳሰር ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜን ያሳጥራል፡፡
የአምቦ ወሊሶ መንገድ የህብረተሰቡን የትራንስፖርት ችግር ከመቅረፍ ባሻገር በአካባቢዉ የሚመረቱ እንደ ጤፍ ፣ እንሰት ፣ ገብስ እና በቆሎ ምርቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲወጣ በማድረግ አምራችና ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
በተጨማሪም የቱሪዝም መዳረሻ የሆነው ‘’የወንጪ ሃይቅ’’ መንገዱ በሚያልፍበት በኩል የሚገኝ በመሆኑ ለቱሪዝም ዘርፉ እድገት ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 4 026 |
| 8 | بدون متن... | 5 984 |
| 9 | የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ የአስፋልት መንገድ በይፋ ተመረቀ
ጅግጅጋ ፣ ግንቦት 14፣ 2018 (ኢመአ)፦ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የሚታየውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ በዘላቂነት ለመቅረፍ ታቅዶ ሲገነባ የቆየው የጅግጅጋ ተለዋጭ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጠናቆ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመርቋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ፣ የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር የትምጌታ አሥራት፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሃመድ አብዱራህማን (ኢንጅነር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል የመንግሥት የሥራ ኅላፊዎች ፣ የሃገር ሽማግሌዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ በበኩላቸው፣ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ለምስራቁ የሀገራችን ክፍል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር ከማጠናከሩ ባለፈ፣ ማህበራዊ ግንኙነታችንን ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል ብለዋል አያይዘውም የመሰረተ ልማቱ መጠናቀቅ በቀጣይ ለምናከናውናቸው ታላላቅ ስራዎች ከፍተኛ መነሳሳትን የሚፈጥር ስኬት እንደሆነም ገልጸዋል።
በግንባታው ሂደት ኃላፊነታቸውን በብቃት ለተወጡ ባለድርሻ አካላት በሙሉ ላቅ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ ያሉ ሲሆን በክልላችን የሚከናወኑ ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችም በተቀመጠላቸው የጥራት ደረጃና የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በአጽኖት ገልጸዋል።"
ዛሬ የምናከብረው የአንድ መንገድ መጠናቀቅን ብቻ አይደለም፤ ዛሬ የምናከብረው የሕዝባችንን የልማት ጥማት የመለሰ፣ የከተማችንን የኢኮኖሚ አቅም ያሳደገ እና የሁለንተናዊ ዕድገታችንን ማሳያ የሆነ ትልቅ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ያሉት የከተማና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ አያይዘውም ጅግጅጋ የብዙ ባሕሎች፣ የፍቅርና የኢኮኖሚ መገናኛ መሆኗ ይታወቃል። ይህ መንገድ ደግሞ ይሄንን መገናኛ ይበልጥ ያሳለጠና ያቀላጠፈ ያደርገዋል ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሃመድ አብዱራህማን በበኩላቸው፣ የፕሮጀክቱን ጥራትና ደረጃ አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር ከመንግሥት በተጣለበት አገራዊ አደራ መሰረት የሀገራችንን የመንገድ መሠረተ-ልማት ግንባታ ለማፋጠን እና የሕዝባችንን ተደራሽነት ለማሻሻል የሚያደርገውን ጉዞ ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
ይህንን ዘመናዊ መንገድ ተንከባክቦ እና ጠብቆ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጥ የማድረግ ኃላፊነት ደግሞ የሁላችንም ነው በተለይም ደግሞ የናንተ የነዋሪው ህዝብ ነው ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈውል።
ይህ 7.3 ኪሎ ሜትር ርዝመትና 30 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ሰፊ መንገድ፣ የእግረኛ መሄጃዎችን ጭምር ያካተተ በመሆኑ ለከተማዋ ልዩ ውበትን ሰጥቷታል።
በተለይም ከቶጎ ጫሌ እና ከደገሀቡር የሚመጡ ከባድና ቀላል የጭነት ተሽከርካሪዎች የከተማዋን መሃል ሳያቋርጡ እንዲያልፉ የሚያስችል አማራጭ በመሆኑ፣ በከተማዋ መግቢያና መውጫ ላይ ይታይ የነበረውን አድካሚ የትራፊክ መጨናነቅ በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል ።
ለግንባታው 672 ሚሊዮን 98 ሺህ 730 ብር ከ28 ሳንቲም ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት የተሸፈነ ሲሆን፣ ሀገር በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ግንባታውን ሲያከናውን፣ ኤልዳ እና ዳምራ አማካሪ ድርጅቶች ደግሞ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን በጋራ አከናውነዋል።
ፕሮጀክቱ የጅግጅጋን ሁለንተናዊ ዕድገት በማፋጠን ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው በምረቃው ወቅት ተመላክቷል።
መንገዱ ግንባታው ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ ደረጃውን የጠበቀ የትራፊክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 4 604 |
| 10 | بدون متن... | 4 491 |
| 11 | +9 WhatsApp Image 2026-05-21 at 11.37.24 AM (1).jpeg | 0 |
| 12 | የዩኒሳ - ቢሾፍቱ የመንገድ ግንባታ ሥራን ለማፋጠን እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኢመአ) በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች መካከል ያለውን ትስስር ለማጠናከር ከሚከናወኑ ዋና ዋና የመግቢያና መውጫ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው የ 16 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር የዩኒሳ - ቢሾፍቱ መንገድ ግንባታና ማስፋፊያ ሥራን ለማፋጠን እየተሰራ ይገኛል።
ይህ ግንባታ የዩኒሳ - ገላን - ቢሾፍቱ - በዩ የመንገድ ፕሮጀክት አካል ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት የዚሁ ፕሮጀክት ክፍል የሆነው የዩኒሳ - ቢሾፍቱ ሎት 3 የመንገድ ግንባታ በይፋ ተጀምሮ ሥራው እየተካሄደ ነው።
ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የራስ ሀይል ኮንስትራክሽን አማካኝነት እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን የመከላከያ ዲዛይን ድርጅት ደግሞ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በኢትዮጵያ መንግሥት በተመደበ 8 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር የሚከናወነው ይህ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት በጅማሬ ላይ በመሆኑ በአብዛኛው የአፈር ቁፋሮ እና የሙሌት ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው።
የመንገዱን መጨናነቅ በዘላቂነት ለመቅረፍ ታስቦ የሚገነባው ይህ መንገድ ቀደም ሲል ከከተማ ውጭ 7 ሜትር፣ በከተማ ውስጥ ደግሞ 14 ሜትር ብቻ የነበረው ስፋቱ ወደ 30 ነጥብ 5 ሜትር ከፍ እንዲል ተደርጎ የሚገነባ በመሆኑ የትራፊክ ፍሰቱን በከፍተኛ ደረጃ ያቀላጥፋል።
ግንባታው አዲስ አበባን እንደ ዱከም፣ ገላንና ቢሾፍቱ ካሉ የኢንዱስትሪ ማዕከላት ጋር በቀጥታ በማገናኘት፣ በመሃል አገርና በክልል ከተሞች መካከል ያለውን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ያሻሽላል ።
በተለይም እስከ ጅቡቲ ወደብ በሚዘልቀው ዋና መስመር ላይ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ በመቀነስ የትራንስፖርት ፍሰቱን ያቀላጥፋል።
ከዚህ በተጨማሪ በከተማዋ የሚገነባው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መግቢያና መውጫ መስመር በመሆን የሚያገለግል ይሆናል።
በተመሳሳይ መልኩ ለቢሾፍቱ የቱሪዝም ዘርፍ መነቃቃትና ለአካባቢው መሠረተ ልማት መዘመን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑ ለአካባቢው ህብረተሰብ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘመናዊና ፈጣን የትራንስፖርት አገልግሎት ተደራሽ ያደርጋል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 3 794 |
| 13 | بدون متن... | 4 180 |
| 14 | بدون متن... | 4 012 |
| 15 | የጊንጪ-ሽኩቴ ሎት 1፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በዚህ አመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት11/2018 (ኢ መ አ):- 62 ነጥብ 2 ኪሎሜትር የሚረዝመው የጊንጪ - ሽኩቴ ሎት 1 አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በዚህ አመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ።
አሁን ላይ 88 በመቶ የሚሆነው የግንባታ ሥራው የተጠናቀቀ ሲሆን 59 ኪሎ ሜትር የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የዉሃ ማፍሰሻና የፉካ ስራዎች ፣ የሰብቤዝ ፣ የቤዝኮርስ ስራ እንዲሁም 58 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተከናውኗል፡፡
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን በማከናወን ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ገምሹ በየነ ጠቅላላ የሥራ ተቋራጭ ነው።
የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ፎርትረስ ኢንጂነሪንግ ከኮንሰልታንትስ ከአሶሼትስ ማህበር ጋር በጥምረት እየሰሩት ናቸው።
የግንባታው 1,150,000,000 (አንድ ቢሊየን አንድመቶ ሀምሳ ሚሊዮን )ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው።
መንገዱ በወረዳ 18 ፣ በቀበሌ 14.2 ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ የሚገኝ በመሆኑ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜን የሚያሳጥር ይሆናል።
የጊንጪ - ሽኩቴ የመንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ በምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኙትን ደንዲ እና ጀልዱ ወረዳዎችን እንዲሁም ሶስት ቀበሌዎችን ጨምሮ የጎጆ እና የሽኩቴ ከተሞችን በቀላሉ ለማስተሳሰር ያስችላል።
በተጨማሪም በአካባቢው የሚገኙትን የስንዴ ፣ የጤፍ ፣ የገብስ እና የቅባት እህል ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማውጣት ያግዛል ፡፡
እንዲሁም በዚሁ በአከባቢ የሚገኘው የጭልሞ ደን ለጎብኚዎች ተደራሽ እንዲሆን በማድረግ ለሀገራችን የቱሪዝም እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡
የዚሁ መንገድ አካል የሆነውን 63 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የሽኩቴ - ጩሉጤ ቀጣይ ክፍል ወደስራ ለማስገባት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 3 516 |
| 16 | بدون متن... | 0 |
| 17 | የቦኖሻ - አጫሞ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ዋና ዋና ሥራዎች በዚህ ዓመት ይጠናቀቃሉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 07/2018 (ኢ መ አ):- የሃዲያ እና ስልጤ ዞኖችን የሚያገናኘው የቦኖሻ - አጫሞ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ዋና ዋና ሥራዎች በዚህ ዓመት ይጠናቀቃሉ ።
የመንገድ ፕሮጀክቱ 22 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል።
አሁን ላይ የ21 ኪ. ሜ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ19 ኪ. ሜ ሰብቤዝ፣ የ7 ኪ. ሜ ቤዝኮርስ፣ የ4 ኪ.ሜ የአስፋልት ንጣፍ እንደዚሁም የውኃ መፋሰሻ ቱቦ እና የከልቨርት ሥራዎች ተሠርተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የ1 ድልድይ ግንባታ ተጠናቅቋል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ አፈጻጸሙ 81 ነጥብ 72 በመቶ ደርሷል። የግንባታውን ዋና ዋና ሥራዎች በቀጣይ ጥቂት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ አስፈላጊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቅቀዋል።
የመንገድ ግንባታውን ሀገር-በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ከፌደራል መንግሥት በተመደበ 682 ሚሊዮን ብር ወጪ በማከናወን ላይ ይገኛል። ጎንዱዋና ኢንጅነሪንግ የፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ያከናውናል።
የመንገድ ግንባታ ሥራው ሲጠናቀቅ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ መቀመጫ የኾነችው ሆሳዕና ከተማ ተነስቶ ወደ ሃላባ እና ሐዋሳ እንዲሁም በዙሪያው የሚገኙ ከተሞች በቀላሉ ለመንቀሳቀስ ያስችላል።
በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የበርበሬ፣ በቆሎ እንዲሁም መሰል የግብርና ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል።
ከዚህ ቀደም ከሆሳዕና ወደ ሃላባ ለመጓዝ በውልባራግ በኩል ይደረግ የነበረውን ረጅም እና አድካሚ ጉዞ በማስቀረት በአቋራጭ ለመጓዝ ያስችላል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 0 |
| 18 | بدون متن... | 0 |
| 19 | የባህርዳር - ጢስ እሳት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀምን ለማሻሻል እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28 2018 ዓ.ም (ኢመአ):- 21 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውን የባህርዳር - ጢስ እሳት የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀምን ለማሻሻል እየተሰራ ይገኛል፡፡
እስካሁን ባለው የመንገዱ ግንባታ የዲዛይንና የቅየሳ ስራዎች ተጠናቀው 16.44 ኪሎ ሜትር የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ 5.02 ኪሎ ሜትር የሰብቤዝ፣ 4.8 ኪሎ ሜትር የቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም 4.5 ኪሎ ሜትር የሚሆን የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተከናውኗል።
ግንባታው በሀገር በቀሉ መልኮን ኮንስትራክሽን እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ጎንድዋና ኢንጅነሪንግ ከዋይ.ኤል.ኤስ ኢንጅነሪንግ ጋር በጥምረት የማማከር ሥራውን እየሰሩት ይገኛሉ።
ለግንባታው የሚውለው 957,930,208.44 (ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ሰባት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰላሳ ሺህ ሁለት መቶ ስምንት ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው።
በመንገዱ ክልል ውስጥ የሚገኙ ንብረቶች በወቅቱ አለመነሳት፣ የካሳ ክፍያ መዘግየት ፣የአካባቢው የፀጥታ ችግሮች እና የሥራ ተቋራጩ አፈፃፀም ማነስ በሥራው ላይ ጫና ፈጥሮ ቆይቷል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ችግሮቹን ለመፍታት ከአካባቢው መስተዳደር ጋር በመሆን ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ የመንገድ ፕሮጀክት የአካባቢውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ከመሆኑ ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ከባህር ዳር ከተማ ጋር በማገናኘት የመጓጓዣ ጊዜንና እንግልትን በመቀነስ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡
በተጨማሪም እንደ ጤፍ፣ ሸንኮራ፣ ሽንኩርት እና ጫት ያሉ የግብርና ምርቶችን በፍጥነት ለገበያ ለማቅረብ ከማስቻሉም በላይ የጢስ አባይ ፏፏቴን ለጎብኚዎች ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንደሚያሳድግ ይታመናል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads | 0 |
| 20 | بدون متن... | 0 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
