2 243
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-5030 days
Posts Archive
Repost from Yeka Education
⭐️ፋኖስ ለተማሪዎች⭐️
✅ፋኖስ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ለሆኑ ተማሪዎች በነጻ የተዘጋጀ የonline የመማሪያ platform ነው።
✅ከ14,000+ በላይ ጥያቄዎችን፣ አጫጭር ማስታወሻዎችን፣ ቪዲዮዎችን እና ፍላሽ ካርዶችን በነጻ የሚያገኙበት።
🫴🫴🫴🫴🫴🫴
https://www.fanoslms.org
👆👆👆👆👆
በፋኖስ በነጻ ያጥኑ!
ቻናላቸው ይህ ነው
🫴👇👇👇👇👇
https://t.me/FanosLMS
🔤🔤🔤🔤 🔤🔤🔤
🔤🔤🔤🅰️ 🔤🔤🔤
🔠🔠🔠🅰️ 🔠🔠🔠
Repost from AASTU POLL AND QUIZ QUESTIONS
ልዩ የትምህርት ድጋፍ እድል ከፋዌ ኢትዮጵያ
ፋዌ ኢትዮጵያ እና ፋዌ አፍሪካ ከ ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በ 2018 ዓ.ም እድሚያቸው ከ 15 እስከ 25 የሆኑ ወጣቶችን በተለይም በዝቅተኛ ኢኮኖሚያዊ ደረጃ የሚገኙ ሴቶችን ፣የአካል ጉዳተኛ ወጣቶችን፣ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮችን እና የውጭ ሀገር ስደተኞች ተጠቃሚ የሚያደርግ የከፍተኛ የትምህርት እድል ተጠቃሚ እንድትሆኑ ሲጋብዝ ታላቅ ደስታ ይሰማዋል፡፡ ድጋፉ ሁሉን አቀፍ የገንዘብ፣የትምህርትና ስልጠና እንዲሁም የማህበራዊ ድጋፍን የሚያካትት ሲሆን የትምህርት ድጋፉ የሚሰጠው በቴክኒክና ሙያ የትምህርት ተቋማት ውስጥ በሚሰጡ የሳይንስ፣ቴክኖሎጂ፣ምህንድስናና ተዛማጅ የትምህርት ዘርፎች/STEM/ ደረጃ 4 እና 5 ኮርሶች ነው፡፡
ትምህርት ስልጠናና ድጋፉ የሚሰጠው በአዲስ አበባ ከተማ በጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ እና አዲስ አበባ ተግባረ እድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች፣ አዳማ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ ሀዋሳ ፖሊ ቴክኒክና ሀዋሳ ተግባረ እድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች እንዲሁም በባህርዳር ፖሊ ቴከኒክ ኮሌጅ በሚሰጡት የመደበኛ የትምህርትና ስልጠና መርሃግብሮች ሲሆን ሙሉ ዝርዝር መረጃ ከስር ባለው ሊንክ ይመልከቱ።
👉 https://shorturl.at/5w9EC
የማመልከቻ ቀን ከ ጥቅምት 17-21 ፤ 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን ከተጠቀሰው ቀነገደብ ዉጭ የሚመጡ አመልካቾችን የማናስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ እንገልጻለን።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥሮች
አዲስ አበባ በ 0981642541
አዳማ በ 0981643411
ባህርዳር በ 0981638351
ሀዋሳ በ 0981630651 በመደወል ወይም በድህረገጻችን www.faweethiopia.org ይጎብኙ፡፡
ምዝገባዉም ሆነ የመረጣው ሂደት ከማንኛዉም ክፍያ ነጻ መሆኑን እናሳዉቃለን!
Repost from N/a
በ2017 ዓም በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 500 እና በላይ ያመጡ የት/ቤታችን ዕንቁ ተማሪዎች ደግሰው አማኑ እና ሙሉጌታ አፈወርቅ በ19/292018 ዓም Samsung Galaxy Tablet ከአዲስ አበባ ት/ቢሮ ተሸልመዋል ።(የተማሪ ሙሉጌታን ሽልማት አባቱ ተቀብለዋል ።)
Repost from ATC NEWS
#National_ID
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ለመቀመጥ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ቅድመ ሁኔታ ተደረገ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት " ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ለፈተና ለመቀመጥ ቅድመ ሁኔታ ነው " ብሏል።
" ማንኛውም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ከፈተና ምዝገባ ቀድሞ ማውጣትና በእጁ መያዝ ይገባዋል " ሲል አሳውቋል።
" ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) የሌለው ተማሪ ለፈተና መመዝገብ ሆነ በማንኛውም ሁኔታ መፈተን አይችልም " ሲል አስገንዝቧል።
ተማሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ይዘው እንዲገኙ ፦
- የተማሪ ቤተሰብ
- መምህራን
- የትምህርት አመራሮች
- የሚዲያ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
#National_ID
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Repost from Yeka Education
✅የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ9-12ኛ ክፍል ይሸፍናል"
✅ የ2018 ዓ.ም. ፈተና ዝግጅትን አስመልክቶ ጥቅምት 06 ቀን 2018 ዓ.ም ከክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጋር በበይነ መረብ ባደረግነው ስብሰባ በቀረበው ምክረ-ሃሳብ ላይ ውይይት በማድረግ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
✅በዚህም መሠረት የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ዝግጅት፡
✔️1. በሥርዓተ-ትምህርቱ መሠረት የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚሽፍን ሲሆን ተማሪዎች የተማሩትን ይዘቶች የሚፈተኑ መሆኑን፤
✅2. ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍሎች የአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት ይዘቶችን መሠረት ያደረገ መሆኑን፤
✔️3. በ2015 ዓ.ም. የሙከራ ትምህርት ቤቶች 9ኛ ክፍልን በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት፤ ሌሎቹ በቀድሞው ሥርዓተ-ትምህርት የተማሩ በመሆኑ ፈተናው ከሁለቱ ሥርዓተ-ትምህርቶች የጋራ የሆኑ ይዘቶች ተጣጥሞ የሚወጣ መሆኑን፤
✔️4. የፈተና ዝግጅቱ ከላይ በተጠቀሱት መሠረት መሆኑን ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ መምህራንና የትምህርት ባለድርሻ አካላት አውቀው ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንዲደረግ እናሳስባለን፡፡
(ትምህርት ሚኒስቴር)
⌨️⌨️⌨️⌨️ ⌨️⌨️⌨️
🔤🔤🔤🔤 🔤🔤🔤
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/dam76
Repost from N/a
14/2/2018 ዓም
ለሚሊኒየም አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ወላጆች
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን ለማላቅ (ለማሻሻል ) በተቀየሰው ስትራቴጂ እቅድ ላይ ለመወያየት እሁድ ጥቅምት 16/2017 ዓም ከጠዋቱ 2:30 አጭር ስብሰባ ስለሚኖረን በተባለው ቀንና ሠዓት በት/ቤት እንድትገኙ እናሳስባለን ።
ማሳሰቢያ :- ወላጆች ለስብሰባ ስትመጡ የወላጅ መጥሪያ ይዘው ይምጡ።
Repost from N/a
ስቲፕ ፕሮጀክት ከ አጋር ትምህርት ቤቶች ጋር በመተባበር በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት ላልመጣላቸው ሴት የሳይንስ ተማሪዎች የሚሆን የ ሬሚዲያል ቱቶሪያል ፕሮግራም፣ ነፃ የፈተና መለማመጃ፣ ወደ ቴክኒክ እና ሙያ መቀላቀል ለሚፈልጉ ደግሞ የጉብኝት እና የመሳሰሉትን አገልግሎቶች አቅርቦላችኋል። ስለዚህ በዚህ እድል ለመጠቀም የምትፈልጉ ከታች ባስቀመጥነው ሊንክ በመመዝገብ ወይም መገናኛ ከግሬስ ሲቲ ሞል አጠገብ ሲሳይ ፕላዛ 3ኛ ፎቅ በሚገኘው የሀሁ ጆብስ ተቋም በአካል በመገኘት መመዝገብ እና አገልግሎቱን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የሪሚዲያል ፕሮግራም #የማያስተናግዱ ዩኒቨርሲቲዎች ፦
1. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
2. አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
3. አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
4. ሲቪል ሰርቪርስ ዩኒቨርሲቲ
5. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
6. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
7. ኮተቤ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ናቸው።
ተማሪዎች የሞሉትን ምርጫ በ student.ethernet.edu.et በኩል ማረጋገጥ የሚችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
Via @tikvahuniversity
Repost from N/a
3/2/2017 ዓም
ለ2017 ዓም 12ኛ ክፍል ለተፈተናችሁ ተማሪዎች በሙሉ
የ12ኛ ክፍል ሠርተፊኬት የመጣ ስለሆነ ከጥቅምት 4 እስከ 5/2018 ዓም ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ት/ቤት በመምጣት እንድትወስዱ እናሳስባለን ።
ት/ቤቱ!
Repost from FanosLMS
የፋኖስ Friday Quiz አሸናፊዎች! 🥳
ለሁላችሁም 🎉እንኳን ደስ አላችሁ! እያንዳንዳችሁ የUnlimited የኢንተርኔት ፓኬጅ ተሸላሚ ሆናችኋል።
🎁
🏆 የዚህ ሳምንት አሸናፊዎቻችን:
ከኢንስታግራም: @abig_u1212
ከቲክቶክ: @fuad@25 21 እና @teshaleamanuel415
ከቴሌግራም: @bleachard
ለተሳተፋችሁ ሁሉ እናመሰግናለን! ቀጣይ አሸናፊ ለመሆን፣ የፋኖስን ሶሻል ሚዲያዎችን ፎሎው አድርጉና ዛሬውኑ በፋኖስ ማጥናት ጀምሩ!
www.fanoslms.org
#Fanos #FridayQuiz #QuizWinners #LearnAndWin #Ethiopia #FanosFriday
29/1/2018 ዓም
ማስታወቂያ
በ2017 ዓም የሀገር አቀፍ ፈተና ውስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ሞልታችሁ ነገር ግን የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ቅሬታ ያላችሁ ተማሪዎች እሰከ መስከረም 30/2018 ዓም 4፡00 ሠዓት ድረስ ት/ቤት በመገኘት እንድታመለክቱ እናስባለን፡፡
የ2018 ዓ ም ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት 300 እና በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች መረጃ የላካቹህል መሆኑ ይታወቃል
በመሆኑም ትምህርት ሚኒስትር በድጋሜ 297 እና በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች የማለፊያ ነጥቡን ያሟሉ ናቸው ብሎ በወሰነው መሰረት በእናንተ ትምሀርት ቤት ከዚህ ቀደም ከላካቹህት የተማሪ ቁጥር ለውጥ መረጃ እንድትልኩል እሳውቃለን
Repost from N/a
29/1/2018 ዓም
ማስታወቂያ
በ2017 ዓም የሀገር አቀፍ ፈተና ውስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ሞልታችሁ ነገር ግን የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ቅሬታ ያላችሁ ተማሪዎች እሰከ መስከረም 30/2018 ዓም 4፡00 ሠዓት ድረስ ት/ቤት በመገኘት እንድታመለክቱ እናስባለን፡፡
Repost from Yeka Education
⭐️የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ።
✅ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የRemedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን አሳውቋል።
✅1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን።
✅2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ።
🌟የመቁረጫ ነጥብ ፦
✅ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216
✅ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204
✅ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
✅ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
✅ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165
via👉#MoE
🔤🔤🔤🔤 🔤🔤🔤
ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇
❤️❤️❤️❤️❤️
https://t.me/dam76
