Milli Yeka Secondary School
Show more
2 239
Subscribers
+524 hours
+237 days
+5430 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
4/9/2016 ዓም
ማስታወቂያ
ለ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች
የሚሊኒየም አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ2016 ዓም 12ኛ ክፍል ተፈታኝ የሆኑ የተወሰኑ ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ እየተገኙ ባለመሆኑ በውጤታቸው ላይ ተጽእኖ ሊኖረው እንደሚችል ከወዲሁ መገመት ይቻላል፡፡ በመሆኑም ከግንቦት 5/2016 ዓም ጀምሮ በትምህርት ገበታቸው ላይ የማይገኙ ተማሪዎችን ባላቸው የቀሪ ብዛትና በተማሪዎች መተዳደሪያ ደንብ ላይ በተቀመጠው የዲስፕሊን ህግ መሰረት አድሚሽን ካርድ የማኝሰጥና ከፈተናም ጭምር ለማገድ የምንገደድ ሲሆን በመቅረታቸው ምክንያት ለሚፈጠረው ችግር ት/ቤቱ ሀላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን፡፡ ወላጆችም ልጆቻችሁ በትምህር ገበታቸው ላይ አንገኙ እንደታደርጉ እናሳስባለን፡፡
በ2016 ዓም የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኝ ተማሪወች ለፈተና ዝግጅትና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ከወላጅ ጋር ለመወያየት ስለፈለግን ወላጆች ግንቦት 11/2016 ዓም ከጠዋቱ 3፡00 ሠዓት ላይ በት/ቤቱ እንድትገኙልን በአክብሮት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
ት/ቤቱ!
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የ2016 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና መርሃ ግብር ይፋ ሆነ፡፡
(ግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም) ከትግራይ ክልል ውጭ በሁሉም ክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች ላሉ ተፈታኞች በወረቀትና በበይነ መረብ የሚሰጠው የፈተና መርሃ ግብር የሚከተለው መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የገለጸ ሲሆን ተፈታኞችና የሚመለከታቸው ሁሉ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስባል፡፡
የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን በጋራ እንከላከል!
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- [email protected]
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
ተማሪ ሀኒ ታሪኩ ከ10ኛ 9 ክፍል በውድድሩ ተሳታፊ ሆና ከ7ቱም 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 1ኛ በመውጣት ት/ቤታችንን ያስጠራች የጀግኖች ጀግኒት ነሽ በርችልን !!!
እንኳን ደስ አላችሁ !!!
ቀን 3/8/2016
✅የየካ ክፍለ ከተማ የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ቡድን ከየካ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር አካሄደ::
✅በውድድሩ 7ቱም የመንግስት 2ኛ ደ/ት/ቤቶች የተሳተፋ ሲቀሆን ውድድሩ እጅግ ፋክክር የበዛበት እና ተማሪዎች በመለያ ጥያቄ የተለዩበት ነበር::
⭐️በውድድሩ ከ1ኛ-3ኛ ለወጡ ት/ቤቶች የምስክር ወረቀት የተበረከተ ሲሆን
✔️ ለአሸናፊ ተማሪዎች የገንዘብ እና የምስክር ወረቀት ሽልማት በየካ ክ/ከተማ የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ቡድን መሪ ወ/ሮ ናናቲ ገዝሙ ተበርክቷል::
በውድድሩም ከ1ኛ -3ኛ የወጡ ት/ቤቶች
✅ሚሊኒየም 2ኛ ደ/ት/ቤት 1ኛ
✅ተ/ብርሀን 2ኛ ደ/ት/ቤት 2ኛ
✅ብርሀን ጉዞ 2ኛ ደ/ት/ቤት 3ኛ
ወጥተዋል
ቻናላች ይህ ነውውውው
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/yeka2016channel
Repost from Yeka Sub City Education Office
✅ኩረጃ ምንድን ነው?
(በድጋሜ የተለጠፈ)
✅ከዚህ ቀደም ቢቢሲ በሰራው አንድ ዘገባም ተማሪዎች ለኩረጃ ይመቻቸው ዘንድ ከጎበዝ ተማሪዎች ጋር በማመሳሰል ስማቸውን በፍርድ ቤት አስለውጠዋል።
✅ኩረጃ በአንድ የፈተና ክፍል ውስጥ ብቻ የሚካሄድ ሳይሆን በዕለት ተዕለት ትምህርት ስርዓት ውስጥ የሚዳብር መሆኑን ጨምረው ያስረዳሉ።
✅የራስ ያልሆነን ስራ እንደራስ አድርጎ ማቅረብ፣ ትክክለኛ ምክንያት ባለመስጠት መምህሩን ማሳሳት እና የማይገባውን ውጤት ለማግኘት የሚደረግ ጥረት፣ ያልተገባ ውጤት ለማግኘት መምህርን ማታለል በአጠቃላይ ኩረጃ ነው ይላሉ ወንድይፍራው (ዶ/ር)።
✅ጓደኛ እንዲኮርጅ መርዳት፣ በግል የተሰጠ ምዘናን ወይንም የቤት ሥራ በቡድን መስራት ሁሉ በኩረጃ ስር እንደሚጠቃለሉ ጨምረው ይገልጻሉ።
✅በትምህርት ቤት ሕይወታቸው ቢያንስ አንድ ጊዜ በኩረጃ ላይ የተሳተፉ ግለሰቦች በርካታ መሆናቸውን በተለያዩ አገራት የተሰሩ ጥናቶች ያሳያሉ።
✅ተማሪዎች የሚኮርጁት ለፈተናው ወይንም ደግሞ ምዘናው በቂ የስነልቦና ዝግጅት ሳይኖራቸው ሲቀር መሆኑን ይናገራሉ።
✅ተማሪዎች በተገቢው መጠን ራሳቸውን ካለመዘጋጀት ውጪ፣ ትምህርትን በአግባቡ አለመከታተል፣ ኩረጃ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሌለው ግንዛቤ መያዝ ወደ ኩረጃ የሚገፉ ሌሎች ምክንያቶች ናቸው ይላሉ።
✅ከዚህም በተጨማሪ ወንድይፍራው (ዶ/ር) እንደሚሉት የወላጆች 'ልጆቼ ተምረው፣ ሕይወቴን ይለውጡኛል' የሚለው ገለጻ ልጆች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳርፋል።ይህ ቤተሰብ የሚያደርገው ጫና ተማሪዎችን ለማበረታታት የተደረገ ነገር ቢሆንም ለኩረጃ እንደሚገፋም ያስረዳሉ።
✅በራሱ ጥረት ወላጆቹ ወዳሰቡለት ስኬት መድረስ ያልቻለ ተማሪም የወላጆቹን ጫና ለመሸሽ ጎበዝ የሚባሉ ተማሪዎችን በመደገፍ ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ይሞክራል በማለት ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ። ኩረጃ ከክፍል ክፍል ሲኬድ እያደገ የሚሄድ ብቻ ሳይሆን፣ በሕይወት ውስጥ ዘላቂ የሆነ ተጽዕኖ እንዳለውም ጨምረው ገልፀዋል።
✅"ጥናቶች እንደሚያመለክቱት በትምህርት ዓለም የነበረን የኩረጃ ሕይወት ወደ ሥራ ዓለም ስንገባም ያንኑ የመተግበር እድሉ ከፍተኛ እንደሆነ እና ተያያዥነት እንዳለው ነው፤ አንድ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ በኩረጃ ታግዞ ወደ ከፍተኛ ተቋም ሲገባ፣ እዚያም በኩረጃ ታግዞ ቢመረቅ በስራው ዓለም መደለያ ለመቀበል አያቅማማም።"
✅ተማሪዎች በጓደኞቻቸው ዘንድ ሰነፍ ሆኖ ላለመታየት፣ በውጤት አንሶ ላለመገኘት፣ ወደ ኩረጃ እንደሚገቡም አክለው ተናግረዋል።ተማሪዎቹ ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባታቸው በፊት፣ ለኩረጃ ሲዘጋጁ ኔትወርክ ፈጥረው፣ የመጀመሪያው እቅድ ባይሳካ በሚል ሁለት እና ሶስት እቅዶችን ነድፈው መሆኑንም ጠቅሰዋል።
✅ከዚህ በተጨማሪ የነደፉት ስልት በፈተና የመጀመሪያ ቀን ካልሰራ፣ ለቀጣዩ ፈተና ቀን ሌላ ስልት ነድፈው እንደሚመጡም ይናገራሉ።ከዚህ የሞባይል ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያደርጉት ኩረጃም ከትምህርት ቤት ውጪ ያሉ ግለሰቦችን እንደሚያካትቱ ጨምረው ያስረዳሉ።
✔️ለፈተና ራሳችንን እናዘጋጅ
✔️ኩረጃን/ስርቆት እንጠየፍ
✅ቻናላችን ይህ ነው✅
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/dam76
ክፍል ሁለት ይቀጥላል
👇👇👇👇👇👇
1/9/2016 ዓም
ለ12ኛ ክፍል መምህራን በሙሉ
በ2/9/2016 ዓም ከጠዋቱ 2:30ሠዓት ላይ አስቸኳይ ስብሰባ ስላለን በቤተ-መፃህፍት እንድትገኙ እናሳስባለን ።
ት/ቤቱ
01/09/2016 ዓም
ለሚሊኒየም አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና አፈታተን እና በትምህርት ዙሪያ አጭር ውይይት ስለሚኖረን ግንቦት 2/2016 ዓም ከጠዋቱ 2፡00 ሠዓት ላይ በት/ቤት ቤተ-መፃህፍት እንደትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
ት/ቤቱ!
29/8/2016 ዓም
ለ12ኛ ክፍል መምህራን በሙሉ
በ30/8/2016 ዓም ከጠዋቱ 3:00ሠዓት ላይ አስቸኳይ ስብሰባ ስላለን በቤተ-መፃህፍት እንድትገኙ እናሳስባለን ።
ት/ቤቱ
✍ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እና በዓሉን ለሚያከብሩ ሁሉ እንኳን ለጌታችን ለመዳንታችን እየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን።
👭በዓሉ የፍቅር፣የደስታና የሰላም ጊዜ ይሁንልን። 🎄🎄🎄
🌸መልካም በዓል!!!
✍Hordoftoonni amantaa Kiristaanaa fi warreen ayyaanicha kabajjan hundi keessan baga Du'aa Ka'uumsa Gooftaa fi Fayyisaa keenya Iyyesuus Kiristoosin isin gahe, nuun gahe. 🌺🌸
👭Ayyaanichi kan jaalalaa, kan gammachuu fi nageenya ittin argannu nuuf haa ta'u. 🌲🌺
🌹Ayyaana gaarii !!!