en
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

Open in Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል! @Alazartewodros1 የጥበብ

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel የጥበብ ማዕድ

Channel የጥበብ ማዕድ (@alazartewodros1) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 171 subscribers, ranking 5 550 in the Religion & Spirituality category and 2 242 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 171 subscribers.

According to the latest data from 16 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -400 over the last 30 days and by -11 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 5.38%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 1.79% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 816 views. Within the first day, a publication typically gains 272 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ዝም ብለህ ተቀላቀል! @Alazartewodros1 የጥበብ

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 17 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 171
Subscribers
-1124 hours
-657 days
-40030 days
Posts Archive
ምስኪን ድህነት ውስጥ ባሷ አምልጣህ እየተከተልካት ስትሮጥ ያለው ስሜት ልብ ላለው አይነገርም።

" ለሕዝቧ ምቹ የሆነች፣ ለጠላቶቿ የማትንበረከክና በአለት ላይ የጸናች ሀገር ለመገንባት በአንድነት መሥራት ይገባል " - ሼይኸ መሀመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ በረከታቸው ይደርብን አይናችንን መግለጥ
" ለሕዝቧ ምቹ የሆነች፣ ለጠላቶቿ የማትንበረከክና በአለት ላይ የጸናች ሀገር ለመገንባት በአንድነት መሥራት ይገባል " - ሼይኸ መሀመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ በረከታቸው ይደርብን አይናችንን መግለጥ እስኪያቅተን ሐብትና እድሜ ይስጠን። ምንም dr.no ቢረግማትም እኔ ሽሬዋለሁ እርግማኑን!😁 ‎

የሄደውን የሚተካ የመጣውን ሚወዳደር  እንደሌለ እስክናይ ድረስ..... የያዝነውን ላለመልቀቅ ያልመጣውን በመጠበቅ ይዘወራል ስጋ ከነፍስ ያልኖሩትን በመናፈቅ .,meron

ነገሩ ነው እንጂ ጥይት ሰው አይገልም!

ቀልዱ ውስጥ ቁምነገር ፤ ቁምነገር ውስጥ ቀልድ አለ!      አይኑ ውስጥ ጣት አለ አይነት ነገር ብቻ ነገሩ ውስብስብ ነው።

፡ ዝ ... ም .... ታ ‎የመቅጣቱን ያህል ‎ ያድናል መልሶ ‎በደል ሲጠወልግ ‎ ፍትህ ቀኑ ደርሶ ✍Mekdi @amen1995

እድሜህን ምታውቀው ያለፍካቸውን ቀኖች የታዘብ ቀን ነው።

አስር ዓይነ ስውሮች እጅ ለእጅ ተያይዘው ወንዝ ይሻገራሉ። ወንዙን ተሻግረው ከሌላኛው የወንዙ ዳርቻ ሲደርሱ ከመካከላቸው አንዱ «ስንት እንደሆንን ብንቆጥር የተሻለ ነው። አይነ ስውሮች በመሆናችን ምናልባት ከመካከላችን አንድ ሰው ወንዝ በልቶት ቀርቶ ሊሆን ይችላል። ወንዙ ኃይለኛ ስለነበር አንድ ሰው ወስዶብን ሊሆን ይችላልና እስኪ ስንት እንደሆንን እንቁጠር» አለ። እናም መቁጠር ጀመሩ። አንደኛው ሲቆጥር የቆጠረው ዘጠኝ ሰው ብቻ ሆነ። ምክኒያቱም መቁጠር የጀመረው እራሱን ትቶ አጠገቡ ካለው ሰው ነበር የጀመረው። ሁለተኛውም እንደገና ሲሞክር የቆጠረው እንደበፊቱ ዘጠኝ ሰዎችን ብቻ ሆነ። ከዚያ በጣም ፈሩ። ከመካከላቸው አንድ ሰው ጠፍቷል! ሶስተኛውም ሰውየ ሲሞክር ያው ዘጠኝ ሰዎች ብቻ ሆኑ። በዚ ዓይነት አንድ ሰው መጉደሉን እርግጠኛ ሆኑ። አጠገባቸው የተቀመጠ አንድ ሌላ ሰውየ የሚያደርጉትን ይመለከት ነበረና በዓይነስውሮቹ ጅልነት በመገረም ሳቀባቸው። ከዚያ ወደእነሱ ቀረብ አለና «ምን ሁናችኋል? ለምንድነው የምታለቅሱት?» ብሎ ጠየቃቸው። «አንድ ጓደኛችን ጠፍቶብናል። ወንዙን ከማቋረጣችን በፊት አስር ነበርን። አሁን ግን ዘጠኛችን ብቻ ነን የቀረነው። ወንዙ አንድ ሰው ወስዶብናል» አሉት። ሰውየው በጣም ግድ የለሽና መቀለድ የሚወድ ሳይሆን አይቀርም። « ግድ የለም አትጨነቁ። አንድ የምነግራቹን ነገር ብቻ አድርጉ። በሰልፍ ቁሙና እኔ በምነግራቹ መሰረት ትቆጥራላቹ ። አንድን ሰው አንድ ግዜ ስኮረኩመው «አንድ» ይላል ከዚያ ሁለተኛውን ሁለት ግዜ ስኮረኩመው «ሁለት» ይላል፤ በመቀጠልም ሶስተኛውን ሰው ሶስት ግዜ ስኮረኩመው «ሶስት» ይላል። በዚህ መልኩ እንቆጥራለን»አላቸው። «ይሄ በርግጥም ትክክለኛ ዘዴ ነው» አሉትና ተስማሙ። እናም መጨረሻ ላይ አስር ሆነው ተገኙ። ሰዎቹ በሙሉ እግሩ ላይ ወድቀው አመሰገኑ «እናመሰግናለን። ከትልቅ ችግር ነው ያዳንከን» ብለው መንገዳቸውን ቀጠሉ። ማስታወሻ:- እናንተ ማሰብ ስትጀምሩ ከራሳችሁ መጀመር አለባቹ። ስህተትም ብትሰሩ ሌላው ተጠያቂ ከማድረግ ይልቅ ኃላፊነትን ውሰዱ። ሌላ ሰው ሁለተኛ ሰው መሆኑን እወቁ።

🌼 ፈካሽ አሉ እንደልማድሽ ‎አማረባት ሲሉ ሰማሁ ቢጫ ለብሳ አጊጣለች ‎አደይ አንቺ ስትታደሽ ‎ናፍቃ ጓጉታ 'ምትጠብቅሽ የበፊቷ እኔ የታለች ✍ Mekdi @amen1995

፡ ኖሬ ኖርኩ የምልበትን ‎ ስቄ ደስ ብሎኝ ውዬ ‎በተስፋ የምኞቴን ቀን ‎ እናፍቃለሁ አንተዬ ‎ ✍ Mekdi @amen1995

፡ ደና ዋልክ ምትዪኝ፡ ምን አለኝ ልዩ ቀን ፥ ሚነገር  ተኑሮ፤ ቁጭ ብዬ ውላለሁ፡ የተዘራው ጤፍ፥      እስኪደርስ ከመዓድ ፡                      ተፈጭቶ ተጋግሮ። የለጠፍሽው ፎቶ፡       ቀኑ እስኪቃጠል ፡ ሌላ እስኪመጣ፤ አያለው ገፅሽን፡    ገንዘብ እንደ ራበው፡             እንደ ዘመኑ ደንብ፡                             ከስርሽ ፡ ሳልወጣ! ደግሞም አጠይቂ! ምን ሰራህ ዛሬ ቀን ፥ ስራ እንዳለው ሰው፤   እውላለው እንጂ፡ ካርዴን እየገበርኩ ፤ ቲክቶኩን ሳምሰው፡ ይልቅ ስጪኝ ልስራ፡             መቅኔዬን ልገብር፡                     ሰውነቴን ላልፋ፤ ትንፋሽ አለኝ ልሩጥ፡    ፈረሷን ጫጭኜ፡                       ከዚ እስከ ሰንዳፍ።    ልዘይራት አንቺው       አላዛር ቴዎድሮስ

በዝምታ ውስጥ ያለ ሰላም የፍጥረታት ፈጣሪ የሆን ያክል ተፈጥሮን እንድትረዳ ያደርግሃል።

ብዙዎቻችን ስልጣን እንጂ ያጣነው በቤታችን ፖለቲካ ስናወራ ጎበዝ ነን።

አትጨነቂ ይሄን ቃል ብዙ ሰዎች ደጋግመውባችሁ አያውቅም?😔 አንቺ ምን አለብሽ?ምን ቸግሮሽ?ምን ጎሎብሽ ነው አይንሽ እስኪያብጥ ምታለቅሽው? ለምንድነው እንዲህ ምቶኝው ፊትሽን በጭንቀት ነጠብጣቦች ስ
አትጨነቂ
ይሄን ቃል ብዙ ሰዎች ደጋግመውባችሁ አያውቅም?😔 አንቺ ምን አለብሽ?ምን ቸግሮሽ?ምን ጎሎብሽ ነው አይንሽ እስኪያብጥ ምታለቅሽው? ለምንድነው እንዲህ ምቶኝው ፊትሽን በጭንቀት ነጠብጣቦች ስለምን ታበላሻለሽ አታርፊም ብለውሽ አያቁም🥺 ወቅሰውሽ ሰድበውሽ ጥጋብ ነው እንዲህ ሚያደርግሽ ተብለሽ አታቂም??? አፍቅረሽ ነው? ብለውሽስ አያውቁም? ጭንቀትሽ ጨጓራሽን ልጦት ምግብ ሲዘጋሽ ፤በመከራ የበላሽውም ቃርቃር ሲልሽ አርግዘሽ እንዳይሆን ብለው አልተሳለቁብሽም??🥺  ወላጆሽ ላንቺ ብለው ስንት መከራ አይተው እነሱን አለመካስሽ ሆድ አስብሶሽ አያውቅም?? ደግመሽ ደጋግመሽ suicide ሞክረሽ አልሳካ ብሎሽ አያቅም??🥺 በቃ ይሄን ስሜት ካለወቅሽ አትጨነቂ አትበይኝ ተይይ 😢

ሰው ያላሸነፈው ድክመቱ ይጥለዋል። ሊጥለኝ ነው መሰል ተፈታተነኝ…

ያየሁባቸውን ሆኜ አየሁት

ነገሮች የሚያልፉበት ቅጽበት እየኖርን መሆኑን ያጠራጥራል። ያሳለፍናቸው ቀናት እና ሁነቶች የምር እንደሆኑ ማረጋገጥ  እስኪከብድ ድራስ ይፈጥናል፡ ።ሁሉም ነገር የኣይን ብልጭታ ያልህ ኣልፏል።ከመልካሙ ይልቅ ግን የክፉው ተጽእኖ ውስጥ ውስጡን ይበላል ኣልፎ ኣያልፍም ተረስቶ ኣይረሳም ። ሁል ግዜ ወደኋላ ሚጎትት ቅሬታ ኣለ። ይቅር ያላልነው ድክመት ሆኖ የቀረ ርዝራዥ.....    ተበደልን ላልነው ነገር ካሳ እየተጠባበቅን ነው? ትላንት ለምን ሁል ግዜ ክፉውን ብቻ ምናስታውስበት ሆነ ። መልካሙን መልካም ያላልንበት ምክንያት ምንድነው ? .

በደስታቸው ቀን ከረሱህ መቼም አያስታውሱህም!

መንፈሳዊነት ከሚታይበት ይልቅ አለማዊው መንፈሳዊውንም አያይዞ ይኖራል።

አዲስ አበበባ ዩንቨርስቲ ሌክቸረር አድርጎ አስቀርቶኝ እኔን ግን በጣም ሲያሳስበኝ የነበረው ከሔሉ ጋር በየቀኑ ልንገናኝ መሆናችን ነበር። እሷም በተገናኘን ቁጥር ታቱውን እንዳይላት የማታደርገው ጥረት የለም። ሴክስ ላይ የኔ ተሳትፎ እሷ እስክትጨርስ ድረስ ቀጥረው እንደቀሩበት ሰው መስኮት መስኮት ማዬት ሆነ። ቢጨንቀኝ አብሮኝ ሰቅሎ ሌክቸረር የሆነ ጓደኛዬን አማከርኩት። ከነገርኩት ሁሉ መያዝ የቻለው ግን ሔለን የኔን ፊት መነቀሷን ብቻ ነው። ይሕ ስህተቴ የህይወቴን ትልቁን ዋጋ አስከፈለኝ። የግቢው ሰው በአንዴ እሷ ላይ ተነሳባት። "Beauty And The Beast!" እያሉ ሲያሾፉብኝ የኖሩ ሰዎች እኔን ንጉስ እሷን ገረድ አድርገው ለመተረክ አላመነቱም። የሳቁብኝን ያህል ተሳለቁባት። የተዘባበቱብኝን ያህል ተዘባበቱባት። መግቢያ መውጫ አሳጧት። በምላሳቸው ብቻ...ፍቅሬን አሳበዱብኝ። በሔደችበት ሁሉ ነገር ስለማያጣት ግቢው ውስጥ የሚወራው ነገር ሁሉ ስለሷ ይመስላት ጀመር።  በሚሆነው እና በሚመስላት መሀል ያለው መስመር ተቀላቀለባት። ሴቶች ከቢሮዬ ገብተው ሲወጡ ተደብቃ ታያለች። ስዞር ያላዬኋት እየመስላት በፍጥነት ትሸሻለች።  ይዤ «ምን ሁነሽ ነው?» ስላት... «ታዋቂ አደረኩህ አሁንማ ካደኝ!» ትላለች። «ከመታወቅ ጋር ምን አገናኘው ይሔ? እነዚህ ሴቶች ማለት'ኮ ማርክ ይሰጠናል ብለው ያሰቡት መምህር ጋ ሁሉ የሚሔዱ አገር አድርሶች ናቸው!» «ምንም ብትል አትሸውደኝም!» በቃ በማያስጨንቀው ሁሉ ተጨንቃ ታስጨንቀኛለች። ክላስ ራሱ አትገባም። ተደብቃ እኔን ስትከትል ነው የምትውለው። አይኔ እያዬ እያመለጠችኝ ላድናት አልቻልኩም። የሆነ ቀን ጉዳዩን ፈፅመን እንደጨረስን «ሰሞኑን መድሀኒት ስትወስጂ አላይሽም! ሌክቸረር ሆነ ብለሽ ልታረግዥብኝ ነውዴ?» አልኳት። አልሳቀችም። ከሷ መውለድ ለኔ የህይወቴ ትልቁ ግቤ እንደሆነ እያወቀች ለዚህ ቀልዴ አልሳቀችልኝም። ዝም ብላ ነገር ስትበላ ሳይ ርቃ እንደሔደች ገባኝና የምር አሳዘነችኝ። እንዲህ የሁለታችንም ህይወት ከሚያቃውሰው ምናለ ይሔ ታቱ ቀርቶ በነበረ አስባለችኝ። ሽንት ቤት ገብቼ ተከዝኩ። ስወጣ የለችም። የለችም ከሩሙ ሳይሆን ከግቢው፣ ከሀገሩም የለችም። እልም ብላ ጠፋች። ልፈልጋት ሞከርኩ። ጓደኞቿም፣ ቤተሰቦቿም ፊት ነሱኝ። ማንም ሊተባበረኝ ፍቃደኛ አልነበረም። ግቢው አስጠላኝ። ሰላም አጣሁ። እየጠጣህ ትገባለህ በሚል በስድስት ወሩ አባረሩኝ። የግል ኮሌጆች ጋር ፓርት ታይም ማስተማር ጀመርኩ። እነሱ በህይወት እስካለሁ ድረስ ምንም ግድ ስሌላቸው ለሱሴ ተመቹኝ። ተማሪዎቹ ናቸው የሚያሳዝኑኝ። ወይ በሰዓት አልገባ። ወይ የጠቀመ ሀሳብ ይዤላቸው አልሔድ። ሙሉ ትኩረቴ የሔለን መሔድ ላይ ብቻ ነበር። ልረሳት አልቻልኩም። አሳይቶ የሚነሳኝ ነገር ሁሉ ሔለንን ያስታውሰኛል። ጎበዝ ተማሪ ሲሰንፍ ሳይ "ሔለን ሆነ" እለዋለሁ። ደመና ሁኖ አልዘንብ ሲል "ሔለን ነች የዛሬዋ ሰማይ" እላለሁ። ሲጋራ መተርኮሻ ፊትለፊታችን አስቀምጦ "ማጨስ ክልክል ነው" የሚል ማስታወቂያ የለጠፈብንን ቤት "ሔለን ሆቴል" እለዋለሁ። አምላክን ራሱ ሔለን ነው የምለው።  እያሳዩ መንሳት! 'ርሳኝ እያሉ ማስታወስ! አለም ላይ ያለ ነገር ሁሉ ሔለን ነው። ልረሳት አልችልም። በሰከርኩ ቁጥር ሒደው ከነገሯት ብዬ ላገኘሁት ሁሉ ነው እየዞርኩ ስለሷ የማወራው። አሁን አሁን ሁሉም ሰልችቻቸው ገና ስጠጋቸው ሒሳብ ከፍለው ይወጣሉ። እኔም ስገባ ሁሉም እንዲዳረስ በቻልኩት መጠን የማያውቀኝ ሰው ፈልጌ እቀመጣለሁ። ቅርንጫፎቹ ሁሉ በሀረግ ተሸፍነውበት ዛፍ ይሁን ጉቶ የማያስታውቅ ብቻውን የቆመ ነገር ካያችሁ...ያ ዛፍ እኔ ነኝ። ፍቅሯን ብቻዬን እንድሸከም ፈርዳብኝ ሒዳ ሰው መሆኔ የማያስታውቅ ባተሌ! ..... ዛሬም ባር ውስጥ እንደገባሁ እንደልማዴ የማያውቀኝ ሰው ፈልጌ ተቀመጥኩ። ገብቼ ከመቀመጤ የታምራት ደስታን «መቼቼቼ ሰለቸኝ አልኩ?» የሚለውን ለቅሶ ከፍቱብኝ። አብሬው ማልቀስ ጀመርኩ። «መጥፎ ትዝታ ቀሰቀሰ?» አለኝ ፊትለፊቴ ያለው ወጣት። «እእእእእ!» አልኩ ቀድሞ ማውራት ስለጀመረ ደስ እያለኝ። «አይዞን እንግዲህ ያለ ነው። ትኩስ ፍቅር ነው መሰል...በቅርብ ነው'ዴ የተለያያችሁት?» «ትኩስ መሆኑን ትኩስ ነው! ግን አምስት አመት ሆኖታል።» አልኩት። ግራ በመጋባት አዬኝ። «ይገርምሀል! ለኔ ሁሉ ነገር ቀርቶብኝ የእግር ጥፍሯን መቁረጥ በቂዬ ነበር። ፍቅረኛዬን ብቻ አይደለም...በልኬ የተሰራችልኝን አምላኬንም ጭምር ነው ያጣሁት።» ይበረግጋል ብዬ ያሰብከትን ያህል አልበረገገም። የምለው ገብቶታል። «ጥሩ ጊዜ አሳለፋችሁ አንድ ላይ?» አለኝ! «በጣም። በጣም እንጂ። በህይወቴ ማንንም ወድጄ አላውቅም። ቤተሰብ...ሀገር...ጓደኛ..እናት...አባት....ማንንም!! ብቸኛዋ ፍጥረት ነች እሷ። ፍቅር የሚባለውን ነገር አሳይታ ነሳችኝ።» «አውቃለሁ የሚመክርህ ሳይሆን የሚያዳምጥህ  ፈልገህ እንደምታወራኝ። ግን አንዳንድ ነገሮች የምናስበውን ያህል መጥፎ አይደሉም።» አለ ፈራ ተባ እያለ። «አቤት?» «እየውልህ ወንድሜ! ታምራት ደስታ ደስ ይላላ?» ራሴን በአወንታ ነቀነቀኩ። «እና ታምራት በመሞቱ ማዘን ይሻላል ወይስ በመፈጠሩ መደሰት?» አለኝ። ለማነፃፀር ዝም አልኩ። የማሰቢያ ጊዜ ሳይሰጠኝ ቀጠለ። «ዙሮ ተዟዙሮ ሁሉም ሰው የሆነ ቦታ ላይ ይለያያል። እድለኛ ብቻ ነው ትዝታ የሚኖረው። እየቆዘምክ በሁለት ቢራ ቋ የምታደረገው ትዝታ ካለህ ህይወት መጥፎ አይደለችም።» «እሱማ ሲመክሩት ቀላል ነው!» «ልክ ነህ። ከባድ ነው። ግን የማይቻልም አይደለም። እኔም የማፈቅራትን ሴት አጥቻለሁ። ሌላ አግብቼ እየኖርኩም አስባታለሁ። ግን ለምን እሷን አላገባሁም? ብዬ ከዩንቨርስ አሰራር ጋር ግጭት ውስጥ አልገባም። አንተም ሰላም ብታወርድ ይሻልሀል።» «አትደስኩረኝ ባክህ!» አልኩ የምመልስለት አጥቼ። «የምሬን ነው። This is life! የኔዋ ከመሔዷ በፊት ያለችኝ አንድ ነገር ነበር። 'ወደድንም ጠላንም በህይወታችን የገባን ሰው ሁሉ መለያዬት የሚባል አዘቅት ይሰለቅጠዋል። ቅርፁ ወደ ትዝታ ተቀይሮ አብሮን ይኖራል። ያ ሰው 'አለ'ም 'የለም'ም ማለት አንችልም።'  እስካሁን ድረስ ይሔንን ንግግሯን ምንም ሀሰት አላገኘሁበትም። አለች ብለህ ላታቅፋት ትችላለህ። የለችም ብለህ ለማልቀስ የሚያበቃ ድምዳሜ ላይ ግን መድረስ አትችልም። ሌላው ቢቀር አንተ ውስጥ የቀረው ትዝታ አለ። ይልቅ ቆፍጠን በልና በህይወትህ ገብታ ማወቋን ሰለብሬት አድርግ ወዳጄ። ትዝታን የሚያህል አንጡራ ሀብት ተሸክመህ እንዲሁ አታባክነው።» ዝም አልኩ እያፈጠጥኩበት። ሁኔታዬን ሲያይ እንዳሸነፈ ተሰምቶት ብርጭቆውን እያነሳ «ቺርስ ለትዝታችን!» አለ። ቤት ገብቼ ለመኝታ እየተዘጋጀሁም የልጁ ንግግር ተከትሎኝ መጥቷል። ያወራኝ ነገር ሁሉ ደግሜ ባሰብኩት ቁጥር የበለጠ ያሳምናል። ከዩንቨርስ/ከአምላክ አሰራር ጋር ሰላም ማውረድ እንዴት ያለ ነገር ነው? አላውቅም...በትዝታ ሀይል የኖርነውን ደግሜ ለመኖር ስል ግን ልሞክረው ፍቃደኛ ነኝ። ሔሉ ከሔደች ቡኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነገ መንቃት ፈለግኩ። ክላስ እንዳይረፍድብኝ አላርም ሞልቼ ተኛሁ። ፨፨፨፨   ✍️ ማይክል አዝመራው