ማራናታ.....MARANATHA
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ማራናታ.....MARANATHA
کانال ማራናታ.....MARANATHA (@maranathawoch) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 17 316 مشترک است و جایگاه 4 693 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 969 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 17 316 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 31 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 308 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 12 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 19.70% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.94% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 3 410 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 374 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 24 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37
የመወያያ ግሩፕ👇
@Marantawoch
Inbox Comment @Thaddyapostolic”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 01 سپتامبر | +6 |
| 2 | የማለዳ ትምህርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል?
ክፍል 9 በጊዜ አለመጸለይ
በተለምዶ ሰው ጸሎትና ምልጃ የሚያበዛው በችግር ጊዜ ብቻ ነው። ችግር ስያጋጥመው፣ የመውጫ መንገድ ስያጣ ወደ እግዚአብሔር መጮኽ ከብሉይ ክዳን ከእስራኤል ዘመን ጀምሮ የተለመደ ሆኖ እስከ ዛሬ ድረስ ደርሶዋል። ነገር ግን እግዚአብሔር የሚጸልገው ይሄንን ህይወት አይደለም። በጊዜውም አለጊዜውም መጸለይና መጽናትን ነው።
ስለዚህ ቅዱስ ሁሉ በምቹ ጊዜ ወደ አንተ ይለምናል፣ ብዙ የጥፋት ውሃም ወደ እርሱ አይቀርብም [መዝ 32፥6] ተብሎ ስለተጻፈ ጥፋትና ችግር ወደ እርሱ እንዳይቀርብ ጻድቅ መለመን ያለበት ጊዜ ሳለ ነው እንጅ ፈተና ደርሶ፣ ጥፋት ደርሶ፣ ቀን መሽቶ ብቻ ወደ እግዚአብሔር መጮኽ የጸሎት መልስ አያመጣም።
ኢየሱስም ስናገር " ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሰራ የማይችልበት ሌሊት ትመጣለች" ይላልና። [ዮሐ 9፥4]
ወንድሞችና እህተች መጸለይ ካለብን በጊዜ፣ ማምለክ ካለብን በጊዜ፣ ማልቀሳ ካለብን፣ መጮኽ ካለብን፣ እምባ ማፍሰስም ካለብን በጊዜ ነው እንጅ የፈተና ሰአት ደርሶ "ሠርገኛ መጣ፥ በርበሬ ቀንጥሱ" እንደሚባለው ተረት መሆን የለብንም።
ኢየሱስ ከዲያብሎስ በተፈተነ ጊዜ በመጀመሪያ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በጾም ጸሎት ቆይቶ ነው እንጅ ፈተና ደርሶት አይደለም። ፈተናና ችግር እንደሚደርሰን ካመንን ሥራውን ለማፍረስና ለማሸነፍ ቀድመን መዘጋጀት አለብን።
ይህ ማለቴ በችግራችን ጊዜ አንጸልይ፣ አይሰማንም ማለቴ አይደለም። ይሰማናል፤ ነገር ግን በኋላ ከሚመጣው ጥፋት ለማምለጥ በእግዚአብሔር ፊት በምቹ ጊዜ መምበርከክ አለብን። "ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ" ብሎዋል እንጅ ፈተና መጥቷልና ጸልዩ አላለም። ወደ ተና እንዳንገባ የሚያደስገን ፀሎት ቀድመን ፀለይነው ፀሎት ነው እንጅ ተፈትነን የሚንልየው ፀሎት አይደለም።
እርሱ ጊዜ ሰጥቶን፣ ሰአት ሰጥቶን፣ ቀን አመቻችቶልን ጸልዩ እያለ እየመከረንእምብ ካልን በኋላ ሰሚ በሌለበት ሰአት በር ተዘግቶ የሚንጸልየው ጸሎት መልስ አይገኝም። ጸሎታችን ለምን ዘገየ እያልን ከመማረርና እግዚአብሔርን ከመወቀስ ውጭ ትስፍ አይኖርም።
ምሳ 1፥24-31 በጠራሁ ጊዜ እምቢ ስላላችሁ፥ እጄን በዘረጋሁ ጊዜ ማንም ስላላስተዋለ፥
25 ምክሬን ሁሉ ግን ቸል ስላላችሁ፥ ዘለፋዬንም ስላልፈቀዳችሁ፤
26 እኔም ስለዚህ በጥፋታችሁ እስቃለሁ፤ ጥፋታችሁም በመጣ ጊዜ አላግጥባችኃለሁ።
27 ድንጋጤ እንደ ጐርፍ በደረሰባችሁ ጊዜ፥ ጥፋታችሁም እንደ ዐውሎ ነፋስ በመጣ ጊዜ፥ ጭንቅና መከራ በወረደባችሁ ጊዜ።
28 የዚያን ጊዜ ይጠሩኛል፥ እኔ ግን አልመልስም፤ ተግተው ይሹኛል፥ ነገር ግን አያገኙኝም።
29 እውቀትን ጠልተዋልና፥ እግዚአብሔርንም መፍራት አልመረጡምና፤
30 ምክሬን አልፈቀዱምና፥ ዘለፋዬንም ሁሉ ንቀዋልና፤
31 ስለዚህ የመንገዳቸውን ፍሬ ይበላሉ፥ ከራሳቸው ምክር ይጠግባሉ።
እግዚአብሔር የሚሰማበት ሰአት እምብ ብለን የማይሰማትና ፊቱን በሰወረበት ሰአት መጮኽ መፍትሄ አይሆንም። እግዚአብሔር ከደጃችን ሳያልፍ በደጃችን እያለ ወደ ቤታችን ማስገባት ነው እንጅ አንኳክቶ አጥቶ ከደጅ ካለ በኋላ ፈልገንም አናገኘውም።
መ/መ/ ዘሰለሞን 5፥2-7 "እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል የውዴ ቃል ነው፥ እርሱም ደጁን ይመታል እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥ በራሴ ጠል፥ በቈንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ ሞልቶበታልና ክፈችልኝ።
3 ቀሚሴን አወለቅሁ እንዴት እለብሰዋለሁ? እግሬን ታጠብሁ እንዴት አሳድፈዋለሁ?
4 ውዴ እጁን በቀዳዳ ሰደደ፥ አንጀቴም ስለ እርሱ ታወከ።
5 ለውዴ እከፍትለት ዘንድ ተነሣሁ እጆቼ በደጅ መወርወሪያ ላይ ከርቤን አፈሰሱ፥ ጣቶቼ ፈሳሹን ከርቤ አንጠበጠቡ።
6 ለውዴ ከፈትሁለት፥ ውዴ ግን ፈቀቅ ብሎ አልፎ ነበር። ነፍሴ ከቃሉ የተነሣ ደነገጠች ፈለግሁት፥ አላገኘሁትም ጠራሁት፥ አልመለሰልኝም።
7 ከተማይቱን የሚዞሩት ጠባቂዎች አገኙኝ መቱኝ፥ አቈሰሉኝም ቅጥር ጠባቂዎችም የዓይነ ርግብ መሸፈኛዬን ወሰዱት።
በጊዜ አለመክፈትና አለመዘጋጀት የሚያመጣው ችግር አያችሁ? ጸሎቴ የት ጠፋ፣ መልሴ ለምን ዘገየ ከማለት ውጭ ምላሽ አናገኝም። ስለዚህ መጸለይ ያለብን ሰአት ቀድመን እንጸልይ፣ መፈለግ ያለብን ሰአትም ቀድመን እንፈልግ እንጅ የእኛ ቅድሜ ሁኔታ ሳናስተካክል ኢየሱስን ጥፋተኛ አናደርግ።
ዮሐ/ ራዕየ 3፥20 እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ፤ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ፥ ወደ እርሱ እገባለሁ ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል። ይህ ሰአት የኢያንዳንዱ ደጅ እያንኳኳ ያለበት ሰአት ነውና ክቡር እንግዳዬ ነህና ና ግባ ብለን እንቀበለው።
ሀሳቤ ልክ ከሆነ ቀጥል በሉኝ፤ ልክ ካልሆንኩኝ አቁም በሉኝ ተባረኩ!
ይቀጥላል........
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
INBOX @Thaddyapostolic
GROUP @MARANTAWOCH | 1 063 |
| 3 | የመገረም ጥግ.mp3 | 1 920 |
| 4 | https://youtu.be/DnaeWyHzg3o?si=A54ntn-XPPwRaCHa | 1 569 |
| 5 | # አድስ ነገር
ጌታ እግዚአብሔር እሱን በመጠባበቅ ላይ ላሉት ታይቶ የማይታወቀውን ልዩና ድንቅ የሆነ ነገር ያደርጋል ፦
1 ቆሮንቶስ 2 ፥ 9፤
ነገር ግን፡— ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።
ጌታ እግዚአብሔር አንድን ነገር ስሰራ በሰው ልክ ተገምቶ የተጠበቀውን ብቻ ሳይሆን ብዙ የተጠበቁ ነገሮች እያሉ ከዛም እጥፍ ድርብ የሆነ ከፍ ያለ ነገር ያደርጋል ፦
ኢሳይያስ 43 ፥ 19፤ እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለህ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተም አታውቁትምን? በምድረ በዳም መንገድን በበረሀም ወንዞችን አደርጋለሁ።20-21፤ ምስጋናዬን እንዲናገሩ ለእኔ የፈጠርሁት ሕዝብ፥ የመረጥሁትን ሕዝቤን አጠጣ ዘንድ በምድረ በዳ ውኃን በበረሀም ወንዞችን ሰጥቻለሁና የምድረ በዳ አራዊት፥ ቀበሮችና ሰጎኖች፥ ያከብሩኛል።
እኛ ያመንነዉ አምላክ በፊትም ስሰራ የኖረ ያ ታማኝ አምላክ ዛረም በእኛ በልጆቹ ላይ በሀይሉ ከፍ ያለ ነገር ድንቅና ታምር ይሰራል፦
ኢዮብ 36 ፥ 22፤ እነሆ፥ እግዚአብሔር በኃይሉ ከፍ ያለውን ነገር ያደርጋል፤ እንደ እርሱስ ያለ አስተማሪ ማን ነው?
በማደሪያው ሆኖ ቃል
የገባ አምላክ
ራእይ 21 ፥ 5፤ በዙፋንም የተቀመጠው፡— እነሆ፥ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ፡ አለ።
በምመጡት ቀናቶች በምመጣዉ አመት ሁሉን ቻይ የሆነ አምላክ
በአድሱ አመት " አድስ ነገር ያድርግልን"
ይደረግልን
ይሁንልን!!!! | 1 767 |
| 6 | ግጥም
እልፍ አርገኝ
የልምምድ ኑሮ እዛው ተቀምጦ
ከፍታ የሌለው ወደታች ሠምጦ
ሁሌ ባለሁበት አዲስ ነገር ሳላይ
አንድ አይነት ነገር ሳሎጣ ወደ ላይ
በጣም ሰልችቶኛል የለመድኩት ልማድ
ከፍታ ሳሎጣ ሁልጊዜ መራመድ
እጄን ዘርግቻለው አንተ እንድትረዳኝ
በራሴ ጥሪያለው መውጣት ግን አቃተኝ
እባክህ ተመልከተኝ አንዴ ብቻ እየኝ
ድካሜ በርትቶ ሀይልን እኮ አሳጣኝ
ፊትህን ጋረደኝ ድምፅህ ራቀብኝ
ተስፋዎቼ ሁሉ በቃ ጨለሙብኝ
ይቅርብኝ ያ ልማድ ድግግሞሽ ይብቃ
አልፌ ልሻገር አሁን ቶሎ ልንቃ
ወዳለመድኩት ወደ አዲስ ነገር
ተሻግሬ ልየው ሁሌ ያንተን ክብር
ድንበሩ ላይ ቆሜ ለምንስ ልመልከት
ተሻግሬ ልሂድ በሀይል በጉልበት
እልፍ እልፍ እልፍ አርገኝ
መራመድ ይብቃና ወደ ላይ አሶጣኝ
ከፍ ከፍ ከፍም አርገኝ
ዝቅታ ይብቃና ክብርህን አሳየኝ
የዛለው ጉልበቴ በድጋሜ ይታደስ
ወደታች የሳበኝ አሁኑኑ ይበጠስ
ተራራውን መዞር ምን ጥቅም ይሰጣል
እዛው ባለሁበት በጣም ይሰለቻል
ሀይልህ ይምጣና ያውጣኝ ወደላይ
ጉልበትን እሻለው ፊትህን እስከማይ
መንሳፈፍ ናፈኩኝ በፀጋህ ዙፋን
እጅግ የሚያስፈልግ በአሁኑ ዘመን
ይፍሰስ በእኔ ላይ ይሄ ቅዱስ መንፈስ
እላይ የሚያወጣ ካሰብኩት የሚያደርስ
አንድ እርምጃ ብቻ አሁን ካለሁበት
እንዳይደጋገም የትላንት ማንነት
አሮጌውም ይሻር በአዲስ ይለወጥ
ማያስፈልግ ነገር ከህይወቴ ይቆረጥ
አብዝቼ ልፈልግህ ወደ አንተ ልሩጥ
ተራራው ቢጋረጥ ከቶ እንዳልደነግጥ
ከሰፈር ልውጣና ልለይ ላንተ ክብር
ከትላንት ማንነት ዛሬ እንድሻገር
ድግግሞሽ በቅቶ የድሮ ልማዴ
ከዛ እልፍ ልበል ካለሁበት አንዴ
አዲስ ነገር ማየት ነውና መሻቴ
አንተን መርጠንሀል እኔ እና ቤቴ
እናም እልፍ አርገኝ አሁን ካለሁበት
ያየሁትን ነገር ወደ ማልደግምበት
አንዴ ብቻ እልፍ አርገኝ
አንድ እርምጃ ፈቀቅ አርገኝ
S/r eyael | 1 623 |
| 7 | እልፍ አርገኝ
የልማድ ጉዞ ሁሌ ሲደጋገም
ለሊቱ ሲነጋ መልሶ ሲጨልም
ወይ ላላልፍ ላልሻገር ቀን ፈጀው ቆሜ ከድንበር
ትላንትና ዛሬን ተክቶት ሲያልፍ
ዛሬ ነገን ሊደርስ በፍጥነት ሲቀዝፍ
ወይ ላላልፍ ላልሻገር ቀን ፈጀው ቆሜ ከድንበር
የተጋረጠውን ተራራ እየዞርኩ ያኔ በማልኩበት ስፍራ ዛሬም ስገኝ
ወይ ላላልፍ ላልሻገር ቀን ፈጀው ቆሜ ከድንበር
ሁሌ አንድ አይነት ህይወት መኖር ሰልችቶኛል
ቆርጦ ለመውጣት ጥሮ መውደቅ ስልችቶኛል
ባለሁበት መራመድ የትም ላልሄድ
ኧረ ምንድነው አንተን ይዞ መንገዳገድ እልፍ አርገኝ
እልፍ አርገኝ ካለሁበት እልፍ አርገኝ
እልፍ አርገኝ ከቆምኩበት እልፍ አርገኝ
እልፍ አርገኝ ጥሼ ልሻገር እልፍ አርገኝ
እልፍ አርገኝ ከስጋ ነገር እልፍ አርገኝ
የከበደኝን ሚያውከኝን ባንተ ላይ ጥዬ
ልሂድ ልሻገር ልለፍ እንጂ ተደላድዬ
የስምህን በትር በእጄ ይዤ ለምን ቆማለሁ
ዮርዳኖስንም ከፍዬበት እሻገራለሁ
እልፍ አርገኝ*2 ካለሁበት እኔን አውጣኝ
ዘይቴ ፈሶ ተመርጬ ተቀብቻለሁ
ታድያ መንደር ውስጥ ከአለም ጋር ምን እስራለሁ
ካልተለየሁኝ ስትለየኝ ስትጠራኝ
ስጋ መሻቱን ጥፍር አርጎ እንዳይገዛኝ እልፍ አርገኝ
አንድ እርምጃ ካለሁበት
አንድ እርምጃ ከቆምኩበት
አንጅ እርምጃ እልፍ አርገኝ
አንዴ ብቻ ፈቀቅ | 1 422 |
| 8 | Tem(2).mp3 | 1 566 |
| 9 | "ታሪክህ እንዲቀየር ኢየሱስን ወደ ህይወትህ ጋብዝ"
ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።
-ማቴዎስ 6:33
በአንድ ሀገር አንድ ንጉሥ በየአመቱ እጣ የማውጣት ባህል ነበረው። እንግዲህ ዕጣው ለወጣለት ሰው ንጉሡ ዜጋው የፈለገውን/የጠየቀውን ነገር ያደርጋል። አንዴም ቃል ስለገባ፤ ከዚህ በፊትም እንዲህ አይነት ልምምድ ስላለ ዕጣው ለወጣለት ሰው ያሻውን ያደርግለታል። የሆነ አመት ላይ ዕጣው ለሆኑ በዕድሜ ለገፉ እናት ይወጣላቸዋል። ከዛ በኃላ ንጉሡ የደህንነት አባላቶቹን ዕጣው መድረሱን እንዲያሳውቋትና ጥያቄዋን ለመቀበል ወደ ሴትዮዋ መንደር ይልኳቸዋል። እነዚህ የደህንነት አባላቶቹ ልክ ሰፈሯ ሲደርሱ መንገዱ አስቸጋሪ የሆነ፣ አከባቢው ላይ ያሉ ቤቶች የደካከሙ እና ሊወድቁ ቀናቶች ብቻ የቀሩት፣ ሴትዮዋም ቤት ሲገቡ ቤቷ እርጅት ያለና ቤቷ ውስጥም ምንም የሚበላ እንኳን የሌለ እንደሆነ ተረዱ። የንጉሡ የደህንነት አባላቶቹ ልክ እንደደረሱ "እንኳን ደስ ያሎዎት እማማ፡ የዘንድሮ ዕጣ ለእርሶዎ ነው የወጣሎት፡ ስለዚህ ከዚህ ደቂቃ ጀምሮ የፈለጉትን ነገር ንጉሡን የመጠየቅ መብት አለዎት።" እሳቸውም ቀጥለው " እንግዲህ እግዚአብሔር ፈቅዶ ዕጣው ለኔ ከወደቀ፡ አንድ ጥያቄ ነው ያለኝ። እሱም ንጉሥ ቤቴ መጥቶ እራት እንዲበላ ነው ምፈልገው።" አሉ! የደህንነት አባላቶቹ ያልጠበቁት አይነት ጥያቄ ስለነበር እጅግ ደነገጡ። "እንደዛማ ሊሆን አይችልም እማማ። እስቲ ከሰፈሮት ብንጀምር እንኳን ንጉሡ ልምጣ ቢል መንገዱ አመቺ አይደለም፡ እጅግ አስቸጋሪ ነው። ቤቶቹ ደግሞ የወዳደቁ እና የደካከሙ ናቸው። እስቲ ዞር ብለው ቤቶትን ይዩ ሊወድቅ ቀናቶች የቀረው ነው በዛ ላይ በስነስርዓት የሚበሉት ምግብ የሚጠጡት ነገር የሎትም። በዚህ ሁኔታ እንዴት ነው የአንድ ሀገር ንጉሥ መጥቶ እራት የሚበላው? ይኼ የማይሆን ነገር ነው እማማ!" ሲሏቸው፡ ወይ ፍንክች " እንግዲህ ሀሳቤን አልቀይርም። የኔ ፍላጎት ንጉሥ መጥቶ አብሮኝ እራት እንዲበላ ነው። ሌላ ጥያቄ የለኝም።" አሏቸው። የደህንት አባላቶቹ ግራ ቢገባቸው ጥያቄውን ወደ ንጉሥ ዘንድ ወሰዱ። ንጉሡም ዕጣ የደረሰው ዜጋው የሚጠይቀውን ለማድረግ ከዚህ በፊት ቃል ስለገባ እንዲሁም የማድረግ ልምምዱም ስላለው እምቢ ማለት ቢቸግረው ጃንደረቦቹን ሰበሰበ። ንጉሡ ከ3 ሳምንታት አስቀድሞ ጃንደረቦቹ ወደ ሴትዮዋ መንደር ሄደው ያለውን ነገር እንዲያዩ ላካቸው። ልክ ሰፈሯ ሲደርሱ መንገዱ የተበላሸ፡ መኪና የማያስገባ ስለነበር አስፓልት ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። አከባቢው ላይ የነበሩ ቤቶች የደካከሙ እና ሊወድቁ አንድ ሐሙስ የቀራቸው ስለነበሩ ሁሉም ፈርሶ እንደገና የሚያምር ቤት ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። ቤቷ ሲደርሱ ቤቷም ያረጀ እና ሊወድቅ ቀናቶች የቀሩት ስለነበረ ፈርሶ ንጉሡን በሚመጥን ልክ ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። እንዲሁም ቤቷ ምንም የሚበላ ነገር ስላልነበረ ንጉሥን በሚመጥን መልኩ ምግብ በየአይነቱ ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። እንግዲህ በዚህ ሁሉ ታሪክ እንድታዩ የፈለኩት በእውነቱ የተሰራውን ነገር አይደለም። ሰው ከምንም ነገር አስቀድሞ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ወደህይወቱ ከጋበዘ በረከት የሚከተል ነገር እንደሆነ እንድትረዱልኝ ነው። እንግዲህ አንድ የሀገር ንገሥ የፈለጉትን ነገር ሊያደርግላቸው ፈቃዱ ሆኖ ሳለ የሳቸው ምላሽ ንጉሡ ወደቤቷ መጥቶ ከእሷ ጋር እራት እንዲበላ መጋበዝ ነበር። ጌታን ወደህይወታችን ስንጋብዝ እኛ ከምናስበው እና ከምንረዳው በላይ ሊያደርግልን ይፈልጋል። የጥያቄ ሁሉ መልስ ኢየሱስ ነው። ታሪክህ/ሽ እንዲቀየር ወደ ህይወትህ/ሽ ኢየሱስን ጋብዝ/ዢው። ልክ ሴትዮዋ ንጉሡን ቤቷ እንዲመጣ ስትጋብዝ ከራሷ አልፋ ለሰፈሯ በረከት እንደሆነችው እኛ ኢየሱስን ወደህይወታችን ስንጋብዝ የኛ ታሪክ ብቻ አይደለም የሚገለበጠው። ለሰዎች የምንተርፍ እንሆናለን። ብቻ ኢየሱስን ወደ እያንዳንዱ ነገራችን እንጋብዘው። አለም ልክ እንደ የደህንነት አባላቶቹ ያልተሳኩ ነገሮቻችንን፡ የወደቅንባቸውን ጊዜያቶች እያመጣ በህሊና ወቀሳ እያሰቃየን፡ አዕምሮአችንን በከንቱ ሀሳብ እየሞላ፡ ማጣታችንን ተጠቅሞ፡ መድከማችንን አይቶ ተስፋ ሊያስቆርጠን ቢሞክርም ንጉሣችንን ኢየሱስን ብቻ ነው ምፈልገው ሌላ ጥያቄ የለኝም ብለን ፀንተን ከቆምን በረከት ይከተለናል። | 1 564 |
| 10 | የማለዳ ትምህርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል ?
ክፍል 8 ራሱን ከፍ አድርጎ በማየት
ጸሎት ማለት ሰውና እግዚአብሔር የሚገናኝበት የስልክ መስመር በመሆኑ መጠን የሚጸልየው ጸሎት በጥንቃቄ መሆን አለበት። ምክንያቱም በስልክ መስመራችን የሚናወራው ወሬአችን ሁሉ በቴሌ እንደሚመዘገብ የጸለይነው ጸሎታችንም እያንዳንዱ ቃላቶች በእግዚአብሔር ፊት የሚመዘገብ ነው።
እየቀለድን የሚናወራቸው ቃላቶች እንኳን በአየር ላይ ተቀምጦ በፍርድ ቀን ተሰብስቦ እንደሚመጡብን በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ስለተጻፈ ሁሉንም ቃላቶቻችን ጥንቃቄ እያደረግን ብናወራ ይሻለናል።
ወደ ዋና አላማዬ ስመለስ ስንጸልይ እራሳችንን ማመጻደቅ ሌላውን ግን መኮነን አያስፈልገንም። የሀጥአት ምዛንና የጽድቅ ምዛን ያለው እግዚአብሔር ጋር ነው። ስንጸልይ እራሳችንን አዋርደን በእምባ፣ በለቅሶ እንጅ እኔ ጻድቅ ስለሆንኩኝ ማለት አያስፈልግም። የበታችነት ስሜት ይሰማን፤ ከሐጥአተኞች ዋና ሐጥአተኛ እኔ ነኝ እያልን መጸለይ አለብን።
መቼስ የሚለምን እጅ የበታች ነው ይባላልና በታችነት ተሰምቶን መጸለይ አለብን። እኛ ወደ እግዚአብሔር ስንጸልይ እግዚአብሔር ግን ከላያችን ያለው ማንነት ሳይሆን ልባችንን ይመረምራል። መርምሮ ካዬ በኋላ የተዋረደውን ከፍ ያደርጋል፤ ከፍ ያለውን ዝቅ ያደርጋል።
ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። መጠምጠሚያውን አውልቅ፥ ዘውዱንም አርቅ፤ ይህ እንዲህ አይሆንም፤ የተዋረደውን ከፍ አድርግ፥ ከፍ ያለውንም አዋርድ። [ት/ሕዝ 21፥26]
፤ ለዘላለም የሚኖር ስሙም ቅዱስ የሆነ፥ ከፍ ያለው ልዑል እንዲህ ይላል። የተዋረዱትን ሰዎች መንፈስ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠውንም ልብ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠና የተዋረደ መንፈስ ካለው ጋር በከፍታና በተቀደሰ ስፍራ እቀመጣለሁ። [ ት/ ኢሳ 57፥15]
የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም። [መዝ 51፥17]
እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤ እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት። [1ጴጥ 5፥6-7]
ችግራችን።፣ ቀምበራችንን፣ ሸክማችንን ሁሉ የሚንጥለው በትዕብት ተሞልተን፣ ከፍ ከፍ ብለን ሳይሆን በፊቱ ተዋርደን ብቻ ነው። እኛ ከእርሱ በታች ሆነን መዋረድ ስንጀምር እርሱ ከፍ ከፍ ማድረግን ይጀምራል። እርሱ ጸሎታችን ሰምቶ ከፍ ባደረገን ቁጥር እኛ ጨምረን ዝቅ ዝቅ ማለትን መለማመድ አለብን።
ኢየሱሰ ለምሳሌ የተጠቀመውን የሁለት ሰዎች ጸሎት እንመልከት፦
የፈረሳዊው ጸሎት፦ ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ። እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤ በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ።
የቀራጩ ጸሎት፦ ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር።
የኢየሱስ ፍርድ፦ እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል።
አንዱ የራሱን ማንነት እያሳየ ከፍ ከፍ ስል ሌላኛው ግን ከሐጥአቴ ውጭ የሚነግርህ ጽድቅ የለኝም ብሎ ገና ከሩቅ ቆሞ ደረቱን እየደቃ ለመነ። በመጨረሻም ሐጥአተኛ ነው ተብሎ የተፈረጀ ቀራጭ ሐጥአቱን አራግፎ በሠላም ወደ ቤቱ ስመለስ ራሱን ከፍ አድርጎ ጽድቁን ያሳየ ሰውዬ ሐጥአቱን ተሸክሞ ወደ ቤቱ ተመልሰዋል።
ዛሬም በእግዚአብሔር ፊት ብልጥ ብልጥ መሆን የሚሰማን ሰዎች አንድ ጊዜ እናስተውልና በፊቱ እንዋረድ፣ ዋና ሐጥአተኛ እኔ ነኝ እንበል። ተዋርደን ጸልየን ከፍ ብለን እንመለስ። አለበለዚያ በልባችን ትዕቢት እግዚአብሔርን እየወቀስን እንኖራለን።
ይቀጥላል.......
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
Comment
INBOX @Thaddyapostolic
GROUP @Marantawoch | 1 628 |
| 11 | በ2019 ዓ.ም የእኛ እቅድ ታጥፎ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሚገለጥበት፣ በሕይወታችንም የእርሱ እጅ የሚታይበት ዓመት ይሁንልን | 1 705 |
| 12 | ዘማሪ ሙሴ ሲሳይ
ርዕስ:ፍቃድህን የሚያደርግ
አለምም ምኞቱም በከንቱ ያልፋሉ
እንደጠዋት ጤዛ ሆነው ይደርቃሉ
ዘላለም ይኖራል ፍቃድህን የሚያደርግ
አስተውሎ ሚኖር የሚሄድ በአንተ ህግ
ፍቃድህ ተገልጦ
አንተን የሚያስደስት በመውጣት መግባቴ
የአንተ ፍቃድ ይሁን ሁል ጊዜ በህይውቴ
በመንገድህ ምራኝ እየሱስ አባቴ
መልካም መልካሙን የምታስብል
ህይወት አቅጣጫዬን አንተ አሳምርልኝ
መልካም ነህ *2 መልካም እየሱስ
አላማህ በኔ ላይ ፍቅር ነው እና
ያቅዱስ መንፈስህ በእኔ ይፈሰስ እና
ይምራኝ ያሳየኝ ክቡር ፍቃድህን
በሀሳብህ ኖሬ ከጥፋት እንድድን
ተገልጦ ይታይ እያበራ
ፍቃድህ በልቤ ተራራ
አላማህ በህይወቴ እንዲታየኝ
ፍቃድህን ጌታ አስታውቀኝ
እኔ ያንተ ብቻ ያንተ ብቻ ነኝ
ማንም ምንም አይሰልጥንብኝ
እኔ ያንተ ብቻ ያንተ ብቻ ሆኛለው
ፍቅርህ ይግዛኝ ያበርታኝ | 1 800 |
| 13 | #ተስፋ
ተስፋ ያለዉ ሰው ነገሩን ሁሉ በእርሱ ላይ የጣለ ሰው ሁሉ እስካለመበት ይደርሳል
ያ ማለት
ተስፋ ሰጪ አምላክ አድራግ አምላክ ነዉ ።
ዘፍጥረት 15 ፥
1፤ ከዚህ ነገር በኋላም የእግዚአብሔር ቃል በራእይ ወደ አብራም መጣ፥ እንዲህ ሲል፡— አብራም ሆይ፥ አትፍራ፤ እኔ ለአንተ ጋሻህ ነኝ፤ ዋጋህም እጅግ ታላቅ ነው።
3፤ አብራምም፡— ለእኔ ዘር አልሰጠኸኝም፤ እነሆም፥ በቤቴ የተወለደ ሰው ይወርሰኛል፡ አለ።
4፤ እነሆም፥ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል መጣለት፡— ይህ አይወርስህም፤ ነገር ግን ከጉልበትህ የሚወጣው ይወርስሃል።
6፤ አብራምም በእግዚአብሔር አመነ፥ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት።
ጌታ እግዝአብሔር ስለልጆቹ የምአስብ
ያለውን የምፈጽምና ተናግሮ የማይዋሽ ቅዱስ አምላክ ነው ለአብርሃም የገባለትን የተስፋ ቃል ፈጸመ
ዘፍጥረት 21 ፥ 1፤ እግዚአብሔርም እንደ ተናገረው ሣራን አሰበ፤ እግዚአብሔርም እንደ ተናገረው ለሣራ አደረገላት።2፤ ሣራም ፀነሰች፥ እግዚአብሔርም በተናገረው ወራት ለአብርሃም በእርጅናው ወንድ ልጅን ወለደችለት።3፤ አብርሃምም የተወለደለትን ሣራ የወለደችለትን የልጁን ስም ይስሐቅ ብሎ ጠራው።
ሀናም ለዘመናት ልጅ ባለማግኘቷ ተጨንቃ በጌታ ተስፋ አድርጋ ጸለየች
1 ሳሙኤል 1 ፥ 11፤ እርስዋም፡— አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ የባሪያህን መዋረድ ተመልክተህ ብታስበኝ፥ እኔንም ባትረሳ፥ ለባሪያህም ወንድ ልጅ ብትሰጥ፥ ዕድሜውን ሁሉ ለእግዚአብሔር እሰጠዋለሁ፥ ምላጭም በራሱ ላይ አይደርስም ብላ ስእለት ተሳለች።
በእሱ ተስፋ ስላደረገች ሆነላት
1 ሳሙኤል 1 ፥ 19፤ ማልደው ተነሥተው በእግዚአብሔር ፊት ሰገዱ፥ ተመልሰውም ወደ አርማቴም ወደ ቤታቸው መጡ። ሕልቃናም ሚስቱን ሐናን አወቃት፤ እግዚአብሔርም አሰባት፤20፤ የመፅነስዋም ወራት ካለፈ በኋላ ሐና ወንድ ልጅ ወለደች፤ እርስዋም፡— ከእግዚአብሔር ለምኜዋለሁ ስትል ስሙን ሳሙኤል ብላ ጠራችው።
አሁንም ተስፋችን እየሱስ ነው
እህት ውንድሞቸ ተስፋ አንቁረጥ
ምንም እንኳ ቀን ብቆይም ሁለም እግዚአብሔር እሱን ተስፋ ከምአደርጉት ጋር ነው ያለውን ይፈጽማል
የዘገየ ብመስልም በእርሱ ተስፋ አድርገን
የጠበቅነዉ ነገር ሁሉ አንድ ቀን በሀይል ይሆናል ይደረግልናል። | 2 010 |
| 14 | የማለዳ ትምህርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል?
ክፍል 6 ከሐጥያት ጋር የሆነ ጸሎት
በዚህ ምድር ላይ እንኳን ሰው ከሰው ጋር መንገድ የሚሄደው ሁለቱም ስሰማሙ ብቻ ነው እንጂ እየተጣሉ ወይንም ተኮራርፈው አብረው መሄድ አይችሉም።
"በውኑ ሁለት ሰዎች ሳይስማሙ በአንድነት ይሄዳሉን?" ት /አሞጽ 3፥3
ሌላው ደግሞ አንድ ሰው ገንዘብ ብያስቸግረው አበድረኝ ወይንም ስጠኝ ብሎ የሚጠይቀው በጣም የሚገናኝና በደምብ የሚስማማ ወይንም የቅርብ ዘመድ የሆነ ወይንም የቅርብ ጓደኛየሆነ ሰው እንጅ ያላወቀ ሰው በመንገድ ላይ ቆሞ አይጠየቅም።
ደግሞም ምንም እንኳ ዘመድ፣ አባት ወይንም ጓደኛ ብሆንም የሚሰጠውና የሚያበድረው፥ የተበዳሪው ሁኔታ አይቶ፣ ከዚህ በፊት ከእኔ ጋር ምን ያህል ቅርርቦሽ አለው? ዛሬ ስለተቸገረ ብቻ ነው የቀረበው ወይስ በፊትም ከእኔ ጋር ጥብቅ ግኑኝነት አለው? ብሎ ከመስጠት በፊት ጀርባውን ያጠናል።
ሃማ ለመርዶክዮስ የ50 ክንድ እንጨት አዘጋጅቶ እንድሰቀል በወሰነ ጊዜ፥ የንጉሡ ምስት አስቴር ለንጉሡ ሄዳ ብትነግርም ከተናገረችው ቃላት ይልቅ መፍትሔ ያመጣው መርዶክዮስ በደጉ ጊዜ ለንጉሡ ያደረገው መልካምነትና ቸርነት በንጉሡ መዝገብ ውስጥ ተመዝግቦ መገኘት ነው። ንጉሡ አርጠክስስ የሃማ ውሳኔ ከሰማ በኋላ ቶሎ ቤት ገብቶ መንገቡን ፈትሹኝ ብሎዋል፤ በፊት ያለው የንጉሡና የመርዶክዮስን ቅርርቦሽ ለመፈተሽ ተገዷል። በዛው ቀን ለመርዶክዮስ በንጉሡ ፊት የሠራው በደልና ሀጥያት ብገኝ ኖሮ የአስቴር ልመና አያድነውም፤ ከመርዶክዮስ አልፎ 127 አገራት ውስጥ የሚኖሩ አይሁድ ሙሉ በሙሉ ተደምስሰው ነበረ። መርዶክዮስ በንጉሡ ፊት መልካም ሆኖ መገኘቱ አዳነው።
በዛውም ልክ ወደ እግዚአብሔር ጸሎታችን ስናቀርብ እግዚአብሔር መጀመሪያ ቶሎ የሚያየው በደህና ጊዜ የሚንሰራው ሥራችን ነው። በእግዚአብሔር ፊት የሐጥአት ነው ወይስ የጽድቅ መዝገብ ነው የሚታይልን? በእርግጥ እግዚአብሔር የማይሰማና የማይመልስ ጥያቄ የለም፤ ነገር ግን ሀጥያት የሚባል ግድግዳ ወይንም መጋረጃ በመሀላችን ገብቶ እንዳንገናኝያደርጋል። እግዚአብሔር ወደ ሰው እንዳይመጣ የሚያደርገው ጨለማ አይደለም፣ ዝናብ አይደለም፣ ፀሀይ አይደለም፣.... ሀጥያት ብቻ ነው።
በት/ኢሳ 59፥1 ላይ የተጻፈው ዋናው የጸሎት እንቅፋት የሚሆን መጋረጃ ሀጥያት መሆኑን ይናገራል ። ይህ ሀጢያት የተባለ መጋረጃ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ገብቶ ጸሎቱ እንዳይደርስ፣ ደርሶም መልስ እንዳይመለስ አድርጎ የሚከለክል በሽታ ነው። ይህ እንዳይሆን የፈለግነውን ነገር ስጠን እያልን ጸሎታችን ከማቅረብ በፊት በመጀመሪያ ሀጢያተኛ ነኝና ማረኝ ከዛም ጸሎተን አድምጠኝ ማለት አለብን።
አቤቱ፥ ወደ አንተ የጮኽሁትን ቃሌን ስማኝ፤ ማረኝና አድምጠኝ። (መዝ 27፥7)
ት/ኢሳ 59፥1-3 "እነሆ፥ የእግዚአብሔር እጅ ከማዳን አላጠረችም፥ ጆሮውም ከመስማት አልደነቈረችም፤ ነገር ግን በደላችሁ በእናንተና በአምላካችሁ መካከል ለይታለች፥ እንዳይሰማም ኃጢአታችሁ ፊቱን ከእናንተ ሰውሮታል።
እጃችሁ በደም ጣታችሁም በበደል ረክሳለች፥ ከንፈራችሁም ሐሰትን ተናግሮአል፥ ምላሳችሁም ኃጢአትን አሰምቶአል።" እያለ ይቀጥላል።
ነገር ግን ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ለመስማማት ያለው ብቸኛ አማራጭ ምሕረት መጠየቅ ብቻ ነው።
ኢዮብ 22፥21-30 አሁንም ከእርሱ ጋር ተስማማ፥ ሰላምም ይኑርህ፤በዚያም በጎነት ታገኛለህ።
.
ሁሉን ወደሚችል አምላክ ብትመለስ፥ ብትዋረድም፥ኃጢአትንም ከድንኳንህ ብታርቅ... ወደ እርሱም ትጸልያለህ፥ እርሱም ይሰማሃል፤ስእለትህንም ትሰጣለህ።
.
እያለ ይቀጥላል። የቀረውን እናንተም አምብቡ። የዚህ የመጽሐፍ ቅድስ ክፍል ማብራሪያ ከዚህ በላይ መስጠት የሚያስፈልግ አይመስለኝም። ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጋር የተስማማ ሰው ብቻ የጸሎቱን መልስ እንደሚያገኝ በግልጽ አስቀምጧልና።
የጸሎታችን መልስ ዋና እንቅፋት ሀጢያት እስከሆነ ድረስ ሀጥአታችን እንቅፋት እንዳይሆንብን መጀመሪያ ሀጥአታችን ከውስጣችን ማስወገድና ቀጥለን የሚያስፈልገንን ነገር መጠየቅ ያዋጣናል።
ት/ሕዝ 18፥20 "...ንስሐ ግቡ ኃጢአትም ዕንቅፋት እንዳይሆንባችሁ ከኃጢአታችሁ ሁሉ ተመለሱ።
የበደላችሁትን በደል ሁሉ ከእናንተ ጣሉ አዲስ ልብና አዲስ መንፈስም ለእናንተ አድርጉ፤ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ስለ ምን ትሞታላችሁ?"
እግዚአብሔር ከሀብታም ጋር አይደለም፣ ከተማረ ሰው ጋር አይደለም፣ ብዙ ጥሩ ዘመድ ካለው ሰው ጋር አይደለም፤ እግዚአብሔር ሁሌ ከጻድቅ ሰው ጋር ብቻ ነው። ይህ ማለቴ ግን የተማረና ሀብታም ሰው ጻድቅና እግዚአብሔርን የሚፈራ የለም ማለቴ አይደለም ። በአጠቃላይ ማንኛውም ሰው ጽድቅን እየሰራ ብለምን መልሱ አይዘገይም።
በመሳፍ ም.6 ላይ እግዚአብሔር ገድዎንን "አንተ ብርቱ፣ ሀያል ሰው" ያለው በሥጋ በኩል ስናይ ገድዎን ለራሱ ሚድያማውያንን ፈርቶ ተደብቆ ያለበት ቦታ ሄዶ አግኝቶት ነው። ገዴዎን ግን ጠላቶቹን ይፍራ እንጅ ውስጡ ጻድቅ ነው፣ ከሀጢአት የተለየ ነው፣ስለዘመዶቹ እየጸለየ የአባቶቻችን አምላክ ትቶናል እያለ በቁጭት ስተክዝ ወዳለበት ቦታ ሄዶ ነው።
ከሀጢአት የራቀ ሰው፣ ቅድስና የጠበቀ ሰው፣ ምሕረትን የሚጠይቅ ሰው እርሱ ሀያል ሰው ነው። ለጸሎቱ መልሱን ቶሎ ያገኛል።
ስለዚህ በአጠቃላይ የጸሎታችን መልስ የሚያዘገየው ዋነኛ እንቅፋት ወይንም መጋረጃ ሀጢያት ነውና ሀጢያትን ከድንኳናችን አስወግደን እንጸልይ።
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
COMMENT
INBOX @Thaddyapostolic
GROUP @Marantawoch | 2 111 |
| 15 | አይቶ እንዳላየ
አይቶ እንዳላየ፣ ሰምቶ እንዳልሰማ፣ መተላለፋችንን ሳይቆጥር፣ አመፃችንን ሳይለካ እንዲሁ እንደ ቀላል ልጆቹን ይቅር አለን፤ ሁሉን ተወልን፤ እዚህም አደረሰን። የአባትነቱ ፍቅር ልጆቹን ማረከ፣ ይቅርታው ፀጋን አበዛልን፣ ምህረቱ በረከትን አደለን። ዛሬ ነገ ጠፋን፣ ዛሬ ነገ ሔድን ስንል ሁሉን ማበጀት የሚያውቅ አምላክ ደንቅን አድርጎ ሌላ እድል ሰጠን፤ ከፊቱ አቆመን፣ ስሙን እንድንጠራ፣ እንድናመሰግነው፣ እንድናወድሰው ፀጋውን አደለን፤ ብርታት በረከቱን ጨመረልን። የሚሰጥ እርሱ የሚነሳ እርሱ፣ የሚያከብር እርሱ የሚያዋርድ እርሱ። ነገር ግን እንደስልጣኑ ሳይሆን እንደ ቸርነቱና እንደ ርህራሔው ስጦታውን አበዛልን፤ ክብርን ጨመረልን፤ በሰው ፊት ሞገስን አደለን፤ በቤቱ አቆየን፤ በመላዕክት ዘንድ ዘወትር የሚወደሰው ስሙን እናወድስና እናከብር ዘንድ እድሉን ሰጠን፤ ወደ እራሱም አስጠጋን።
አይቶ እንዳላየ፣ ሰምቶ እንዳልሰማ ሁሉን ትቶልህ፣ ሁሉን ረስቶልህ የተወልህን አምላክህን ለማመስን፣ ስሙን ለመጥራት፣ ከፍከፍም ለማድረግ አንደበትህ ባይፈታ፣ ቃላት ባይሰናዱልህ እንዲህ እያልክ ስራውን አክብር፤ ለምህረቱ አመስግን፤ ይቅርታውንም ዳግም ተማፀን። " ሁሉን እያወክብኝ ዝም አልክልኝ፣ ሁሉን እያየህብኝ አለፍክልኝ። ስራዬ ይቅርታ ባይገባውም፣ ተግባሬ አንተ ፊት ባያቆመኝም፣ ክፋቴ ስምህን ለመጥራት ባያበቃኝም አንተ ግን ሁሉን ተውክልኝ፤ ይቅር አልክልኝ፤ ከፊትህም በምህረት አቆምከኝ፤ ስምህን እንድጠራ ፈቀድክልኝ። ምንም ባወራ፣ ምንም ባደርግ በምላሴ እንዳልጠፋ፣ በተግባሬ እንዳልሰናከል ዘወትር የምትጠብቀኝ፣ የከፋውን መንገድ ለልጆችህ እንዳልጠቁም፣ ከእኔ መጥፋት በላይ ሌሎችን ወደ ጥፋት እንዳልመራ ዘወትር እየጠበክ የምትገስፀኝ፣ መንገዱን የምትመራኝ ደጉ አባቴ አመሰግናለሁ።
ክፋት ያደክማል፤ ህግጋትህን መተላለፍ ያስጨንቃል፤ ከቤትህ መራቅ ያስፈራል ነገር ግን ይህን ሁሉ በማስጨነቁ አልተወኩትም፤ በማድከሙ አላቆምኩትም፤ በአስፈሪነቱ አልተለየውትም። ህግጋትህን እያወኩ ሰበርኩት፣ ትዕዛዝህን ተረድጄ ከመተግበረ አፈነገጥኩ። አምላኬ እንደ ምህረትህ እንጂ እንደ ጥፋቴ፣ እንደ ቸርነትህ እንጂ እንደ በደሌ እዚህ አልደረስኩምና እንደ ቀድሞው ሁሉ መተላለፌን አትቁጠርብኝ፤ ጥፋቴን አትይብኝ። ማድረግ የሚገባኝን ረስቼ ማድረግ የማይገባኝን፣ የማይወክለኝ፣ የማይገልፀኝን እርሱን አደርጋለሁና አንተ አስተዋይ ልቦናን ስጠኝ፤ በምህረት እጆችህ ዳሰኝ፤ አንደበቴን ጠብቅልኝ፤ ተግባሬንም ቀድስልኝ። " በማለት አክብሮት ልመናህን አድርስ። ልመናህ እንደሚሆንም በሙሉ ልብህ አምነህ ተቀበል።
ውብ ምሽት ይሁንልን! | 2 072 |
| 16 | ሰው ያለውን ነው የሚሰጠው ።
በልባችን ምንድነው የሞላው❓
በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፉ ይናገራልና መልካም ሰው ከልብ መልካም መዝገብ መልካሙን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከልብ ክፉ መዝገብ
ክፉውን ያወጣል።" ሉቃስ 6:45
#በልባችን ምን ሞላቷል ❓በልባችን የሞላው ስራችንን ይገልፃል ።
✍ በልባችን የሞላው መልካም ከሆነ የምናደርገው የምንሰራው መልካም ነው ።
ክፉ ከሆነ ከልባችን ክፋትን እናውጣለን።
✍ አንድ ታሪክ ላስታውሳቹ
በአንድ መንደር የሚኖሩ ሰዎች ነበሩ በአንዳንድ ጉዳይ ላይ ባለመስማማታቸው የሚኖሩበትን መሬት ለሁለት ተካፈሉ
አንደኞች በግራ ሌሎች በቀኝ መኖር ቀጠሉ ።
በግራ ያሉት ወደ ቀኝ የተጠቀሙበትን ቆሻሻ መጣል ጀመሩ ።
በቀኝ ያሉት ደሞ ወደ ግራ ፍራፍሬ ሙዝ ፣ ማንጎ ብርትኳን ... ይጥሉ ጀመር ።
በግራ ያሉት ወደ ቀኝ ቆሻሻ መጣል በቀኝ ያሉት ወደ ግራ ፍራፍሬ አዘውትረው ሁል ጊዜ መጣላቸውን ቀጠሉ ።
ከእለታት አንድ ቀን በግራ ያሉት በቀኝ ያሉትን እንዲ ሲሉ ጥያቄ ይጠይቃሉ ፦
እኛ ቆሻሻ ስንጥልባቹ እናንተ ግን የሚበላ ጥሩ ነገር ትጥሉልናላቹ
ግን ለምን ❓ አሉ
በቀኝ ያሉት እንዲ ሲሉ መለሱ ፦
ሰው ለሰው የሚሰጠው ያለውን ነገር ነው። ውስጡ ክፋት ካለ ክፋትን መልካምነት ካለ ደግሞ መልካምነትን ይሰጣል
እኛም ለናንተ የሰጠነው ያለንን ነገር ነው አሉ ።
እኛስ በውስጣችን ምን አለ❓
መልካም የምናደርገው ሰው መልካም ሰላረገልን ሳይሆን ያለንን ነው የምናሳየው
መልካም ነን ወይስ ክፉ❓
ስራችንን እንመልከት ስራችን መልስ ይሆነናል ።
ሰው የሚሰጠው ያለው ነው ምን አለን ❓
@MARANATHAWOCH | 2 326 |
| 17 | የማለዳ ትምህርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል?
ክፍል 6 ለሰዎች ለመተያየት ብለን ስንጸልይ
ኢየሱስ በማቴ 6፥5 ላይ ለሰዎች እንዳስተማረው ብዙ ሰዎች ችግራቸውን ለእግዚአብሔር ከመናገር ይልቅ ለአጠገባቸው ላሉ ሰዎች ለማሳየት የሚናገሩ የሚመስል ጸሎት ይጸልያሉ። የጎረቤት ሰዎች እገለ ጸላይ ነው፤ ምሽት ተነስቶ እየጸለየ ነው እንድባሉ ፈልገው ብቻ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ይጸልያሉ።
ኢየሱስ ግን ስያስተምር ያለው በሰማይ ያለው አባታችሁ ገና ሳትነግሩ የልባችሁን መሻትና ፍላጎት ያውቃልና ድምጻችሁን ሳታወጡ በሰውር ጸልዩ አላቸው። ለሰው ለመታየት ብሎ የሚጸለየው ጸሎት ወደ ሰማይ አይደርስም፣ በከንቱ ድካም ሆኖ ይቀራል። ምክንያቱም ዋጋቸውን ከዚህ ምድር ተቀብሎዋሉና ይላል። ጸሎት ግን ሰማይ ደርሶ ከሰማይ መልስ ይዞ መምጣት አለበት። አለበለዚያ መልሳችን ለምን ዘገየ እያልን ከመኖር ውጭ ጥቅም አይኖርም።
ጸሎታችን እኛና እግዚአብሔር ብቻ የሚንነጋገርበትና የሚናወቅ መሆን አለበት። ጸሎት የግል ጉዳይ እስከሆን ድረስ የአጠገባችን ሰው መስማት የለበትም። በእርግጥ የጋራ ጸሎትም አለ፤ እዚህ ቦታ እኔ እያልኩ ያለሁትኝ ስለ ግል ጸሎት ነው።
ነገር ግን ድምጽ ከፍ አድርጎ ለሰው ለመተያየት የሚጸለየው ጸሎት የግብዞች ነው ይላል። እንደዚህ አይነት ጸሎት መኩራቦች ይወዳሉ፤ ለሰዎች ለመተያየት ብለው መንገድ ይወጣሉ፤ ዋጋቸውን ከሰማይ ሳይሆን ከዚህ ይቀበላሉ።
ማቴ 6፥5 ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና በመንገድ ማዕዘን ቆመው መጸለይን ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።
አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።
አሕዛብም በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደ እነርሱ በከንቱ አትድገሙ።
ስለዚህ አትምሰሉአቸው፤ ሳትለምኑት አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና።
የቃላት መደጋገም፦ ለመተያየት ብለን ቃላቶችን መደጋገም አያስፈልገንም። እኛ ሳንነግረው እንኳ የልባችን መሻትና ፍላጎት የሚያውቅ አምላክ ነው።
የሐና ጸሎትን አስተውሉ፦ ስንጸልይ እንደ ሐና እብድ እስክንመስል ድረስ ከንፈራችንን ብቻ እያንቀሳቀስን እንጸልይ።
ሐና ስትጸልይ በልቧና በከንፈርዋ ነው እንጅ በአፏ አውጥታ ኦየተናገረች ያዙኝ ልቀቁኝ አይነት ጸሎት አልጸለየችም። እንደው ካህኑ ዔል "ስካርሽ እስከመቼ ነው? የወይን ጠጅሽን ከአንቺ አርቂው" እስክላት ድረስ ከንፈሩዋን ብቻ እያንቀሳቀሰች ነበረ።
1ሳሙ 1፥12-14 ጸሎትዋንም በእግዚአብሔር ፊት ባበዛች ጊዜ ዔሊ አፏን ይመለከት ነበር።
ሐናም በልብዋ ትናገር ነበር፤ ድምፅዋም ሳይሰማ ከንፈርዋን ታንቀሳቅስ ነበር፤ ዔሊም እንደ ሰከረች ቈጠራት።
ዔሊም። ስካርሽ እስከ መቼ ነው? የወይን ጠጅሽን ከአንቺ አርቂው አላት።
ሐናም። ጌታዬ ሆይ፥ አይደለም፥ እኔስ ልብዋ ያዘነባት ሴት ነኝ፤ ጠጅና ሌላ የሚያሰክር ነገር አልጠጣሁም፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ነፍሴን አፈሰስሁ፤.....
መልስ ይዞ የሚመጣ ጸሎት ይህ ነው ማለት ነው። እግዚአብሔር የልብ ጸሎት እንጅ የአፍ ጸሎት አይፈልግም። ይህ ማለት ከልብህ የሚመነጭ ወይንም ምርር ያለ ጸሎት ይፈልጋል እንጅ ሰው ለማየት ብቻ ወይንም ጸሎት ነው ስለተባለ ብቻ ምዛን የሌለ፤ ያልተመሰጠ ጸሎት መጸለይ መልሳችንን ያዘገያልና እንጠነቀቅ። ሐና በሰውር የለመነችውን ልመና በግልጥ ከፍሎላታል። ሰው ስደረገልን ወይም ስሆንልን ብቻ ነው መስማት ያለበት እንጅ ስንጸልይ ማየት የለበትም።
እግዚአብሔር የመተያየት ጸሎት አይፈልግም፤ እሱ የግብዞች ጸሎት ነውና። ጸሎታችን ለምን ዘገየ ማለት ብቻ ትተን በምን ምክንያት ነው፣ ምኑ ጋር ነው የተበላሸው የሚለውን ለመፈተሽ እነዚህ ትምህርት ክፍሎች መከታተል ወሳኝ ነው ብዬ አምናለሁ።
ትምህርት በዚህ ሁኔታ ከተመቻችሁ ይቀጥላልና ይቀጥል በሉኝ።
ይቀጥላል........
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
COMMENT
Inbox @Thaddyapostolic
Group @Marantawoch | 2 311 |
| 18 | #እምነት
የሁል ግዘ ጥያቀያችን ፣ ለምን እንዴት አለሆነልኝም? እንዴትስ አይሳካልኝም ? ብዙ ለፋሁ ብዙ ጣርኩ ነዉ በልባችን የምመላለሰዉ ከራስ ጋር የሁል ግዘ ትግላችን እሱ ነዉ
በዋናነት እንዳይሳካልንና እንዳይሆንልን ማደርገዉ ነገር ምንድነዉ ብለን ስንቶቻችን ነን በመንፈስ ሆነን ራሳችንን ጠይቀን
ምናውቀው ?
በመጻፍ ቅዱስ የአንድ ነገር አለመሆን መንስኤ
አለማመን ውይም እምነት ማጣት እንደሆነ ይገልጽልናል።
ማቴዎስ 21 ፥ 20፤ ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው፡— በለሲቱ ያንጊዜውን እንዴት ደረቀች? ብለው ተደነቁ።21፤ ኢየሱስም መልሶ፡— እውነት እላችኋለሁ፥ እምነት ቢኖራችሁ ባትጠራጠሩም፥ በበለሲቱ እንደ ሆነባት ብቻ አታደርጉም፤ ነገር ግን ይህን ተራራ እንኳ፡— ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር፡ ብትሉት ይሆናል፤
ለምአምኑት ምንስ ያደርጋል??
ማርቆስ 10 ፥ 51፤ ኢየሱስም መልሶ፡— ምን ላደርግልህ ትወዳለህ? አለው። ዕውሩም፡— መምህር ሆይ፥ አይ ዘንድ፡ አለው።52፤ ኢየሱስም፡— ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል፡ አለው። ወዲያውም አየ በመንገድም ተከተለው።
እህት ውንድሞቸ እስት ልጠይቃችዉ
1.የእናንተ ችግር ከተራራ በላይ ይሆናልን?
2.እናንተ ያቃታችሁ ለሱ ያቅተዋልን ?
ማቴዎስ 21 ፥ 22፤ አምናችሁም በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ ትቀበላላችሁ፡ አላቸው።
ላመኑት ብዙ ታምር የሰራ ጌታ
ባለማመናችን ስለበደልነዉ ሀሉ
ምህረቱን ይላክልን!!!!!!
የምናደርገውን ሀሉ በእምነት እንድናደርግ ጌታ ይርዳን ይጎበኘን
ያግዘን 🙏🙏 | 2 545 |
| 19 | https://youtu.be/imKdw6Bx--c?si=OTnb-j5V5e7x8SUc | 2 499 |
| 20 | بدون متن... | 231 |
