ch
Feedback
ማራናታ.....MARANATHA

ማራናታ.....MARANATHA

前往频道在 Telegram

ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic

显示更多

📈 Telegram 频道 ማራናታ.....MARANATHA 的分析概览

频道 ማራናታ.....MARANATHA (@maranathawoch) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 17 381 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 4 709,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 984

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 17 381 名订阅者。

根据 03 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 350,过去 24 小时变化为 22,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 19.50%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.09% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 388 次浏览,首日通常累积 1 406 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 23

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic

凭借高频更新(最新数据采集于 04 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

17 381
订阅者
+2224 小时
+1097 天
+35030 天

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+88
在2个频道中
八月 '26
+349
在17个频道中
Get PRO
七月 '26
+376
在9个频道中
Get PRO
六月 '26
+358
在17个频道中
Get PRO
五月 '26
+289
在15个频道中
Get PRO
四月 '26
+319
在26个频道中
Get PRO
三月 '26
+405
在19个频道中
Get PRO
二月 '26
+243
在19个频道中
Get PRO
一月 '26
+253
在18个频道中
Get PRO
十二月 '25
+280
在18个频道中
Get PRO
十一月 '25
+292
在17个频道中
Get PRO
十月 '25
+229
在17个频道中
Get PRO
九月 '25
+270
在11个频道中
Get PRO
八月 '25
+350
在16个频道中
Get PRO
七月 '25
+333
在16个频道中
Get PRO
六月 '25
+243
在9个频道中
Get PRO
五月 '25
+340
在17个频道中
Get PRO
四月 '25
+306
在9个频道中
Get PRO
三月 '25
+447
在12个频道中
Get PRO
二月 '25
+277
在12个频道中
Get PRO
一月 '25
+349
在8个频道中
Get PRO
十二月 '24
+408
在7个频道中
Get PRO
十一月 '24
+350
在6个频道中
Get PRO
十月 '24
+346
在6个频道中
Get PRO
九月 '24
+402
在8个频道中
Get PRO
八月 '24
+474
在7个频道中
Get PRO
七月 '24
+442
在8个频道中
Get PRO
六月 '24
+495
在17个频道中
Get PRO
五月 '24
+589
在13个频道中
Get PRO
四月 '24
+448
在10个频道中
Get PRO
三月 '24
+529
在9个频道中
Get PRO
二月 '24
+480
在8个频道中
Get PRO
一月 '24
+515
在7个频道中
Get PRO
十二月 '23
+536
在18个频道中
Get PRO
十一月 '23
+416
在12个频道中
Get PRO
十月 '23
+478
在8个频道中
Get PRO
九月 '23
+236
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+187
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+210
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+187
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+253
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+281
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+110
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+98
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+226
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+180
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+152
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+128
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+176
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+212
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+317
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+177
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+108
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+134
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+103
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+59
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+92
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+41
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+119
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+144
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+204
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+152
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+262
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+290
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+189
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+219
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+229
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+209
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+214
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+2 623
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
04 九月+28
03 九月+22
02 九月+18
01 九月+20
频道帖子
🌻🌻 2017 🌻🌻 ዘማሪ ሹሚ ኤልያስ አሳለፍከኝ ያንን አመት እንደ ሃጢአቴ ሳትሆንብኝ በማይዝል ትከሻ የሱስ ተሸክመህ በምህረት እጆችህ አጠንክረህ ይዘህ በከፍታዎች ላይ በድል አራመድከኝ ክፉ እንዳይነካኝ በክንፍህ ከልለህ አሳለፍከኝ ያንን አመት እንደጥያቴ ሳትሆንብኝ ክበር ሌላ ምን እላለው ሞገስ ሆንከኝ አከብርሀለው

2
🌼«ለአዲስ ዓመት የምሆን መዝሙር »🌼 ዘማሪ ወንድም በረከት እግዚአብሔር አሻገርኝ እግዚአብሔር አሻገርኝ መከራዬን እየሰረሳኝ ከፊት ሆኖ እየመራኝ ዛሬን አየሁ ተሻገርከኝ |2× አልሆንም እንደ ጠላቴ ቀደምልኝ ደጉ አባቴ እጄን ይዞ እያሳለፍን መደገፊያ ጋሻ ሆኖልኝ ዛሬን አየሁኝ ለዚህ በቃሁ |2× እኔም  ዛሬ ቀን ወቶልኛል የታመንኩት እዚህ አድርሶኛል ያልጠፋሁት በምህረቱ  ነው መደገፍያ ጋሻ ሆኖኝ ነው |2× 1| ኢየሱስ ምህረቱን በህይወቴ አብዝቶ ዘመን ዓመትን ሲያሳልፍኝ የጠላቴን ሀሳብ ከንቱ እያረገ ከፊት ለፊቴ እየመራኝ ዛሬ ፈቱ ቆመ ሰሙን እንዳከብር አለሁ በህይወት ክንዱ  ደግፎኝ ጉዞ ያስጀመረኝ መልካሙ እረኛዬ በክፉ  ቀንም መሸሻግያየ |2× እኔም ዛሬ ቀን.... 2| እረ ማነው እንደኔ ያለ ያመሰግነው ክብር እያለ |2× እረ ማነው እንደኔ ያለ ያክብርው እልል እያለ |2× እኔ ነኝ ዛሬ በደስታዬ እኔ ነኝ የሱስን ላመልከው እኔ ነኝ ጥበቃው በዝቶልኝ በፊቱ ሞገስ ያገኘሁት እኔ ነኝ የምህረቱ ውጤት እኔ ነኝ በእርሱ መልካምነት ኤረ እንዴት መልካም እረኛ  ነው ብዘምር ይሄም ሲያንሰበት ነው ይክብር |2× በምስጋናዬ ይክብር |2× በእልልታዬ  አሻገሬነኝ ኢየሱስ ጌታዬ |2× እኔም  ዛሬ ቀን...
2
3
በማይዝል.... (1).m4a
1 546
4
# የቃሉ ሀይል የእግዝአብሔር  ቃል ሰማይን አጽንቶ ያቆመ በሰማይና በምድር ያሉትን አራዊት ሁሉ ይሁን ብሎ የፈጠረ  ከምንም ነገር በላይ ሀይል ያለዉ ነዉ፦        ዘፍጥረት 1 ፥ 1፤ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።3፤ እግዚአብሔርም፡— ብርሃን ይሁን፡ ኣለ፤ ብርሃንም ሆነ።5፤ እግዚአብሔርም ብርሃኑን ቀን ብሎ ጠራው፥ ጨለማውንም ሌሊት፡ አለው። ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ፥ አንድ ቀን። 6፤ እግዚአብሔርም፡— በውኆች መካከል ጠፈር ይሁን፥ በውኃና በውኃ መካከልም ይክፈል፡ አለ።7፤ እግዚአብሔርም ጠፈርን አደረገ፥ ከጠፈር በታችና ከጠፈር በላይ ያሉትንም ውኆች ለየ፤ እንዲሁም ሆነ። 11፤ እግዚአብሔርም፡— ምድር ዘርን የሚሰጥ ሣርንና ቡቃያን በምድርም ላይ እንደ ወገኑ ዘሩ ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን ታብቅል፡ አለ፤ እንዲሁም ሆነ።14፤ እግዚአብሔርም አለ፡— ቀንና ሌሊትን ይለዩ ዘንድ ብርሃናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ፤ ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ፤15፤ በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር ብርሃናት ይሁኑ፤ እንዲሁም ሆነ። 16፤ እግዚአብሔርም ሁለት ታላላቆች ብርሃናትን አደረገ፤ ትልቁ ብርሃን በቀን እንዲሠለጥን፥ ትንሹም ብርሃን በሌሊት እንዲሰለጥን፤ ከዋክብትንም ደግሞ አደረገ።17፤ እግዚአብሔርም በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር አኖራቸው፤      የሆነዉ ነገር ሁሉ በእርሱ ሆነ      የተደረገውንም  ሁሉ በቃሉ አደረገ ዮሐንስ 1 ፥ 3፤ ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም።         የእግዚአብሔር ቃል የሞተዉን ያነሳል         የቃሉ  ሀይል እዉሩን ያበራል ቃሉ ህዉይታችን ያለመልማል ቃሉ መንፈሳችን ያድሳል ቃሉ ሀይል አለዉ ። የእግዝአብሔር  ቃል  በሀይል ይሰራል ሁል ግዘ የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት እንትጋ  ከምንም ነገር አስበልጠን ተናግረን  ብለን  ቃሉን ለመስማት እንትጋ እግዝአብሔር በአንድም በሌላም ይናገራል ተብሎ ተጽፈዋል ስለዝ  ሀል ግዘ ውደፊቱ ቀርበን የምትናገረው አለና ተናግን እንበል።
1 582
5
አዲሱን አመት አዲሱን ዘመን *2 ያገልግሎት የሰላም የፍቅር ዘመን አድርግልን ነፍሳት ከያቅጣጫው የሚጎርፉበት በወንድማማች ፍቅር የምንዋደድበት ቤተክርስትያን አድጋ እሰይ የምንልበት ይሁን እየሱሴ አንተ ምትከብርበት ያገልግሎት... አዲሱን አመት... የእያሪኮ ግንብ የሚፈርስበት ይህ እውነት በአለም ዙሪያ አንድ የሚሆንበት የሀዋርያት ወንጌል ብቻ ሚሰበክበት ይሁን እየሱሴ አንተ ምትከብርበት እሺ ዝቅ እያልን የምንዋደድበት ወንድሜ ሆይ በርታ አይዞህ የምንልበት ልብህ ተደስቶ እሰይ የምትልበት ይሁን የድል አመት አንተ ምትክብርበት አዲሱን አመት... በፆምም በፀሎት የምንበረታበት ሀይልህም ከሰማይ የሚወርድበት ጥላቻ እርቆ ፍቅር የሚሰፍንበት ይሁን የድል አመት አንተ ምትነግስበት @MARANATHAWOCH
1 342
6
የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል? ክፍል 12 ለተቀበልነው ነገር አለማመስገን እግዚአብሔር መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልም የሚገባው አምላክ ነው። ብዙ ጊዜ ሰው ግን ስጠኝ ማለት እንጂ እንካ፥ ተቀበል ማለት ይረሳል። እግዚአብሔር መስጠት እንደሚችል እንዳመንን እንዲሁ መቀበልም እንደሚችል ማመን ወሳኝ ነው። ከሁሉም ነገር እግዚአብሔር የሚፈልገው ነገር ብኖር ለሰጠው ነገር ሁሉ እንድናመሰግነው ነው። ስላደረገልን ነገር እያመሰገንን እንደገና እንዲያደርግልን ለፈለግነው ነገር መጸለይ አለብን። በዚህ ምድር ላይ ሰው እንኳ ለተቸገረ ሰው የፈለገውን እርዳታ ሰጥቶ ምላሽ ስያጣ "ይህ ሰው ውለታ ቢስ ነው፤ ምስጋና የለውም " ይላል። እንደገና ተቸግሮ እንዳኝ ስል ለባለፈው ነገር መች አመሰገንከኝና አሁን ሊጨምርልህ የሚል ምላሽ ይሰጣል። በዛውም ልክ ከእግዚአብሔር ለተቀበልነው ነገር ሳናመሰገንን ለመቀበል ብቻ መቸኮል ለጸሎታችን መልስ አያስገኝም። እኛ አናውቅም እንጅ ያልተሰጠን ነገር ምን አለ? እኛ በእጃችን የሚታይ ንብረትና ገንዘብ አይተን ለማመስገን እንፈልጋለን። ነገር ግን ከገንዘብ የበለጠ ሀብታችን እንዳለን እንረሳለን። ዋና ሀብታችን መዳናችን፣ ሠላማችንና ጤናችን ብቻ ለማመስገን በቂ ምክንያት ነው። በሰውነታችን ውስጥ ያለውን እያንዳንዱን የሰውነት ክፍላችን ወደ ብር ብንቀይር ስንት ይሆን ነበረ? ለምሳሌ  የአንድ ጥርስ ዋጋ ስንት ብር ነው? በ32 አባዙ። የአንዱ ኩላልታችን ዋጋ ስንት ነው? በ2 አባዙ። የአንድ አይናችን ዋጋ ስንት ነው? በ2 አባዙ፤...... የሁሉንም ሰውነታችን አካል ክፍል ወደ ብር ቀይሩ እስቲ። ይህ ሁሉ በሠላም በጤና ተጠብቆ የሚኖር ነገር ግን ለእኛ የማይታይ ሀብታችን ነው። እኛ ጧት ተነስተን እጃችንና ፊታችን ሊንታጠብ እንሮጣለን፤ ሌላው ግን በየጧቱ ኩላሊቱን ሊታጠብ የሚሮጥ አለ። ከእኛ ውስጥ ብያንስ አንድ ሰውነቱ ክፍል ታምሞ መታከም የሚችል ማነው? መጀመሪያ ላለን ሠላም ሳናመሰግን ገንዘብ ከለከለን ብለን እንወቅሳለን። እርሱ ግን መጀመሪያ ባለህ ነገር አመስግን ይለናል። ሌላው ብቀር መዳናችን ብቻ በብር የሚተመን ነው? ስንት ቢሊየን ያላቸው ሰዎች ይህንን መዳን ሳያገኙ ይሞታሉ? ለእኛ ግን አንድ ብር ለሌለን ሰዎች ይህንን መዳን በነጻ ሰጥቶን በቤቱ አኑሮናል። ይህ ብቻ የሚናመሰገንበት ትልቅ ምክንያት ነው። "እጅ ያለው ወርቅ እንደ መዳብ ይቆጠራል" እንደሚባለው ነው ምንም ያልመሰለን እንጅ በእጃችን ያለው ነገር በዋጋ የሚተመን አይደለም። ዘዳግ 28፥47&48 ሁሉን አብዝቶ ስለ ሰጠህ አምላክህን እግዚአብሔርን በፍሥሐና በሐሤት አላመለክህምና በራብና በጥማት በዕራቁትነትም ሁሉንም በማጣት እግዚአብሔር ለሚልክብህ ለጠላቶችህ ትገዛለህ፤ እስኪያጠፋህም ድረስ በአንገትህ ላይ የብረት ቀንበር ይጭናል። እስራኤል ለሠራላቸው ተአምራት የማያመሰገኑ ናቸው፥ ነገር ግን ለሚሰጣቸው ነገር ብቻ የሚለምኑ፤ይህ ነገር መጨረሻቸውን አላሳመረላቸውም። ውለታውን ፈጥነውም እየረሱ ስያስቸግሩ የለመኑትንም ሁሉ ሰጣቸው፤ ለነፍሳቸው ግን ክሳትን ላከ ይላል። መዝ 106፥13-15 "ፈጥነውም ሥራውን ረሱ፥ በምክሩም አልታገሡም። በምድረ በዳም ምኞትን ተመኙ፥ በበረሃም እግዚአብሔርን ተፈታተኑት። የለመኑትንም ሰጣቸው፤ ለነፍሳቸው ግን ክሳትን ላከ።" እግዚአብሔር የለመንነውን ቶሎ ብመለስልን እንኳ የሰጠን በረከት ለነፍሳችን የማይጠቅም ከሆነ ምን ዋጋ አለን? ለእስራኤል ይህንን የነፍስ ክሳት ያመጣው ውለታውን መርሳት ነው እንጂ አለማመን አይደለም። ሥጋችንን አወፍሮ ነፍሳችንን የሚያከሳ በረከት አሁንም ቤታችን አይግባ። ስንጸልይ ይህንን የሰጠሄን አንተ ነህና ተመስገን እያልን ምስጋና እየሰጠን አሁንም የቀረውን አንተ ታውቃለህ እንድንል ይፈልጋል እንጂ ለኔ፣ ለኔ፣ ለኔ ብቻ የሚል ጸሎት አይሰማም። በቆላስ 4፥12 "ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ"ይላል። ጸሎት ከምስጋና ጋር ነው እንጂ በእምባና በለቅሶ ጋር ብቻ አይደለም። እንኳን ለተሰጠን ነገርና ላልተሰጠን ነገርም የሚናመሰግን አምላክ ነው። ሰጥቶም ነስቶም እርሱ አምላክ ነውና። ኢዮብ ይህ ሁሉ ፈተና ደርሶለት እያለ አንድም ቀን እግዘብሔርን አልበደለም። ይልቅ እግዚአብሔር ሰጠ፤ እግዚአብሔር ነሳ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን"አለ እንጂ። እኛ ዛሬ እንኳን ልጆቻችንና እንስሳቶቻችን ማለቅ ይቅርና 1000 ብር ከክሳችን ወጥቶ ብጠፋ እግዚአብሔር አላወቀኝም፤ እግዚአብሔር እኔን ይጠላል እያልን እስከ ስድብ እንደርሳለን። ልጁ ሞቶበት ማነው እግዚአብሔር ይመስገን የሚል? እንዲህም አለ። ራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን ወጥቻለሁ፥ ራቁቴንም ወደዚያ እመለሳለሁ፤ እግዚአብሔር ሰጠ፥ እግዚአብሔርም ነሣ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን። ፤ በዚህ ሁሉ ኢዮብ አልበደለም፥ ለእግዚአብሔርም ስንፍናን አልሰጠም። በእኛ ዘመን እንኳን ትንሽ የታገሰ ሰው ነው የሚንለው ሰው እግዚአብሔር ሰጠ፤እግዚአብሔር ነሳ የሚል ሰው ብኖር ነው። የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን የሚልማ ተፈልጎም አይገኝም። ስለዚህ ለተቀበልነው ነገር አለማመስገን ለሚንቀበለው ነገር መንገድ አይሰጥምና እንጠነቀቅ። መቀበል ብቻ ሳይሆን መስጠትንም እንልመድ። ፊልጵ 4፥6 ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ። ይቀጥላል..... @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH INBOX @Thaddyapostolic GROUP @Marantawoch
1 489
7
Adama ACOE ደቡብ አጥቢያ New apostolic song Singer: fechatu Title: ባንተ ተሻግሬ ባንተ ተሻግሬ ባንተ ሁሉን አልፌ ባንተ ይሄው ቆሜ ባንተ ዛሬን አይቼ ላንተ አቀርባለሁ ምስጋናዬን ላንተ አቀርባለሁ እልልታዬን ላንተ አቀርባለሁ የድል መዝሙር ላንተ አቀርባለሁ ይሄው የሱስ ይሄው/*2 የሱስ/*4 1/ረዳቴ አንተው ነህ እኔን የረዳሄኝ   አቅሜ ሆነኸኝ የሱስ ያሻገርከኝ ምን ብልህ ይሻላል ምንስ ይመጥናል ምስጋና አምልኮ ይሄው አፌ  ሞልቷል ላንተ ይሁን ምስጋናዬ ይሁን አምልኮዬ ይሁን ለስምህ ይሁን ክብር ላንተ ሁሉን ለምትችል ሁሉን ላደረከው ኤልሻዳይ ለሆንከው 2/አቀበት ቁልቁለት ስወጣ ተራራውን በእሳት በሀሩር ውስጥ የነበርክ ከኔጋር (በሀሩሩ መሀል የነበርክ ከኔጋር) አይኖቼን አንስቼ አንተን ስመለከት ነይ ልጄ ብለኸኝ ይዘህ ያራመድከኝ   ረዳቴ ከወዴት ይምጣልኝ አይኖቼን አንስቼ እየጠበኩ እኔን የሚረዳኝ የሚያግዝ ባልኩኝ ስዓት ደረስክ እየሱስ ረዳኸኝ/*2 አገዝከኝ/*2 ይሄው ለክብር አቆምከኝ 3/ሁሉን የምትችል ክንደ ብርቱ አምላክ ጉልበት ስልጣን ያለህ በእውነት ምትታመን የማትለዋወጥ በዘመናት መሀል ተመስገን እየሱስ ክብር ይገባሀል  እልል/*4 ለስምህ ክብር ይሁንልህ ኤልሻዳዩ አምላክ እየሱስ ውዳሴ አምልኮ ይቅረብልህ
1 567
8
የዛሬው ጥያቄና መልስ በጣም ጥሩ ተወዳዳሪዎች የተገኙበት ውድድር ነው። ይሁን እንጅ አብዘኞቹ AI ,App በመጠቀም ነው የሠሩት። ስለዚህ ለወደፊት ጥንቃቄ አድርጉ ማለት እወዳለሁ። ካልሆነ ይህንን ፕሮግራም አቆማለሁ። የሁሉንም ውጤት ለማጣራት ሞክረያለሁ ከእነዚህ ውስጥ ያለ AI ከሠሩት ውስጥ 1, እህት Tina 10/10 አብዘኞቹ ግን 9/10 ናቸው። ስለዚህ የፈለገችውን PDF የሚትሸለመው እህት Tina ነች ማለት ነው በዚህ ከቀጠላችሁ የጥያቀና መልስ ፕሮግራም ይቆማል። ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ምን ያህል እየተከታተልኩ ነኝ የሚለውን ማሳያ ነው እንጅ ከክፍል ወደ ክፍል ማለፊያ አይደለም። app መስራት የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀት መለክያ አይደለም።
1 573
9
አሁን መልስ ተለቋል አቁሙ
437
10
መልስ 1, ጓጉንቸሮች። ዘፀዓት 8፥13 እግዚአብሔርም ሙሴ እንዳለ አደረገ፤ ጓጕንቸሮቹም ከቤት ከወጀድም ከሜዳም ሞቱ። 14 እንደ ክምርም አድርገው ሰበሰቡአቸው፤ ምድርም ገማች። 2, 7 ቀን። ዘፀዓት 7፥25 እግዚአብሔርም ወንዙን ከመታ በኋላ ሰባት ቀን ተፈጸመ። 3, 12 ወራት ነው። አሥር 2፥12 የመንጻታቸውም ወራት ስድስት ወር ያህል በከርቤ ዘይት፥ ስድስት ወርም በጣፋጭ ሽቱና በልዩ ልዩም በሚያነጻ ነገር ይፈጸም ነበርና እንደ ሴቶች ወግ አሥራ ሁለት ወር እንዲሁ ከተደረገላት በኋላ ወደ ንጉሡ ወደ አርጤክስስ ለመግባት የአንዳንዲቱ ቆንጆ ተራ በደረሰ ጊዜ፥...... 4, ሄጌ ይባላል። አስተር 2፥3 ሴቶችን ከሚጠብቅ ከንጉሡ ጃንደረባ ከሄጌ እጅ በታች እንዲያደርጓቸው መልከ መልካሞቹን ደናግል ሁሉ ወደ ሱሳ ግንብ ወደ ሴቶች ቤት ይሰበስቡአቸው ዘንድ ንጉሡ በመንግሥቱ አገሮች ሁሉ ሹማምቶችን ያኑር፤ ቅባትና የሚያስፈልጋቸውም ይሰጣቸው፤ 5, የሙሴ ሦስት ሲፓራም። 25 ሲፓራም ሚስቱ ባልጩት ወሰደች፥ የልጅዋንም ሸለፈት ገረዘች፥ ወደ እግሩም ጣለችው፡— አንተ ለእኔ የደም ሙሽራ ነህ አለች። 6, የሞከብ ንጉሥ ዔግሎም። መጻፍ 3፥17 ለሞዓብም ንጉሥ ለዔግሎም ግብሩን አቀረበ፤ ዔግሎምም እጅግ ወፍራም ሰው ነበረ። 7, ሐ ሠለሞን 2ዜና 9፥17 እና 1ነግ 10፥18ንጉሡም ደግሞ ከዘሆን ጥርስ ታላቅ ዙፋን አሠራ፥ በጥሩ ወርቅም ለበጠው። 8, ሐ ዕዝራ። ዕዝራ 7፥6 የእስራኤልም አምላክ እግዚአብሔር በሰጠው በሙሴ ሕግ ፈጣን ጸሐፊ ነበረ፤ የአምላኩም የእግዚአብሔር እጅ በእርሱ ላይ ነበረችና ንጉሡ የሻውን ሁሉ ሰጠው። 9, ለ 10, ሀ ለ9&10 የራዕይ ትርጉም መጽሐፍ አምብቡ @MARANATHAWOCH አስተያየት @Thaddyapostolic ላይ ጻፉ
1 655
11
+10 ደቂቃ
323
12
ጥያቄና መልስ መልስ @Thaddyapostolic ላይ ብቻ inbox አድርጉልኝ አደራ። #ማሳሰቢያ፦ ከ1-6 ላለው ጥያቄ ከነ ቃሉ ጥቅስ ማስረጃ ጋር መልሱ። ካልሆነ መልሱ ትክክል ብሆንም ግማሽ ይሰጣል። የተሰጠ ሰአት 30 ደቂቃ ነው 1, የግብፅ ምድር ሙሉ የገማው መች ነው ማለትም የትኛው መቅሰፍት በወረደ ጊዜ ነው? 2, በፈርኦን ልብ ደንዳናነት ምክንያት በግብፅ ምድር ውሀ ወደ ደም ተለውጦ ስንት ቀን ቆየ? 3, በንጉሡ አርጠክስስ ዘመን የነበሩ ሴቶች ወደ ንጉሡ ለመቅረብ እራሳቸውን እያስዋቡ በተመረጠ ቤት ውስጥ ምን ያህል ቆዩ? 4, ለንጉሡ አርጠክስስ የሚሆኑ ሴቶች መርጦ ቅባትና የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ እየሰጣቸው ሴቶችን የሚያይዋብ የንጉሡ ጀንደረባ ማነው? 5, በመጽሐፍ ቅዱስ ታርክ ውስጥ የራሷን ልጅ በባልጩት የገረዘች ሴት ማን ነች? 6, ከሞአብ ህዝብ ሁሉ እጅግ ወፍራም ሰው ማን ነበረ? 7, ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ታላቅ ዙፋን የነበረው ንጉሥ ማነው? ሀ ዳዊት ለ ናቡከድናፆር ሐ ሰለሞን መ ሙሴ 8, የአምላኩ የእግዚአብሔር እጅ ከእርሱ ጋር ነበረች የተባለለት ፈጣን ፀሐይ ማን ይባላል? ሀ ያቤጽ ለ አሳፍ ሐ ዕዝራ  መ ኤርምያስ 9, ከሰባቱም አብያተ ቤተክርስቲያናት ውስጥ የአመንዝራ ቤተክርስቲያን ምሳሌ የሆነች ቤተክርስቲያን የትኛው ነች? ሀ ሰርደስ ለ ቲያጥሮን ሐ ጰርጋመን መ ሎዶቂያ 10, "የጥንቱ ሀይማኖት ሰጠን" ተብሎ የተዘመረው በየትኛው ቤተክርስቲያን ዘመን ነው? ሀ ፍላደልፍያ ለ ኤፈሶን ሐ ሰርደስ መ ሎዶቂያ @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH መልስ @Thaddyapostolic ላይ ብቻ መልሱልኝ
1 659
13
ማሳሰብያ፦ ሐሙስ የጥያቄና መልስ ምሽት ውድ የማራናታ ተለግራም ቻናል ቤተሰብ እንደምን ቆያችሁ? ዛሬ ማታ ማለትም ሐሙስ ምሽት ልክ 2: 00 ላይ የጥያቄና መልስ ውድድር ይኖረናል። በጊዜ ገብታችሁ እንድትሳተፉ አሳስባችኋለሁ። አንደኛ ለወጣ ተወዳዳሪ ከታች ከተዘረዘሩት pdf የፈለገውን pdf እንሸልማለን። pdf 1, የዘፍጥረት እንቁዎች ብሾፕ ዳዊት ጦሼ 2 ገንዘብና መንፈሳዊ ህይወት ብሾፕ አንዱአለም 3 የመዳን እውቀት መፅሐፍ ብ/ ደጉ 4 በሥርአት ታነፁ ብሾፕ ተ/ማሪያም 5 የራዕይ ትርጉም pdf ብሾፕ ደጉ 6, የእውነት ወንጌል ጥሪ ፓስተር በረከት 7 ኢየሱስን ማን ይሉታል ብሾፕ ተ/ማርያም 8 ቃሉ  ይናገር ብሾፕ ተ/ማርያም 10 የሥላሴ አጠያያቂ ምስጥር ቄስ ኤልያስ ሸባባው 11 የንስር መንገድ 12 መፅሐፍ ቅዱስ ትምህርት ለጀማሪዎች ብሾፕ ተክሌ 13 ህይወት የሚገኝበት ትምህርት ብሾፕ ደጉ 14 ወደ መዳን የሚያደርስ እውነት ብሾፕ ደጉ 15 መንፈሳዊ ወጣት 16 እውነት እና ምህረት 17 እምነት በእግዚአብሔር ቃል 18 የመዳናችን ምስጥር 19 የመልዕክቶች አጠቃላይ ትምህርት ብሾፕ ተክሌ 20 Eschatology Final destiny of humanity ብሾፕ ጌታሁን 21 የአንድ አምላክ ልጆች ይለይ 22 መሠረታዊ የክርስትና ትምህርቶች . . . ከእነዚህና ሌሎችንም መርጦ #አንዱን ይወስዳል። ለጓደኞቻችሁ ሼር አድርጉ። ልብ በሉ ! መልስ @Thaddyapostolic ላይ ብቻ ይመለሳል @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH
1 341
14
ዛሬም_አለ_የጎፋ_ቢ_መዘምራን_Apostolic_Church_of_Ethiopia360p.mp3
1 842
15
''የአምላክ ምህረት እንዳልተለየን የኔ፣ የእናንተ፣ የሁላችን በህይወት መኖር አንዱ ማሳያ ነው።'' ✍ እኛ ሰዎች ደካሞች ፥ ሀጢያተኞች፥ ክፉ አሳቢዎች፥ ትቢያዎች። ግን በምህረቱ ኗሪዎች ። የተሸከምነው ስጋ፥ ያጌጥንባቸው አልባሳቶች፥ ያደረግነው ጫማ፥ የአለም መልክ ሁለንተናችንን ይዞ ፈጣሪን አስረስቶናል። ልባችን በአለም ምኞት ታውሮ፥ የልብ አይናችን ጠፍቷል። ማሰቢያችንን ተነጥቀናል። ልባችን ከማስተዋል ርቋል። “ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?” የሚለውን ቅዱስ ቃል ተላልፈን ከነፍሳችን ይልቅ ገደብ ለታጣው ለሥጋችን አምሮት ብለን እልፍ ሀጢያት ውስጥ ተዘፍቀናል። ያለምንም ድካም፥ ያለምንም ክፍያ ሰማያዊ ዜጋ የመሆን ምርጫ በእጃችን ሳለ በገዛ ፈቃዳችን፥ ከዲያብሎስ መንደር ገሃነም ለመግባት እንሽቀዳደማለን። እውነቱን መረዳት መልካም ነው። የብርሃንን ጥቅም ለመረዳት የጨለማን ጎጅነት ማወቅ አለብን። ያኔ ለብርሃን ዋጋ መስጠት እንጀምራለን። ✍ እኛ አላዋቂዎች፥ ስጋ ለባሾች ስሜታችን ገፍቶን ከፈጣሪ አጣልቶናል። ግን አምላክ መሀሪ ነውና ይኸው አለን። ለሰጠን ነገር ሳናመሰግነው፥ የጎደለን  እየጠየቅን እናማርራለን። ችግሩኮ መለመኑ አይደለም። እስቲ ስለተቀበልነው እናመስግነው! ተመስገን ማለት ይልመደን። እኛ ጥዋት ተነስተን ፊታችንን ስንታጠብ፥ ሌላው ጥዋት ተነስቶ ኩላሊቱን 'ሚታጠብ አለና ተመስገን እንበለው። ምስጋናን ልማድ እናድርገው። ✍ እንዳለመታደል ሆኖ እኛ ሰዎች ካልተጎዳን አንማርም፥ ካልተቀጣን አናስተውልም፥ ካላመመን ጤነኛ የሆንን ይመስለናል። የአምላክ ምህረት እንዳልተለየን የኔ፣ ያንተ፣ ያንቺ በህይወት መኖር አንዱ ማሳያ ነው። በሃጢአታችን ልክ ሳይቀጣን፥ በህይወት ያቆየን ፅድቃችን በዝቶ ሳይሆን ምህረቱ ጋርዶን ነው። ይኸው ዛሬም አለን በምህረቱ። እርግጥ ነው በእግዚአብሔር ምህረት ነው እስካሁኗ ደቂቃ በህይወት የቆየነው ግን እስከመቼ ነው ምህረቱን ተማምነን የሀጢያታችንን ጉድፍ በንሰሃ ውሃ እያነጻን የምንኖረው? ማስተዋልን ይስጠን! ✍ ጊዜአችንን፣ ገንዘባችንን፣ ጉልበታችንን ሰውተን በገዛ ፈቃዳችን ከጥፋት ሳንወዳጅ የምህረት እጁን እንዲልክልን፥ የልብ አይናችንን እንዲያበራልን ልዑል ወደሆነው እግዚአብሔር በተሰበረ ልብ ፀሎት እንቅረብ! አምላክ መሀሪ ነውና! ልብ እንበል ዛሬ መኖራችን ምህረቱን አብዝቶ ዕድሜ ስለጨመረልን ነው። አለን በምህረቱ!!!!! የምህረት ጌታ ይመስገን! ምህረቱ አይለየን! አሜን!!! @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH
1 726
16
የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል? 11, የጸሎታችን ክብደት በማነስ ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት ተመዝኖ የሚታይ ምዛናዊ ንግግር ነው። በዚህ ምድር ላይ በመንገድ ዳር ተቀምጦ የሚለምን ለማኝ እንኳን የሰውን ቀልብ ለመሳብና ሰው እንድራራለት ብሎ እስክደክም ድረስ አቅሙ የሚፈቅደውን ሁሉ አድርጎ ይለምናል። ነገር ግን በመንገድ ላይ ስለተቀመጠ፣ ለማኝ ነው ስለተባለ ብቻ ሰዎች አይራሩለትም። የሚናገረው ንግግር፣ የሚያወጣው ቃላቶች የሰዎችን ሆድና አንጀት የሚበላና የሚላወስ መሆን አለበት፤ ሰዎች አጥብቆ ለለመነ ሰው ነው የሚሰጡት። ለመለመን እውነተኛ ድሃ መሆን ያስፈልጋል። አንዳንድ ለማኞች በመንገድ ላይ ስቀመጡ ለመዝናኛ የተቀመጠ ሰው የሚመስሉም አሉ። ለመለመን ወጥቷሉ ግን የመለመን ዘዴ አላወቁም። አንድ ብርም ሳይወስዱ ማታ ጨርቃቸውን ሰብስበው ወደ ቤት ይመለሳሉ፤ ሌሎች ግን የሰውን አንጀት በቃላቶቻቸው በልተው ብዙ ብር ሰብስበው ይገባሉ። ይህ የልዩነታቸው ምስጥር የቃላቶች ክብደትና ቅለት ላይ የተፈጠረ ነው። በዛውም ልክ እግዚአብሔር የሚያየው አጥብቆ የሚጸልየው ሰው ብቻ ነው። አንዳንድ ሰው በልቡ ሌላ ነገር እያሰበ የአጠገቡ ሰው ሰለተምበረከከ ብቻ ተምበርክኮ ለመንኩ ብሎ መልስ ይጠብቃል። ጸሎቱ ከልቡ የመነጨ ስላልሆነ መልሱን አያገኝም። በእርግጥ የአንድ ሰው የነገሩ ክብደት ሰውዬ እንዳደረገው ይሆናል። ይህ ማለት ለነገሩ ክብደት ሳይሰጥ ቀለል አድርጎ ካዬ ለእሱ ቀላል ነው፤ ከባድ ነው ብሎ value ሰጥቶ ካሰበ ይከብዳል፤ በክብደቱ ልክም ይጸልያል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ቦታ እግዚአብሔር ለጸሎታቸው መልስ የሰጣቸው ሰዎች ስንመለከት በጸሎታቸው ጀርባ "አጥብቀው ጸለዩ፣ አጥብቀው ለመኑ፣አብዝተው ጮኹ፣እምባቸውን አፈሰሱ፣... የሚሉ ቃላቶችን እናገኘዋለን። የዛን ቦታ ደግሞ ጸሎታቸውን ሰማ፣ መለሰላቸው፣ ፈወሳቸው... የሚሉ ቃላቶች አሉ። የጸሎት መልስ ያለው አጥብቆ በመጸለይ ላይ ነው እንጂ በምኞትና እንደ ተራ ነገር አድርገን ከፈለክ ስጠኝ ካልፈለክ ተውው እነደሚባል አይነት ጸሎት በመጸለይ አይደለም። ስፈልግ መጸለይ ካልፈለገ መተው፣ ቀጠሮ እየሰጠ እንደ dim-light ብርሃን ቦግ-ጥርቅም ማለት የጸሎት ባህርይ አይደለም። ያዕ 5፥17-18 የኤልያስ ጸሎት እንመልከት ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች። መልስ ያለው በማጣበቅ ላይ ነው እንጂ ፈዛዛ ጸሎት ጸልየህ ኢየሱስን ጥፋተኛ አታደርግ። የሃናም በጸሎት እንመልከት፦ ሃና በየአመቱ ሊትጸልይ ወደ ኢየሩሳሌም ትወጣ ነበረች። ነገር ግን ነገሩ ስከብድባትና ስጨንቃት በመጨረሻ ላይ አጥብቃ ጸለየች። የተጠቀመችው ቃላቶችም የሚገርሙና የእግዚአብሔርን ልብ የሚነኩ ናቸው። 1ሳሙ 1፥10-11እርስዋም በልብዋ ትመረር ነበር፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸለየች፥ ጽኑ ልቅሶም አለቀሰች። እርስዋም። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ የባሪያህን መዋረድ ተመልክተህ ብታስበኝ፥ እኔንም ባትረሳ፥ ለባሪያህም ወንድ ልጅ ብትሰጥ፥ ዕድሜውን ሁሉ ለእግዚአብሔር እሰጠዋለሁ፥ ምላጭም በራሱ ላይ አይደርስም ብላ ስእለት ተሳለች። ይህ ንንግሯ ነው የእግዚአብሔርን ሆድ የበላው። በፊትም እግዚአብሔር ጸሎቷን ያቆየው ወደ እርሱ ስላልደረሰ ሳይሆን ከአንደበቷ የፈለገው ቃላቶችና የጸሎት ክብደት አለ ማለት ነው። ማህጸኗንም አውቆ እንደ ዘጋ በቁ.6 ላይ ይናገራል። የጸሎቷ ቃላቶች በክሎ ተመዝኖ ክብደት ካገኘ በኋላ ነው የመለሰላት። እግዚአብሔር የፈለገውን ደረጃ ደርሰን እስክንጸልይ ድረስ የጸሎታችን መልስ እንደማይመልስ ይህ ጥሩ ማሳያ ነው። ዛሬ ለእኛም የትኛው ቃላት ጠብቆ እንዳቆየን መፈለግ አለብን። በሉቃ 18፥35 እና ማር 10፥46 ላይ የተጻፈው የጤሜዎስ ልጅ ዕውሩ በርጠሜወስ አብዝቶ ባይጮኽና ሰዎች ዝም በል ስሉት ዝም ብል እፈወስ ነበረ? ምን አስጮኸው? የችጎሩ ክብደት ስለታየውና ይህ ፈዋሹ አምላክ በአጠገበ ወጥቶ ሳያልፍ እድለን ልሞክር ብሎ ነው። ሁለተኛ ይህንን ዕድል አላገኝም ብሎ ሳይፈራ አብዝቶ ጮኾ ተፈወሰ። መጮህ ማለት ኢየሱስ ሳያልፍ አጠገብህ እያለ ነውና ዛሬ ጮሄህ ተፈወስ ወንድሜ። አብዝቶ መለመንና አብዝቶ መጮህ ለጥያቄ መልስ ይሰጣል። በመሀል gap እየሰጠን የሚንጸለየው ጸሎትና ትዝ ስለን ብቻ ጌታ ሆይ እኔን መቼ ትመለከተኛለህ? ማለት ለጸሎታችን መልስ ያዘገያል፤ እንጠነቀቅ። ሉቃ 18፥1-8 ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥ እንዲህ ሲል። በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች። ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለው ነበር። አያሌ ቀንም አልወደደም፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ። ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር፥ ይህች መበለት ስለምታደክመኝ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ አለ። ጌታም አለ። ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ። እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? እላችኋለሁ፥ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን? ወንድሞችና እህቶች በእግዚአብሔር ፊት መጸለያችን ካልቀረ ሚዛኑን የሚያነሳ ጸሎት እንጸልይ እንጂ ክብደት የሌለውን ጸልየን እግዚአብሔርን አንወቅስ። አንዳንድ ሰው ተቸግሮ አንድ ማታ ከጸለየ 2ኛው ቀን እግዚአብሔር ረሳኝ ጸሎተን አይመልስም ብሎ ለውቀሳ ይቸኩላል። እንኳን ኢየሱስ አንተን ሊረሳና የራስህን ጸጉር ቁጥር ያውቃል። መጀመሪያ ጸሎትህን አስተካክል፤ እረሱ እንደሚፈልግህ ሆነህ ቅረብ። ሐዋ ሥራ 2፥5 ላይ ጴጥሮስ በወህኒ ስታሰር ምዕመናን ወደ ቤተክርስቲያን ገብተው አጥብቀው ጸለዩለት። እጅ እግሩን በሰንሰለት የታሰረውን ጸሎት ብቻ ፈታች። እስክ አንተ/ች አጥብቀህ/ሺ ጸልይ/ዪ ጸሎት እንደማይፈታ ታያለህና/ሺና። ነገር ግን አጥብቀህ/ሺ ሳትጸልይ/ዪ እግዚአብሔርን አትወቅስ/ሺ። ይቀጥል የሚትሉ ወንድሞችና እህቶች በግሩፕ ላይ ብያንስ 10 ሰው add አድርጉ። ይቀጥላል...... @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH INBOX @Thaddyapostolic GROUP @Marantawoch
1 993
17
#የሐሰተኞች_ነቢያት_ባሕሪያት 1) እግዚአብሔር ሳይናገር ትንቢት የሚናገሩ ናቸው ሕዝ 22፡28 2) ሳይላኩ የሚሄዱ ናቸው ኤር 23፡1፤የሐዋ-ሥራ 15፡24 3) ይሳካልሃል እያሉ ገዥዎቸንና ባለጠጎችን የሚያታልሉ ናቸው 1ነገሥ 22፡5-6፤የሐዋ.ሥራ 13፡6-12 4) ተሳዳቢዎች ናቸው 2ጴጥ 2፡9-12፣ይሁዳ 1፡10 ራዕይ 13፡5 5) ዳፋሮችና ኩሩዎች ናቸው 2ጴጥ 2፡10 6) ቅንን መንገድ የሳቱ ናቸው 2ጴጥ 2፡15፤ይሁዳ 1፡15 7) ኃጢኣትን የማይተው ናቸው 2ጴጥ 2፡14 8) የሚያጠፋ ኑፋቁ አሾልከው የሚያገቡ ናቸው 2ጴጥ 2፡1 9) ብዙዎችን በመዳራታቸው የሚያስከትሉ ናቸው 2ጰጥ 2፡2 10) ገንዘብን ያአግባብ በመሰብስብ የተጠመዱ ናቸው 2ጴጥ 2፡3 11) ክንቱ የሆነ ከመጠን በላይ ቃል ይናገራሉ 2ጴጥ 2፡18 ራዕይ 13፡5 12) ራሳቸውን ከመጠን በላይ ከፍ ከፍ የሚያድርጉ ናቸው 2ተስሎንቄ 2፡4 13) ውኃ የሌለባቸው ምንጮችና ዝናብ የሌለባቸው ደመናዎች ናቸው 2ጴጥ 2፡17፤ ይሁዳ ቁ-12 14) የሚንከራተቱ ከዋክበት ናቸውጨይሁዳ ቁ- 13 15) የሰይጣን ስህተት አሠራር መሣሪያዎች ናቸው 2ተስሎንቄ 2፡7-12 16) የጥፋት ባሪያዎች ሆነው አርነት ትወጣላችሁ የሚሉ ናቸው 2ጴጥ 2:19 17) ጸጋውን በሴሰኝነት የሚለውጡ ናቸው ይሁዳ 1:4 ቁ.7 2ጴጥ2:18 18) በሀሰተኛ ድንቆችና ታኣምራቶች የታጀቡ ናቸው 2ተሰሎንቄ 2:9-10; ማቴ 24:24; ራዕይ 13:13 19) ያለእውነተኛው ኢየሱስ እውቅና በውሸት አጋንንት የሚያስወጡ ናቸው ማቴ 7:22 20) የእውነተኛ አገልጋዮች መልክ የያዙ ግን በውስጣቸው ነጣቂዎች ናቸው ሜቴ 7:15; 2ቆሮ 11:13 21) እውነተኛውን ኢየሱስን የሚሰብኩ ይመስላሉ ነገር ግን በሥራቸው የካዱ ናቸው ይሁዳ 1:4; ቲቶ 1:16 22) የማይጸኑ ነፍሳትን የሚያታልሉ ናቸው 2ጴጥ 2:14 23) እየሳቱ የሚያስቱ ናቸው 2ጢሞ 3:13 24) ለፍርድ የተመደቡ ናቸው ይሁዳ 1:4 ቁ-14 25) ውሸተኞች ሐዋሪያትና ተንከለኞች ሠራተኞች ናቸው 2ቆሮ 11:13 26) እንደብርሃን መልአክ ራሳቸውን ልለውጡ ይችላሉ 2ቆሮ11 27) ታላቅ ነገርና ስድብ የሚናገሩበት አፍ አላቸው ራዕይ 13:5 28) አጋንንታዊ ግን ማራኪ ትምህርት ያስተምራሉ 1ጢሞ 4:1 29) ዓለምን ሀብትና ክብር ሰይጣን ለኢየሱስ የሰበካውን ይሰብካሉ ማቴ 4:6 30) ያለሥርዓት የሚሄዱና የሚኖሩ ናቸው 2ተሰሎንቄ 3:11 31) ነውረኛ ረብ ለማግኘት የሚተጉ ናቸው ቲቶ 1:11-12 32) የማይታዘዙ፤ከንቱ የሚናገሩና የሚያታልሉ ናቸውቲቶ 1:10 33) እውነተኛውን የእግዚአብሔርን ቃል ገልብጠው የምናገሩ ናቸው ዘፍ 3:4 ፤ቲቶ1:1 34) መንፈሳዊ የሚመስል የተድላ ዘፈን የሚዘፍኑ ናቸው 2ጴጥ 2፡13 35) ከሰማይ እሳት እስኪያወርዱ ታላላቅ ምልክቶችን ሊያደርጉ ይችላሉ ራዕይ 13:13 36) በምዕመናን መካከል ወይም በባልና በሚሰት መካክል መለያያትን የሚዘሩ ናቸው ሮሜ 16፡17፤ቲቶ 3፡10-11 37) ወደምዕመናን መካክል ሾልከው የሚገቡ ናቸው 2ጢሞ 3፡6-7፤ይሁዳ ቁ- 4 38) ክርስቶስን ለመምሰል የሚስማማ ጤናማ ትምህርት የማያስተምሩ ናቸው1ጠሞ 6፡3 39) በትዕቢት የተነፉ ናቸው 1ጢሞ 6፡4 40) እግዚአብሔርን መምሰል ማትረፊያ አድርገው የሚጠቀሙ ናቸው 1ጢሞ 6፡5 41) ለሆድ የተገዙ ናቸው ሮሜ16፡18፤ፊልጵ 3፡19 42) በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግር የሚያታልሉ ናቸውሮሜ 16፡18 43) እውነትን የተቀሙ ናቸው 1ጠሞ 6፡5 44) ቃሉን የሚያጣምሙ ናቸው 2ጼጥ 3:16 45) ዓመፀኞች ናቸው 2ጴጥሮስ 3:17; 2:13 46) ሥልጣን ያላቸውን/መሪዎችን በድፍረት ይሳደባሉ 2ጴጥ 2:10 47) ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ናቸው የሐዋ 20:29 48) ደቀ መዛሙርትን ወደኃላ የሚስቡ ናቸው የሐዋ 20:30 49) ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ናቸው ሐዋ 20:30 50) የተማራችሁትን እውነተኛ ትምህርት የሚቃወሙ ናቸው ሮሜ 16:17 51) መለያየትንና ማሰናከያ የሚያደርጉ ናቸው ሮሜ 16:17 52) በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግር ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ ሮሜ 16:18 53) የዋጃቸውን ጌታ የሚክዱ ናቸው 2ጴጥ 2፡1፤ይሁዳ ቁ-4) 54) ፍጻሜአቸው ግን እንደሥራቸው ይሆናል! 2ቆሮ 11:15 ማጠቃለያ ሮሜ 16:17 ወንድሞች ሆይ እናንተ የተማራችሁትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና ማሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንድትመለከቱ እለምናችኋለሁ ከነእርሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH
1 907
18
📌የሙት ባህር ጥቅልሎች (The Dead Sea Scrolls) ⚜በታሪክ፣ በሃይማኖት እናበአርኪኦሎጂ ዘርፍ እጅግ አስፈላጊ እና በዓለም ታዋቂ የሆኑ ጥንታዊ የጽሁፍ ሰነዶች ናቸው። ስለ እነዚህ ጥቅልሎች ማወቅ የሚገቡዎትን ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው አዘጋጅቼላቸዋለሁ፦ 1. 📌ግኝቱ (Discovery)ጥቅልሎቹ የተገኙት በ1947 እና በ1956 መካከል፣ በምዕራብ ባንክ በሚገኘው ቁምራን (Qumran) በተባለ ቦታ አቅራቢያ በሚገኙ ዋሻዎች ውስጥ ነው። በአጋጣሚ የተገኙት በአንድ በዱር በግ እረኛ ወጣት ሲሆን፣ በሸክላ ማሰሮዎች ውስጥ ተጠቅልለው ለዘመናት ሳይበላሹ ቆይተው ነበር። 2. 📌ይዘታቸው (What are they?) በድምሩ ወደ 900 የሚጠጉ የእጅ ጽሁፎች ተገኝተዋል። እነዚህም በዋነኝነት የተጻፉት በዕብራይስጥ፣ በአረማይክ እና በጥቂቱ በግሪክ ቋንቋዎች ነው። ዋና ይዘታቸውም የሚከተሉትን ያጠቃልላል፦ •   የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች፦ ከመጽሐፈ አስቴር በስተቀር፣ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በሙሉ (ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል) ተገኝተዋል። ከነዚህ መካከል በጣም የታወቀው የኢሳይያስ ትንቢት ሙሉ ጥቅልል ነው። •   የኑሮ መመሪያዎች፦ በቁምራን ይኖሩ የነበሩ ሰዎች (አሴንስ ይባላሉ ተብሎ ይታመናል) ህጎች፣ የጸሎት መጽሐፍት እና የስርዓተ አምልኮ ደንቦች። •   የአፖካሊፕቲክ ጽሁፎች፦ ስለ መጨረሻው ዘመን፣ ስለ ብርሃን እና ጨለማ ልጆች ትግል የሚያወሱ ምስጢራዊ ጽሁፎች። 3. 📌ለምን አስፈላጊ ናቸው? የሙት ባህር ጥቅልሎች በዓለም የሃይማኖት ታሪክ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ያመጡበት ምክንያቶች፡- •  📌 የብሉይ ኪዳን አስተማማኝነት፦ እነዚህ ጥቅልሎች ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ250 እስከ ክርስቶስ ልደት በኋላ ባለው ጊዜ የተጻፉ ናቸው። ከነዚህ ጥቅልሎች በፊት የነበሩን የብሉይ ኪዳን ቅጂዎች ከዘጠነኛው ክፍለ ዘመን በኋላ የተጻፉ ነበሩ። በሁለቱ መካከል የሺህ ዓመት ልዩነት ቢኖርም፣ የጽሁፎቹ ይዘት እጅግ ተመሳሳይ መሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ጽሁፎች በጊዜ ሂደት ሳይለወጡ እንደተጠበቁ የሚያሳይ ጠንካራ ማስረጃ ሆነ። •   የጁዳይዝም እና የክርስትና መነሻ፦ ጥቅልሎቹ በኢየሱስ ክርስቶስ ዘመን የነበረውን የአይሁድ እምነት ሁኔታ፣ አስተሳሰብ እና የኑሮ ሁኔታ በግልጽ የሚያሳዩ ናቸው። የክርስትና መነሻ ከነበረው የአይሁድ ባህል ጋር ያለውን ግንኙነት ለመረዳት ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። 4. 📌ማን ጻፋቸው? ምሁራን በአብዛኛው እንደሚያምኑት፣ እነዚህን ጽሁፎች የጻፉት አሴንስ (Essenes) የሚባሉ የአይሁድ ቡድን አባላት ናቸው። እነዚህ ሰዎች ከኢየሩሳሌም ከተማ በመውጣት፣ ከብክለት ለመራቅ እና በንጽህና ለመኖር ወደ በረሃው ገብተው ይኖሩ እንደነበር ይገመታል። 📌 5. አሁን የት አሉ? አብዛኛዎቹ የጥቅልል ክፍሎች የሚገኙት በኢየሩሳሌም በሚገኘው "የመጽሐፍ ቤተ መቅደስ" (Shrine of the Book) ውስጥ ነው። ይህ ህንጻ የተገነባው ጥቅልሎቹ በተገኙበት የሸክላ ማሰሮ ቅርጽ ተመስሎ ነው። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH
1 870
19
አስተማሪ ታርክ #አንዲነታችን_ይጠበቅ 🐂 የጅቡና የሶስቱ በሬዎች ተረት ከዕለታት አንድ ቀን ነጭ፣ ቀይና ጥቁር የሆኑ ሶስት በሬዎች አብረው ይኖሩ ነበር። አንድነታቸውም ስለጠነከረ አውሬዎች ቢመጡባቸው በአንድነት ይዋጉ ነበር። አንድ ጅብ ግን በሬዎቹን አይቶ፦ “እነዚህን ሶስቱን አብረው እያሉ መብላት አልችልም፤ መከፋፈል አለብኝ” ብሎ አሰበ። ጅቡም በሬዎቹን ከሩቅ እየተመለከተ አንድ ቀን መጣና ነጩን በሬ ነጥሎ፦ “እናንተ ቀይና ጥቁሮች በጨለማ አትታዩም። እኛ ግን ነጩን በሬ ከሩቅ እያየን ነው የምንመጣው። እሱን ብታባርሩት እናንተን አንረብሽም” አላቸው። በሬዎቹም የጅቡን ቃል አምነው፣ ነጩን በሬ ከመካከላቸው አባረሩት። ጅቦቹም ነጩን በሬ ለብቻው አግኝተው በሉት። ከዚያም ጅቡ ወደ ጥቁሩና ቀዩ በሬ ተመልሶ ጥቁሩን፦ “አንተ ጥቁር ስለሆንክ በጨለማ አትታይም፤ ቀዩ ግን ከሩቅ ይታያል። እሱን ብታስወግድ ሰላም ታገኛለህ” ብሎ አሳመነው። በመጨረሻም ቀዩን በሬ ከጥቁሩ በሬ አለያዩት። ጅቦቹም ቀዩን በሬ ለብቻው አግኝተው በሉት። ጥቁሩ በሬ ብቻውን ሲቀር ጅቦቹ በቀላሉ ከበቡት። በዚያን ጊዜ ጥቁሩ በሬ ተንኮሉን ተረዳ፤ ግን በጣም ዘግይቶ ነበር። ስለዚህ “ጠላት አንድነትን ማፍረስ ከቻለ ማሸነፍ ይችላል። ስለዚህ በተለያዩ ምክንያቶች መከፋፈል ሳይሆን አንድነትን መጠበቅ ያስፈልጋል። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH
1 984
20
ግጥም አገልጋዮች እንሁን 〰〰〰〰〰〰〰 ይድረስ ለወጣቶች በዚ ዘመን ላለን የቅዱስ የእግዚአብሔር ልጆቹ ለሆንን የኢየሱስን ስራ ድቃድቁን ላየን ከጥፋት ሊያድነን በደሙ ለገዛን እግዚአብሔር ለስራው ሰውን ይፈልጋል ወታደር ሊያደርገን ጌታ የሱስ ይሻል ታዲያ ወንድሜ ሆይ አንቺም የኔ እህት ተዘጋጅተን ይሆን ልፈፅም እቅዱን ለእግዚአብሔር ስራ አገልጋይ ለመሆን እግዚአብሔር ሰርቷል ጥንት በነቢያት ህዝቡን አስተምሯል ባባቶች አንደበት በሙሴ ተጠቅሞ ህዝቡን ሲያሶጣ በልጁ በእያሱ አህዛብን ሲቀጣ እንደልቤ ባለው ጎልያድን ሲመታ ደግሞም በኤልያስ በአልን ሲረታ በፈጠረው ፍጥረት ያውም በሰው ልጅ ነው ለቅዱስ አላማ አገልጋይ ያረገው ሐዋሪያትን መርጦ ወንጌልን ሲያሰብክ ከለም ዳር እስከዳር ፍጥረትን ሲማርክ አባቶችም ደግሞ ይህን ተረክበው እዚ አድርሰዋል በአገልግሎት ኖረው እናም በዚ ዘመን አንተን እኔን መርጧል እግዚአብሔር ለስራው ሰውን ይፈልጋል ታዲያ ወንድሜ ሆይ አንቺም የኔ እህት ተዘጋጅተን ይሆን ልፈፅም እቅዱን ለእግዚአብሔር ስራ አገልጋይ ለመሆን የቱ ይጠቅመናል የቱስ ይሻለናል? አለምን ወደናት አገልግሎት ትተን ግያዝን እንሁን ምንወርስ ሀጢያትን ወይስ ካባቶች ጎን ሳጠፋ ሳንለይ መሆን እደ ኤልሳዕ በእጥፍ አገልጋይ እንምረጥ መልካሙን የሂወት ጎዳና አገልጋዮች ያርገን ያዎጣናልና። @MARANATHAWOCH
2 013