ማራናታ.....MARANATHA
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic
Показати більше📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ማራናታ.....MARANATHA
Канал ማራናታ.....MARANATHA (@maranathawoch) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 17 423 підписників, посідаючи 4 703 місце в категорії Релігія і духовність та 1 984 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 17 423 підписників.
За останніми даними від 04 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 375, а за останні 24 години на 27, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 19.33%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 8.05% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 363 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 400 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 22.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37
የመወያያ ግሩፕ👇
@Marantawoch
Inbox Comment @Thaddyapostolic”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 05 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 05 вересня | +26 | |||
| 04 вересня | +28 | |||
| 03 вересня | +22 | |||
| 02 вересня | +18 | |||
| 01 вересня | +20 |
| 2 | ሰላም ይብዛችሁ የኢየሱስ ልጆች
✍ማንም ሰው በአንቴ/በአንች ምክንያት በእግዘአብሔር ፊት ተንበርክኮ እንዳይለቅስ ተጠንቀቅ::
የፍቅር መገለጫ ቅርበት ሲሆን ወንድማችን እና እህታችን መውደድ ግን የመዳናችን ትልቁ ምስጥር ነው:: | 1 178 |
| 3 | የማለዳ ትምሀርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል ?
ክፍል 13 መቅደም ያለበት ነገር አለማስቀደም
የብዙ ሰው ጸሎት የሚያተኩረው በግል ጥቅሙ ላይ ነው እንጂ ለእግዚአብሔር በሚጠቅም ላይ አይደለም። ከዛም አልፎ በዚህ አለም ላይ የራሱን ስም ከፍ ከፍ ለሚያደርጉ ነገሮች ላይ አትኩሮ ይጸልያል። ነገር ግን በዚህ አካሄድ ሰውና እግዚአብሔር አይገናኙም። እግዚአብሔር አስቀድሙ ያለው ለጽድቅና የእግዚአብሔርን መንግስት ነው እንጂ በዚህ ምድር ላይ የሚቀር ጥቃቅን ነገሮችን አይደለም። ይህ እናንተ ተጨነቅን ተብላችሁ የሚትለምኑት ነገር ዋናውን ከፈለጋችሁ የሚጨመርላችሁ ነገር ነው ይላል።
የቀደመውን አስቀድመን እንድንኖር ኢየሱስ ይርዳን።
በእግዚአብሔር ዘንድ ጸሎት ነው ተብሎ ሚዛኑን የሚያነሳ ጸሎት ማለት አስቀድመን ለመንግስቱ ስንጸልይ ነው። እኛ ግን ብዙ ጊዜ የግላችን ጥቅም ለማስከበር፣ በዚህ ምድር ላይ ከእገለ በለጥን ለማለት፣ እገለ ሳልደርስ ሊሞት ነው በማለት ለምድራዊ ነገር ብቻ ያተኮረ ጸሎት እየጸለይን እንቆያለን።
የእግዚአብሔር አላማ በእኛ ላይ ያለው ግን እሱ አይደለም።ይህ እኛ የማንፈልገው ጭራ ነው። ቀንዱን ትተን ጭራን አንለምን! ቀንዱ ጽድቅና የእግዚአብሔር መንግስት ስሆን ጭራ ምድራዊ የሆነ የእኛ ፍላጎት ነው። ስለዚህ ነው እግዚአብሔርን መለመን ያለብንን ነገር ለይተን አውቀን እስክንጸልይ ዝም የሚለን።
በእርግጥ በዚህ ምድር ላይ የጸሎቱን መልስ የማይፈልግ ሰው የለም። ይሁን እንጂ ወደ ጸሎት ሰምው ጋር የመቀራረብ ሁኔታ ብቻ ነው ጸሎትን የሚያቆየው እንጂ። ስለዚህ በዚህ ርዕሰ ጀምረን እየተማርን ያለነው ትምህርቶች ተግባራዊ እያደረገ ለሚጸልይ ሰው መልሱ ቶሎ ይመለሳል ብየ በእርግጠኝነት አምናለሁ።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር በሚገርም ሁኔታ ያስቀመጠው፥ ሰው ግን ያልተረዳው የጸሎት መልስ መንገዶች አሉ።
1, የሚንበላውንና የሚንጠጣውን ነገር ከፈለግን አስቀድመን ጽድቅንና የእግዚአብሔርን መንግስት መፈለግ/መጸለይ/ ማቴ 6፥25-33, ሮሜ 14፥17
2, ለህመማችን ፈውስ ከፈለግን አስቀድመን ምህረቱን መጠየቅ። ማር 2፥1, ሉቃ 5፥18, ማቴ 9፥1, ሮሜ 9፥16
3, ሀብታም መሆን ከፈለግን አስቀድመን ጌታን መከተል። ማቴ 19፥27, ማር 10፥28
4, ከእግዚአብሔር አትርፈን መቀበል ከፈለግን ቀድመን ያለንን ለእርሱ መስጠት። ሉቃ 6፥38, ምል 3፥8, 2ቆሮ 9፥6-10
5, በምድር ላይ አርፈን በእረፍት መቀመጥ ከፈለግን ቀምበሩን ተሸክመን እርሱን መከተል። ማቴ 11፥28
እነዚህ ናቸው ማስቀደም ያለብን እንጂ ፍላጎታችን አይደለም። የእኛ ችግር ግን የኋለኛውን ፊት ለፊት ማምጣት ነው። በዚህ ሁኔታ ካልጸለይን መልሳችን አይመጣምና እንጠነቀቅ። ብመለስም እንኳ ለነፍሳችን እረፍት የሚሰጥ አይሆንም። እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩትን ካላደረግን ስጠኝ ማለት እንጅ ምዛኑን አያነሳም።
ከላይ የተዘረዘሩት ነጥቦች ማቢራርያ ካስፈለገ በተለግራማችን ቻናል ውስጥ በሰፊው አለና "የቀደመውን አስቀድም" ብላችሁ search አድርጉ፤ እዚህ ለማብራራት ጊዜ ይፈጃልና።
ሌላው ደግሞ ከልመናችን በፊት ማስቀደም ያለብን ነገር እርሱ እንደሚፈልገን ሆነን መቅረብ። ለዚህ ሀሳብ መነሻ የሚሆንልን የንግስቲቱ የአስቴር ታርክ ስናነብ፦ አስቴር ስለ ዘሩዋ አይሁድና ስለ መርዶክዮስ ሊትለምን ወደ ባሏ ወደ ንጉሡ አርጤክስስ በገባች ጊዜ ሀሳቧን ከመንገሯ በፊት "ለንጉሡ መልካም ሆኖ ብታይ ንጉሡ ወዳዘጋጀሁለት ግብዣ ከሐማ ጋር ዛሬ ይምጣ" አለች።
አስቴር 5፥3-5 ንጉሡም። ንግሥት አስቴር ሆይ፥ የምትለምኚኝ ምንድር ነው? የምትሺውስ ምንድር ነው? እስከ መንግሥቴ እኵሌታ እንኳ ቢሆን ይሰጥሻል አላት።
አስቴርም። ለንጉሡ መልካም ሆኖ ቢታይ ንጉሡ ወዳዘጋጀሁለት ግብዣ ከሐማ ጋር ዛሬ ይምጣ አለች።
ንጉሡም። አስቴር እንዳለች ይደረግ ዘንድ ሐማን አስቸኵሉት አለ። ንጉሡና ሐማ አስቴር ወዳዘጋጀችው ግብዣ መጡ።
አስቴር ከጥያቄዋ በፊት ግብዣ ነው ያቀረበችው። ምክንያቱም ቀልቡን ለመሳብ፤ የበላና የጠገበ ሰው መቼስ -ve መልስ አይመለስምና። ባሌ ነው፥ ደፍሬ ብጠይቅ ምን ያመጣል አላለችም። ለግብዣ እራሱ በትህትና ነው የጠየቀችው።
እኛም እግዚአብሔር አባታችን ብሆንም እንኳ ልጁ የአባቱን ሆድ ለማረሰረስ ምርቃትን ለመቀበል የማያደርገው ጥረት የለምና በዛው ልክ የቀደመዉን አስቀድመን እንቅረብ።
እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩትን ሳታስቀድሙ ለምናችሁ እግዚአብሔርን ጥፋተኛ ወይንም መልስ የማይመልስ ጨካኝ አምላክ አታደርጉት። እርሱ ምንም ብትሉት ሥርአቱን ጠብቆ የሚሠራ አምላክ ነው እንጅ ያለ ሥርአት ዘው ብሎ አይገባምና። ሰይጣን ብቻ ነው ያለ ሥርአት የሚገባው እንጅ እግዚአብሔር የሥርአት አምላክ ነው።
የቀደመውን አስቀድማችሁ ጠይቁ!!
ከተመቻችሁ ይቀጥላል......
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
INBOX @Thaddyapostolic
GROUP @Marantawoch | 1 592 |
| 4 | 6 በሄዱ ጊዜ፥ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ።
መዝሙር ዳዊት 126*6 | 1 |
| 5 | 🌻🌻 2017 🌻🌻
ዘማሪ ሹሚ ኤልያስ
አሳለፍከኝ ያንን አመት
እንደ ሃጢአቴ ሳትሆንብኝ
በማይዝል ትከሻ የሱስ ተሸክመህ
በምህረት እጆችህ አጠንክረህ ይዘህ
በከፍታዎች ላይ በድል አራመድከኝ
ክፉ እንዳይነካኝ በክንፍህ ከልለህ
አሳለፍከኝ ያንን አመት እንደጥያቴ ሳትሆንብኝ
ክበር ሌላ ምን እላለው
ሞገስ ሆንከኝ አከብርሀለው | 2 200 |
| 6 | 🌼«ለአዲስ ዓመት የምሆን መዝሙር »🌼
ዘማሪ ወንድም በረከት
እግዚአብሔር አሻገርኝ
እግዚአብሔር አሻገርኝ
መከራዬን እየሰረሳኝ
ከፊት ሆኖ እየመራኝ ዛሬን አየሁ ተሻገርከኝ |2×
አልሆንም እንደ ጠላቴ
ቀደምልኝ ደጉ አባቴ
እጄን ይዞ እያሳለፍን
መደገፊያ ጋሻ ሆኖልኝ
ዛሬን አየሁኝ ለዚህ በቃሁ |2×
እኔም ዛሬ ቀን ወቶልኛል
የታመንኩት እዚህ አድርሶኛል
ያልጠፋሁት በምህረቱ ነው
መደገፍያ ጋሻ ሆኖኝ ነው |2×
1| ኢየሱስ ምህረቱን በህይወቴ አብዝቶ ዘመን ዓመትን ሲያሳልፍኝ
የጠላቴን ሀሳብ ከንቱ እያረገ ከፊት ለፊቴ እየመራኝ
ዛሬ ፈቱ ቆመ ሰሙን እንዳከብር አለሁ በህይወት ክንዱ ደግፎኝ
ጉዞ ያስጀመረኝ መልካሙ እረኛዬ በክፉ ቀንም መሸሻግያየ |2×
እኔም ዛሬ ቀን....
2| እረ ማነው እንደኔ ያለ ያመሰግነው ክብር እያለ |2×
እረ ማነው እንደኔ ያለ ያክብርው እልል እያለ |2×
እኔ ነኝ ዛሬ በደስታዬ እኔ ነኝ የሱስን ላመልከው
እኔ ነኝ ጥበቃው በዝቶልኝ በፊቱ ሞገስ ያገኘሁት
እኔ ነኝ የምህረቱ ውጤት እኔ ነኝ በእርሱ መልካምነት
ኤረ እንዴት መልካም እረኛ ነው ብዘምር ይሄም ሲያንሰበት ነው
ይክብር |2× በምስጋናዬ
ይክብር |2× በእልልታዬ
አሻገሬነኝ ኢየሱስ ጌታዬ |2×
እኔም ዛሬ ቀን... | 2 |
| 7 | በማይዝል.... (1).m4a | 2 197 |
| 8 | # የቃሉ ሀይል
የእግዝአብሔር ቃል ሰማይን አጽንቶ ያቆመ በሰማይና በምድር ያሉትን አራዊት ሁሉ ይሁን
ብሎ የፈጠረ ከምንም ነገር በላይ ሀይል
ያለዉ ነዉ፦
ዘፍጥረት 1 ፥ 1፤ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።3፤ እግዚአብሔርም፡— ብርሃን ይሁን፡ ኣለ፤ ብርሃንም ሆነ።5፤ እግዚአብሔርም ብርሃኑን ቀን ብሎ ጠራው፥ ጨለማውንም ሌሊት፡ አለው። ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ፥ አንድ ቀን።
6፤ እግዚአብሔርም፡— በውኆች መካከል ጠፈር ይሁን፥ በውኃና በውኃ መካከልም ይክፈል፡ አለ።7፤ እግዚአብሔርም ጠፈርን አደረገ፥ ከጠፈር በታችና ከጠፈር በላይ ያሉትንም ውኆች ለየ፤ እንዲሁም ሆነ።
11፤ እግዚአብሔርም፡— ምድር ዘርን የሚሰጥ ሣርንና ቡቃያን በምድርም ላይ እንደ ወገኑ ዘሩ ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን ታብቅል፡ አለ፤ እንዲሁም ሆነ።14፤ እግዚአብሔርም አለ፡— ቀንና ሌሊትን ይለዩ ዘንድ ብርሃናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ፤ ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ፤15፤ በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር ብርሃናት ይሁኑ፤ እንዲሁም ሆነ።
16፤ እግዚአብሔርም ሁለት ታላላቆች ብርሃናትን አደረገ፤ ትልቁ ብርሃን በቀን እንዲሠለጥን፥ ትንሹም ብርሃን በሌሊት እንዲሰለጥን፤ ከዋክብትንም ደግሞ አደረገ።17፤ እግዚአብሔርም በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር አኖራቸው፤
የሆነዉ ነገር ሁሉ በእርሱ ሆነ
የተደረገውንም ሁሉ በቃሉ አደረገ
ዮሐንስ 1 ፥ 3፤ ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም።
የእግዚአብሔር ቃል የሞተዉን ያነሳል
የቃሉ ሀይል እዉሩን ያበራል
ቃሉ ህዉይታችን ያለመልማል
ቃሉ መንፈሳችን ያድሳል
ቃሉ ሀይል አለዉ ።
የእግዝአብሔር ቃል በሀይል ይሰራል
ሁል ግዘ የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት እንትጋ ከምንም ነገር አስበልጠን ተናግረን ብለን ቃሉን ለመስማት እንትጋ
እግዝአብሔር በአንድም በሌላም ይናገራል
ተብሎ ተጽፈዋል ስለዝ ሀል ግዘ ውደፊቱ
ቀርበን የምትናገረው አለና ተናግን እንበል። | 2 171 |
| 9 | አዲሱን አመት አዲሱን ዘመን *2
ያገልግሎት የሰላም የፍቅር ዘመን አድርግልን
ነፍሳት ከያቅጣጫው የሚጎርፉበት
በወንድማማች ፍቅር የምንዋደድበት
ቤተክርስትያን አድጋ እሰይ የምንልበት
ይሁን እየሱሴ አንተ ምትከብርበት
ያገልግሎት...
አዲሱን አመት...
የእያሪኮ ግንብ የሚፈርስበት
ይህ እውነት በአለም ዙሪያ አንድ የሚሆንበት
የሀዋርያት ወንጌል ብቻ ሚሰበክበት
ይሁን እየሱሴ አንተ ምትከብርበት
እሺ ዝቅ እያልን የምንዋደድበት
ወንድሜ ሆይ በርታ አይዞህ የምንልበት
ልብህ ተደስቶ እሰይ የምትልበት
ይሁን የድል አመት አንተ ምትክብርበት
አዲሱን አመት...
በፆምም በፀሎት የምንበረታበት
ሀይልህም ከሰማይ የሚወርድበት
ጥላቻ እርቆ ፍቅር የሚሰፍንበት
ይሁን የድል አመት አንተ ምትነግስበት
@MARANATHAWOCH | 1 828 |
| 10 | የማለዳ ትምህርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል?
ክፍል 12 ለተቀበልነው ነገር አለማመስገን
እግዚአብሔር መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልም የሚገባው አምላክ ነው። ብዙ ጊዜ ሰው ግን ስጠኝ ማለት እንጂ እንካ፥ ተቀበል ማለት ይረሳል። እግዚአብሔር መስጠት እንደሚችል እንዳመንን እንዲሁ መቀበልም እንደሚችል ማመን ወሳኝ ነው።
ከሁሉም ነገር እግዚአብሔር የሚፈልገው ነገር ብኖር ለሰጠው ነገር ሁሉ እንድናመሰግነው ነው። ስላደረገልን ነገር እያመሰገንን እንደገና እንዲያደርግልን ለፈለግነው ነገር መጸለይ አለብን።
በዚህ ምድር ላይ ሰው እንኳ ለተቸገረ ሰው የፈለገውን እርዳታ ሰጥቶ ምላሽ ስያጣ "ይህ ሰው ውለታ ቢስ ነው፤ ምስጋና የለውም " ይላል። እንደገና ተቸግሮ እንዳኝ ስል ለባለፈው ነገር መች አመሰገንከኝና አሁን ሊጨምርልህ የሚል ምላሽ ይሰጣል። በዛውም ልክ ከእግዚአብሔር ለተቀበልነው ነገር ሳናመሰገንን ለመቀበል ብቻ መቸኮል ለጸሎታችን መልስ አያስገኝም።
እኛ አናውቅም እንጅ ያልተሰጠን ነገር ምን አለ? እኛ በእጃችን የሚታይ ንብረትና ገንዘብ አይተን ለማመስገን እንፈልጋለን። ነገር ግን ከገንዘብ የበለጠ ሀብታችን እንዳለን እንረሳለን። ዋና ሀብታችን መዳናችን፣ ሠላማችንና ጤናችን ብቻ ለማመስገን በቂ ምክንያት ነው።
በሰውነታችን ውስጥ ያለውን እያንዳንዱን የሰውነት ክፍላችን ወደ ብር ብንቀይር ስንት ይሆን ነበረ? ለምሳሌ የአንድ ጥርስ ዋጋ ስንት ብር ነው? በ32 አባዙ። የአንዱ ኩላልታችን ዋጋ ስንት ነው? በ2 አባዙ። የአንድ አይናችን ዋጋ ስንት ነው? በ2 አባዙ፤...... የሁሉንም ሰውነታችን አካል ክፍል ወደ ብር ቀይሩ እስቲ። ይህ ሁሉ በሠላም በጤና ተጠብቆ የሚኖር ነገር ግን ለእኛ የማይታይ ሀብታችን ነው።
እኛ ጧት ተነስተን እጃችንና ፊታችን ሊንታጠብ እንሮጣለን፤ ሌላው ግን በየጧቱ ኩላሊቱን ሊታጠብ የሚሮጥ አለ። ከእኛ ውስጥ ብያንስ አንድ ሰውነቱ ክፍል ታምሞ መታከም የሚችል ማነው? መጀመሪያ ላለን ሠላም ሳናመሰግን ገንዘብ ከለከለን ብለን እንወቅሳለን። እርሱ ግን መጀመሪያ ባለህ ነገር አመስግን ይለናል።
ሌላው ብቀር መዳናችን ብቻ በብር የሚተመን ነው? ስንት ቢሊየን ያላቸው ሰዎች ይህንን መዳን ሳያገኙ ይሞታሉ? ለእኛ ግን አንድ ብር ለሌለን ሰዎች ይህንን መዳን በነጻ ሰጥቶን በቤቱ አኑሮናል። ይህ ብቻ የሚናመሰገንበት ትልቅ ምክንያት ነው። "እጅ ያለው ወርቅ እንደ መዳብ ይቆጠራል"
እንደሚባለው ነው ምንም ያልመሰለን እንጅ በእጃችን ያለው ነገር በዋጋ የሚተመን አይደለም።
ዘዳግ 28፥47&48 ሁሉን አብዝቶ ስለ ሰጠህ አምላክህን እግዚአብሔርን በፍሥሐና በሐሤት አላመለክህምና በራብና በጥማት በዕራቁትነትም ሁሉንም በማጣት እግዚአብሔር ለሚልክብህ ለጠላቶችህ ትገዛለህ፤ እስኪያጠፋህም ድረስ በአንገትህ ላይ የብረት ቀንበር ይጭናል።
እስራኤል ለሠራላቸው ተአምራት የማያመሰገኑ ናቸው፥ ነገር ግን ለሚሰጣቸው ነገር ብቻ የሚለምኑ፤ይህ ነገር መጨረሻቸውን አላሳመረላቸውም። ውለታውን ፈጥነውም እየረሱ ስያስቸግሩ የለመኑትንም ሁሉ ሰጣቸው፤ ለነፍሳቸው ግን ክሳትን ላከ ይላል።
መዝ 106፥13-15 "ፈጥነውም ሥራውን ረሱ፥ በምክሩም አልታገሡም። በምድረ በዳም ምኞትን ተመኙ፥ በበረሃም እግዚአብሔርን ተፈታተኑት። የለመኑትንም ሰጣቸው፤ ለነፍሳቸው ግን ክሳትን ላከ።"
እግዚአብሔር የለመንነውን ቶሎ ብመለስልን እንኳ የሰጠን በረከት ለነፍሳችን የማይጠቅም ከሆነ ምን ዋጋ አለን? ለእስራኤል ይህንን የነፍስ ክሳት ያመጣው ውለታውን መርሳት ነው እንጂ አለማመን አይደለም። ሥጋችንን አወፍሮ ነፍሳችንን የሚያከሳ በረከት አሁንም ቤታችን አይግባ።
ስንጸልይ ይህንን የሰጠሄን አንተ ነህና ተመስገን እያልን ምስጋና እየሰጠን አሁንም የቀረውን አንተ ታውቃለህ እንድንል ይፈልጋል እንጂ ለኔ፣ ለኔ፣ ለኔ ብቻ የሚል ጸሎት አይሰማም።
በቆላስ 4፥12 "ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ"ይላል። ጸሎት ከምስጋና ጋር ነው እንጂ በእምባና በለቅሶ ጋር ብቻ አይደለም። እንኳን ለተሰጠን ነገርና ላልተሰጠን ነገርም የሚናመሰግን አምላክ ነው። ሰጥቶም ነስቶም እርሱ አምላክ ነውና።
ኢዮብ ይህ ሁሉ ፈተና ደርሶለት እያለ አንድም ቀን እግዘብሔርን አልበደለም። ይልቅ እግዚአብሔር ሰጠ፤ እግዚአብሔር ነሳ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን"አለ እንጂ። እኛ ዛሬ እንኳን ልጆቻችንና እንስሳቶቻችን ማለቅ ይቅርና 1000 ብር ከክሳችን ወጥቶ ብጠፋ እግዚአብሔር አላወቀኝም፤ እግዚአብሔር እኔን ይጠላል እያልን እስከ ስድብ እንደርሳለን። ልጁ ሞቶበት ማነው እግዚአብሔር ይመስገን የሚል?
እንዲህም አለ። ራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን ወጥቻለሁ፥ ራቁቴንም ወደዚያ እመለሳለሁ፤ እግዚአብሔር ሰጠ፥ እግዚአብሔርም ነሣ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን። ፤ በዚህ ሁሉ ኢዮብ አልበደለም፥ ለእግዚአብሔርም ስንፍናን አልሰጠም።
በእኛ ዘመን እንኳን ትንሽ የታገሰ ሰው ነው የሚንለው ሰው እግዚአብሔር ሰጠ፤እግዚአብሔር ነሳ የሚል ሰው ብኖር ነው። የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን የሚልማ ተፈልጎም አይገኝም። ስለዚህ ለተቀበልነው ነገር አለማመስገን ለሚንቀበለው ነገር መንገድ አይሰጥምና እንጠነቀቅ። መቀበል ብቻ ሳይሆን መስጠትንም እንልመድ።
ፊልጵ 4፥6 ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።
ይቀጥላል.....
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
INBOX @Thaddyapostolic
GROUP @Marantawoch | 1 998 |
| 11 | Adama ACOE
ደቡብ አጥቢያ
New apostolic song
Singer: fechatu
Title: ባንተ ተሻግሬ
ባንተ ተሻግሬ
ባንተ ሁሉን አልፌ
ባንተ ይሄው ቆሜ
ባንተ ዛሬን አይቼ
ላንተ አቀርባለሁ ምስጋናዬን
ላንተ አቀርባለሁ እልልታዬን
ላንተ አቀርባለሁ የድል መዝሙር
ላንተ አቀርባለሁ ይሄው የሱስ
ይሄው/*2 የሱስ/*4
1/ረዳቴ አንተው ነህ እኔን የረዳሄኝ
አቅሜ ሆነኸኝ የሱስ ያሻገርከኝ
ምን ብልህ ይሻላል ምንስ ይመጥናል
ምስጋና አምልኮ ይሄው አፌ ሞልቷል ላንተ
ይሁን ምስጋናዬ
ይሁን አምልኮዬ
ይሁን ለስምህ
ይሁን ክብር ላንተ
ሁሉን ለምትችል
ሁሉን ላደረከው
ኤልሻዳይ ለሆንከው
2/አቀበት ቁልቁለት ስወጣ ተራራውን
በእሳት በሀሩር ውስጥ የነበርክ ከኔጋር
(በሀሩሩ መሀል የነበርክ ከኔጋር)
አይኖቼን አንስቼ አንተን ስመለከት
ነይ ልጄ ብለኸኝ ይዘህ ያራመድከኝ
ረዳቴ ከወዴት ይምጣልኝ
አይኖቼን አንስቼ እየጠበኩ
እኔን የሚረዳኝ የሚያግዝ
ባልኩኝ ስዓት ደረስክ እየሱስ
ረዳኸኝ/*2
አገዝከኝ/*2
ይሄው ለክብር አቆምከኝ
3/ሁሉን የምትችል ክንደ ብርቱ አምላክ
ጉልበት ስልጣን ያለህ በእውነት ምትታመን
የማትለዋወጥ በዘመናት መሀል
ተመስገን እየሱስ ክብር ይገባሀል
እልል/*4
ለስምህ ክብር ይሁንልህ
ኤልሻዳዩ አምላክ እየሱስ
ውዳሴ አምልኮ ይቅረብልህ | 2 159 |
| 12 | የዛሬው ጥያቄና መልስ በጣም ጥሩ ተወዳዳሪዎች የተገኙበት ውድድር ነው። ይሁን እንጅ አብዘኞቹ AI ,App በመጠቀም ነው የሠሩት። ስለዚህ ለወደፊት ጥንቃቄ አድርጉ ማለት እወዳለሁ።
ካልሆነ ይህንን ፕሮግራም አቆማለሁ።
የሁሉንም ውጤት ለማጣራት ሞክረያለሁ ከእነዚህ ውስጥ ያለ AI ከሠሩት ውስጥ
1, እህት Tina 10/10
አብዘኞቹ ግን 9/10 ናቸው። ስለዚህ የፈለገችውን PDF የሚትሸለመው እህት Tina ነች ማለት ነው
በዚህ ከቀጠላችሁ የጥያቀና መልስ ፕሮግራም ይቆማል። ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ምን ያህል እየተከታተልኩ ነኝ የሚለውን ማሳያ ነው እንጅ ከክፍል ወደ ክፍል ማለፊያ አይደለም። app መስራት የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀት መለክያ አይደለም። | 1 888 |
| 13 | አሁን መልስ ተለቋል አቁሙ | 437 |
| 14 | መልስ
1, ጓጉንቸሮች። ዘፀዓት 8፥13 እግዚአብሔርም ሙሴ እንዳለ አደረገ፤ ጓጕንቸሮቹም ከቤት ከወጀድም ከሜዳም ሞቱ።
14 እንደ ክምርም አድርገው ሰበሰቡአቸው፤ ምድርም ገማች።
2, 7 ቀን። ዘፀዓት 7፥25 እግዚአብሔርም ወንዙን ከመታ በኋላ ሰባት ቀን ተፈጸመ።
3, 12 ወራት ነው። አሥር 2፥12 የመንጻታቸውም ወራት ስድስት ወር ያህል በከርቤ ዘይት፥ ስድስት ወርም በጣፋጭ ሽቱና በልዩ ልዩም በሚያነጻ ነገር ይፈጸም ነበርና እንደ ሴቶች ወግ አሥራ ሁለት ወር እንዲሁ ከተደረገላት በኋላ ወደ ንጉሡ ወደ አርጤክስስ ለመግባት የአንዳንዲቱ ቆንጆ ተራ በደረሰ ጊዜ፥......
4, ሄጌ ይባላል። አስተር 2፥3 ሴቶችን ከሚጠብቅ ከንጉሡ ጃንደረባ ከሄጌ እጅ በታች እንዲያደርጓቸው መልከ መልካሞቹን ደናግል ሁሉ ወደ ሱሳ ግንብ ወደ ሴቶች ቤት ይሰበስቡአቸው ዘንድ ንጉሡ በመንግሥቱ አገሮች ሁሉ ሹማምቶችን ያኑር፤ ቅባትና የሚያስፈልጋቸውም ይሰጣቸው፤
5, የሙሴ ሦስት ሲፓራም። 25 ሲፓራም ሚስቱ ባልጩት ወሰደች፥ የልጅዋንም ሸለፈት ገረዘች፥ ወደ እግሩም ጣለችው፡— አንተ ለእኔ የደም ሙሽራ ነህ አለች።
6, የሞከብ ንጉሥ ዔግሎም።
መጻፍ 3፥17 ለሞዓብም ንጉሥ ለዔግሎም ግብሩን አቀረበ፤ ዔግሎምም እጅግ ወፍራም ሰው ነበረ።
7, ሐ ሠለሞን
2ዜና 9፥17 እና 1ነግ 10፥18ንጉሡም ደግሞ ከዘሆን ጥርስ ታላቅ ዙፋን አሠራ፥ በጥሩ ወርቅም ለበጠው።
8, ሐ ዕዝራ። ዕዝራ 7፥6 የእስራኤልም አምላክ እግዚአብሔር በሰጠው በሙሴ ሕግ ፈጣን ጸሐፊ ነበረ፤ የአምላኩም የእግዚአብሔር እጅ በእርሱ ላይ ነበረችና ንጉሡ የሻውን ሁሉ ሰጠው።
9, ለ
10, ሀ
ለ9&10 የራዕይ ትርጉም መጽሐፍ አምብቡ
@MARANATHAWOCH
አስተያየት @Thaddyapostolic ላይ ጻፉ | 1 915 |
| 15 | +10 ደቂቃ | 323 |
| 16 | ጥያቄና መልስ
መልስ @Thaddyapostolic ላይ ብቻ inbox አድርጉልኝ አደራ።
#ማሳሰቢያ፦ ከ1-6 ላለው ጥያቄ ከነ ቃሉ ጥቅስ ማስረጃ ጋር መልሱ። ካልሆነ መልሱ ትክክል ብሆንም ግማሽ ይሰጣል።
የተሰጠ ሰአት 30 ደቂቃ ነው
1, የግብፅ ምድር ሙሉ የገማው መች ነው ማለትም የትኛው መቅሰፍት በወረደ ጊዜ ነው?
2, በፈርኦን ልብ ደንዳናነት ምክንያት በግብፅ ምድር ውሀ ወደ ደም ተለውጦ ስንት ቀን ቆየ?
3, በንጉሡ አርጠክስስ ዘመን የነበሩ ሴቶች ወደ ንጉሡ ለመቅረብ እራሳቸውን እያስዋቡ በተመረጠ ቤት ውስጥ ምን ያህል ቆዩ?
4, ለንጉሡ አርጠክስስ የሚሆኑ ሴቶች መርጦ ቅባትና የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ እየሰጣቸው ሴቶችን የሚያይዋብ የንጉሡ ጀንደረባ ማነው?
5, በመጽሐፍ ቅዱስ ታርክ ውስጥ የራሷን ልጅ በባልጩት የገረዘች ሴት ማን ነች?
6, ከሞአብ ህዝብ ሁሉ እጅግ ወፍራም ሰው ማን ነበረ?
7, ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ታላቅ ዙፋን የነበረው ንጉሥ ማነው?
ሀ ዳዊት ለ ናቡከድናፆር ሐ ሰለሞን መ ሙሴ
8, የአምላኩ የእግዚአብሔር እጅ ከእርሱ ጋር ነበረች የተባለለት ፈጣን ፀሐይ ማን ይባላል?
ሀ ያቤጽ ለ አሳፍ ሐ ዕዝራ መ ኤርምያስ
9, ከሰባቱም አብያተ ቤተክርስቲያናት ውስጥ የአመንዝራ ቤተክርስቲያን ምሳሌ የሆነች ቤተክርስቲያን የትኛው ነች?
ሀ ሰርደስ ለ ቲያጥሮን ሐ ጰርጋመን መ ሎዶቂያ
10, "የጥንቱ ሀይማኖት ሰጠን" ተብሎ የተዘመረው በየትኛው ቤተክርስቲያን ዘመን ነው?
ሀ ፍላደልፍያ ለ ኤፈሶን ሐ ሰርደስ መ ሎዶቂያ
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
መልስ @Thaddyapostolic ላይ ብቻ መልሱልኝ | 1 821 |
| 17 | ማሳሰብያ፦ ሐሙስ የጥያቄና መልስ ምሽት
ውድ የማራናታ ተለግራም ቻናል ቤተሰብ እንደምን ቆያችሁ?
ዛሬ ማታ ማለትም ሐሙስ ምሽት ልክ 2: 00 ላይ የጥያቄና መልስ ውድድር ይኖረናል። በጊዜ ገብታችሁ እንድትሳተፉ አሳስባችኋለሁ። አንደኛ ለወጣ ተወዳዳሪ ከታች ከተዘረዘሩት pdf የፈለገውን pdf እንሸልማለን።
pdf
1, የዘፍጥረት እንቁዎች ብሾፕ ዳዊት ጦሼ
2 ገንዘብና መንፈሳዊ ህይወት ብሾፕ አንዱአለም
3 የመዳን እውቀት መፅሐፍ ብ/ ደጉ
4 በሥርአት ታነፁ ብሾፕ ተ/ማሪያም
5 የራዕይ ትርጉም pdf ብሾፕ ደጉ
6, የእውነት ወንጌል ጥሪ ፓስተር በረከት
7 ኢየሱስን ማን ይሉታል ብሾፕ ተ/ማርያም
8 ቃሉ ይናገር ብሾፕ ተ/ማርያም
10 የሥላሴ አጠያያቂ ምስጥር ቄስ ኤልያስ ሸባባው
11 የንስር መንገድ
12 መፅሐፍ ቅዱስ ትምህርት ለጀማሪዎች ብሾፕ ተክሌ
13 ህይወት የሚገኝበት ትምህርት ብሾፕ ደጉ
14 ወደ መዳን የሚያደርስ እውነት ብሾፕ ደጉ
15 መንፈሳዊ ወጣት
16 እውነት እና ምህረት
17 እምነት በእግዚአብሔር ቃል
18 የመዳናችን ምስጥር
19 የመልዕክቶች አጠቃላይ ትምህርት ብሾፕ ተክሌ
20 Eschatology Final destiny of humanity ብሾፕ ጌታሁን
21 የአንድ አምላክ ልጆች ይለይ
22 መሠረታዊ የክርስትና ትምህርቶች
.
.
.
ከእነዚህና ሌሎችንም መርጦ #አንዱን ይወስዳል። ለጓደኞቻችሁ ሼር አድርጉ።
ልብ በሉ ! መልስ @Thaddyapostolic ላይ ብቻ ይመለሳል
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH | 1 481 |
| 18 | ዛሬም_አለ_የጎፋ_ቢ_መዘምራን_Apostolic_Church_of_Ethiopia360p.mp3 | 2 093 |
| 19 | ''የአምላክ ምህረት እንዳልተለየን የኔ፣ የእናንተ፣ የሁላችን በህይወት መኖር አንዱ ማሳያ ነው።''
✍ እኛ ሰዎች ደካሞች ፥ ሀጢያተኞች፥ ክፉ አሳቢዎች፥ ትቢያዎች። ግን በምህረቱ ኗሪዎች ። የተሸከምነው ስጋ፥ ያጌጥንባቸው አልባሳቶች፥ ያደረግነው ጫማ፥ የአለም መልክ ሁለንተናችንን ይዞ ፈጣሪን አስረስቶናል። ልባችን በአለም ምኞት ታውሮ፥ የልብ አይናችን ጠፍቷል። ማሰቢያችንን ተነጥቀናል። ልባችን ከማስተዋል ርቋል። “ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?” የሚለውን ቅዱስ ቃል ተላልፈን ከነፍሳችን ይልቅ ገደብ ለታጣው ለሥጋችን አምሮት ብለን እልፍ ሀጢያት ውስጥ ተዘፍቀናል። ያለምንም ድካም፥ ያለምንም ክፍያ ሰማያዊ ዜጋ የመሆን ምርጫ በእጃችን ሳለ በገዛ ፈቃዳችን፥ ከዲያብሎስ መንደር ገሃነም ለመግባት እንሽቀዳደማለን። እውነቱን መረዳት መልካም ነው። የብርሃንን ጥቅም ለመረዳት የጨለማን ጎጅነት ማወቅ አለብን። ያኔ ለብርሃን ዋጋ መስጠት እንጀምራለን።
✍ እኛ አላዋቂዎች፥ ስጋ ለባሾች ስሜታችን ገፍቶን ከፈጣሪ አጣልቶናል። ግን አምላክ መሀሪ ነውና ይኸው አለን። ለሰጠን ነገር ሳናመሰግነው፥ የጎደለን እየጠየቅን እናማርራለን። ችግሩኮ መለመኑ አይደለም። እስቲ ስለተቀበልነው እናመስግነው! ተመስገን ማለት ይልመደን።
እኛ ጥዋት ተነስተን ፊታችንን ስንታጠብ፥ ሌላው ጥዋት ተነስቶ ኩላሊቱን 'ሚታጠብ አለና ተመስገን እንበለው። ምስጋናን ልማድ እናድርገው።
✍ እንዳለመታደል ሆኖ እኛ ሰዎች ካልተጎዳን አንማርም፥ ካልተቀጣን አናስተውልም፥ ካላመመን ጤነኛ የሆንን ይመስለናል። የአምላክ ምህረት እንዳልተለየን የኔ፣ ያንተ፣ ያንቺ በህይወት መኖር አንዱ ማሳያ ነው። በሃጢአታችን ልክ ሳይቀጣን፥ በህይወት ያቆየን ፅድቃችን በዝቶ ሳይሆን ምህረቱ ጋርዶን ነው። ይኸው ዛሬም አለን በምህረቱ። እርግጥ ነው በእግዚአብሔር ምህረት ነው እስካሁኗ ደቂቃ በህይወት የቆየነው ግን እስከመቼ ነው ምህረቱን ተማምነን የሀጢያታችንን ጉድፍ በንሰሃ ውሃ እያነጻን የምንኖረው? ማስተዋልን ይስጠን!
✍ ጊዜአችንን፣ ገንዘባችንን፣ ጉልበታችንን ሰውተን በገዛ ፈቃዳችን ከጥፋት ሳንወዳጅ የምህረት እጁን እንዲልክልን፥ የልብ አይናችንን እንዲያበራልን ልዑል ወደሆነው እግዚአብሔር በተሰበረ ልብ ፀሎት እንቅረብ! አምላክ መሀሪ ነውና! ልብ እንበል ዛሬ መኖራችን ምህረቱን አብዝቶ ዕድሜ ስለጨመረልን ነው። አለን በምህረቱ!!!!!
የምህረት ጌታ ይመስገን!
ምህረቱ አይለየን! አሜን!!!
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH | 1 863 |
| 20 | የማለዳ ትምህርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል?
11, የጸሎታችን ክብደት በማነስ
ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት ተመዝኖ የሚታይ ምዛናዊ ንግግር ነው። በዚህ ምድር ላይ በመንገድ ዳር ተቀምጦ የሚለምን ለማኝ እንኳን የሰውን ቀልብ ለመሳብና ሰው እንድራራለት ብሎ እስክደክም ድረስ አቅሙ የሚፈቅደውን ሁሉ አድርጎ ይለምናል። ነገር ግን በመንገድ ላይ ስለተቀመጠ፣ ለማኝ ነው ስለተባለ ብቻ ሰዎች አይራሩለትም። የሚናገረው ንግግር፣ የሚያወጣው ቃላቶች የሰዎችን ሆድና አንጀት የሚበላና የሚላወስ መሆን አለበት፤ ሰዎች አጥብቆ ለለመነ ሰው ነው የሚሰጡት።
ለመለመን እውነተኛ ድሃ መሆን ያስፈልጋል። አንዳንድ ለማኞች በመንገድ ላይ ስቀመጡ ለመዝናኛ የተቀመጠ ሰው የሚመስሉም አሉ። ለመለመን ወጥቷሉ ግን የመለመን ዘዴ አላወቁም። አንድ ብርም ሳይወስዱ ማታ ጨርቃቸውን ሰብስበው ወደ ቤት ይመለሳሉ፤ ሌሎች ግን የሰውን አንጀት በቃላቶቻቸው በልተው ብዙ ብር ሰብስበው ይገባሉ። ይህ የልዩነታቸው ምስጥር የቃላቶች ክብደትና ቅለት ላይ የተፈጠረ ነው።
በዛውም ልክ እግዚአብሔር የሚያየው አጥብቆ የሚጸልየው ሰው ብቻ ነው። አንዳንድ ሰው በልቡ ሌላ ነገር እያሰበ የአጠገቡ ሰው ሰለተምበረከከ ብቻ ተምበርክኮ ለመንኩ ብሎ መልስ ይጠብቃል። ጸሎቱ ከልቡ የመነጨ ስላልሆነ መልሱን አያገኝም።
በእርግጥ የአንድ ሰው የነገሩ ክብደት ሰውዬ እንዳደረገው ይሆናል። ይህ ማለት ለነገሩ ክብደት ሳይሰጥ ቀለል አድርጎ ካዬ ለእሱ ቀላል ነው፤ ከባድ ነው ብሎ value ሰጥቶ ካሰበ ይከብዳል፤ በክብደቱ ልክም ይጸልያል።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ቦታ እግዚአብሔር ለጸሎታቸው መልስ የሰጣቸው ሰዎች ስንመለከት በጸሎታቸው ጀርባ "አጥብቀው ጸለዩ፣ አጥብቀው ለመኑ፣አብዝተው ጮኹ፣እምባቸውን አፈሰሱ፣... የሚሉ ቃላቶችን እናገኘዋለን። የዛን ቦታ ደግሞ ጸሎታቸውን ሰማ፣ መለሰላቸው፣ ፈወሳቸው... የሚሉ ቃላቶች አሉ። የጸሎት መልስ ያለው አጥብቆ በመጸለይ ላይ ነው እንጂ በምኞትና እንደ ተራ ነገር አድርገን ከፈለክ ስጠኝ ካልፈለክ ተውው እነደሚባል አይነት ጸሎት በመጸለይ አይደለም።
ስፈልግ መጸለይ ካልፈለገ መተው፣ ቀጠሮ እየሰጠ እንደ dim-light ብርሃን ቦግ-ጥርቅም ማለት የጸሎት ባህርይ አይደለም።
ያዕ 5፥17-18 የኤልያስ ጸሎት እንመልከት
ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች።
መልስ ያለው በማጣበቅ ላይ ነው እንጂ ፈዛዛ ጸሎት ጸልየህ ኢየሱስን ጥፋተኛ አታደርግ።
የሃናም በጸሎት እንመልከት፦ ሃና በየአመቱ ሊትጸልይ ወደ ኢየሩሳሌም ትወጣ ነበረች። ነገር ግን ነገሩ ስከብድባትና ስጨንቃት በመጨረሻ ላይ አጥብቃ ጸለየች። የተጠቀመችው ቃላቶችም የሚገርሙና የእግዚአብሔርን ልብ የሚነኩ ናቸው።
1ሳሙ 1፥10-11እርስዋም በልብዋ ትመረር ነበር፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸለየች፥ ጽኑ ልቅሶም አለቀሰች።
እርስዋም። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ የባሪያህን መዋረድ ተመልክተህ ብታስበኝ፥ እኔንም ባትረሳ፥ ለባሪያህም ወንድ ልጅ ብትሰጥ፥ ዕድሜውን ሁሉ ለእግዚአብሔር እሰጠዋለሁ፥ ምላጭም በራሱ ላይ አይደርስም ብላ ስእለት ተሳለች። ይህ ንንግሯ ነው የእግዚአብሔርን ሆድ የበላው።
በፊትም እግዚአብሔር ጸሎቷን ያቆየው ወደ እርሱ ስላልደረሰ ሳይሆን ከአንደበቷ የፈለገው ቃላቶችና የጸሎት ክብደት አለ ማለት ነው። ማህጸኗንም አውቆ እንደ ዘጋ በቁ.6 ላይ ይናገራል። የጸሎቷ ቃላቶች በክሎ ተመዝኖ ክብደት ካገኘ በኋላ ነው የመለሰላት። እግዚአብሔር የፈለገውን ደረጃ ደርሰን እስክንጸልይ ድረስ የጸሎታችን መልስ እንደማይመልስ ይህ ጥሩ ማሳያ ነው። ዛሬ ለእኛም የትኛው ቃላት ጠብቆ እንዳቆየን መፈለግ አለብን።
በሉቃ 18፥35 እና ማር 10፥46 ላይ የተጻፈው የጤሜዎስ ልጅ ዕውሩ በርጠሜወስ አብዝቶ ባይጮኽና ሰዎች ዝም በል ስሉት ዝም ብል እፈወስ ነበረ? ምን አስጮኸው? የችጎሩ ክብደት ስለታየውና ይህ ፈዋሹ አምላክ በአጠገበ ወጥቶ ሳያልፍ እድለን ልሞክር ብሎ ነው። ሁለተኛ ይህንን ዕድል አላገኝም ብሎ ሳይፈራ አብዝቶ ጮኾ ተፈወሰ። መጮህ ማለት ኢየሱስ ሳያልፍ አጠገብህ እያለ ነውና ዛሬ ጮሄህ ተፈወስ ወንድሜ።
አብዝቶ መለመንና አብዝቶ መጮህ ለጥያቄ መልስ ይሰጣል። በመሀል gap እየሰጠን የሚንጸለየው ጸሎትና ትዝ ስለን ብቻ ጌታ ሆይ እኔን መቼ ትመለከተኛለህ? ማለት ለጸሎታችን መልስ ያዘገያል፤ እንጠነቀቅ።
ሉቃ 18፥1-8 ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥ እንዲህ ሲል። በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ።
በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች። ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለው ነበር።
አያሌ ቀንም አልወደደም፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ። ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር፥
ይህች መበለት ስለምታደክመኝ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ አለ። ጌታም አለ። ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ።
እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? እላችኋለሁ፥ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?
ወንድሞችና እህቶች በእግዚአብሔር ፊት መጸለያችን ካልቀረ ሚዛኑን የሚያነሳ ጸሎት እንጸልይ እንጂ ክብደት የሌለውን ጸልየን እግዚአብሔርን አንወቅስ። አንዳንድ ሰው ተቸግሮ አንድ ማታ ከጸለየ 2ኛው ቀን እግዚአብሔር ረሳኝ ጸሎተን አይመልስም ብሎ ለውቀሳ ይቸኩላል። እንኳን ኢየሱስ አንተን ሊረሳና የራስህን ጸጉር ቁጥር ያውቃል።
መጀመሪያ ጸሎትህን አስተካክል፤ እረሱ እንደሚፈልግህ ሆነህ ቅረብ።
ሐዋ ሥራ 2፥5 ላይ ጴጥሮስ በወህኒ ስታሰር ምዕመናን ወደ ቤተክርስቲያን ገብተው አጥብቀው ጸለዩለት። እጅ እግሩን በሰንሰለት የታሰረውን ጸሎት ብቻ ፈታች። እስክ አንተ/ች አጥብቀህ/ሺ ጸልይ/ዪ ጸሎት እንደማይፈታ ታያለህና/ሺና።
ነገር ግን አጥብቀህ/ሺ ሳትጸልይ/ዪ እግዚአብሔርን አትወቅስ/ሺ።
ይቀጥል የሚትሉ ወንድሞችና እህቶች በግሩፕ ላይ ብያንስ 10 ሰው add አድርጉ።
ይቀጥላል......
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
INBOX @Thaddyapostolic
GROUP @Marantawoch | 2 164 |
