en
Feedback
Ethio Fm 107.8

Ethio Fm 107.8

Open in Telegram

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Ethio Fm 107.8

Channel Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 18 534 subscribers, ranking 12 141 in the News & Media category and 1 817 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 18 534 subscribers.

According to the latest data from 05 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -92 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 8.93%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.82% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 655 views. Within the first day, a publication typically gains 1 264 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 4.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

18 534
Subscribers
-124 hours
-37 days
-9230 days
Posts Archive
ጥቃት የደረሰባቸው ዜጎች ጉዳይ ግድ ይለናል- ዶ/ር አበራ አደባ የአጋር ኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አጋር ኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ማህበር ላለፉት 21 ዓመታት በተለይም ከስደት ተመላሽ ለሆኑ እና ጥቃት ለደረሰባቸው ዜጎች ከስነ ልቦና ድጋፍ አንስቶ፣ የመጠለያ፣ የስልጠና እና ወደ መደበኛ ህይወታቸው እንዲመለሱ የማቋቋሚያ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዛሬው ዕለት ደግሞ በአማራ ክልል  ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች እና ሕፃናት ላይ የሚያከናውነውን ተግባር ስራውን በተጠናከረ ሁኔታ የሚያከናውንበትን ስምምነት ተፈራሯሟል፡፡ ከዚህ ቀደም ከ 8 ዓመታት በላይ አገልግሎቱን በኪራይ መጠለያ ሲሰጥ የቆየው አጋር ኢትዮጵያ ዛሬ የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመተባባር ባስገነቡት ህንፃ አገልግሎት ለመስጠት ኃላፊነቱን ተረክቧል፡፡ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ወደ መደበኛ ሕይወታቸው እንዲመለሱና በሙያ ሰልጥነው ከራሳቸው አልፈው ቤተሰቦቻቸውን ጭምር እንዲያግዙ የሚስችል ስልጠናና ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን የአጋር ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር አበራ አደባ ተናግረዋል፡፡ አጋር ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል በሚገኙ ማዕከላቱ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ በማንሳትም ከችግሩ አሳሳቢነት አኳያ ስራውን ለማስፋት የተለያዩ ጅምሮች መኖራቸውንም አሳውቀዋል፡፡ ዶ/ር አበራ አደባ የአማራ ክልል መንግስት በተለይም የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ለድርጅቱ ላሳየው እምነትና ለሰጠው ትልቅ ሰብአዊ ኃላፊነት ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ የተጣለባቸውን ታላቅ አደራ በአግባቡ ለመወጣት ማኅበሩ በሙሉ አቅሙና በትጋት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

photo content
+4

ጎልደን ስፖርት በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ ፖርቹጋል ከስፔን የሚያደርጉትን የአለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ የሚያስተላለፍ ይሆናል፡፡
ጎልደን ስፖርት በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ ፖርቹጋል ከስፔን የሚያደርጉትን የአለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ የሚያስተላለፍ ይሆናል፡፡

በሱዳን ባለፉት ስድስት ወራት ከ3መቶ በላይ ህፃናት በድሮን ጥቃትና በጦርነት ሰለባ መሆናቸው ተገለጸ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ደም አፋሳሽ ጦርነት ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከ3መቶ በላይ ህፃናት መ
+1
በሱዳን ባለፉት ስድስት ወራት ከ3መቶ በላይ ህፃናት በድሮን ጥቃትና በጦርነት ሰለባ መሆናቸው ተገለጸ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ደም አፋሳሽ ጦርነት ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከ3መቶ በላይ ህፃናት መገደላቸውንና ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን የተባበሩት መንግስታት የህፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) አስታወቀ። እንደ ዩኒሴፍ መግለጫ ከሆነ፤ ለእነዚህ ህፃናት ሞትና መቁሰል በዋነኝነት እንደ ምክንያት የተጠቀሰው እየተበራከተ የመጣው የድሮን ጥቃት ነው። ከሚያዚያ 2023 ጀምሮ በሱዳን መደበኛ ጦር እና በፈጥኖ ደራሹ ኃይሎች መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት አሁንም እልባት ሳያገኝ ቀጥሏል። በዚህ ግጭት ውስጥ ህፃናት ዋነኛ ሰለባ እየሆኑ መሆናቸውን የገለጸው ድርጅቱ፤ በተለይም ባለፉት ስድስት ወራት የታየው የህፃናት ሰለባ ቁጥር እጅግ አሳሳቢ መሆኑን አመልክቷል። ግጭቱ በጀመረበት ወቅት የተፈጠረው አለመረጋጋት ወደ ሰብዓዊ ቀውስ ማምራቱንና በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ህፃናትን ለከፋ አደጋ ማጋለጡ ይታወቃል። ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች ጦርነቱን እንዲያቆሙና ለሲቪሎች ጥበቃ እንዲያደርጉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተደጋጋሚ ጥሪ እያቀረቡ ቢሆንም፣ ሱዳን ግን አሁንም በጦርነት ማጥ ውስጥ ትገኛለች ሲል የዘገበው የአል- አረቢያ ነዉ፡፡ ልዑል ወልዴ ሰኔ 29/2018

photo content

በሱዳን ባለፉት ስድስት ወራት ከ3መቶ በላይ ህፃናት በድሮን ጥቃትና በጦርነት ሰለባ መሆናቸው ተገለጸ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ደም አፋሳሽ ጦርነት ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከ3መቶ በላይ ህፃናት መ
+1
በሱዳን ባለፉት ስድስት ወራት ከ3መቶ በላይ ህፃናት በድሮን ጥቃትና በጦርነት ሰለባ መሆናቸው ተገለጸ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ደም አፋሳሽ ጦርነት ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከ3መቶ በላይ ህፃናት መገደላቸውንና ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን የተባበሩት መንግስታት የህፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) አስታወቀ። እንደ ዩኒሴፍ መግለጫ ከሆነ፤ ለእነዚህ ህፃናት ሞትና መቁሰል በዋነኝነት እንደ ምክንያት የተጠቀሰው እየተበራከተ የመጣው የድሮን ጥቃት ነው። ከሚያዚያ 2023 ጀምሮ በሱዳን መደበኛ ጦር እና በፈጥኖ ደራሹ ኃይሎች መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት አሁንም እልባት ሳያገኝ ቀጥሏል። በዚህ ግጭት ውስጥ ህፃናት ዋነኛ ሰለባ እየሆኑ መሆናቸውን የገለጸው ድርጅቱ፤ በተለይም ባለፉት ስድስት ወራት የታየው የህፃናት ሰለባ ቁጥር እጅግ አሳሳቢ መሆኑን አመልክቷል። ግጭቱ በጀመረበት ወቅት የተፈጠረው አለመረጋጋት ወደ ሰብዓዊ ቀውስ ማምራቱንና በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ህፃናትን ለከፋ አደጋ ማጋለጡ ይታወቃል። ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች ጦርነቱን እንዲያቆሙና ለሲቪሎች ጥበቃ እንዲያደርጉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተደጋጋሚ ጥሪ እያቀረቡ ቢሆንም፣ ሱዳን ግን አሁንም በጦርነት ማጥ ውስጥ ትገኛለች ሲል የዘገበው የአል- አረቢያ ነዉ፡፡ ልዑል ወልዴ ሰኔ 29/2018

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ በፓርላማ ይቀርባሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ በፓርላማ ይቀርባሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባሉ፡፡ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው 30ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በምክር ቤቱ ተገኝተው የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት ዓመታዊ በጀት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ በተያያዘም ምክር ቤቱ ፣ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ የበጀት አዋጁን እንደሚያፀደቅ ይጠበቃል፡፡ የጉባኤው ሙሉ ሂደትም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡ ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

በአንድ ሳምንት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ሩሲያ በኬዬቭ ላይ በፈጸመችው ጥቃት ቢያንስ 11 ሰዎች ተገደሉ የኪየቭ የድንገተኛ አደጋ አገልግሎት ዛሬ ማለዳ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ በሕይወት የተረፉ ሰዎችን በቦምብ ከተመቱ ሕንፃዎች እያወጣ ነበር አምስት ህጻናትን ጨምሮ 46 ሰዎች መቁሰላቸውን እና የማዳን ጥረቱ ከ 20 በላይ ቦታዎች መቀጠሉን ቲሙር ትካቼንኮ ገልጿል የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ከፕሬዚዳንት ትራምፕ ጋር ሊነጋገሩ በሚጠበቅበት በቱርክ ናቶ የመሪዎች ጉባኤ ዋዜማ ነው ጥቃቱ የደረሰው የመጨረሻው ጥቃት የተፈጸመው ከሰዓታት በፊት ዜለንስኪ ሞስኮ በኪዬቭ ላይ ሀሙስ እለት 30 ሰዎችን የገደለውን ጥቃት ተከትሎ ለሁለተኛ ጊዜ ሩሲያ ለጥቃት እየተዘጋጀች መሆኑን ካስጠንቀቁ በኋላ ነበር ከንቲባ ቪታሊ ክሊችኮ የሩስያ ባሊስቲክ ሚሳኤሎች በከተማዋ የሚገኙ በርካታ ሕንፃዎችን በመምታታቸው በአንዳንድ አፓርትመንት ቤቶች ውስጥ የእሳት ቃጠሎ መድረሱን መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል ሃሙስ ምሽት ላይ ከድሮን እና ከሚሳኤል ጥቃት በኋላ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች በከተማው ዙሪያ ወደሚገኙ የሜትሮ ጣብያዎች ለቀው ወተዋል ዩክሬን ሞስኮን በጥቃቱ ሆን ብላ በሲቪል አካባቢዎች ላይ ጥቃት አድርሳለች ስትል ከሳለች በቅርቡ ዩክሬን በሩሲያ የሃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ ያደረሰችውን ጥቃት ተከትሎ ሩሲያ የዩክሬንን ወታደራዊ እና የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ኢላማ አድርጌያለሁ ስትል ተናግራለች ሲል ቢቢሲ አክሎ ገልጿል፡፡     ሰላማዊት ዲታ ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

photo content

በአዲስ አበባ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከ97 በመቶ በላይ ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ ክፍል ተሸጋገሩ በ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 97.48 በመቶ የሚሆኑት 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ የፈተና ውጤቱን ይፋ ለማድረግ ለተለያዩ የሚዲያ ተቋማት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፤ በከተማ አስተዳደሩ ፈተናውን ከወሰዱ 84 ሺህ 257 ተማሪዎች መካከል 82 ሺህ 137 የሚሆኑት ውጤታማ መሆን ችለዋል። ይህ የዘንድሮው አፈጻጸም በ2017 ዓ.ም ከነበረው የ95 በመቶ የማለፍ ምጣኔ አንጻር ሲታይ ከፍተኛ እድገት ያሳየ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፤ ውጤቱ እንዲመዘገብ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ መምህራን፣ የትምህርት አመራሮች፣ ባለሙያዎች፣ ወላጆችና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። ዘንድሮ ለተመዘገበው አመርቂ ውጤት የከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ሥራው ልዩ ትኩረት መስጠቱ፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉ እንዲሁም የሂሳብና እንግሊዘኛ ትምህርት ስትራቴጂ ተነድፎ በትኩረት መሠራቱ በዋናነት ተጠቃሽ መሆናቸውን ዶክተር ዘላለም አብራርተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የመማሪያና ማስተማሪያ ግብዓቶች በበቂ ሁኔታ መቅረባቸው እና ከወላጆች ጋር በቅንጅት መሠራት መቻሉ ለስኬቱ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ተገልጿል። በከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ሥርዓቱ የብዝሃ ቋንቋ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ የተማሩ ተማሪዎች በትምህርት ዓይነቶቹ ፈተና መውሰዳቸውን ኃላፊው አስታውሰዋል። የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናን ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከልም 543 ያህሉ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸው በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁሟል። ተፈታኝ ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ የተዘጋጀውን ይፋዊ የኢንተርኔት ሊንክ በመጠቀም ውጤታቸውን መመልከት የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል። ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

photo content

በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል አሉ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር
በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል አሉ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)   የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል   2018 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።   ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እያካሄደ ይገኛል። በግምገማ መድረኩላይ የተገኙት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል።   በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ 10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት በተሰራው ስራ ዕቅዱን መቶ በመቶ ማሳካት መቻሉን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል፡፡   ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ዋና መሥሪያ ቤትና በተጠሪ ተቋማት አማካኝነት በተከናወኑ የተቀናጁ የሪፎርም ሥራዎች፣ የወጪ ምርቶች ጥራትን በማረጋገጥና በተዘረጉ ዘመናዊ አሠራሮች መሆኑን ተናግረዋል።   በበጀት ዓመቱ 3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች የንግድ ፈቃድ፣ ምዝገባና ዕድሳት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ፣ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑት አገልግሎት መስጠት መቻሉን ገልጸዋል።   ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

📢የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት🎯 ነገ እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ 132 ኪ.ቮ ሃይል አስተላላፊ መስመር ሰበታ ወጪ መስመር ላይ የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦                                          ✅ከንጋቱ 12፡00 እስከ ጠዋቱ 2፡00 ድረስ:-   👉በልደታ ክፍለ ከተማ ዙሪያ እና በጭድተራ ፊት ለፊት፣መላው የመርካቶ ዙሪያ፣ ፔፕሲ ፋብሪካ፣ የድሮው አትክልት ተራ፣ ኤሊያና ሆቴል፣ ሰባራ ባቡር፣ አዲስ ከተማ ቴሌ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ኮል ሴንተር እና አካባቢው ፣ 👉በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ዙሪያ፣ ሰንጋተራ፣ ጥቁር አንበሳ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ የደም ባንክ፣ ፋና ሚዲያ፣  ንብ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት እና ጎላ ሚካኤል ሙሉ፣ በህንፃ ኮሌጅ ዙሪያ፣ ኮካ፣ አብነት፣ መድር-ኃይል፣ 👉ጦር ኃይሎች ሆስፒታል እና ቶሎሳ ሰፈር፣ በልደታ ደሴ ሆቴል ዙሪያ፣ መላው ብስራተ ገብርኤል ዙሪያ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት (Commercial Bank of Ethiopia HQ)፣ ፍልውሃ፣ ዘውዲቱ ሆስፒታል፣ 👉ጋንዲ ሆስፒታል፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ አራት ኪሎ (ባሻ ወልዴ፣1080)፣ ቅድስት ማርያም፣ አንድነት ፓርክ፣ መላው የጨርቆስ ዙሪያ፣ ፌደራል ፖሊስ፣ በልደታ ፀበል ዙሪያ፣ በልደታ ኮንዶሚኒየም ዙሪያ እና አካባቢው ፣  👉ኮሜርስ  ኮሌጅ (Commerce)፣ ጥቁር አንበሳ፣ ቴሌ ዳታ ሴንተር፣ አድዋ ዜሮ ዜሮ (Adwa 00)፣ ወዳጅነት ፓርክ እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡ ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን። #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት ሰኔ 27/2018 ዓ.ም

photo content

የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽንና ቴክኖ ኢትዮጵያ የሀገርን ገፅታ በቴክኖሎጂ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ የሀገርን ገፅታ ለመገንባትና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በቴክኖሎጂ የታገዘ የማስተዋወቅ
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽንና ቴክኖ ኢትዮጵያ የሀገርን ገፅታ በቴክኖሎጂ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ የሀገርን ገፅታ ለመገንባትና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በቴክኖሎጂ የታገዘ የማስተዋወቅ ስራ ለመስራት የሚያስችል ስልታዊ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈርሟል ። ስምምነቱ የተፈረመው ቴክኖ ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን እና ከቦርድ ሴል ፎን አዲስ አበባ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው 3ኛው ዙር የፎቶ ኤግዚቢሽን መክፈቻ ላይ ነው። በሕፃናትና ወጣቶች ትያትር ኮምፕሌክስ በይፋ በተከፈተው በዚህ ኤግዚቢሽን ላይ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን እና ቴክኖ ኢትዮጵያ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውል ተፈራርመዋል። ይህም ሁለቱ ተቋማት በቱሪዝም እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ በቅንጅት በመስራት፣ የሀገር ውስጥ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግና ማህበረሰቡ የሀገሩን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ እሴቶች እንዲያውቅ ለማስቻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሏል። በኤግዚቢሽኑ ላይ አዳዲስ የካሜራ እና የሰው ሰራሽ አስተዋፅኦ ወይም AI ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተነሱ ከ100 በላይ ልዩ ልዩ የፎቶግራፍ ስራዎች ለዕይታ ቀርበዋል። ቴክኖሎጂን ለሀገር ገፅታ ግንባታና ለኪነጥበብ እድገት ማዋል ላይ ትኩረት ያደረገው ይህ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ ለሚቀጥሉት 10 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን፤ ከ10 ሺህ በላይ ታዳሚዎች ይጎበኙታል ተብሎ ይጠበቃል። ድርጊቱ በዘርፉ ላሉ ባለሙያዎችና ለቱሪዝም ኢንዱስትሪው አዲስ መነቃቃትን እንደሚፈጥርም ተነግሯል። ልዑል ወልዴ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የ3 ቢሊዮን ዶላር የቡና ወጪ ንግድ ዕቅዷን ማሳካቷን አቶ አዲሱ አረጋ ገለጹ በባለፈው በጀት ዓመት 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተገኘ ሲሆን፤ ይህን ቁጥር ዓመት ባልሞላ
ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የ3 ቢሊዮን ዶላር የቡና ወጪ ንግድ ዕቅዷን ማሳካቷን አቶ አዲሱ አረጋ ገለጹ በባለፈው በጀት ዓመት 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተገኘ ሲሆን፤ ይህን ቁጥር ዓመት ባልሞላ ጊዜ ዉስጥ ማሻሻል መቻሉን ግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው አስታውቀዋል ፡፡ መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የቡናውን ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ሥራዎች መሠራታቸው በተለይም ለቡና ምርት ጥራት ትኩረት መደረጉ ለዕቅዱ ስኬት ድርሻው ከፍተኛ ነው ብለዋል ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ፡፡ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

ዘምዘም ባንክ የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡንና በካፒታል ገበያ ታሪክ ከወለድ ነፃ ቀዳሚ ባንክ መሆኑን አስታወቀ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጠው ዘ
ዘምዘም ባንክ የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡንና በካፒታል ገበያ ታሪክ ከወለድ ነፃ ቀዳሚ ባንክ መሆኑን አስታወቀ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጠው ዘምዘም ባንክ፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ። ባንኩ ይህን የገለፀው፣ 6 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸውን 6 ሚሊዮን ነባርና አዳዲስ አክሲዮኖቹን በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን  አስመዝግቦ ያስፀደቀ የመጀመሪያው ከወለድ ነፃ የፋይናንስ ተቋም መሆኑን ይፋ ባደረገበት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። እንደ ባንኩ መግለጫ፣ የተመዘገበው የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ35 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። በተመሳሳይ የባንኩ ጠቅላላ ገቢ ከ2.2 ቢሊዮን ብር ወደ 3 ቢሊየን ብር በማደግ የ36 በመቶ ጭማሪ ማስመዝገቡ ተጠቅሷል። በተያያዘም የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ መሊካ በድሪ ዘምዘም ባንክ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪክ አክሲዮኖቹን በይፋ አስመዝግቦ ያስፀደቀ ቀዳሚው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ ተቋም በመሆን ታሪክ  ሰርቷል ብለዋል። ባንኩ ከግብይት አማካሪው ወጋገን ኢንቨስትመንት ባንክ ጋር በመሆን በካፒታል ገበያ መመሪያ በተቀመጠው መሠረት ነባርና አዳዲስ አክሲዮኖቹን አስመዝግቧል። ባንኩ የባለአክሲዮኖችን መብት በማስጠበቅና አዳዲስ አክሲዮኖችን ለሕዝብ በማቅረብ፣ አጠቃላይ ካፒታሉን ወደ 15 ቢሊዮን ብር ለማድረስ አቅዶ እየሠራ እንደሚገኝ ተገልጿል። አዲስዓለም አበበ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

በሰሜናዊ ናይጄሪያ ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ ረሃብ መጋለጣቸው ተገለጠ በሰሜናዊ ናይጄሪያ በተከሰተ የጸጥታ ችግር እና በእርዳታ አቅርቦት መቋረጥ ምክንያት ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ የረ
በሰሜናዊ ናይጄሪያ ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ ረሃብ መጋለጣቸው ተገለጠ በሰሜናዊ ናይጄሪያ በተከሰተ የጸጥታ ችግር እና በእርዳታ አቅርቦት መቋረጥ ምክንያት ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ የረሃብ አደጋ መጋለጣቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) አስታወቀ። ተቋሙ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ በአካባቢው ያለው አለመረጋጋት በርካታ ቤተሰቦችን ከቤት ንብረታቸው ከማፈናቀሉም በላይ ገበሬዎች ወደ እርሻቸው እንዳይሰማሩ እንቅፋት ሆኖባቸዋል። ይህም በክልሉ ያለውን የምግብ ዋስትና ችግር ይበልጥ አባብሶታል። በተለይም የቦርኖ ግዛት የችግሩ ዋነኛ ሰለባ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን፣ በዚሁ ግዛት ብቻ ከ3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አጣዳፊ ለሆነ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የዓለም የምግብ ፕሮግራም በአሁኑ ወቅት ሰብአዊ ድጋፍ ለማቅረብ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ቢሆንም፣ የጸጥታው ሁኔታ እርዳታውን ለተቸገሩ ወገኖች ለማድረስ አስቸጋሪ እንዳደረገው ገልጿል። ተቋሙ በክልሉ የጀመረውን የምግብ እና የሥርዓተ-ምግብ ድጋፍ አጠናክሮ ለማስቀጠል በአስቸኳይ 89 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገው ጥሪ አቅርቧል DW Africa እንደዘገበው። ልዑል ወልዴ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ከዛሬ ጀምሮ ለሰባት ቀናት በኢራን እና በኢራቅ ከተሞች እንደሚከናወን ተገለፀ ባለፈው መጋቢት ወር ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የቀብር ሥነ-ሥርዓት በአሜሪካ-እስራኤል እና በኢራን መካከል ባለው ጦርነት ምክንያት እንዲራዘም ተደርጓል። የ86 ዓመቱ አሊ ኻሜኒ ጦርነቱ በፈነዳበት የመጀመሪያ ቀን የካቲት 28 በመኖሪያ ግቢያቸው ላይ በተሰነዘረ የጋራ የአሜሪካ እና የእስራኤል የአየር ጥቃት ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገደላቸው ይታወሳል። ከ1989 ጀምሮ ኢራንን የመሩት ኻሜኒ የአገሪቱን ወታደራዊ መዋቅር የቀረጹ መሪ ነበሩ። ይህ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ከሕዝብ ዕይታ ተሰውረው የቆዩት ልጃቸው እና ተተኪያቸው ሞጅታባ ኻሜኒ ሥልጣን ከያዙ በኋላ የሚከናወን የመጀመሪያው ትልቅ የመንግሥት ሥነ-ሥርዓት ነው። የሰባት ቀናት የቀብር ሥነ-ሥርዓት መርሃ-ግብሩ ከዛሬ ከፈረንጆቹ ሐምሌ 3 ጀምሮ በዋና ከተማው ቴህራን የሚጀምር ሲሆን፥የዓለም መሪዎችና ከፍተኛ ባለሥልጣናት ክብራቸውን ይገልጻሉ። በመቀጠልም በሐምሌ 4 እና 5 የሟቹ አስከሬን ሕዝቡ የመጨረሻ ስንብት እንዲያደርግለት በቴህራኑ ግራንድ ሞሳላ መስጊድ የሚቆይ ሲሆን፥በሐምሌ 6 እና 7 የሽኝት ሰልፉ ወደ ታዋቂው የሺዓ ሃይማኖታዊ ትምህርት ማዕከል ቆም ከተማ ይጓዛል። በመቀጠልም አስከሬኑ ወደ ጎረቤት አገር ኢራቅ በመጓዝ በሐምሌ 8 ቀን በናጃፍ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ይፋዊ አቀባበል ከተደረገለት በኋላ ታሪካዊ በሆኑት ናጃፍ እና ካርባላ ከተሞች የሕዝብ የሽኝት ሰልፍ ይካሄዳል። በመጨረሻም በሐምሌ 9 ቀን አስከሬኑ ወደ ኢራን ተመልሶ በኻሜኒ የትውልድ ስፍራ እና የሺዓ እስልምና እጅግ የተቀደሰ ከተማ በሆነችው መሻድ በሚገኘው የኢማም ሬዛ መቅደስ የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ይፈጸማል ሲል አልጄዚራ ዘግቧል። ሳራ ዮሐንስ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

photo content