en
Feedback
Ethio Fm 107.8

Ethio Fm 107.8

Open in Telegram

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Ethio Fm 107.8

Channel Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 18 590 subscribers, ranking 12 273 in the News & Media category and 1 808 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 18 590 subscribers.

According to the latest data from 14 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -127 over the last 30 days and by -8 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 9.95%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.76% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 851 views. Within the first day, a publication typically gains 1 257 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 5.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 15 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

18 590
Subscribers
-824 hours
-257 days
-12730 days
Posts Archive
የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ-ግብር ዛሬ በይፋ ተጀመረ መርኃ-ግብሩን ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ “በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደ
+4
የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ-ግብር ዛሬ በይፋ ተጀመረ መርኃ-ግብሩን ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ “በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን” ብለዋል። የሀገሪቱ ርዕሰ መስተዳደር ‎ዜጎች ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጭው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራቸውን እንዲያኖሩም ጥሪ አቅረበዋል። ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

እስራኤል በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ስምምነት ቢደረግም ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ በተቆጣጠረቻቸው አካባቢዎች እንደሚቆይ አስታወቀች የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሰላም ስምምነት ቢደረግም የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ፣ በሶሪያ እና በጋዛ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ቆይታውን ይቀጥላል። እስራኤል ‹‹ምንም ዓይነት የአሁኑም ሆነ የወደፊት ጫናዎች ቢኖሩም›› ጦሯን ከሊባኖስ የማስወጣት እቅድ እንደሌላት በሚኒስትሩ መግለጫ ተመላክቷል። ካትዝ አክለውም የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ይህንን አቋም ለአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ለሌሎች ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣናት በግልፅ ማሳወቃቸውን ገልጸዋል። ‹‹እኔም ይህንኑ ጉዳይ ለአሜሪካ የመከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴዝ በግልፅ አሳውቄያለሁ›› ብለዋል ካትዝ። ሚኒስትሩ በሊባኖስ ካለው ሁኔታ ጋር ተያይዞ ቴህራን በእስራኤል ላይ ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ፤ እስራኤል ‹‹ባላት አቅም ሁሉ›› በኢራን ላይ ጥቃት እንደምትሰነዝር አስጠንቅቀዋል። የእስራኤል የብሔራዊ ደህንነት ሚኒስትር ኢታማር ቤን-ጊቪር በበኩላቸው የአሜሪካ-ኢራንን ስምምነት በመንቀፍ ‹‹የትራምፕ ስምምነት ቴል አቪቭን አያስገድዳትም›› ሲሉ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እሁድ እለት ከኢራን ጋር የሰላም ስምምነት መጠናቀቁን በይፋ አስታውቀዋል። ስምምነቱ የሊባኖስን ግንባር ጨምሮ በሁሉም አቅጣጫዎች ጦርነት እንዲቆም፣ የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ እንዲከፈት እና በኢራን ላይ የተጣለው የአሜሪካ የባህር ኃይል እገዳ እንዲነሳ የሚሉ ነጥቦችን የያዘ ነው። ሆኖም ይህ በተባለ ማግስት የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ ላይ የአየር ጥቃቱን ቀጥሏል። እንደ ሊባኖስ ባለስልጣናት መረጃ ከሆነ፤ካለፈው መጋቢት ጀምሮ በእስራኤል ጥቃት ከ3 ሺህ 7መቶ በላይ ሰዎች ሲገደሉ፣ወደ 11 ሺህ 5መቶ የሚጠጉ ቆስለዋል እንዲሁም ከ1.5 ሚሊየን በላይ የሚሆኑት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ያለዉ አናዶሉ ነዉ። እስከዳር ግርማ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

photo content

የጥገና ሼል ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሼል ለማከናወን ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦   ✅ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00 👉መድሓኒዓለም ቤ/ክ ፣ ኤድናሞል ፣ ሸገር ህንፃ ፣ ፍሬንድሺፕ ሆቴል ፣ ዳውንታውን ሆቴል፣ አውራሪስ ሆቴል፣ አዲሱ ስታዲየም፣ ካልዲስ ቡና፣ ኢምፔሪያል እና አካባቢው፣ 22 ቃል ገስት ሀውስ ጎላጎል ኤጂ ግሬስ ኤምፔሪያል አትላስ ሆቴል እና አካባቢው፣   👉ከጎፋ ገብርኤል ከፍ ብሎ ቀበሌ 43 መዝናኛ አጠገብ ፣ አልማዝዬ ሜዳ፣ ሶፍያ ሞል አካባቢ፣ ሐመልማል ቤት፣ ቄራ በረት፣ ጎፋ ፖሊስ፣ áŒŽá‹ ገብርኤል እና አካባቢው፣ 👉ቡልቡላ ማሪያም፣ ኬኬ ብርድ ልብስ ፋብሪካ ፣ ቂሊንጦ ኮንዶሚኒየም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ፣ ኢንዱስትሪ መንደር፣ ዋልያ ቢራ እና አካባቢው፣   ✅ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30 👉 ገፋ ኮንዶሚኒየም፣ ጀርመን አደባባይ፣ ጉራጌ ሰፈር፣ ትግሬ ሰፈር፣ ካፍ ነዳጅ ማደያ ጀርባ á‹ˆá‹­áˆŤ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢው፣                                                                                                                            👉አቡነ እጨጌ ቤተክርስትያን፣ ጦር ኃሎች ሆስፒታል፣ መኮንኖች ክበብ፣ ገዳመ ኢየሱስ፣ አውጉስታ እና አካባቢው፣ ✅ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30 👉ዳውንታውን ሆቴል፣ አውራሪስ ሆቴል፣ አዲሱ ስታዲየም፣ ካልዲስ ቡና፣ መድሓኒዓለም ቤ/ክ እና አካባቢው፣ ✅ከጠዋቱ 4፡00 – 11፡00 👉በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች በሙሉ፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢው፣   ✅ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡30 👉አየር ጤና፣ ሳሚ ካፈ ፣ ታቦት ማደሪያ፣ መሐንዲስ ሰፈር፣ ቴሌ፣ ኤሞሌስ ፋብሪካ፣ ካሰዴ፣ ጣፎ፣ 44 ማዞሪያ ፣ ሰንዳፋ ጫፍ፣ ቦሌ ሁላሳ ፣ ሰበታ፣ ዓለም ገና፣ ዋን ውሃ ፣ አባሃዋ ትሬዲንግ እና አካባቢው፣     ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን ሲል ገልጿል ፡፡ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

photo content

ማንኛውም ተቋም የሚያመነጨው መረጃ በኢትዮጵያ የዳታ ጥራት ቁጥጥር ማዕቀፍ ውስጥ ማለፍ እንደሚኖርበት ተደነገገ በስታቲስቲክስ ተግባር የተሰበሰበ የግለሰብ መረጃ በማንኛውም ተቋማት ዘንድ ለምርመራ ለደ
ማንኛውም ተቋም የሚያመነጨው መረጃ በኢትዮጵያ የዳታ ጥራት ቁጥጥር ማዕቀፍ ውስጥ ማለፍ እንደሚኖርበት ተደነገገ በስታቲስቲክስ ተግባር የተሰበሰበ የግለሰብ መረጃ በማንኛውም ተቋማት ዘንድ ለምርመራ ለደህንነት ለህግ ወይም ለአስተዳደራዊ ዉሳኔዎች እንዳይዉል ረቂቅ አዋጅ ይከለክላል ተብሏል ። ይህ ረቂቅ አዋጅ ግንቦት 18 በተካሄደው 55ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምራቱ ይታወሳል። የዜጎች የግል መረጃ ምስጢራዊነት አጠባበቅን በተመለከተም በስታቲስቲክስ ተግባር የተገኘ የግለሰብ ዳታ ለስታቲስቲክስ ዓላማ ብቻ የሚያገለግል ነዉ ተብሏል። በማንኛውም ሀገራዊ ወይም የዓለም አቀፍ ተቋማት ዘንድ ለምርመራ፣ ለደህንነት፣ ለሕግ ወይም ለአስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ ላይ ሊውል እንደማይችል ረቂቁ አሳስቧል። የግለሰቦችን ማንነት የሚገልጽ መረጃ አሳልፎ መስጠት በረቂቁ መሰረት በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑ ተመላክቷል። ረቂቅ አዋጁ በመረጃ አሰባሰብ ሂደት ላይ ለሚታዩ መሰናክሎች የቅጣት ድንጋጌዎችን አስቀምጧል። ማንኛውም መረጃ እንዲሰጥ የተጠየቀ አካል የተሳሳተ መረጃ ቢሰጥ ወይም ለመተባበር ፈቃደኛ ባይሆን በወንጀል ሕግ መሠረት ተጠያቂ ይሆናል ነዉ የተባለው። ሊዲያ ደሳለኝ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

በዩክሬን በተሰነዘሩት የሩሲያ ጥቃቶች የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፤ በታዋቂው የኪቭ ካቴድራል ላይ የእሳት አደጋ ተከሰተ የሩሲያ ጦር በተለያዩ ዋና ዋና ከተሞች ላይ በሰነዘረው ተከታታይ ጥቃት በዩክሬን ቢያንስ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። የኪቭ ወታደራዊ አስተዳደር ኃላፊ ቲሙር ትካቼንኮ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‹‹በኪቭ አንድ ሕፃንን ጨምሮ 23 ሰዎች ቆስለዋል በሚያሳዝን ሁኔታም የሟቾች ቁጥር ወደ አራት አድጓል›› ብለዋል። ቀደም ሲል የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ኢጎር ክሊሜንኮ እንደገለጹት፤በሰሜን ምስራቅ ዩክሬን በምትገኘው ካርኪቭ ከተማ ‹‹የእሳት ማጥፋት ሥራ ላይ የነበሩ አምስት የሀገር ውስጥ ድንገተኛ አደጋ አገልግሎት አባላት ተገድለዋል።›› ክሊሜንኮ በቴሌግራም ገጻቸው ላይ ‹‹ቢያንስ ሌሎች 5 ሰዎች ቆስለዋል›› ሲሉ የጻፉ ሲሆን፤ ጉዳቱ የደረሰው ሩሲያ በድጋሚ በሰነዘረችው ጥቃት መሆኑን አንስተዋል። የከተማዋ ከንቲባ ቪታሊ ክሊ ሰኞ ዕለት እንደተናገሩት በታዋቂው የኪቭ ፔቸርስክ ላቭራ የኦርቶዶክስ ገዳማት ግቢ ውስጥ የሚገኘው ዶርሚሽን ካቴድራል በሩሲያ ጥቃቶች ምክንያት የእሳት አደጋ ደርሶበታል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከሞስኮ በስተደቡብ 200 ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው ቱላ በተባለችው የሩሲያ ከተማ ላይ የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላን በሰነዘረው ጥቃት ሦስት ሰዎች ሲገደሉ፤ ሌሎች ሦስት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የክልሉ ገዥ ሰኞ ዕለት አስታውቀዋል። ዲሚትሪ ሚልዬቭ ‹‹ዛሬ ምሽት የቱላ ከተማ የመኖሪያ መንደር በሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ደርሶበታል›› ብለዋል፡፡ አክለውም ‹‹በጣም የሚያሳዝነው በደረሰን የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ መሠረት ሦስት ሰዎች ተገድለዋል የአንድ ዓመት ሕፃንን ጨምሮ ሌሎች ሦስት ሰዎች ቆስለዋል›› ሲሉ ገልጸዋል። ሀና ሰይፉ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

photo content

የአሜሪካ እና ኢራን ስምምነት የነዳጅ ዋጋን ቀነሰ አሜሪካ እና ኢራን የሆርሙዝ የባህር መስመርን ለመክፈትና ጦርነቱን ለማቆም የስምምነት ማዕቀፍ ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ከፍ
የአሜሪካ እና ኢራን ስምምነት የነዳጅ ዋጋን ቀነሰ አሜሪካ እና ኢራን የሆርሙዝ የባህር መስመርን ለመክፈትና ጦርነቱን ለማቆም የስምምነት ማዕቀፍ ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ከፍተኛ ለውጥ ታይቷል። ስምምነቱን ተከትሎ የጃፓንና የደቡብ ኮሪያ አክሲዮን ገበያዎች እስከ 5.7 በመቶ የደረሰ ታሪካዊ ጭማሪ አሳይተዋል። በአንጻሩ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በ4.5 በመቶ በመቀነስ በአንድ በርሜል ከ83.40 ዶላር በታች ወርዷል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ የተጣለው የባህር ኃይል እገዳ እንዲነሳ ማዘዛቸውን ያስታወቁ ሲሆን፤ ይፋዊው የፊርማ ሥነ-ሥርዓት አርብ ዕለት በስዊዘርላንድ እንደሚካሄድ ተገልጿል። ስምምነቱ ሊባኖስን ጨምሮ የተኩስ አቁም ማድረግን፣ የማዕቀብ መነሳትን እና የ24 ቢሊየን ዶላር የኢራን ሀብት መልቀቅን ያጠቃልላል ተብሏል። የባህር መስመሩ መከፈቱ የዓለምን የነዳጅ እጥረት የሚያቃልል ቢሆንም፤ የተከማቹ መርከቦችን ለማፅዳትና የባህር ውስጥ ፈንጂዎችን ስጋት ለመቅረፍ ግን ወራትን ሊወስድ እንደሚችል ባለሙያዎች አስታውቀዋል። ሳራ ዮሐንስ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ 1መቶ99 የፈተና ጣቢያዎች፣ የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መል
+2
የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ 1መቶ99 የፈተና ጣቢያዎች፣ የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዛሬው ዕለት በይፋ መሰጠት መጀመሩን የከተማዋ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ከዛሬ ሰኔ 8 ጀምሮ እስከ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ሦስት ቀናት የሚቆየውን ይህንን ከተማ አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 85 ሺህ 17 ተማሪዎች ተመዝግበው ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸው ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ በሰጡት መግለጫ፤ ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ በየደረጃው የኮማንድ ፖስት አደረጃጀቶች መዋቀራቸውን ገልጸዋል። ለፈተናው ሂደት ጥራትና ተዓማኒነት ሲባልም፣ ልምድ ያላቸው የፈተና አስፈጻሚዎች ተመልምለው በየጣቢያዎቹ እንዲመደቡ መደረጉን ጠቁመዋል። ከጸጥታ አኳያም ፈተናው ያለምንም ችግር እንዲከናወን አስፈላጊው የጸጥታ አካላት ጥበቃና የክትትል ሥራ መመቻቸቱ ተመላክቷል። በአሁኑ ሰዓት በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች ሂደቱን የሚከታተሉ የቢሮው አመራሮችና ባለሙያዎች በሥራ ላይ እንደሚገኙ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያ
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ፋና ዲጂታል ከቤተሰቦቹ ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

ደቡብ አፍሪካ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከ2 ሺህ 7መቶ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎችን ወደ ሀገራቸው መለሰች ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ በህገ-ወጥ ስደት ላይ ጠንከር ያለ እርምጃ እንደሚወስዱ ቃል ከገቡ በኋላ ባለው አንድ ሳምንት ውስጥ፤ደቡብ አፍሪካ 2 ሺህ 7መቶ45 የውጭ ሀገር ዜጎችን ወደ ሀገራቸው መመለሷን የሀገሪቱ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ገልጸዋል፡፡ ከአፍሪካ ግዙፍ ኢኮኖሚዎች አንዷ የሆነችው ደቡብ አፍሪካ፤ከመላው አህጉሪቱ በህጋዊም ሆነ በህገ-ወጥ መንገድ የሚመጡ ስደተኛ ሰራተኞችን ለረጅም ጊዜ ስትስብ ቆይታለች። ሆኖም ከ30 በመቶ በላይ በሆነ ከፍተኛ የስራ አጥነት መጠን የተጠመደችው ሀገሪቱ በቅርብ ሳምንታት የተከሰቱ አዳዲስ ግጭቶችን ጨምሮ ተደጋጋሚ በስደተኞች ላይ ያነጣጠሩ ብጥብጦች አስተናግዳለች። ዱላ፣ ጅራፍ እና ጋሻ የያዙ ደቡብ አፍሪካውያ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እየተዘዋወሩ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገር ዜጎች እስከ ሰኔ 30 ድረስ ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ ሲያስተላልፉ ሰንብተዋል። ንግዶች በመዘረፋቸው እና የውጭ ዜጎች ዒላማ በመደረጋቸው ምክንያት እየጨመረ የመጣው የደህንነት ስጋት የናይጄሪያ፣ ማላዊ፣ ጋና፣ ዚምባብዌ እና ሞዛምቢክ ዜጎች በመንግስታቶቻቸው አማካኝነት የተዘጋጀውን በፍቃደኝነት ወደ ሀገር የመመለስ ጥሪ እንዲቀበሉ አድርጓቸዋል። መንግስት እንደገለጸው ወደ ሀገራቸው ከተመለሱት መካከል አብዛኞቹ በሀገሪቱ ውስጥ በህገ-ወጥ መንገድ ይኖሩ የነበሩ ናቸው። መንግስት እሁድ ዕለት እንደገለጸው የስደተኛ መጠለያ ካምፖችን የማያስተዳድር ሲሆን፤ በጊዜያዊነትም ቢሆን የማቋቋም ዕቅድ የለውም። እንደ ሀገሪቱ የስታስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ከሦስት ሚሊየን በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ይኖራሉ፤ ይህም ከጠቅላላው የህዝብ ብዛት 5.1 በመቶ ያህሉ ነው። እስከዳር ግርማ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

photo content
+1

በደቡብ ምስራቅ እስያ በህገ-ወጥ ደላሎች ተታለው የነበሩ ከ1 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ በደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት በተለይም በሚያንማር፣ በካምቦዲያና በላኦስ ችግር ውስጥ የነ
በደቡብ ምስራቅ እስያ በህገ-ወጥ ደላሎች ተታለው የነበሩ ከ1 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ በደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት በተለይም በሚያንማር፣ በካምቦዲያና በላኦስ ችግር ውስጥ የነበሩ ከ1 ሺህ 3መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን ንጋት ግሎባል ኢኒሼቲቭ የተሰኘው ድርጅት አስታወቀ። ተመላሾቹ በህገ-ወጥ ደላሎች አማካኝነት "ከፍተኛ ክፍያ ያለው ሾል አለ" በሚል ተታለው ወደ ታይላንድ ከተጓዙ በኋላ፣ በግዳጅ ድንበር ተሻግረው በሚያንማር በሚገኙ የኢንተርኔት ማጭበርበሪያ ማዕከላት ውስጥ ታስረው እንዲሰሩ ይገደዱ እንደነበር ተገልጿል። ንጋት ግሎባል ኢኒሼቲቭ እንደገለጸው፥ እነዚህ ዜጎች በታጠቁ አካላት እየተጠበቁ ለወራት በሰው መብት ረገጣና በከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ቆይተዋል። ድርጅቱ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ከአለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት ጋር በመተባበር ዜጎቹን የማስመለስና የመልሶ ማቋቋም ሾል ሲሰል መቆየቱን ገልጿል። ወደ ሀገር ቤት የተመለሱ ዜጎች የተጎዳ የስነ-ልቦና ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙና የጤና ሚኒስቴር ባወጣው መለኪያ መሰረት አብዛኞቹ ከተገቢው የአዕምሮ ጤና ደረጃ በታች መሆናቸው በጥናት መረጋገጡ ተጠቁሟል። ህብረተሰቡ በተለይም የተማሩ ወጣቶች በማህበራዊ ሚዲያ በሚለቀቁ ሀሰተኛ የስራ ማስታወቂያዎች እንዳይታለሉ ድርጅቱ አሳስቧል። ሊዲያ ደሳለኝ   ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

"የኮንስትራክሽን ደህንነት ቅንጦት አይደለም" ሲሉ የዘርፉ ባለሙያዎች አሳስበዋል፡፡ በኢትዮጵያ አደጋዎች ሲከሰቱ የመደበቅና መረጃዎችን በአግባቡ የመመዝገብ ችግር እንዳለ ተገለጸ። በኢትዮጵያ አደጋዎች ሲከሰቱ የመደበቅና መረጃዎችን በአግባቡ የመመዝገብ ችግር እንዳለ የተገለጸው በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን ጤናና ደህንነት ኮንፈረንስ ላይ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ውስጥ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና አጠባበቅን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመው ይህ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂና ማኔጅመንት ባለሙያዎች ማህበር ከጄኔቫው ዓለም አቀፍ የማህበራዊ ዋስትና ማህበር (ISSA) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ በዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችና መፍትሄዎቻቸው በስፋት ተመክሮባቸዋል፤ በዘርፉ የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲመጣም ጥሪ ቀርቧል፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ኢንጅነር ሶፎንያስ ደነቀ ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ኢትዮጵያ እንዲህ ያለውን መድረክ በማዘጋጀት ከአፍሪካ ሶስተኛዋ ሀገር መሆን ችላለች ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ በሀገሪቱ ያለው የኮንስትራክሽን እድገት ፈጣን ቢሆንም፣ ከደህንነትና ጤና አጠባበቅ አንጻር ግን አሁንም በጅማሮ ደረጃ ላይ መሆናችንን ጠቁመዋል። ኢንጅነር ሶፎንያስ "ቪዥን ዜሮ" (Vision Zero) የተሰኘውን ዓለም አቀፍ መርህ በማንሳት፣ ይህ መርህ በግንባታ ሂደት ላይ ምንም ዓይነት አደጋ እንዳይከሰት የማድረግ ግብ ያለው ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ ግን አደጋዎች ሲከሰቱ የመደበቅና መረጃዎችን በአግባቡ የመመዝገብ ችግር እንዳለ ገልጸዋል። ይህንን ለመቅረፍም "ኒር ሚስ" (Near miss) የሚባሉ፣ ለጥቂት የተረፉ አደጋዎችን ጭምር መዝግቦ የሚይዝ የቴክኖሎጂ ሥርዓትና ዳታቤዝ ለመፍጠር ማህበሩ እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። በዘርፉ የሚታየውን ትልቁን ተግዳሮት ሲያስረዱም፣ "የኮንስትራክሽን ደህንነት እንደ ቅንጦት እና እንደ ተጨማሪ ወጪ የሚታይበት የተሳሳተ አመለካከት ሊቀየር ይገባል" ብለዋል። ግንባታዎች ከዲዛይን ጀምሮ እስከ ፍጻሜያቸው ድረስ ለባለሙያዎችና ለአካባቢው ማህበረሰብ ደህንነት ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው፣ ለዚህም የባለሀብቶች፣ የኮንትራክተሮችና የሱፐርቫይዘሮች በጋራ ተጠያቂነት ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በኮንፈረንሱ የአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ ባለስልጣናትን ጨምሮ ከጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኦስትሪያና ናይጄሪያ የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል፡፡ አዲስ አለም አበበ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

photo content

ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል። አደጋው የደረሰው በዛሬው ዕለት ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡ በአደጋው ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪም በርካታ ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ፖሊስ ገልጿል፡፡ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት 100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ውስጥ መግባቱን አሚኮ ዘግቧል፡፡ በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ ርብርብ እየተደረገ ሲሆን፥ የአደጋው ምክንያት በመጣራት ላይ ይገኛል፡፡ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

አሜሪካ እና ኢራን የገቡበትን ጦርነት ለመቋጨት የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ደርሰዋል ስምምነቱ ዐርብ የሚፈረም ሲሆን ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ኢራን ጥቃት ማድረሷን አንደምትገታ ገልፃለች። የፓኪስታኑ ጠቅላይ
አሜሪካ እና ኢራን የገቡበትን ጦርነት ለመቋጨት የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ደርሰዋል ስምምነቱ ዐርብ የሚፈረም ሲሆን ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ኢራን ጥቃት ማድረሷን አንደምትገታ ገልፃለች። የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሻሪፍ ሀገሬ በሁለቱ ኃይሎች መካከል  የተፈጠረውን ልዩነት ለማጥበብ ስትሰራ ቆይታለች ብለዋል። ዘላቂ ተኩስ አቁም ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ላይ ቴህራንና ዋሽንግተን መድረሳቸውን ያስታወሱት ሻሪፍ፥ ሊባኖስንም ያጠቃለለ ውል መሆኑን አረጋግጠዋል። የኳታር አደራዳሪዎች ከ14 እስከ 15 ሰዓታት ከፍተኛ ውይይት አድርገው የመጣ ውጤት መሆኑም ታውቋል። በስምምነቱ መሰረት ሆርሙዝ ሰርጥ ሙሉ ለሙሉ ይከፈታም ተብሏል። አሜሪካም ሰርጡን በ30 ቀናት ውስጥ የመክፈት ግዴታ ይኖርባታል። ስምምነቱ በአሜሪካ ቁርጠኝነት ልክ የሚመዘን መሆኑን ያስታወሰችው ቴህራን፥ዋሽንግተን የቤት ስራዋን መስራት እንዳለባትም አሳስባለች። አሜሪካ በኢራን ዙሪያ ካሉ አካባቢዎች ጦሯን ማንሳትም ይኖርባታል። በ60 ቀናት ውስጥ ኑክሌርን ጨምሮ ቁልፍ ጉዳዮች ውይይት እየተደረገባቸው መፍትሔ እየተሰጣቸው ይሄዳል ፤ለቀጣናውም ሰላም ይመጣል የሚል እምነት ተጥሏል። ያም ሆኖ ግን ስምምነቱ ጥያቄ ያለበት መሆኑን የአሜሪካ ፖለቲከኞች ማንሳት ጀምረዋል። ሪፐብሊካኑ ሴናተር ሊንዲሴይ ግርሃም እና የቀድሞው የትራምፕ ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስ á‰°áŒ á‰ƒáˆ˝ ናቸው። ጀርመን፣ጃፓን ፣ጣሊያን ፣ፈረንሳይ ፣እንግሊዝ፣ቱርክ እና ኒውዚላንድ ስምምነቱን በበጎ ከተመለከቱት አገራት መካከል ናቸው። የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝም ለስምምነቱ የሰሩትን ሁሉ አመስግነዋል ሲሉ ዘ ዋሽንግተን ፖስትና ሲ ኤን ኤን ዘግበዋል። ልዑል ወልዴ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

እስራኤል በቤሩት ላይ የፈፀመችውን ጥቃት "ትርጉም የለሽ " ሲሉ ትራምፕ አጣጣሉ የአሜሪካ እና የኢራን ስምምነት መቃረቡን ተከትሎ ትራምፕ በቤሩት የተፈጸሙ ጥቃቶችን በመኮንን ሁሉም ወገኖች እንዲቆጠቡ
እስራኤል በቤሩት ላይ የፈፀመችውን ጥቃት "ትርጉም የለሽ " ሲሉ ትራምፕ አጣጣሉ የአሜሪካ እና የኢራን ስምምነት መቃረቡን ተከትሎ ትራምፕ በቤሩት የተፈጸሙ ጥቃቶችን በመኮንን ሁሉም ወገኖች እንዲቆጠቡ አሳሰቡ ​ፕሬዚዳንት ትራምፕ በዛሬው ዕለት እስራኤል በቤሩት የሰነዘረችውን ጥቃት በመኮነን በሊባኖስ የሚደረጉ ጥቃቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ​ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ጥቃቱ “ሊፈጸም የማይገባው ነበር” በማለት፤ ማንም ሰው ላልተገደለበት ወይም ላልቆሰለበት ክስተት የተሰጠ “ኢምንትና ትርጉም የለሽ” ምላሽ ሲሉ ገልጸውታል። ​ቀጣይ መካካር ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔን ሊያደናቅፍ እንደሚችል ያስጠነቀቁት ትራምፕ፤ ቀጣናዊ ስምምነቱ “በጣም መቃረቡን” እና ሊባኖስንም በዚሁ ሰፊ የሰላም ማዕቀፍ ውስጥ ሊያካትት እንደሚችል አጽንኦት ሰጥተዋል። ሰኔ 07/2018 ዓ.ም

ትራምፕ የአሜሪካ-ኢራን ስምምነት እሁድ ዕለት እንደሚፈረም ሲናገሩ፣ ቴህራን ግን በጊዜው ላይ ጥርጣሬ አላት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለውን ውጊያ ለማቆም የተዘጋጀው ስምምነት እሁድ ዕለት እንዲፈረም ቀጠሮ መያዙን ሲናገሩ ፤ ኢራን ግን በፊርማው ጊዜ ላይ ጥርጣሬ እንዳላት ገልፃለች ። የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃኢ ስለ ስምምነቱ ጊዜ ጥንቃቄ የተሞላበት አስተያየት የሰጡ ሲሆን፥ "የመግባቢያ ሰነዱ የሚፈረምበትን ትክክለኛ ቀን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፣ ሆኖም ግን ነገ [እሁድ] አይሆንም" ብለዋል። ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስምምነቱ አንዴ ተቀባይነት ካገኘ በኋላ ቁልፍ የባህር ትራንስፖርት መስመር የሆነው የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ "ለሁሉም ክፍት" እንደሚሆን ገልጸዋል። ቅዳሜ ዕለት፣ ዋና አገናኝ የሆነችው ፓኪስታንም ስምምነቱ በ24 ሰዓታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ "በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠበቅ" እና "ለዲጂታል (የኤሌክትሮኒክስ) ፊርማ ዝግጅት እያደረጉ" መሆኑን አስታውቃለች። ከዶናልድ ትራምፕ አስተያየት በፊት የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃኢ ስለ ስምምነቱ ጊዜ ጥንቃቄ የተሞላበት አስተያየት የሰጡ ሲሆን፥ "የመግባቢያ ሰነዱ የሚፈረምበትን ትክክለኛ ቀን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፣ ሆኖም ግን ነገ [እሁድ] አይሆንም" ብለዋል። በንግግሩ ውስጥ ሌላኛዋ አገናኝ የሆነችው የኳታር ልዑካን ቡድን እሁድ ዕለት ቴህራን መድረሱን የኢራን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የዋሽንግተን ፖስት ዘገባ እንዳስነበበው ይህ ጉብኝት ኢራን ስምምነቱን ትፈርማለች ተብሎ በሚጠበቅበት ጊዜ ላይ ተፅዕኖ ይኑረው አይኑረው በግልጽ የታወቀ ነገር የለም። ትራምፕ ቅዳሜ ዕለት በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፡ "ስምምነቱ ነገ እንዲፈረም ቀጠሮ ተይዟል፣ ከተፈረመ በኋላ ወዲያውኑ የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ለሁሉም ክፍት ይሆናል" ብለዋል። ትራምፕ የኢራንን የዳበረ ዩራኒየም ክምችት ለመጠቆም በፈለጉበት ግልጽ በሆነ ንግግራቸው "በትክክለኛው ጊዜ፣ ሁሉም ነገር ሲረጋጋ፣ እኛ ገብተን 'የኑክሌር ብናኙን' (Nuclear Dust) እንወስዳለን" ያሉ ሲሆን፣ ከጊዜ በኋላም እንደሚወድም አክለው ገልጸዋል። ሰኔ 07/2018 ዓ.ም