en
Feedback
Ethio Fm 107.8

Ethio Fm 107.8

Open in Telegram

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Ethio Fm 107.8

Channel Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 18 482 subscribers, ranking 12 144 in the News & Media category and 1 871 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 18 482 subscribers.

According to the latest data from 01 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -15 over the last 30 days and by -5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 10.12%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.44% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 870 views. Within the first day, a publication typically gains 1 375 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 3.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 02 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

18 482
Subscribers
-524 hours
-87 days
-1530 days
Posts Archive
የቆጣሪ ካርድ መሙላት አገልግሎት መዘግየት አጋጥሟል አለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቅድመ ክፍያ (Prepaid) አገልግሎት መስጫ ማዕከላቱ ሲስተም ላይ ባጋጠ
የቆጣሪ ካርድ መሙላት አገልግሎት መዘግየት አጋጥሟል አለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቅድመ ክፍያ (Prepaid) አገልግሎት መስጫ ማዕከላቱ ሲስተም ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት የቆጣሪ ካርድ መሙላት አገልግሎት መዘግየት እንዳጋጠመው አሳውቋል። ተቋሙ አክሎም፣ ችግሩን ፈትቶ መደበኛ አገልግሎቱን ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጿል። በዚህ አጋጣሚ ለተፈጠረው እንግልት ከልብ ይቅርታ የጠየቀው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ደንበኞች በትዕግሥት እንዲጠባበቁ ጥሪ አቅርቧል። ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

የህዝብ ክብረ _ በዓላትን በማጎልበት ብሔራዊ አንድነትንና ልማትን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ  የኢትዮጵያ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በ 2019 የሚከበሩ ብሔራዊ ሀይማኖታዊና የአደባባይ በአላት አከባበርን አስመልክቶ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የህዝብ ክብረ _ በዓላትን በማጎልበት ብሔራዊ አንድነትንና ልማትን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጿል ። የባህል áŠĽáŠ“ ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ  የሆኑት ነፊሳ አልመሃዲ እንደገለጹት በ2019 በጀት ዓመት በሀገሪቱ ህዝቦች ዘንድ የሚታወቁ የህዝብ ክብረ በዓላትን በማልማትና በማስተዋወቅ ባህል በትውልድ ቅብብሎሽ እንዲዳብር ከማድረግ ባሻገር የጋራ እና የተናጥል እሴቶችን በማጉላት የመደጋገፍ፣ የመተባበር እና የአብሮነት መንፈስ እንዲጎልብት ብሎም ሀገራዊ አንድነት እንዲጠናከር እየተደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል። ኢትዮጵያ የብዙ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ሀገር እንደመሆኗ መጠን፣ ይህን ልዩ ባህላዊ ሀብትዋን ለማልማት  እና ለማበረታታት ብሔራዊ የባህል ልማት ፖሊሲን ተግባራዊ  እየተደረገ እንደሚገኝ በመግለጫው ተገልጿል ። በ2018 በጀት ዓመት ብቻ፣ ለሦስት ወራት የቆየ የባህል ንቅናቄ  በማድረግ 46 ሚሊዮን ህዝብን በማሳተፍ ባህላዊ እሴቶችንና አገር በቀል እውቀቶችን ማጉላት መቻሉን  የባህል áŠĽáŠ“ ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልመሃ ተናግረዋል ። በመጨረሻም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የህዝብ ክብረ በዓላት በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ያላቸው እና የማህበረሰብን  ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የሚያጠናክሩ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታዋ  አክለው ገልጸዋል ።   ሰላማዊት ዲታ   ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

photo content

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፡- ✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 11፡00 👉 አስኮ ሰብስቴሽን፣ አቡነሀብተ ማርያም ቤተክርስትያን፣ አስኮ አዲስ ሰፈር፣ ቡራዩ ወለጋ ሰፈር ፣ኢራን ጋዝ አካባቢ፣ ሙገር ሳይት፣ አወልያ አካባቢ፣ ካኦጄጄ፣ አስኮ፣ ዊንጌት ት/ቤት፣ ድሬ ቆዳ ፣ ጊዮን በረኪና፣ ሾሌ ሰፈር ጨረታ ✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 7፡00 👉 ቃሊቲ አካባቢ፣ ሸዋ ዳቦ ጀርባ፣ 40/60 ኮንዶሚኒየም ጀርባ፣ ቼራሊያ እና አካባቢው፣ ቸራሊያ ፊት ለፊት ኢንዱስትሪ መንደር በከፊል፣ ዩሮ ኬብል እና አካባቢው ✅ ከጠዋቱ 2፡10 - 9፡30 👉 ግብፅ ኤምባሲ፣ 6 ኪሎ ዩኒቨርስቲ፣ የካቲት 12 ሆስፒታል፣ ኤፍቢ ግቢ፣ ናይጄሪያ ኤምባሲ፣ 20 ቀበሌ፣ ፈረንሳይ ድልድይ፣አቦ፣ ቲኤምኤስና አካባቢው ✅ ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡00 👉 ቡራዩ ከተማ ሙሉ ፣ ቡራዩ ኢንዱስትሪ መንደር፣ ታጠቅ አካባቢ ገብርኤል ቤተክርስትያን፣ ሻካ ሞልና ኩሳዬ አካባቢ ✅ ከጠዋቱ 1፡30 - 9፡30 👉ባህርዳር ምድረገነት አዲሱ አስፋልት መንደር ✅ ከ4፡30 – 10፡00 👉 ባህር ዳር አባይ ማዶ ገብርኤል ጀርባ፣ ዘንዘልማ የገበያ ማዕከል፣ ዩሐንስ ቤተክርስትያን አካባቢ፣ አየርጤና፣ አዲሱ ድልድይ፣ ቾይዝ ውኃ፣ ቤዛዊትና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡ ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

photo content

የዘንድሮው የጳጉሜ ወር“የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሐሳብ በታላቅ ድምቀት ይከበራል ተባለ። ​የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት  በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ፥ በ2018 ዓ.ም የተመዘገቡ ታሪካዊ ሀገራዊ ስኬቶችን መነሻ በማድረግ አምስቱም የጳጉሜ ቀናት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ከፍታ በሚያሳዩ አምስት መርሃ ግብሮች እንደሚከበሩ አስታውቋል። በዚህም መሰረት የግብርና ምርታማነት ማደጉ፣ የገቢ አሰባሰብ ከ1.5 ትሪሊየን ብር መሻገሩ እና ከውጭ ንግድ 10.2 ቢሊየን ዶላር መገኘቱ ተጠቃሽ ምክንያቶች በመሆን ጳጉሜ 1 "የእመርታ" ቀን ተብሎ ይከበራል። ሀገሪቱ ከጎታች ማነቆዎች ተላቃ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሳየት የጀመረችበት እና ማዕድን፣ ቱሪዝም እና ዲጂታል ኢኮኖሚ የዕድገት ምሰሶዎች መሆናቸውን ያረጋገጠችበት አመት በመሆኑ ደግሞ ጳጉሜ 2 "የማንሰራራት" ቀን በመባል ተሰይሟል። የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ያጸኑ ጀግኖች የሚዘከሩበትና በሁሉም ተቋማት የሰንደቅ ዓላማ መስቀል ሥነ-ሥርዓት የሚከናወንበት ጳጉሜ 3 "የጽናት ቀን" ተብሎ ሲከበር፥ ለ1መቶ50 ሺህ ወገኖች ነፃ የጤና ምርመራ እና የበጎ አድራጎት ሥራዎች የሚከናወኑበት ጳጉሜ 4 ደግሞ "የኅብር ቀን" ተብሏል። የመጨረሻው የጳጉሜ ዕለት "ኢትዮጵያ ነገን ዛሬ ላይ እየሠራች ነው" በሚል መሪ ሐሳብ የዲጂታል ኢኮኖሚ አቅምን መጠቀም እና ወጣቶችን በክህሎት ማብቃት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ጳጉሜ 5 "የነገ ቀን" በመባል እንደሚከበር አገልግሎቱ በመግለጫው አስታውቋል። ሐመረ ፍሬው ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

photo content

አሜሪካ በፈፀመችው የቦምብ ጥቃት በሰርግ ቦታ ላይ የነበሩ ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውንየኢራን ቀይ መስቀል ማህበር ገለፀ ። የኢራን ቀይ መስቀል ማህበር እንዳስታወቀው፣ በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ
አሜሪካ በፈፀመችው የቦምብ ጥቃት በሰርግ ቦታ ላይ የነበሩ  áŠ•áŒšáˆƒáŠ• ዜጎች መገደላቸውንየኢራን ቀይ መስቀል ማህበር ገለፀ ። የኢራን ቀይ መስቀል ማህበር እንዳስታወቀው፣ በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ የሰርግ ስነ-ሰርዓት ላይ በአሜሪካ ጥቃት ምክንያተት አራት ሰዎች (አንድ ህጻን ጨምሮ) ህይወታቸው አልፏል፤ ከ50 በላይ ሰዎችም ቆስለዋል። ቀይ መስቀል በማህበራዊ ትስስር ገጹ  á‰ŁáŒ‹áˆŤá‹  áŒ˝áˆáá¤ "በአሜሪካ የሚሳኤል ጥቃት የቦምብ ፍንጣሪ በሆርሞዝጋን ግዛት በሲሪክ ወረዳ ኩሄስታክ ከተማ የሰርግ ዝግጅት እየተካሄደበት በነበረ የመኖሪያ ቤት ላይ አርፎ የሰዎችን ህይወት አጥፍቱዋል" ብሏል። ማህበሩ አክሎም "ከ50 በላይ ሰዎች ቆስለዋል፤ አንድን ህጻን ጨምሮ አራት ሰዎችም ሰማዕትነት ተቀብለዋል" ሲል ገልጿል። የኢራን የመንግስት ይፋ ያደረገው ቪዲዮ፣ በሲሪክ በሚገኘው የሰርግ ስፍራ ላይ የደረሰውን ሰፊ ፍርስራሽ እና ጉዳት የሚያሳይ ሲሆን፣ በስተጀርባም የሰዎችን ድምጽና ጩኸት ማድመጥም ተችሏል። የአሜሪካ ባለስልጣናት እስካሁን ድረስ ስለተባለው ድርጊት መረጋገጥ የሰጡት አስተያየት የለም፤ነገር ግን ኢራን ለደረሰው ጥቃት አፀፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ ዝታለች፡፡ በደቡባዊቷ ሲሪክ ወረዳ የምትገኘው ስፍራ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ባለው የሆርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ ትገኛለች።   ሀና ሰይፉ   ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

ሃይኒከን ኢትዮጵያ “15 ዓመታት ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ ማደግ” በሚል መሪ ቃል አከበረ ኩባንያው በኢትዮጵያ ባለፉት 15 ዓመታት ከ1 ቢሊዮን ዩሮ በላይ ኢንቨስት አድርጓል። ሃይኒከን ኢትዮጵያ በሀገሪ
+2
ሃይኒከን ኢትዮጵያ “15 ዓመታት ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ ማደግ” በሚል መሪ ቃል አከበረ   ኩባንያው በኢትዮጵያ ባለፉት 15 ዓመታት ከ1 ቢሊዮን ዩሮ በላይ ኢንቨስት አድርጓል።   ሃይኒከን ኢትዮጵያ በሀገሪቱ ያደረገውን የ15 ዓመት የኢንቨስትመንት እና አጋርነት ጉዞውን “15 ዓመታት ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ ማደግ” በሚል መሪ ቃል በቂሊንጦ ፋብሪካው ትላንት አክብሯል፡፡   በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት የሃይኒከን ኢትዮጵያ ዋና ሾል አስፈጻሚ ባርት ዲ ኬኒንክ እንደገለጹት፤ ኩባንያው ባለፉት 15 ዓመታት ከ1 ቢሊዮን ዩሮ በላይ ኢንቨስት አድርጓል። እንዲሁም ሃይኒከን ኢትዮጵያ ስምንት ተከታታይ ዓመታት የሀገሪቱ ከፍተኛ የግል ግብር ከፋይ በመሆን ከ103 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማድረጉ ተገልጿል።   ኩባንያው በግብርናው ዘርፍም ከ120 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን፣ ከ2023 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ሀገር በቀል ገብስ በመጠቀም የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል ብለዋል ዋና ሾል አስፈጻሚው ።   ኩባንያው በቀጥታ እና በእሴት ሰንሰለቱ ከ137 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል፤ በህብረተሰብ ልማት ሥራዎቹም ከ82 ሺህ በላይ ሰዎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስችሏል።   በተጨማሪም የቂሊንጦ ፋብሪካውን ሙሉ በሙሉ ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ በማድረግ በካርቦን ነፃ አሰራር ቀዳሚ ለመሆን ማቀዱን ይፋ አድርጓል። በዕለቱ ለ15 ዓመታት የጉዞ አጋር ለነበሩ ተቋማትም እውቅና ተሰጥቷል።   ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

በበዓል ሰሞን የሚታየውን ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር ጥብቅ ክትትል እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ የአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደገለፁት የበዓል ገበያን ተገን
በበዓል ሰሞን የሚታየውን ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር ጥብቅ ክትትል እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ የአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሎ ሀቢባ ሲራጅ እንደገለፁት የበዓል ገበያን ተገን በማድረግ የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመከላከል በመላው ከተማዋ ጥብቅ የቁጥጥር ሾል መጀመሩን አስታውቋል። ቢሮው በተለይም የኢንዱስትሪ ምርቶች በሚሸሸጉባቸው መጋዘኖች ላይ ድንገተኛ ፍተሻዎችን እያከናወነ ሲሆን፣ ምርት በመደበቅና ሰው ሰልሽ እጥረት በመፍጠር ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል። የቁጥጥር ስራው የምርት ጥራትንና ደረጃን ማረጋገጥን የሚያካትት ሲሆን፣ ጊዜያቸው ያለፈባቸውና ለጤና ጎጂ የሆኑ ምርቶች ለገበያ እንዳይቀርቡ በየደረጃው ያሉ ተቆጣጣሪዎች ስምሪት ተሰጥቷቸዋል። በተለይም በስጋ ቤቶች፣ በዱቄትና በዳቦ መሸጫዎች ላይ የሚታዩ የምርት መጠን ማነስ ችግሮችን ለመከላከል ክትትል እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። ህገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ዝውውርን ለመቆጣጠርም ከጸጥታ ግብረ-ኃይሉ ጋር በመቀናጀት በመግቢያ በሮችና በዋና ዋና የንግድ ማዕከላት ላይ ጥበቃና ፍተሻው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተደርጓል። የቁጥጥር ሰራተኞቹ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል ልዩ መለያ (ባጅ) እና ባርኮድ ያለው መታወቂያ እንዲይዙ የተደረገ ሲሆን፣ ይህም ደንበኞችን ከሐሰተኛ ተቆጣጣሪዎች ለመጠበቅ ይረዳል ተብሏል። ህብረተሰቡ በገበያ ውስጥ የሚታዩ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪዎችን፣ የምርት ጥራት ጉድለቶችንና ሌሎች ህገ-ወጥ ተግባራትን ሲመለከት በነጻ ስልክ መሾመር 8588 ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠይቋል።   ሊዲያ ደሳለኝ   ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

የኮንስትራክሽን ባለስልጣን ከግል ዘርፉ ጋር በመቀናጀት የአሰራር ስታንዳርዶችን እያሻሻለ መሆኑን አስታወቀ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የግንባታ ዘርፉን አሰራር ዘመናዊ ለማድረግ ከግል ባለድር
የኮንስትራክሽን ባለስልጣን ከግል ዘርፉ ጋር በመቀናጀት የአሰራር ስታንዳርዶችን እያሻሻለ መሆኑን አስታወቀ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የግንባታ ዘርፉን አሰራር ዘመናዊ ለማድረግ ከግል ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ዶ/ር) አዲስ የተዘጋጀውን የግንባታ ፊዚካል አፈጻጸም መለኪያ ስታንዳርድ ባስተዋወቁበት መድረክ ላይ ሲናገሩ፤ "ተቋሙ በደንብ ቁጥር 524/2014 የተሰጠውን ኃላፊነት ለመወጣት በመደመር መርህ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ይገኛል" ብለዋል። አዲሱ የሪፖርት ማዕቀፍ ስታንዳርድ በሀገር አቀፍ ደረጃ ወጥ የሆነ የቁጥጥርና የተጠያቂነት ባህል እንዲሰፍን እንደሚያደርግ ተገልጿል። ለዘርፉ ተዋንያን የሚሰጠው ስልጠናም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና በቀጣይ በየተቋማቱ ተግባራዊ እንዲሆን ጥሪ ቀርቧል።   አዲስዓለም አበበ   ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

በመዲናዋ ብቃታቸው የተረጋገጠ ከ4 መቶ በላይ ስፔሻላይዝድ የጥርስ ህክምና ተቋማት መኖራቸው ተገለፀ ‎ ‎የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በከተማዋ 4መቶ2 ብቃታቸው የተረጋገጠ ስፔሻላይዝድ የጥርስ ህክምና ተቋማት መኖራቸውን አስታውቋል። ‎ ‎ባለስልጣኑ የሚቆጣጠራቸውን እነዚህን ተቋማት እውቅና ለመስጠት መዘጋጀቱንም ገልጿል። ‎ ‎ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከሮቫ ኤቨንትስ እና መልቲሚዲያ ጋር በመተባበር በጥርስ ሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ የላቀ ሥራ ላከናወኑ የጥርስ ሕክምና ተቋማትና ባለሙያዎች ያዘጋጀውን የእውቅና እና የሽልማት መድረክ ይፋ አድርጓል። ‎ ‎ፕሮግራሙ በታካሚ እንክብካቤ፣ በክሊኒካዊ ብቃት፣ በንጽህና እና በማህበረሰብ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ በማሳደር ረገድ የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ተቋማትን እውቅና መስጠትን ግብ ያደረገ ነው። ‎ ‎ፕሮግራሙ እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሰፊ ሀገራዊ ፋይዳ እንዳለው ‎ ተነስቷል። ‎ ‎የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሉእመቤት ታደሰ፥ የዕውቅናው አላማ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ የጥርስ ሕክምና ማዕከላት እንዲስፋፉ ማድረግ እንደሆነ አንስተዋል። ‎ ‎15 የዕውቅና መስፈርቶች መኖራቸው የተገለፀ ሲሆን፥ ተቋማቱ ከአንድ በላይ በሆኑ መስፈርቶች መወዳደር እንደሚችሉ ተነስቷል። ‎ ‎ለዚህ ሲባል የተዘጋጀ ዌብሳይት መኖሩም ተገልጿል። ‎ ‎የዕውቅና ሽልማቱ 70 በመቶ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ግምገማ እና 30 በመቶ በህዝብ ድምፅ እና ምርጫ የሚደረግ ይሆናል። ‎ ‎በየዓመቱ ደረጃውን እና ፕሮፌሽናሊዝምን በጠበቀ መልኩ የሚከናወን መርሀ ግብር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ‎ ‎ሽልማቱ በጥቅምት 2019 የሚካሄድ መሆኑም ተገልጿል። ‎ ‎እስከዳር ግርማ ‎ ‎ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

photo content
+1

ከ3.7 ሚሊዮን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት ለዘመን መለወጫ በአል እንደሚቀርብ  የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተናገረ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ  የመጪዉ የአዲስ አመት በአል አስመልክቶ የበዓሉን የገበያ አቅርቦትና የንግድ እንቅስቃሴ ዝግጅት ዙሪያ በዛሬዉ እለት መግለጫ ሰጥቷል። የቢሮዉ ሃላፊ ወ/ሎ  ሀቢባ ሲራጅ  አዲስ ዓመት በዓል በማስመልከት የሚፈጠረውን የኅብረተሰብ ከፍተኛ የመሰረታዊ ፍጆታ ምርቶች ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችል ሰፊ የዝግጅት፣ የአቅርቦትና የቁጥጥር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በበአሉ ከቄራ እንስሳት አቅርቦት ጋር በተያያዘ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዶሮዎች እና  ከ42.7 ሚሊዮን በላይ እንቁላል ለገበያ እንደሚቀርቡ ተጠቅሷል። ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ በግና ፍየል እንዲሁም 62 ሺህ 600 ደረቅ ከብቶች ለበዓሉ ገበያ እንደሚቀርቡ የከተማዋ ንግድ ቢሮ ተናግሯል። ለበዓሉ ገበያ 
7መቶ 8ሺህ 266 ኩንታል ቀይ ሽንኩርት
እንደሚቀርብ የተናገሩት የቢሮዉ ሀላፊ ሀቢባ ሲራጅ  ፤ 227 ሺህ 8 መቶ 85 ኩንታል የጤፍ ምርት ለማቅረብ መታቀዱን በመግለጫቸው ገልፀዋል። ከ3.7 ሚሊዮን ሊትር በላይ ፈሳሽ የምግብ ዘይት ለኅብረተሰቡ ለማቅረብ ዝግጅት መጠናቀቁን á‹¨á‰˘áˆŽ ሃላፊ ወ/ሎ ሃላፊ ሀቢባ ሲራጅ ተናግረዋል። ለህብረተሰቡ በጥራትና በበቂ ሁኔታ ለማዳረስ ሲባል  የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የፋብሪካ ምርቶች መሸጫ ማዕከላት አገልግሎቱ እንዲሰጡ ይደረጋል ተብሏል። 5 የቀንድ እንስሳት መሸጫ ማዕከላት እና 2መቶ 64 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በሳምንቱ ሙሉ ክፍት ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ መወሰኑን ሀላፊዋ ጠቁመዋል። ሊዲያ ደሳለኝ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

photo content

በኔፓል የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,000 በላይ መድረሱ ተገለጸ በኔፓል በተከሰተው ከባድ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 1,003 መድረሱን የአገሪቱ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣን አስታወቀዋል። ባ
በኔፓል የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,000 በላይ መድረሱ ተገለጸ በኔፓል በተከሰተው ከባድ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 1,003 መድረሱን የአገሪቱ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣን አስታወቀዋል። ባለስልጣኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ከሟቾቹ በተጨማሪ በርካታ ሰዎች የደረሱበት ያልታወቀ ሲሆን፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የነፍስ አድን ሰራተኞች አሁንም አስከሬኖችን ፍለጋ እና በጎርፍ የተከበቡ ሰዎችን የማውጣት ስራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል። በጎርፉ ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ በመሰረተ ልማቶችና በመኖሪያ ቤቶች ላይም ከፍተኛ ውድመት መድረሱ ተገልጿል። የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣኑ የሟቾች ቁጥር አሁንም ሊጨምር እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል። ልዑል ወልዴ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚታየውን የሪፖርት መዛባት የሚቀርፍ አዲስ ስታንዳርድ ይፋ ሆነ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኮንስትራክሽን ማናጅመንት ኢንስቲትዩት እና የሚድሮክ ኮንሰልቲንግ አርክቴ
+3
በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚታየውን የሪፖርት መዛባት የሚቀርፍ አዲስ ስታንዳርድ ይፋ ሆነ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኮንስትራክሽን ማናጅመንት ኢንስቲትዩት እና የሚድሮክ ኮንሰልቲንግ አርክቴክትስና ኢንጅነርስ በመተባበር ያዘጋጁት አዲስ የግንባታ ፊዚካል አፈጻጸም መለኪያና የሪፖርት ማዕቀፍ ስታንዳርድ ይፋ ተደርጓል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ እስካሁን በዘርፉ ወጥ የሆነ የግንባታ አፈጻጸም መለኪያ ባለመኖሩ ምክንያት ፕሮጀክቶችን በጊዜ፣ በወጪና በጥራት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ ቆይቷል። ይህ አዲስ ስታንዳርድ "ትክክለኛ መረጃ፣ ትክክለኛ መለኪያ፣ ተዓማኒነት ያለው ሪፖርት እና ትክክለኛ ውሳኔ" የሚለውን የሥራ ሰንሰለት በተግባር ለማዋል ያለመ ነው ተብሏል። በተለይም በተለያዩ ተቋማትና ፕሮጀክቶች መካከል የሚታየውን የሪፖርት አለመጣጣም በመቅረፍ፣ የግንባታ አፈጻጸም ግምገማን ግልጽና ተነጻጻሪ ለማድረግ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው ተጠቁሟል። በዝግጅቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የክልልና የፌዴራል የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።   አዲስዓለም አበበ   ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

የሮቦት ማፅጃ ካሜራን በመጠቀም ሚስጥራዊ ምስል የቀረፀው የታይዋን ዜጋ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣ ​አንድ የታይዋን ዜጋ የባለቤቱን ሌላ የፍቅር ግንኙነት በሮቦት የቤት ማፅጃ ካሜራ አማካኝነት ያለፍቃ
+2
የሮቦት ማፅጃ ካሜራን በመጠቀም ሚስጥራዊ ምስል የቀረፀው የታይዋን ዜጋ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣ ​አንድ የታይዋን ዜጋ የባለቤቱን ሌላ የፍቅር ግንኙነት በሮቦት የቤት ማፅጃ ካሜራ አማካኝነት ያለፍቃዷ ቀርፆ በመያዙ በአምስት ወር የእስራት ፍርድ እና በ150,000 የታይዋን ዶላር መቀጮ ተቀጥቷል። ​ግለሰቡ በ2023 በሁለተኛ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በተፈጠረ ጥርጣሬ ተነሳስቶ፣ በሞባይል መተግበሪያ የቤቱን ሮቦት ማፅጃ በርቀት በማስነሳት ባለቤቱ ከሌላ ወንድ ጋር ሆና በካሜራ ይዟታል። ባል ምስሉን ለቀጣይ የሕግ ክስ እንደ ማስረጃ ለመጠቀም በማሰብ መቅረፁን የቀጠለ ሲሆን፣ በቪዲዮው ታግዞም ለደረሰበት የሞራል ጉዳት ከባለቤቱና ከፍቅር አጋሯ 500,000 የታይዋን ዶላር ካሳ አግኝቷል። ሆኖም ግን፣ ስኬቱ ባለቤቱ ባቀረበችበት የመልስ ክስ ምክንያት ጥላ ያረፈበት ሆኗል። በሮቦት ማፅጃው የተቀረፀው የቪዲዮ ማስረጃ የባለቤቱን አለመታመን ያረጋገጠ ቢሆንም፣ ሁለቱን ፍቅረኞች ያለፍቃዳቸው መቅረፁንም አረጋግጧል። ባል ድርጊቱ ተገቢ እንደነበር ቢከራከርም፣ ፍርድ ቤቱ ግን የጋብቻ ግዴታዎች የሰዎችን የግል ሕይወት የመጠበቅ መብት አያልፉም በማለት ውድቅ አድርጎታል። በዚህም መሠረት በታይዋን ሕግ የሰዎችን የግል እንቅስቃሴ ያለፍቃዳቸው መቅረፅ ወንጀል በመሆኑ፣ ባል የካሳ አሸናፊ ቢሆንም በወንጀሉ ምክንያት የእስራትና የገንዘብ መቀጮ ፍርድ ተፈርዶበታል።   ሐመረ ፍሬው   ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

በሶሪያ ሱዌዳ ግዛት በተቀሰቀሰ ግጭት 10 የመንግስት የጸጥታ አባላት ቆሰሉ በደቡባዊ ሶሪያ፣ አብዛኛው ነዋሪ የድሩዝ ማህበረሰብ በሆነባት ሱዌዳ ግዛት፣ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በአካባቢው ታጣ
በሶሪያ ሱዌዳ ግዛት በተቀሰቀሰ ግጭት 10 የመንግስት የጸጥታ አባላት ቆሰሉ በደቡባዊ ሶሪያ፣ አብዛኛው ነዋሪ የድሩዝ ማህበረሰብ በሆነባት ሱዌዳ ግዛት፣ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በአካባቢው ታጣቂ ቡድኖች መካከል ግጭት መከሰቱ ተነግሯል ። የሶሪያ የመንግስት መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ፣ በዚህ ግጭት 10 የመንግስት የጸጥታ አባላት ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሷል። ግጭቱ የተቀሰቀሰው በጸጥታ ኃይሎች እና በአካባቢው ባሉ ታጣቂዎች መካከል በነበረ የቃላት ምልልስ እና አለመግባባት እንደሆነ ተገልጿል። የሱዌዳ ግዛት ለዓመታት ከመንግስት ጋር በተያያዘ በተቃውሞዎች እና አልፎ አልፎ በሚከሰቱ ግጭቶች የምትታወቅ ሲሆን፣ የዛሬው ግጭትም በቀጠናው ያለውን ውጥረት ዳግም እንዳባባሰው ተዘግቧል። ሾለ ታጣቂዎቹ ጉዳት እስካሁን የተገለጸ መረጃ የለም።   ልዑል ወልዴ   ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም