ar
Feedback
Ethio Fm 107.8

Ethio Fm 107.8

الذهاب إلى القناة على Telegram

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethio Fm 107.8

تُعد قناة Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 18 534 مشتركاً، محتلاً المرتبة 12 141 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 1 817 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 18 534 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 05 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -92، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 8.93‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 6.82‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 1 655 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 264 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 4.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 06 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.

18 534
المشتركون
-124 ساعات
-37 أيام
-9230 أيام
أرشيف المشاركات
በአንድ ሳምንት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ሩሲያ በኬዬቭ ላይ በፈጸመችው ጥቃት ቢያንስ 11 ሰዎች ተገደሉ የኪየቭ የድንገተኛ አደጋ አገልግሎት ዛሬ ማለዳ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ በሕይወት የተረፉ ሰዎችን በቦምብ ከተመቱ ሕንፃዎች እያወጣ ነበር አምስት ህጻናትን ጨምሮ 46 ሰዎች መቁሰላቸውን እና የማዳን ጥረቱ ከ 20 በላይ ቦታዎች መቀጠሉን ቲሙር ትካቼንኮ ገልጿል የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ከፕሬዚዳንት ትራምፕ ጋር ሊነጋገሩ በሚጠበቅበት በቱርክ ናቶ የመሪዎች ጉባኤ ዋዜማ ነው ጥቃቱ የደረሰው የመጨረሻው ጥቃት የተፈጸመው ከሰዓታት በፊት ዜለንስኪ ሞስኮ በኪዬቭ ላይ ሀሙስ እለት 30 ሰዎችን የገደለውን ጥቃት ተከትሎ ለሁለተኛ ጊዜ ሩሲያ ለጥቃት እየተዘጋጀች መሆኑን ካስጠንቀቁ በኋላ ነበር ከንቲባ ቪታሊ ክሊችኮ የሩስያ ባሊስቲክ ሚሳኤሎች በከተማዋ የሚገኙ በርካታ ሕንፃዎችን በመምታታቸው በአንዳንድ አፓርትመንት ቤቶች ውስጥ የእሳት ቃጠሎ መድረሱን መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል ሃሙስ ምሽት ላይ ከድሮን እና ከሚሳኤል ጥቃት በኋላ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች በከተማው ዙሪያ ወደሚገኙ የሜትሮ ጣብያዎች ለቀው ወተዋል ዩክሬን ሞስኮን በጥቃቱ ሆን ብላ በሲቪል አካባቢዎች ላይ ጥቃት አድርሳለች ስትል ከሳለች በቅርቡ ዩክሬን በሩሲያ የሃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ ያደረሰችውን ጥቃት ተከትሎ ሩሲያ የዩክሬንን ወታደራዊ እና የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ኢላማ አድርጌያለሁ ስትል ተናግራለች ሲል ቢቢሲ አክሎ ገልጿል፡፡     ሰላማዊት ዲታ ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

photo content

በአዲስ አበባ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከ97 በመቶ በላይ ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ ክፍል ተሸጋገሩ በ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 97.48 በመቶ የሚሆኑት 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ የፈተና ውጤቱን ይፋ ለማድረግ ለተለያዩ የሚዲያ ተቋማት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፤ በከተማ አስተዳደሩ ፈተናውን ከወሰዱ 84 ሺህ 257 ተማሪዎች መካከል 82 ሺህ 137 የሚሆኑት ውጤታማ መሆን ችለዋል። ይህ የዘንድሮው አፈጻጸም በ2017 ዓ.ም ከነበረው የ95 በመቶ የማለፍ ምጣኔ አንጻር ሲታይ ከፍተኛ እድገት ያሳየ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፤ ውጤቱ እንዲመዘገብ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ መምህራን፣ የትምህርት አመራሮች፣ ባለሙያዎች፣ ወላጆችና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። ዘንድሮ ለተመዘገበው አመርቂ ውጤት የከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ሥራው ልዩ ትኩረት መስጠቱ፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉ እንዲሁም የሂሳብና እንግሊዘኛ ትምህርት ስትራቴጂ ተነድፎ በትኩረት መሠራቱ በዋናነት ተጠቃሽ መሆናቸውን ዶክተር ዘላለም አብራርተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የመማሪያና ማስተማሪያ ግብዓቶች በበቂ ሁኔታ መቅረባቸው እና ከወላጆች ጋር በቅንጅት መሠራት መቻሉ ለስኬቱ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ተገልጿል። በከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ሥርዓቱ የብዝሃ ቋንቋ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ የተማሩ ተማሪዎች በትምህርት ዓይነቶቹ ፈተና መውሰዳቸውን ኃላፊው አስታውሰዋል። የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናን ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከልም 543 ያህሉ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸው በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁሟል። ተፈታኝ ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ የተዘጋጀውን ይፋዊ የኢንተርኔት ሊንክ በመጠቀም ውጤታቸውን መመልከት የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል። ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

photo content

በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል አሉ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር
በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል አሉ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)   የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል   2018 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።   ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እያካሄደ ይገኛል። በግምገማ መድረኩላይ የተገኙት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል።   በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ 10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት በተሰራው ስራ ዕቅዱን መቶ በመቶ ማሳካት መቻሉን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል፡፡   ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ዋና መሥሪያ ቤትና በተጠሪ ተቋማት አማካኝነት በተከናወኑ የተቀናጁ የሪፎርም ሥራዎች፣ የወጪ ምርቶች ጥራትን በማረጋገጥና በተዘረጉ ዘመናዊ አሠራሮች መሆኑን ተናግረዋል።   በበጀት ዓመቱ 3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች የንግድ ፈቃድ፣ ምዝገባና ዕድሳት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ፣ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑት አገልግሎት መስጠት መቻሉን ገልጸዋል።   ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

📢የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት🎯 ነገ እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ 132 ኪ.ቮ ሃይል አስተላላፊ መስመር ሰበታ ወጪ መስመር ላይ የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦                                          ✅ከንጋቱ 12፡00 እስከ ጠዋቱ 2፡00 ድረስ:-   👉በልደታ ክፍለ ከተማ ዙሪያ እና በጭድተራ ፊት ለፊት፣መላው የመርካቶ ዙሪያ፣ ፔፕሲ ፋብሪካ፣ የድሮው አትክልት ተራ፣ ኤሊያና ሆቴል፣ ሰባራ ባቡር፣ አዲስ ከተማ ቴሌ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ኮል ሴንተር እና አካባቢው ፣ 👉በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ዙሪያ፣ ሰንጋተራ፣ ጥቁር አንበሳ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ የደም ባንክ፣ ፋና ሚዲያ፣  ንብ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት እና ጎላ ሚካኤል ሙሉ፣ በህንፃ ኮሌጅ ዙሪያ፣ ኮካ፣ አብነት፣ መድር-ኃይል፣ 👉ጦር ኃይሎች ሆስፒታል እና ቶሎሳ ሰፈር፣ በልደታ ደሴ ሆቴል ዙሪያ፣ መላው ብስራተ ገብርኤል ዙሪያ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት (Commercial Bank of Ethiopia HQ)፣ ፍልውሃ፣ ዘውዲቱ ሆስፒታል፣ 👉ጋንዲ ሆስፒታል፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ አራት ኪሎ (ባሻ ወልዴ፣1080)፣ ቅድስት ማርያም፣ አንድነት ፓርክ፣ መላው የጨርቆስ ዙሪያ፣ ፌደራል ፖሊስ፣ በልደታ ፀበል ዙሪያ፣ በልደታ ኮንዶሚኒየም ዙሪያ እና አካባቢው ፣  👉ኮሜርስ  ኮሌጅ (Commerce)፣ ጥቁር አንበሳ፣ ቴሌ ዳታ ሴንተር፣ አድዋ ዜሮ ዜሮ (Adwa 00)፣ ወዳጅነት ፓርክ እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡ ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን። #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት ሰኔ 27/2018 ዓ.ም

photo content

የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽንና ቴክኖ ኢትዮጵያ የሀገርን ገፅታ በቴክኖሎጂ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ የሀገርን ገፅታ ለመገንባትና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በቴክኖሎጂ የታገዘ የማስተዋወቅ
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽንና ቴክኖ ኢትዮጵያ የሀገርን ገፅታ በቴክኖሎጂ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ የሀገርን ገፅታ ለመገንባትና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በቴክኖሎጂ የታገዘ የማስተዋወቅ ስራ ለመስራት የሚያስችል ስልታዊ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈርሟል ። ስምምነቱ የተፈረመው ቴክኖ ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን እና ከቦርድ ሴል ፎን አዲስ አበባ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው 3ኛው ዙር የፎቶ ኤግዚቢሽን መክፈቻ ላይ ነው። በሕፃናትና ወጣቶች ትያትር ኮምፕሌክስ በይፋ በተከፈተው በዚህ ኤግዚቢሽን ላይ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን እና ቴክኖ ኢትዮጵያ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውል ተፈራርመዋል። ይህም ሁለቱ ተቋማት በቱሪዝም እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ በቅንጅት በመስራት፣ የሀገር ውስጥ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግና ማህበረሰቡ የሀገሩን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ እሴቶች እንዲያውቅ ለማስቻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሏል። በኤግዚቢሽኑ ላይ አዳዲስ የካሜራ እና የሰው ሰራሽ አስተዋፅኦ ወይም AI ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተነሱ ከ100 በላይ ልዩ ልዩ የፎቶግራፍ ስራዎች ለዕይታ ቀርበዋል። ቴክኖሎጂን ለሀገር ገፅታ ግንባታና ለኪነጥበብ እድገት ማዋል ላይ ትኩረት ያደረገው ይህ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ ለሚቀጥሉት 10 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን፤ ከ10 ሺህ በላይ ታዳሚዎች ይጎበኙታል ተብሎ ይጠበቃል። ድርጊቱ በዘርፉ ላሉ ባለሙያዎችና ለቱሪዝም ኢንዱስትሪው አዲስ መነቃቃትን እንደሚፈጥርም ተነግሯል። ልዑል ወልዴ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የ3 ቢሊዮን ዶላር የቡና ወጪ ንግድ ዕቅዷን ማሳካቷን አቶ አዲሱ አረጋ ገለጹ በባለፈው በጀት ዓመት 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተገኘ ሲሆን፤ ይህን ቁጥር ዓመት ባልሞላ
ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የ3 ቢሊዮን ዶላር የቡና ወጪ ንግድ ዕቅዷን ማሳካቷን አቶ አዲሱ አረጋ ገለጹ በባለፈው በጀት ዓመት 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተገኘ ሲሆን፤ ይህን ቁጥር ዓመት ባልሞላ ጊዜ ዉስጥ ማሻሻል መቻሉን ግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው አስታውቀዋል ፡፡ መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የቡናውን ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ሥራዎች መሠራታቸው በተለይም ለቡና ምርት ጥራት ትኩረት መደረጉ ለዕቅዱ ስኬት ድርሻው ከፍተኛ ነው ብለዋል ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ፡፡ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

ዘምዘም ባንክ የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡንና በካፒታል ገበያ ታሪክ ከወለድ ነፃ ቀዳሚ ባንክ መሆኑን አስታወቀ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጠው ዘ
ዘምዘም ባንክ የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡንና በካፒታል ገበያ ታሪክ ከወለድ ነፃ ቀዳሚ ባንክ መሆኑን አስታወቀ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጠው ዘምዘም ባንክ፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ። ባንኩ ይህን የገለፀው፣ 6 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸውን 6 ሚሊዮን ነባርና አዳዲስ አክሲዮኖቹን በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን  አስመዝግቦ ያስፀደቀ የመጀመሪያው ከወለድ ነፃ የፋይናንስ ተቋም መሆኑን ይፋ ባደረገበት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። እንደ ባንኩ መግለጫ፣ የተመዘገበው የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ35 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። በተመሳሳይ የባንኩ ጠቅላላ ገቢ ከ2.2 ቢሊዮን ብር ወደ 3 ቢሊየን ብር በማደግ የ36 በመቶ ጭማሪ ማስመዝገቡ ተጠቅሷል። በተያያዘም የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ መሊካ በድሪ ዘምዘም ባንክ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪክ አክሲዮኖቹን በይፋ አስመዝግቦ ያስፀደቀ ቀዳሚው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ ተቋም በመሆን ታሪክ  ሰርቷል ብለዋል። ባንኩ ከግብይት አማካሪው ወጋገን ኢንቨስትመንት ባንክ ጋር በመሆን በካፒታል ገበያ መመሪያ በተቀመጠው መሠረት ነባርና አዳዲስ አክሲዮኖቹን አስመዝግቧል። ባንኩ የባለአክሲዮኖችን መብት በማስጠበቅና አዳዲስ አክሲዮኖችን ለሕዝብ በማቅረብ፣ አጠቃላይ ካፒታሉን ወደ 15 ቢሊዮን ብር ለማድረስ አቅዶ እየሠራ እንደሚገኝ ተገልጿል። አዲስዓለም አበበ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

በሰሜናዊ ናይጄሪያ ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ ረሃብ መጋለጣቸው ተገለጠ በሰሜናዊ ናይጄሪያ በተከሰተ የጸጥታ ችግር እና በእርዳታ አቅርቦት መቋረጥ ምክንያት ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ የረ
በሰሜናዊ ናይጄሪያ ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ ረሃብ መጋለጣቸው ተገለጠ በሰሜናዊ ናይጄሪያ በተከሰተ የጸጥታ ችግር እና በእርዳታ አቅርቦት መቋረጥ ምክንያት ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ የረሃብ አደጋ መጋለጣቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) አስታወቀ። ተቋሙ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ በአካባቢው ያለው አለመረጋጋት በርካታ ቤተሰቦችን ከቤት ንብረታቸው ከማፈናቀሉም በላይ ገበሬዎች ወደ እርሻቸው እንዳይሰማሩ እንቅፋት ሆኖባቸዋል። ይህም በክልሉ ያለውን የምግብ ዋስትና ችግር ይበልጥ አባብሶታል። በተለይም የቦርኖ ግዛት የችግሩ ዋነኛ ሰለባ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን፣ በዚሁ ግዛት ብቻ ከ3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አጣዳፊ ለሆነ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የዓለም የምግብ ፕሮግራም በአሁኑ ወቅት ሰብአዊ ድጋፍ ለማቅረብ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ቢሆንም፣ የጸጥታው ሁኔታ እርዳታውን ለተቸገሩ ወገኖች ለማድረስ አስቸጋሪ እንዳደረገው ገልጿል። ተቋሙ በክልሉ የጀመረውን የምግብ እና የሥርዓተ-ምግብ ድጋፍ አጠናክሮ ለማስቀጠል በአስቸኳይ 89 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገው ጥሪ አቅርቧል DW Africa እንደዘገበው። ልዑል ወልዴ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ከዛሬ ጀምሮ ለሰባት ቀናት በኢራን እና በኢራቅ ከተሞች እንደሚከናወን ተገለፀ ባለፈው መጋቢት ወር ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የቀብር ሥነ-ሥርዓት በአሜሪካ-እስራኤል እና በኢራን መካከል ባለው ጦርነት ምክንያት እንዲራዘም ተደርጓል። የ86 ዓመቱ አሊ ኻሜኒ ጦርነቱ በፈነዳበት የመጀመሪያ ቀን የካቲት 28 በመኖሪያ ግቢያቸው ላይ በተሰነዘረ የጋራ የአሜሪካ እና የእስራኤል የአየር ጥቃት ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገደላቸው ይታወሳል። ከ1989 ጀምሮ ኢራንን የመሩት ኻሜኒ የአገሪቱን ወታደራዊ መዋቅር የቀረጹ መሪ ነበሩ። ይህ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ከሕዝብ ዕይታ ተሰውረው የቆዩት ልጃቸው እና ተተኪያቸው ሞጅታባ ኻሜኒ ሥልጣን ከያዙ በኋላ የሚከናወን የመጀመሪያው ትልቅ የመንግሥት ሥነ-ሥርዓት ነው። የሰባት ቀናት የቀብር ሥነ-ሥርዓት መርሃ-ግብሩ ከዛሬ ከፈረንጆቹ ሐምሌ 3 ጀምሮ በዋና ከተማው ቴህራን የሚጀምር ሲሆን፥የዓለም መሪዎችና ከፍተኛ ባለሥልጣናት ክብራቸውን ይገልጻሉ። በመቀጠልም በሐምሌ 4 እና 5 የሟቹ አስከሬን ሕዝቡ የመጨረሻ ስንብት እንዲያደርግለት በቴህራኑ ግራንድ ሞሳላ መስጊድ የሚቆይ ሲሆን፥በሐምሌ 6 እና 7 የሽኝት ሰልፉ ወደ ታዋቂው የሺዓ ሃይማኖታዊ ትምህርት ማዕከል ቆም ከተማ ይጓዛል። በመቀጠልም አስከሬኑ ወደ ጎረቤት አገር ኢራቅ በመጓዝ በሐምሌ 8 ቀን በናጃፍ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ይፋዊ አቀባበል ከተደረገለት በኋላ ታሪካዊ በሆኑት ናጃፍ እና ካርባላ ከተሞች የሕዝብ የሽኝት ሰልፍ ይካሄዳል። በመጨረሻም በሐምሌ 9 ቀን አስከሬኑ ወደ ኢራን ተመልሶ በኻሜኒ የትውልድ ስፍራ እና የሺዓ እስልምና እጅግ የተቀደሰ ከተማ በሆነችው መሻድ በሚገኘው የኢማም ሬዛ መቅደስ የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ይፈጸማል ሲል አልጄዚራ ዘግቧል። ሳራ ዮሐንስ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

photo content

በታክስ አስተዳደር ለውጦች፣ ተግዳሮቶችና መልካም ተሞክሮዎች ላይ ያተኮረ  መድረክ ተካሄደ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) ከዓለም አቀፉ የግል ኢንተርፕራይዝ ማዕከል (ሳይፕ) ጋር በመተባበር 5ኛውን የመንግስትና የግሉ ዘርፍ የጋራ የምክክር መድረክ አካሄደ። በታክስ አስተዳደር ለውጦች፣ ተግዳሮቶችና መልካም ተሞክሮዎች ላይ ያተኮረው ይህ መድረክ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የገቢዎች ቢሮ አመራሮችን ጨምሮ የንግዱን ማህበረሰብ አባላት አሳትፏል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ቢሯቸው አገልግሎቱን ለማዘመን እየሰራ መሆኑን ገልጸው፣ የግሉ ዘርፍ የሚያነሳቸውን የግብር ቅሬታዎች ከአዲስ ቻምበር ጋር በተደራጀ መልኩ እየፈቱ መሆኑን ጠቅሰዋል። የአዲስ ቻምበር ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ዘሐራ መሐመድ በበኩላቸው፣ ጠንካራ ማክሮ ኢኮኖሚ ለመገንባት ፍትሐዊ፣ ቀልጣፋና ሊተነበይ የሚችል የግብር ሥርዓት መኖር ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል። በውይይቱ ወቅት ተሻሽሎ በወጣው የገቢ ግብር አዋጅ ላይ ድርጅቶች ቢከስሩ እንኳ ከዓመታዊ ሽያጫቸው 2.5 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ የሚደነግገው ሕግና የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ታክስ ከፋዮች የቅድሚያ ክፍያ ሥርዓት በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ጫና እየፈጠረ መሆኑ እንደ ስጋት ተነስቷል። አዲስ ቻምበር በመድረኩ የተነሱትን ተግዳሮቶች በዝርዝር አጠናቅሮ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እንደሚያቀርብ አስታውቋል። ሐመረ ፍሬው ሰኔ 25/2018 ዓ.ም

photo content
+3

ለምክክር ጉባኤዉ የቀረቡ አጀንዳዎች ላይ የተበታተኑ የሚመስሉ ይዘቶችን ኮሚሽኑ በድጋሜ ሊያያቸዉ ይገባል ተባለ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮምሽን ሀምሌ ስምንት በሚያካሂደው ጉባኤ ዙሪያ በምክክር ወቅት ሙያዊ ማብራሪያ ከሚያቀርቡት ባለሙያዎች ጋር በዛሬዉ ዕለት ዉይይት አካሂዷል። ኮሚሽኑ ለጉባኤዉ የመረጣቸዉ አጀንዳዎች ይፋ ከመሆናቸዉ አስቀድሞ በአጀንዳዎቹ ዙሪያ ከባለሙያዎች ጋር ዉይይት ማድረግ ነበረበት የሚል ሀሳብ በዚህ ዉይይት  ተንፀባርቋል። ኮሚሽኑ ለጉባኤው ስምንት ያህል አጀንዳዎች እንደሚቀርቡ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን፥ እነዚህ የምክክር አጀንዳዎች ዙሪያ ባለሙያዎቹ ሀሳባቸውን ተናግረዋል። ከዚህ ዉስጥ የሆኑት ዶ/ር የማርሸት ታደሰ  አንዳንድ አጀንዳዎች የተበታተኑ የሚመስሉ ሆነዉ እንደሚታዩ ተናግረዋል። በእነዚህ አጀንዳዎች ዉስጥ ያሉ የተጠያቂነት፣የእርቅ እና የይቅርታ ይዘት ያላቸዉ ጉዳዩች የተበታተኑ ሆነዋልም ይላሉ። ለማሳያም የአጀንዳ 4፣5 እና 8 ላይ ያሉ ይዘቶችን ጠቅሰዋል። ዶ/ር የማርሸት የተበታተኑ የሚመስሉ አጀንዳዎች በመጨረሻዉ ምክረሀሳብን  ለመፃፍ እንደሚያስቸግር ይገልፃሉ። በዚህም የተበታተኑ ጉዳዮችን ሰብሰብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በዉይይት መድረኩ ሌላዉ ከተሳታፊ ባለሙያዎች የተነሳዉ ጥያቄ በአጀንዳ ሶስት ላይ የተቀመጠዉ የፌደራል ከተሞች ጉዳይን የተመለከተዉ ነዉ። በዚህ የአጀንዳ ክፍል ይዘት የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማን በተናጠል አጀንዳ አድርጎ ማቅረብ ያስፈለገበትን ምክንያት ኮሚሽኑ እንዲያስረዳ ተጠይቋል። ይህ የአጀንዳ ክፍል በአጀንዳ ሁለት ከተቀመጠዉ የመንግስት አወቀቀር ጉዳይ በሚለው አጀንዳ ስር  መካተት የነበረበት እንደሆነም ተነስቷል። የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በዚህ አጀንዳ ክፍል የተነሳዉን የባለሙያዎች ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡም፥በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ጉዳይ ዙሪያ ከህገመንግስት አቀራረፅ እስከ ስልጣን ክፍፍል ጥያቄ የሚነሳበት መሆኑን ገልፀዋል። በእነዚህ ከተሞች ዙሪያ ራሱን የቻለ አጀንዳ አድርጎ ለማስቀመጥ የነበሩ ጥያቄዎችን መሠረት ያደረገ በመሆኑ ራሳቸዉን ችለዉ በአጀንዳነት እንዲቀርቡ ሆኗል ሲሉም ኮሚሽነሮቹ ምላሽ ሰጥተዉበታል። ከዚህ ውጭ በምክክር ወቅት ሙያዊ ማብራሪያ ከሚያቀርቡ ባለሙያዎች ጋር በነበረዉ ዉይይት፥ሙስና እና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች የያዘዉ የአጀንዳ ክፍል በምክክሩ ወቅት ሊኖረዉ ስለሚችለዉ ጭብጥ እና ፋይዳ ተጠይቋል። የመካተቱ አስፈላጊነትም ጥያቄ የተነሳበት እና የሚታይበት ሌላ ሁኔታ ሊኖር እንደሚገባዉ ተነስቷል። ኮሚሽኑ ሙስናን በአጀንዳነት ማካተት ሙስናን የተመለከቱ ህጎች ተፈፃሚነት አነስተኛ የመሆን እና ያሉ ህጎችም በቂ ያለመሆን ነገር በአጀንዳነት ለመቅረቡ እንደምክንያት አቅርቧል። ኮሚሽኑ ለጉባኤዉ የሚሰይመዉ የባለሙያዎች ቡድን ቴክኒካዊ ምክር መስጠት፣ ጥናትና ትንተና ማካሄድ፣ የመነሻ ሰነዶችን ማዘጋጀት፣ ውስብስብ ፅንሰ ሀሳቦችን በቀላሉ ማብራራት የምክክር ቡድኖችን መደገፍ፣ እንዲሁም የመጨረሻ ምክረ ሐሳቦችን ማዘጋጀት የሚጠበቅበት ይሆናልም ተብሏል። ቁምነገር አየለ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም

photo content
+1

ገዳ ባንክ 1 ቢሊየን ብር በማትረፍ አጠቃላይ ሀብቱ 16.6 ቢሊየን ብር መድረሱን ገለፀ የገዳ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ወልዴ ቡልቱ ባንኩ በ2018 የበጀት ዓመት ያስመዘገበውን የሥራ አፈጻጸም ይፋ ባደ
+2
ገዳ ባንክ 1 ቢሊየን ብር  በማትረፍ አጠቃላይ ሀብቱ 16.6 ቢሊየን ብር መድረሱን ገለፀ የገዳ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ወልዴ ቡልቱ ባንኩ በ2018 የበጀት ዓመት ያስመዘገበውን የሥራ አፈጻጸም ይፋ ባደረጉበት ወቅት፥ባንኩ በበጀት ዓመቱ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከሁለት እጥፍ በላይ ወይም የ1መቶ13 በመቶ ዕድገት በማሳየት ከታክስ በፊት 1 ቢሊየን ብር ማትረፍ መቻሉን አስታውቀዋል። እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለፃ የባንኩ አጠቃላይ ሀብት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ64 በመቶ ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ 16.6 ቢሊየን ብር ደርሷል። በተመሳሳይ ሁኔታ የደንበኞች የተቀማጭ ሀብት በ64 በመቶ በማደግ 12.64 ቢሊየን ብር መድረስ ችሏል። ባንኩ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የቅርንጫፎቹን ቁጥር 1መቶ10 ማድረሱ የተገለፀ ሲሆን፥ ከነዚህም መካከል 10 ያህሉ ቅርንጫፎች በዘንድሮው የበጀት ዓመት የተከፈቱ  መሆናቸው ተጠቁሟል:: በተጨማሪም የባንኩን ዘላቂ ዕድገትና ጥንካሬ የሚያበስረው የዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ ግንባታ ሒደት በይፋ መጀመሩን አቶ ወልዴ ቡልቱ አንስተዋል። ባንኩ አሁን ላይ ለአምስት ዓመታት የሚያገለግሉ ስትራቴጂዎችን ቀርጾ ማጽደቅ ችሏል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፥እነዚህ ስትራቴጂዎች በተለይም የባንኩን የውስጥና የቴክኖሎጂ ደህንነት ማጠናከር ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ገዳ ባንክ "የአዲሱ ትውልድ ባንክ" በሚለው መሪ ቃሉ መሰረት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎትን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በማስፋፋት በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ የገበያ ድርሻ መያዝ መቻሉን በተግባር እንዳሳየም አንስተዋል። ሀና ሰይፉ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም

ናይጀሪያ ዜጎቼ ላጡት ንብረት ካሳ እፈልጋለሁ አለች ናይጄሪያ ሕገ ወጥ ስደተኞችን ያነጣጠሩ የቅርብ ጊዜ ተቃውሞዎችን ተከትሎ አገሪቱን ለቀው ለወጡ ዜጎቿ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካሳ እንደምትጠይቅ
+1
ናይጀሪያ  ዜጎቼ  ላጡት ንብረት ካሳ እፈልጋለሁ አለች ናይጄሪያ ሕገ ወጥ ስደተኞችን ያነጣጠሩ የቅርብ ጊዜ ተቃውሞዎችን ተከትሎ አገሪቱን ለቀው ለወጡ ዜጎቿ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካሳ እንደምትጠይቅ  አስታውቃለች። የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኪሚኢቢ ኢሞሞቲሚ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፥ ይህ ጉዳይ በሁለቱ መንግሥታት መካከል በከፍተኛ ደረጃ ውይይት ይደረግበታል ብለዋል። በደቡብ አፍሪካ የናይጄሪያ ጊዜያዊ ከፍተኛ ኮሚሽነር አሌክሳንደር አጃዪ መንግሥት በናይጄሪያውያን የተተዉ የንግድ ተቋማትን እና ንብረቶችን መመዝገብ ጀምሯል ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ከ600 በላይ ናይጄሪያውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት ወደ አገራቸው የሄዱ ሰዎች በአገሪቱ ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ ይኖሩ የነበሩ ናቸው ቢሉም ናይጄሪያ ግን ነገሩን አስተባብላለች። አንዳንድ ስደተኞችን የሚቃወሙ ቡድኖች ሕገ ወጥ የውጭ አገር ዜጎችን የሚቃወሙ ሰልፎች በቀጣይ ሳምንታት እንደሚቀጥሉ የተናገሩ ሲሆን፥ ማክሰኞ ዕለትም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት ሰልፍ ተደርጎ ነበር። ሰልፎቹ በአብዛኛው ሰላማዊ የነበሩ ቢሆንም በውጭ አገር ዜጎች ላይ የተነጣጠሩ የተናጠል የጥቃት ክስተቶች ታይተዋል ሲል ቢቢሲ አክሎ አስነብቧል። ሀናን ሽምሱ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም

ናይጀሪያ ዜጎቼ ላጡት ንብረት ካሳ እፈልጋለሁ አለች ናይጄሪያ ሕገ ወጥ ስደተኞችን ያነጣጠሩ የቅርብ ጊዜ ተቃውሞዎችን ተከትሎ አገሪቱን ለቀው ለወጡ ዜጎቿ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካሳ እንደምትጠይቅ
+1
ናይጀሪያ  ዜጎቼ  ላጡት ንብረት ካሳ እፈልጋለሁ አለች ናይጄሪያ ሕገ ወጥ ስደተኞችን ያነጣጠሩ የቅርብ ጊዜ ተቃውሞዎችን ተከትሎ አገሪቱን ለቀው ለወጡ ዜጎቿ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካሳ እንደምትጠይቅ  አስታውቃለች። የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኪሚኢቢ ኢሞሞቲሚ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፥ ይህ ጉዳይ በሁለቱ መንግሥታት መካከል በከፍተኛ ደረጃ ውይይት ይደረግበታል ብለዋል። በደቡብ አፍሪካ የናይጄሪያ ጊዜያዊ ከፍተኛ ኮሚሽነር አሌክሳንደር አጃዪ መንግሥት በናይጄሪያውያን የተተዉ የንግድ ተቋማትን እና ንብረቶችን መመዝገብ ጀምሯል ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ከ600 በላይ ናይጄሪያውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት ወደ አገራቸው የሄዱ ሰዎች በአገሪቱ ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ ይኖሩ የነበሩ ናቸው ቢሉም ናይጄሪያ ግን ነገሩን አስተባብላለች። አንዳንድ ስደተኞችን የሚቃወሙ ቡድኖች ሕገ ወጥ የውጭ አገር ዜጎችን የሚቃወሙ ሰልፎች በቀጣይ ሳምንታት እንደሚቀጥሉ የተናገሩ ሲሆን፥ ማክሰኞ ዕለትም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት ሰልፍ ተደርጎ ነበር። ሰልፎቹ በአብዛኛው ሰላማዊ የነበሩ ቢሆንም በውጭ አገር ዜጎች ላይ የተነጣጠሩ የተናጠል የጥቃት ክስተቶች ታይተዋል ሲል ቢቢሲ አክሎ አስነብቧል። ሀናን ሽምሱ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም