ar
Feedback
Ethio Fm 107.8

Ethio Fm 107.8

الذهاب إلى القناة على Telegram

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethio Fm 107.8

تُعد قناة Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 18 485 مشتركاً، محتلاً المرتبة 12 078 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 1 847 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 18 485 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 31 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -10، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -7، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 9.92‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 7.42‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 1 835 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 371 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 3.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 01 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.

18 485
المشتركون
-724 ساعات
-87 أيام
-1030 أيام
أرشيف المشاركات
በመዲናዋ ብቃታቸው የተረጋገጠ ከ4 መቶ በላይ ስፔሻላይዝድ የጥርስ ህክምና ተቋማት መኖራቸው ተገለፀ ‎ ‎የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በከተማዋ 4መቶ2 ብቃታቸው የተረጋገጠ ስፔሻላይዝድ የጥርስ ህክምና ተቋማት መኖራቸውን አስታውቋል። ‎ ‎ባለስልጣኑ የሚቆጣጠራቸውን እነዚህን ተቋማት እውቅና ለመስጠት መዘጋጀቱንም ገልጿል። ‎ ‎ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከሮቫ ኤቨንትስ እና መልቲሚዲያ ጋር በመተባበር በጥርስ ሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ የላቀ ሥራ ላከናወኑ የጥርስ ሕክምና ተቋማትና ባለሙያዎች ያዘጋጀውን የእውቅና እና የሽልማት መድረክ ይፋ አድርጓል። ‎ ‎ፕሮግራሙ በታካሚ እንክብካቤ፣ በክሊኒካዊ ብቃት፣ በንጽህና እና በማህበረሰብ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ በማሳደር ረገድ የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ተቋማትን እውቅና መስጠትን ግብ ያደረገ ነው። ‎ ‎ፕሮግራሙ እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሰፊ ሀገራዊ ፋይዳ እንዳለው ‎ ተነስቷል። ‎ ‎የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሉእመቤት ታደሰ፥ የዕውቅናው አላማ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ የጥርስ ሕክምና ማዕከላት እንዲስፋፉ ማድረግ እንደሆነ አንስተዋል። ‎ ‎15 የዕውቅና መስፈርቶች መኖራቸው የተገለፀ ሲሆን፥ ተቋማቱ ከአንድ በላይ በሆኑ መስፈርቶች መወዳደር እንደሚችሉ ተነስቷል። ‎ ‎ለዚህ ሲባል የተዘጋጀ ዌብሳይት መኖሩም ተገልጿል። ‎ ‎የዕውቅና ሽልማቱ 70 በመቶ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ግምገማ እና 30 በመቶ በህዝብ ድምፅ እና ምርጫ የሚደረግ ይሆናል። ‎ ‎በየዓመቱ ደረጃውን እና ፕሮፌሽናሊዝምን በጠበቀ መልኩ የሚከናወን መርሀ ግብር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ‎ ‎ሽልማቱ በጥቅምት 2019 የሚካሄድ መሆኑም ተገልጿል። ‎ ‎እስከዳር ግርማ ‎ ‎ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

photo content
+1

ከ3.7 ሚሊዮን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት ለዘመን መለወጫ በአል እንደሚቀርብ  የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተናገረ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ  የመጪዉ የአዲስ አመት በአል አስመልክቶ የበዓሉን የገበያ አቅርቦትና የንግድ እንቅስቃሴ ዝግጅት ዙሪያ በዛሬዉ እለት መግለጫ ሰጥቷል። የቢሮዉ ሃላፊ ወ/ሮ  ሀቢባ ሲራጅ  አዲስ ዓመት በዓል በማስመልከት የሚፈጠረውን የኅብረተሰብ ከፍተኛ የመሰረታዊ ፍጆታ ምርቶች ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችል ሰፊ የዝግጅት፣ የአቅርቦትና የቁጥጥር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በበአሉ ከቄራ እንስሳት አቅርቦት ጋር በተያያዘ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዶሮዎች እና  ከ42.7 ሚሊዮን በላይ እንቁላል ለገበያ እንደሚቀርቡ ተጠቅሷል። ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ በግና ፍየል እንዲሁም 62 ሺህ 600 ደረቅ ከብቶች ለበዓሉ ገበያ እንደሚቀርቡ የከተማዋ ንግድ ቢሮ ተናግሯል። ለበዓሉ ገበያ 
7መቶ 8ሺህ 266 ኩንታል ቀይ ሽንኩርት
እንደሚቀርብ የተናገሩት የቢሮዉ ሀላፊ ሀቢባ ሲራጅ  ፤ 227 ሺህ 8 መቶ 85 ኩንታል የጤፍ ምርት ለማቅረብ መታቀዱን በመግለጫቸው ገልፀዋል። ከ3.7 ሚሊዮን ሊትር በላይ ፈሳሽ የምግብ ዘይት ለኅብረተሰቡ ለማቅረብ ዝግጅት መጠናቀቁን የቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሃላፊ ሀቢባ ሲራጅ ተናግረዋል። ለህብረተሰቡ በጥራትና በበቂ ሁኔታ ለማዳረስ ሲባል  የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የፋብሪካ ምርቶች መሸጫ ማዕከላት አገልግሎቱ እንዲሰጡ ይደረጋል ተብሏል። 5 የቀንድ እንስሳት መሸጫ ማዕከላት እና 2መቶ 64 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በሳምንቱ ሙሉ ክፍት ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ መወሰኑን ሀላፊዋ ጠቁመዋል። ሊዲያ ደሳለኝ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

photo content

በኔፓል የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,000 በላይ መድረሱ ተገለጸ በኔፓል በተከሰተው ከባድ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 1,003 መድረሱን የአገሪቱ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣን አስታወቀዋል። ባ
በኔፓል የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,000 በላይ መድረሱ ተገለጸ በኔፓል በተከሰተው ከባድ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 1,003 መድረሱን የአገሪቱ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣን አስታወቀዋል። ባለስልጣኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ከሟቾቹ በተጨማሪ በርካታ ሰዎች የደረሱበት ያልታወቀ ሲሆን፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የነፍስ አድን ሰራተኞች አሁንም አስከሬኖችን ፍለጋ እና በጎርፍ የተከበቡ ሰዎችን የማውጣት ስራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል። በጎርፉ ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ በመሰረተ ልማቶችና በመኖሪያ ቤቶች ላይም ከፍተኛ ውድመት መድረሱ ተገልጿል። የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣኑ የሟቾች ቁጥር አሁንም ሊጨምር እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል። ልዑል ወልዴ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚታየውን የሪፖርት መዛባት የሚቀርፍ አዲስ ስታንዳርድ ይፋ ሆነ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኮንስትራክሽን ማናጅመንት ኢንስቲትዩት እና የሚድሮክ ኮንሰልቲንግ አርክቴ
+3
በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚታየውን የሪፖርት መዛባት የሚቀርፍ አዲስ ስታንዳርድ ይፋ ሆነ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኮንስትራክሽን ማናጅመንት ኢንስቲትዩት እና የሚድሮክ ኮንሰልቲንግ አርክቴክትስና ኢንጅነርስ በመተባበር ያዘጋጁት አዲስ የግንባታ ፊዚካል አፈጻጸም መለኪያና የሪፖርት ማዕቀፍ ስታንዳርድ ይፋ ተደርጓል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ እስካሁን በዘርፉ ወጥ የሆነ የግንባታ አፈጻጸም መለኪያ ባለመኖሩ ምክንያት ፕሮጀክቶችን በጊዜ፣ በወጪና በጥራት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ ቆይቷል። ይህ አዲስ ስታንዳርድ "ትክክለኛ መረጃ፣ ትክክለኛ መለኪያ፣ ተዓማኒነት ያለው ሪፖርት እና ትክክለኛ ውሳኔ" የሚለውን የሥራ ሰንሰለት በተግባር ለማዋል ያለመ ነው ተብሏል። በተለይም በተለያዩ ተቋማትና ፕሮጀክቶች መካከል የሚታየውን የሪፖርት አለመጣጣም በመቅረፍ፣ የግንባታ አፈጻጸም ግምገማን ግልጽና ተነጻጻሪ ለማድረግ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው ተጠቁሟል። በዝግጅቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የክልልና የፌዴራል የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።   አዲስዓለም አበበ   ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

የሮቦት ማፅጃ ካሜራን በመጠቀም ሚስጥራዊ ምስል የቀረፀው የታይዋን ዜጋ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣ ​አንድ የታይዋን ዜጋ የባለቤቱን ሌላ የፍቅር ግንኙነት በሮቦት የቤት ማፅጃ ካሜራ አማካኝነት ያለፍቃ
+2
የሮቦት ማፅጃ ካሜራን በመጠቀም ሚስጥራዊ ምስል የቀረፀው የታይዋን ዜጋ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣ ​አንድ የታይዋን ዜጋ የባለቤቱን ሌላ የፍቅር ግንኙነት በሮቦት የቤት ማፅጃ ካሜራ አማካኝነት ያለፍቃዷ ቀርፆ በመያዙ በአምስት ወር የእስራት ፍርድ እና በ150,000 የታይዋን ዶላር መቀጮ ተቀጥቷል። ​ግለሰቡ በ2023 በሁለተኛ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በተፈጠረ ጥርጣሬ ተነሳስቶ፣ በሞባይል መተግበሪያ የቤቱን ሮቦት ማፅጃ በርቀት በማስነሳት ባለቤቱ ከሌላ ወንድ ጋር ሆና በካሜራ ይዟታል። ባል ምስሉን ለቀጣይ የሕግ ክስ እንደ ማስረጃ ለመጠቀም በማሰብ መቅረፁን የቀጠለ ሲሆን፣ በቪዲዮው ታግዞም ለደረሰበት የሞራል ጉዳት ከባለቤቱና ከፍቅር አጋሯ 500,000 የታይዋን ዶላር ካሳ አግኝቷል። ሆኖም ግን፣ ስኬቱ ባለቤቱ ባቀረበችበት የመልስ ክስ ምክንያት ጥላ ያረፈበት ሆኗል። በሮቦት ማፅጃው የተቀረፀው የቪዲዮ ማስረጃ የባለቤቱን አለመታመን ያረጋገጠ ቢሆንም፣ ሁለቱን ፍቅረኞች ያለፍቃዳቸው መቅረፁንም አረጋግጧል። ባል ድርጊቱ ተገቢ እንደነበር ቢከራከርም፣ ፍርድ ቤቱ ግን የጋብቻ ግዴታዎች የሰዎችን የግል ሕይወት የመጠበቅ መብት አያልፉም በማለት ውድቅ አድርጎታል። በዚህም መሠረት በታይዋን ሕግ የሰዎችን የግል እንቅስቃሴ ያለፍቃዳቸው መቅረፅ ወንጀል በመሆኑ፣ ባል የካሳ አሸናፊ ቢሆንም በወንጀሉ ምክንያት የእስራትና የገንዘብ መቀጮ ፍርድ ተፈርዶበታል።   ሐመረ ፍሬው   ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

በሶሪያ ሱዌዳ ግዛት በተቀሰቀሰ ግጭት 10 የመንግስት የጸጥታ አባላት ቆሰሉ በደቡባዊ ሶሪያ፣ አብዛኛው ነዋሪ የድሩዝ ማህበረሰብ በሆነባት ሱዌዳ ግዛት፣ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በአካባቢው ታጣ
በሶሪያ ሱዌዳ ግዛት በተቀሰቀሰ ግጭት 10 የመንግስት የጸጥታ አባላት ቆሰሉ በደቡባዊ ሶሪያ፣ አብዛኛው ነዋሪ የድሩዝ ማህበረሰብ በሆነባት ሱዌዳ ግዛት፣ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በአካባቢው ታጣቂ ቡድኖች መካከል ግጭት መከሰቱ ተነግሯል ። የሶሪያ የመንግስት መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ፣ በዚህ ግጭት 10 የመንግስት የጸጥታ አባላት ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሷል። ግጭቱ የተቀሰቀሰው በጸጥታ ኃይሎች እና በአካባቢው ባሉ ታጣቂዎች መካከል በነበረ የቃላት ምልልስ እና አለመግባባት እንደሆነ ተገልጿል። የሱዌዳ ግዛት ለዓመታት ከመንግስት ጋር በተያያዘ በተቃውሞዎች እና አልፎ አልፎ በሚከሰቱ ግጭቶች የምትታወቅ ሲሆን፣ የዛሬው ግጭትም በቀጠናው ያለውን ውጥረት ዳግም እንዳባባሰው ተዘግቧል። ስለ ታጣቂዎቹ ጉዳት እስካሁን የተገለጸ መረጃ የለም።   ልዑል ወልዴ   ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

በኔፓል በጭቃ በተሞሉ ዋሻዎች ዉስጥ ይገኛሉ የተባሉ ከ6መቶ በላይ ሠራተኞችን ለማዳን አደገኛ የፍለጋ ሥራ እየተከናወነ ነው በኔፓል ትሪሹሊ ወንዝ ዳርቻ በተቆፈሩ እና በጭቃ በተሞሉ ረጅም ዋሻዎች ውስጥ ተቀርቅረዋል ተብለው የሚገመቱ ከ600 በላይ ሠራተኞች፤ ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በሕይወት ይገኛሉ የሚል ተስፋ ሰንቀዋል። የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የተረፉ ሰዎችን ለማዳን ያለው ወሳኝ ጊዜ እያለቀ ነው ከሚል ስጋት በመነሳት ወደ ትሪሹሊ-3ኤ ፕሮጀክት ቦታ አዉሮፕላን ለማስገባትና መንገድ ለመክፈት ኮረብታውን በፈንጂ በማፈንዳት የሕይወት አድን ጥረታቸውን ቀጥለዋል። በኔፓል እና ቲቤት ድንበር ላይ በደረሰው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 9መቶ39 መድረሱን የሀገሪቱ የአደጋ ስጋት አመራር ባለስልጣን አስታውቋል። መሥሪያ ቤቱ የጠፉ ሰዎች ቁጥር 3ሺ9መቶ25 መድረሱን የገለጸ ሲሆን፤ከነዚህም መካከል 5መቶ92 ያህሉ የውጭ ሀገር ዜጎች እንደሆኑ አሳውቋል። የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስትር ባሌንድራ ሻህ እንደተናገሩት፤ በሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች ውስጥ ይሠሩ ከነበሩ ሠራተኞች መካከል 2 መቶ79 ሰዎች መዳናቸውን ገልጸዋል። የማዳን ሥራው በቻይና እና ኔፓል ወታደራዊ አባላት በተቋቋመ ዓለም አቀፍ ቡድን እየተመራ የሚገኝ ሲሆን፤በተጨማሪም የሕንድ፣ የኮሪያ እና የአውስትራሊያ ባለሙያዎች በሥራው ላይ በመሳተፍ ላይ ናቸው። ነገር ግን ከነፍስ አድን ሰራተኞች መካከል አንድ ቡድን ሰኞ ዕለት ማለዳ ወደ አንዱ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ በሚወስደው ዋሻ ውስጥ መግባት የቻለ ቢሆንም ምንም ሰው ሳያገኝ ተመልሷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት፤ የሕይወት አድን ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አንስተዉ፤ በሀገሪቱ ጎርፉ ‹‹የተለመደ›› ክስተት አለመሆኑንም ጠቁመው፤ ይህ አጋጣሚ በሂማላያ ክልል ውስጥ የሚገጥሙን አደጋዎች ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ እየጨመሩ መሆናቸውን ያሳያል ብለዋል። ሀና ሰይፉ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

photo content
+1

ቴህራን በቂ የውጭ ምንዛሬ አላት ሲሉ የኢራን ማዕከላዊ ባንክ ገዢ ለትራምፕ ተናገሩ ማዕከላዊ ባንኩ 2 ቢሊየን ዶላር ወደ ምንዛሬ ገበያው ለማስገባት ዝግጁ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ምንም እንኳን የአሜሪካ ማዕቀብ እና የኢኮኖሚ ጫና ቢበረታም፤ኢራን በቂ የውጭ ምንዛሬ እንዳላት የማዕከላዊ ባንክ ገዢ አብዱልናስር ሄማቲ ተናግረዋል። ተስኒም የዜና ወኪል እንደዘገበው፤ማዕከላዊ ባንኩ 2 ቢሊየን ዶላር ወደ ውጭ ምንዛሬ ገበያው ለማስገባት ዝግጁ ነው። የአሜሪካን የኢኮኖሚ ውድቀት ክስ ውድቅ ያደረጉት ሄማቲ፤ኢራን የውጭ ምንዛሬ ገቢዎችን እና ተከፋይ ሂሳቦችን መሰብሰቧን እንደቀጠለች ገልጸው፤ዝርዝራቸው ሊገለጽ የማይችል የአገር ውስጥ ክምችትና ሌሎች ሀብቶች እንዳሏትም ተናግረዋል። የአገሪቱ የኢኮኖሚ ሥርዓት በአዲሱ ማዕቀብ ውስጥም መስራቱን እንደቀጠለ የገለጹት ሄማቲ፤የሪያል ዋጋ በቅርቡ መውረድ በአብዛኛው ከሥነ-ልቦናዊ ሁኔታዎች ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢራን ወደ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ውስጥ ገብታለች የሚለውን ሀሳብ ውድቅ በማድረግ፤ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እና ሰፊ የኢኮኖሚ ጫና ቢኖርም ይህ የመከሰቱ ዕድል አነስተኛ መሆኑን ተናግረዋል። በጦርነቱ እና በአንዳንድ መሰረተ ልማቶች ላይ በደረሰው ውድመት ምክንያት የስራ አጥነት ቁጥር መጨመሩን ያመኑት ሄማቲ፤በሁለተኛው የኢራን ዓመት አጋማሽ ላይ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ንግዶች የፋይናንስ ድጋፍ ቅድሚያ እንደሚሰጥ አክለዋል። እነዚህ አስተያየቶች የተሰጡት የኢራን ሪያል ከአሜሪካ ዶላር ጋር ባለው ዋጋ ላይ አዲስ ተጽዕኖ እየገጠመው ባለበት እና በአሜሪካ-እስራኤል ጦርነት የኢኮኖሚ መዘዝ እንዲሁም በጠነከረው የአሜሪካ ማዕቀብ ወቅት ነው። ዋሽንግተን በቅርቡ በቴህራን ላይ የምታደርገውን የኢኮኖሚ ጫና ዘመቻ ያሰፋች ሲሆን፤ ዋና ዋና የኢራን ገቢ ምንጮችን እና ዓለም አቀፍ ንግድን ኢላማ አድርጋለች። ኢራን እና አሜሪካ በሰኔ ወር ጦርነቱን ለማቆም ያለመ ባለ 14 ነጥብ የመግባቢያ ስምምነት ቢፈራረሙም፤ ጊዜያዊ ስምምነቱ ግን በፍጥነት መፍረሱ ይታወሳል። ሀና ሰይፉ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

photo content

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ውጥረት በማገርሸቱ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ ከሳምንታት አንጻራዊ ሰላም በኋላ፤ በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የተጀመረው አዲስ ወታደራዊ ፍጥጫ በመካከለኛ
+1
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ውጥረት በማገርሸቱ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ ከሳምንታት አንጻራዊ ሰላም በኋላ፤ በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የተጀመረው አዲስ ወታደራዊ ፍጥጫ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ስጋት ዳግም ቀስቅሶታል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ኢራን በድርጊቷ የምትቀጥል ከሆነ ‹‹በከባድ ሁኔታ›› እንደሚያጠቋት መዛታቸውን ተከትሎ፤በዛሬው ዕለት በዓለም አቀፍ ገበያ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተቀሰቀሰው ወታደራዊ ፍጥጫ እና የቃላት ምልልስ፤ሁኔታው ወደ ሰፊ ቀጣናዊ ጦርነት ሊያመራ ይችላል የሚል ስጋት በኢንቨስተሮች ዘንድ እንዲፈጠር አድርጓል። በዚህም ምክንያት የነዳጅ ዋጋ ዛሬም ጭማሪው ቀጥሏል፡፡ የነዳጅ ገበያ ተንታኞች እንደሚሉት ከሆነ፤በመካከለኛው ምስራቅ ያለው አለመረጋጋት በቀጠለ ቁጥር የነዳጅ አቅርቦት ላይ መስተጓጎል ሊፈጠር ይችላል የሚለው ስጋት የዋጋ ግሽበትን ሊያባብሰው ይችላል። ልዑል ወልዴ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በኢንተርፕራይዝ ልማት በኩል 2መቶ95 ቢሊየን ብር የገበያ ትስስር መፈጠሩን ገለፀ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የዘርፉን የአምስት ዓመታት የልማትና የሪፎርም ጉዞን የሚገመግምበት
+1
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በኢንተርፕራይዝ ልማት በኩል 2መቶ95 ቢሊየን ብር የገበያ ትስስር መፈጠሩን ገለፀ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የዘርፉን የአምስት ዓመታት የልማትና የሪፎርም ጉዞን የሚገመግምበት እና የቀጣይ የልማት ዘመን አቅጣጫዎችን የሚያስቀጥበት ሀገር አቀፍ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈርያት ካሚል፤ 1መቶ66 ቢሊየን ብር የመንግሥት የብድር ድጋፍ ለኢንተርፕራይዞች መቅረቡን እና 6መቶ23 ሺህ 26 ሄክታር መሬት ለኢንተርፕራይዞች እንዲዘጋጅ መደረጉን አብራርተዋል። ወ/ሮ ሙፈሪያት ከ2014 እስከ 2018 ዓ.ም ድረስ በሀገር ውስጥ 19 ሚሊየን 40 ሺህ 6መቶ39 የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውን ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት በኩልም 1 ሚሊየን 6መቶ60 ሺህ 9መቶ81 ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረጉን ሚኒስትሯ አስረድተዋል። በክህሎት ልማት ዘርፍ ደግሞ ከ20 ሚሊየን በላይ ዜጎች በአጭር ጊዜ ሥልጠና መሳተፋቸውን ገልጸዋል። ሊዲያ ደሳለኝ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

ዘለንስኪ ፑቲን ‹‹በግል›› ተጨማሪ ጦርነት ይፈልጋሉ ሲሉ ከሰሱ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት አብዛኛው የሩሲያ ማህበረሰብ ጦርነቱ አሁን እንዲቆም ይስማማል፡፡ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለ
ዘለንስኪ ፑቲን ‹‹በግል›› ተጨማሪ ጦርነት ይፈልጋሉ ሲሉ ከሰሱ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት አብዛኛው የሩሲያ ማህበረሰብ ጦርነቱ አሁን እንዲቆም ይስማማል፡፡ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ እንደተናገሩት፤ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በሁለቱ ሀገራት መካከል አምስተኛ ዓመቱን የያዘውን ጦርነት ለመቀጠል ‹‹በግላቸው›› ፍላጎት አላቸው። ዘለንስኪ ባስተላለፉት መልዕክት፤አብዛኛው የፑቲን የገዛ ማህበረሰብ ጦርነቱ አሁን ላይ እንዲቆም እንደሚስማማ ገልጸዋል። ለጊዜው ግን በሚያሳዝን ሁኔታ የእኛም ሆነ የአጋሮቻችን መረጃዎች እንዲሁም ከሩሲያ የሚመጡ ምልክቶች ሁሉ እንደሚያመለክቱት የሩሲያው መሪ በግላቸው ተጨማሪ ጦርነት ይፈልጋሉ ብለዋል። ዘለንስኪ አክለውም ከአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ እና የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማች ከሆኑት ጃሬድ ኩሽነር ጋር በስልክ መነጋገራቸውን ገልጸዋል። ውይይቱም ከሩሲያ ወገን ጋር ስለሚደረግ ስብሰባ እና ተጨማሪ ግንኙነት ዝግጅት፤ እንዲሁም ወደ ዩክሬን ሊያደርጉት ስለሚችሉት ጉብኝት የሚመለከት ነበር። ሩሲያ ጦርነቱን ወደ ማቆም እንድትመጣ ምን መደረግ እንዳለበት ተወያይተናል ብለዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ተወካዮች ምን ማሳካት እንደሚችሉ እናያለን። መስከረም ወር ብዙ ነገሮችን ሊለውጥ ይችላል ሲሉ አክለዋል። እስከዳር ግርማ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 500 አዳዲስ የኤሌክትሪክ አዉቶብሶችን ሊያስገባ ነዉ። ከኢትዮ ኤፍኤም ጋር ቆይታ ያደረጉት የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 500 አዳዲስ የኤሌክትሪክ አዉቶብሶችን ሊያስገባ ነዉ። ከኢትዮ ኤፍኤም ጋር ቆይታ ያደረጉት የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው፤የከተማዋን የትራንስፖርት ዘርፍ ወደ ቴክኖሎጂ ለማሸጋገር በተያዘዉ ዕቅድ 5መቶ አዳዲስ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶችን ለመግዛት በሂደት ላይ መሆኑን አስታውቋል። በአሁኑ ወቅት 1መቶ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶች አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ሲሆን፤ እነዚህ ተሽከርካሪዎች በዘመናዊ ካሜራዎችና በጂፒኤስ የተገጠሙ በመሆናቸው ስምሪታቸውን ከመሃል ሆኖ ለመቆጣጠር አመቺ ሆነዋል ብለዋል። ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አውቶቡሶች ከተመደበላቸው መስመር እንዳይወጡና የአገልግሎት ጥራታቸው እንዲጠበቅ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ ነው ተብሏል። አውቶቡሶቹ በውስጣቸው ባላቸው ካሜራ አማካኝነት የአሽከርካሪዎችን ስነ-ምግባርና የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለመጠበቅ የሚያስችል አሰራር ተዘርግቶላቸዋል። የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙ በሰው ኃይል የሚደረገውን ቁጥጥር በማቀላጠፍና የህገ-ወጥ ድርጊቶችን ዕድል በማጥበብ ረገድ ትልቅ ለውጥ እያመጣ ነው። አዲስ አበባ በኤሌክትሪክ ትራንስፖርት አጠቃቀም በአፍሪካ ግንባር ቀደም ከተማ ለመሆን በምታደርገው ጥረት እነዚህ አውቶቡሶች እንደ ትልቅ ምሰሶ እንደሚቆጠሩ ተመልክቷል። ሊዲያ ደሳለኝ ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም

አዲስ አበባ በየዓመቱ 100 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ማቀዷን አሳወቀች አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት ከ496 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶችን መገንባቱን ተገልጿል፡፡ አዲስ ሚዲያ ኔት
አዲስ አበባ በየዓመቱ 100 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ማቀዷን አሳወቀች   አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት ከ496 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶችን መገንባቱን ተገልጿል፡፡   አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ እንደዘገበው ቢሮው በቀጣዮቹ አምስት ዓመታትም በየዓመቱ 100 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ማቀዱን ገልጿል።   "ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑ ሁለገብ የቤት ልማት ሥራዎች ከ496 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶችን መገንባት ተችሏል" ብለዋል የአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ፡፡   ኃላፊዋ እንዳሉት ማኅበራትን በማደራጀት፣ የ40/60 እና የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎችን እንዲሁም የመንግሥት ሠራተኞችንና የተለያዩ ኅብረተሰብ ክፍሎችን በማቀፍ የቤት ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።   ነሐሴ 25 /2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ገቢ በ2018 በጀት ዓመት 11.2 ቢሊዮን ዶላር ደረሰ የመንግስትን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ተከትሎ በ2018 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ስኬት አስመዝግቧል ብሏ
የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ገቢ በ2018 በጀት ዓመት 11.2 ቢሊዮን ዶላር ደረሰ   የመንግስትን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ተከትሎ በ2018 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ስኬት አስመዝግቧል ብሏል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር  ፡፡   ከወጪ ንግድ 11.2 ቢሊዮን ዶላር በማግኘት የዕቅዱን 119 በመቶ ማሳካት ተችሏል።   በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ 9.4 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ የአፈፃፀሙ ውጤት ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በከፍተኛ ደረጃ አድጓል ።   የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር  በማህበራዊ ትስስር ገጹ እንዳጋራው መረጃ የማዕድን ዘርፍ 5.07 ቢሊዮን ዶላር በማስመዝገብ ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ፤ የግብርና ምርቶች 3.83 ቢሊዮን ዶላር፣ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ 493 ሚሊዮን ዶላር፣ እንዲሁም የኤሌክትሪክና ሌሎች ዘርፎች 425 ሚሊዮን ዶላር አስገኝተዋል።   ውጤታማ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ፣ በህገ-ወጥ ንግድ ላይ የተደረገ ጥብቅ ቁጥጥር፣ የዋጋ ተመን ክለሳ እንዲሁም የሎጀስቲክስና የትራንስፖርት መሻሻሎች ለዚህ ታሪካዊ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ አበርክተዋል።   ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም

አሜሪካ እና ኢራን ከሳምንታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ተኩስ ተለዋወጡ የአሜሪካ ኃይሎች በሆርሙዝ ሰርጥ በሚገኘው የላራክ ደሴት ባሉ ሁለት የሮኬት ማስወንጨፊያዎች ላይ ጥቃት ካደረሱ በኋላ ሁለቱ ሀገራት
+1
አሜሪካ እና ኢራን ከሳምንታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ተኩስ ተለዋወጡ የአሜሪካ ኃይሎች በሆርሙዝ ሰርጥ በሚገኘው የላራክ ደሴት ባሉ ሁለት የሮኬት ማስወንጨፊያዎች ላይ ጥቃት ካደረሱ በኋላ ሁለቱ ሀገራት ተኩስ ተለዋውጠዋል። ከሐምሌ መጨረሻ ወዲህ የመጀመሪያው በተባለው የአሜሪካ ጥቃት የሁለት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ሌሎች ሁለት ሰዎች መጎዳታቸውን የኢራን ኢስላማዊ አብዮታዊ ዘብ አስታውቋል፡፡ ቡድኑ «ምላሽ እና ቅጣት» እንደሚኖርም ዝቷል። የዩኤስ ማዕከላዊ ዕዝ ሴንትኮም በሆርሙዝ ሰርጥ ውስጥ የተደቀነን አጣዳፊ ስጋት ለመከላከል በቦምብ አጥማጅ ኃይሎች ላይ የተወሰነ እና ትክክለኛ እርምጃ መውሰዱን ገልጿል። ኢራን በበኩሏ ለዚህ ጥቃት ምላሽ ይሆን ዘንድ በዮርዳኖስ የሚገኙ የዩኤስ ወታደራዊ ቦታዎችን መምታቷን ገልፃለች። በተመሳሳይ የዮርዳኖስ ጦር ሰኞ ማለዳ ስምንት ሚሳዔሎችን ማክሸፉን አስታውቋል። የኢራን መንግሥት ቴሌቪዥን የኢራን ጦር በኤምሬትስ የሚገኝን የአየር ኃይል ጣቢያ በድሮን ኢላማ ማድረጉን ዘግቧል። ነገር ግን የኤምሬትስ የመከላከያ ሚኒስቴር የአል-ሚንሃድ አየር ኃይል ጣቢያ ተመታ የተባለው ዘገባ «መሰረት የሌለው» ነው ብሏል፤ ሆኖም ኤምሬትስ አንድ ድሮን መትታ መጣሏን አረጋግጣለች። ሀና ሰይፉ ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም

የሩሲያ እና የቻይና መሪዎች በሻንጋይ ትብብር ድርጅት ጉባዔ ላይ ሊገናኙ መሆኑ ተገለፀ የሩሲያው ቭላድሚር ፑቲን እና የቻይናው ዢ ጂንፒንግን ጨምሮ ሌሎች መሪዎች ለዓመታዊው የድርጅቱ ጉባኤ በኪርጊስታ
+1
የሩሲያ እና የቻይና መሪዎች በሻንጋይ ትብብር ድርጅት ጉባዔ ላይ ሊገናኙ መሆኑ ተገለፀ የሩሲያው ቭላድሚር ፑቲን እና የቻይናው ዢ ጂንፒንግን ጨምሮ ሌሎች መሪዎች ለዓመታዊው የድርጅቱ ጉባኤ በኪርጊስታን ዋና ከተማ ቢሽኬክ ይሰበሰባሉ። መሪዎቹ ይህንን መድረክ የባለብዙ-ዋልታ ዓለም ራዕያቸውን ለማራመድ እና በምዕራባውያን ላይ የተቀናጀ ግንባር ለማሳየት እንደሚጠቀሙበት ይጠበቃል። ምንም እንኳን የድርጅቱ የምስረታ መግለጫ ቡድኑ በሌሎች አገሮች ላይ ያነጣጠረ ጥምረት አይደለም ቢልም፤ባለፈው ዓመት በተደረገው ስብሰባ ላይ ፑቲን ምዕራባውያንን የዩክሬንን ጦርነት በመቀስቀስ ሲከሱ፣ ዢ ጂንፒንግ ደግሞ በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ያለውን ውጥረት በመጥቀስ የማስፈራራት ድርጊቶችን ኮንነዋል። በዚህ ዓመት ከ10ሩ ቋሚ አባላት በተጨማሪ የሕንድ፣ የፓኪስታን፣ የኢራን እንዲሁም አባል ያልሆነችው የቱርክ መሪዎች በጉባዔው ላይ ይገኛሉ። የኢራኑ ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዜሽኪያን ከፑቲን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት እንደሚያደርጉ የሚጠበቅ ሲሆን፤አገራቸው ከሩሲያ ጋር የጠበቀ ወታደራዊ ግንኙነት እንዲሁም ከቻይና ጋር የኃይል ትስስር አላት። ይህ ስብሰባ የተዘጋጀው የአሜሪካው የገንዘብ ሚኒስትር ስኮት ቤሰንት የቻይናን የ1.2 ትሪሊየን ዶላር ዓለም አቀፍ የንግድ ትርፍ ዘላቂነት የሌለው ሲሉ በኮነኑ ማግስት ነው። ቤሰንት የቻይና ኢኮኖሚ ደካማ በመሆኑ ምርቶቿን ወደ ውጭ ለመላክ እየሞከረች መሆኑን ገልጸው፤የጂ20 አባላት ከቤጂንግ ጋር ያላቸውን የንግድ ውል ድጋሚ እንዲፈትሹ እንደሚያበረታቱ ተናግረዋል። ሳራ ዮሐንስ ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም