Ethio Fm 107.8
前往频道在 Telegram
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
显示更多📈 Telegram 频道 Ethio Fm 107.8 的分析概览
频道 Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 18 514 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 12 315,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 831 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 18 514 名订阅者。
根据 27 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -22,过去 24 小时变化为 5,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 9.37%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.06% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 735 次浏览,首日通常累积 1 307 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 4。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”
凭借高频更新(最新数据采集于 28 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
18 514
订阅者
+524 小时
+187 天
-2230 天
帖子存档
18 514
+1
ቻድ ከዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ለመውጣት ማቀዷን አስታወቀች
ቻድ ከቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ፣ ኒጀር እና ቬንዙዌላ በመቀጠል ፍርድ ቤቱን የመልቀቅ ሂደቱን እንደምትጀምር መግለጿ፣ለዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ሌላው ተጨማሪ ስጋት ሆኗል።
የቻድ መንግሥት ባወጣው መግለጫ፤የፍርድ ቤቱ ውጤታማነት ‹‹ውስን እና ያልተመጣጠነ›› መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤መቀመጫውን በሄግ ያደረገው ተቋም ትኩረቱን በአፍሪካ አገራት ላይ ብቻ ያደርጋል ሲል ከሷል።
መግለጫው ‹‹ፍርድ ቤቱ በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ሰባት ሰዎች ብቻ ሲሆኑ፣ ከእነዚህም መካከል ስድስቱ በአፍሪካ ጉዳዮች ክስ የተመሰረተባቸው ናቸው›› ብሏል።
ይህ የተገለጸዉ፤ቻድ በጎረቤት አገር ሱዳን በሠራዊቱ እና በከፊል ወታደራዊ ኃይሎች መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት ውስጥ እጇ አለበት የሚል ጥርጣሬ ባለበት ወቅት ነው።
ባለፈው ሳምንት የቻድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፌስቡክ ገጽ፣ አሜሪካ ቻድ የICC አባልነቷን ድጋሚ እንድታስብ ግፊት እያደረገችባት መሆኑን አስፍሮ ነበር።
ሆኖም ሚኒስትሩ በኋላ ላይ አሜሪካ ከውሳኔው በስተጀርባ መሆኗን ያስተባበሉ ሲሆን፤ ይልቁንም ቻድ ‹‹ፍርድ ቤቱ በአሁኑ ጊዜ ከሚሠራበት መንገድ ጋር አብራ መጓዝ አልቻለችም›› ሲሉ ተናግረዋል።
ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ግለሰቦችን በጦር ወንጀሎች እና በሰብአዊነት ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች በሕግ ይጠይቃል።
ሀና ሰይፉ
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
18 514
በምክክር ጉባዔው እስካሁን የተወሰነ ነገር የለም - ኮሚሽኑ
እየተካሄደ በሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ እስካሁን የተወሰነ ነገር አለመኖሩን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ የምክከሩን የእስካሁን ሂደት በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በመግለጫቸውም ላለፉት ሁለት ቀናት አራት ሺህ ተሳታፊዎች በጥቃቅን ቡድን ተከፋፍለው(በ50 ቡድን) አስር አስር በመሆን በተሰጣቸው አጀንዳዎች ላይ ሲመክሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡
የመከሩባቸው ጉዳዮችም እየተሰነዱ መሆኑንና ተመካካሪዎች የሚያቀርቧቸው ሃሳቦች በሚገባ እየተሰነዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በመጀመሪያው የምክከር ሂደት(የጥቃቅን ቡድን) ወደ ንዑስ ቡድን ተሻጋግሮ በሚገባ ምክክር እንደሚደረግም ዋና ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል፡፡
በምክክሩ ሁሉም ተመካካሪዎች ሃሳባቸውን በነጻነት እና በግልጽ እያቀረቡ እንደሚገኙ ገልጸው እስካሁን ያለቀና የተወሰነ ነገር አለመኖሩን አብራርተዋል፡፡
ሀሳቦች እየተቀራረቡ ቢሆንም ነገር ግን ውሳኔ የሚቀርብበት ምዕራፍ ላይ ገና አልተደረሰም ሲሉም አስታውቀዋል፡፡
የፊታችን ሰኞ የ2መቶ50ዎቹ (ስልታዊ ቡድን) ምዕራፍ ተጠናቆ ወደ 500ዎቹ እንሸጋገራለን የሚል እምነት እንዳላቸውም ዋና ኮሚሽነሩ ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ጠቁመዋል፡፡
የኮሚሽኑ ዓላማ ሁሉም በእኩልነት እንዲነጋገር መሆኑን ጠቁመውም የምክክሩ ስነ ዘዴ ሁሉም እኩል አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ የሚያስችል መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
18 514
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ትራምፕ ጋር ለመወያየት ዋሽንግተን ገቡ
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በዋይት ሀውስ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር የሚገናኙ ሲሆን፥ በዋናነትም በኢራን ላይ የተከፈተው ጦርነት በአጀንዳነቱ ቀዳሚ ቦታ ይይዛል።
ይህ ጉብኝት ሁለቱ ሀገራት በየካቲት ወር በቴህራን ላይ ጥቃት በመሰንዘር ጦርነቱን ከጀመሩ ወዲህ ኔታንያሁ ከትራምፕ ጋር የሚያደርጉት የመጀመሪያው ውይይት ነው።
በተጨማሪም ጉብኝቱ በዌስት ባንክ የእስራኤል ወረራ እና እስራት በበረታበት እንዲሁም ከሶስት ወራት በኋላ በእስራኤል ምርጫ በሚካሄድበት ወቅት ላይ መሆኑ ትኩረት ስቧል።
የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ኔታንያሁ ለምርጫው የትራምፕን ድጋፍ ለማግኘት እየጣሩ ነው።
ኔታንያሁ ወደ አሜሪካ የመጡት በሐምሌ 11 ቀን በሞቱት የሪፐብሊካን ሴናተር ሊንድሴ ግራሃም የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ለመገኘት ሲሆን፥ የቀብሩ ሥነ-ሥርዓት ከመጀመሩ በፊት ከትራምፕ ጋር ለመወያየት ቀጠሮ ይዘዋል።
በውይይቱም ላይ ከኢራን ጦርነት በተጨማሪ በእስራኤል እና በሊባኖስ መካከል ስላለው ግጭት እንዲሁም የአብርሃም ስምምነትን ስለማስፋፋት እንደሚመክሩ ተገልጿል።
ሆኖም የሁለቱ መሪዎች የውይይት ውጤት ለሕዝብ ይፋ ይደረጋል ተብሎ አይጠበቅም ተብሏል።
ሳራ ዮሐንስ
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
18 514
+1
ዘመን ባንክ አጠቃላይ የሀብቱ መጠን 1መቶ16 ቢሊየን ብር መድረሱን ገለጸ
ባንኩ ከ10 ቢሊየን ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡንም አስታዉቋል
የዘመን ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ እንዬ ቢምር ባደረጉት ንግግር፤ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የላቀ ውጤት መገኘቱን ገልጸው፤ ለዚህ ስኬት ለባንኩ የማኔጅመንት አባላትና ሠራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የባንኩ የተከፈለ ካፒታል ከ14 ቢሊየን ብር በላይ፤ አጠቃላይ ገቢው 17.8 ቢሊየን ብር፣ ጠቅላላ ካፒታሉ 26 ቢሊየን ብር መድረሱን ተነግሯል፡፡
የባንኩ የደንበኞች ተቀማጭ ገንዘብ መጠን ካለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ32 በመቶ አድጎ 85.4 ቢሊየን ብር የደረሰ ሲሆን፤ የውጭ ምንዛሬ ግኝቱ ደግሞ 6መቶ98 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ሆኗል፡፡
ዘመን ባንክ የቅርንጫፎቹን ቁጥር ወደ 1መቶ42 ማሳደጉን አስታዉቋል፡፡
ባንኩ ባለፉት 18 ዓመታት የሥራ አድማሱን በማስፋትና በአንድ ቅርንጫፍ ከሚሰጥ ኮርፖሬት አገልግሎት በመነሳት ቅርንጫፎቹን በማብዛት ለሁሉም ደንበኞቹ ይበልጥ ተደራሽ ሆኗል፡፡
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
18 514
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ1ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተባለ፡፡
በሳምንት ውስጥ በተደረገ 8 ዙር በረራ የተመለሱት 1ሺህ 604 ወንዶችና 1መቶ92 ሴቶች አመት እንዲሁም 38 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ፤ ከተመላሾች መካከል 53 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል ተብሏል።
የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታዉቋል፡፡
በተጨማሪም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት ሄደው የሚመለሱ የፍልሰት ተጎጂዎችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራትን በትብብር እያከናወነ መሆኑን ገልጿል፡፡
ወደፊትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ህብረተሰቡን ለማስገንዘብ፣ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከልና ደህንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።
በአጠቃላይ 1ሺህ 8መቶ 34 ዜጎች ወደ አገር ዉስጥ ተመልሰዋል መባሉን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
18 514
በበጀት አመቱ ከ6መቶ ሺህ በላይ የዲጂታል የነዋሪነት መታወቂያ መስጠት ተችሏል
የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የ2018 በጀት ዓመት ያከናወናቸውን ስራዎች ይፋ አድርጓል፡፡
በበጀት አመቱ ከ6መቶ 43 ሺህ 8መቶ25 ዲጂታል የነዋሪነት መታወቂያ መስጠት ተችሏል ተብሏል
ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ዮሴፍ ንጉሴ እንደገለፁት፤1መቶ96 ሺህ 1መቶ32 ያላገባ አገልግሎት ለመስጠት የተቻለ ሲሆን፤ ካለፈው በጀት አመት ጋር ሲነጻጸር በ22 በመቶ ብልጫ እንደሚያሳይ አንስተዋል።
ኤጀንሲው በየወረዳው የሚገኙ በሚሊየን የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን የወረቀት መዛግብትንና ማህደርን በስካኒንግ ማሽን ወደ ዲጂታል ሰነድ ማስተዳደሪያ ሥርዓት የመቀየር ተግባራት አከናዉኗል።
ኤጀንሲው የገፅ ለገፅ ግንኙነትን በማስቀረት ነዋሪዎች ባሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት ማግኘት የሚችሉበትን መተግበሪያ በማዘጋጀት በዚህ መተግበሪያ አማካኝነት ኦንላይን የልደት ካርድ፣ የነዋሪነት መታወቂያ፣ያላገባ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ 1 ሚሊየን 8መቶ 28 ሺህ 8መቶ 46 ዜጎችን መመዝገብ የተቻለ ሲሆን፤ እስካሁን ድረስ 8 ሚሊየን ዜጎችን በፋይዳ መታወቂያ ለመመዝገብ ተችሏል፡፡
ተቋሙ ብልሹ ተግባራትን እና አደጋዎች በማጋለጥ ተጠያቂነት ለማስፈን የተወሰደ ተጨባጭ እርምጃዎችን በተመለከተ በበጀት ዓመቱ ውስጥ 13 አመራር፣ 78 ፈጻሚ እና 14 ባለጉዳይ በድምሩ 1መቶ5 ሰዎችን ተጠያቂ መደረጉ ተገልጿል፡፡
ሊዲያ ደሳለኝ
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
18 514
+1
አቢሲንያ ባንክ በኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕል ንዋዮች ገበያ (ESX) ዋና መድረክ ላይ በይፋ መመዝገቡን አስታወቀ
የባንኩ መመዝገብ በኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕል ንዋዮች ገበያ የግብይት መድረክ በተካሄደ የደወል መደወል ሥነ-ሥርዓት የተከበረ ሲሆን፤ በሁነቱ ላይ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የአቢሲንያ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድና ከፍተኛ አመራሮች፣ የገበያ ተሳታፊዎች፣ ኢንቨስተሮችና የልማት አጋሮች ተገኝተዋል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕል ንዋዮች ገበያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ጥላሁን እስማኤል፤ባደረጉት ንግግር የባንኩን ገበያውን የተቀላቀለበትን ሁኔታና የሂደቱን ጠቃሚነት አብራርተዋል።
ዶ/ር ጥላሁን በንግግራቸው እንደገለጹት፤ በገበያው ላይ የሚደረግ እያንዳንዱ አዲስ ምዝገባ የሰነደ መዋዕል ንዋዮችን መሠረት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተናግረዋል።
አክለውም የአቢሲንያ ባንክ በገበያው ላይ በይፋ ለመመዝገብ ያደረገው ውሳኔ በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ላይ በተቋማት ዘንድ እየጨመረ የመጣውን እምነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህም የኢትዮጵያ መሪ ኩባንያዎች ከፍተኛ የተቋማዊ አስተዳደር፣ ግልጽነት እና የኢንቨስተሮች ተሳትፎ መርሆዎችን እየተቀበሉ መሆናቸውን እንደሚያመላክት ገልጸዋል።
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ከኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ጋር አብሮ ያደገው አቢሲንያ ባንክ በገበያው በይፋ መመዝገቡ በበለጠ ግልጽነት፣ በተሻለ ተቋማዊ አስተዳደር፣ለባለሃብቶች ባለው ከፍተኛ ተጠያቂነትና ከኢንቨስተሮች ጋር በሰፊው ተሳትፎ ወደሚያደርግበት አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሽጋግረዉም ተገልጿል።
ለዓለም አሰፋ
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
18 514
ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን ከሕፃናት ፓውደር ጋር በተያያዙ የካንሰር ክሶች 5.5 ቢሊየን ዶላር ሊከፍል ነዉ
ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ‹‹ለማህፀን ካንሰር መንስኤ ሆኗል›› ተብሎ የቀረበበትን በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ክሶች ለመፍታት የ5.5 ቢሊየን ዶላር ክፍያ ለመፈጸም ተስማምቷል።
ግዙፉ የመድኃኒት አምራች ኩባንያ ባወጣው መግለጫ፤ ስምምነቱ በፌዴራል እና በግዛት ፍርድ ቤቶች የሚገኙ 69,000 የሚሆኑ ጉዳዮችን የሚሸፍን ሲሆን፣ ስምምነቱ የሚፀናው በክፍለ ግዛት ወይም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ካሉ ከሳሾች መካከል 95 በመቶዎቹ ስምምነቱን ሲቀበሉት ብቻ ይሆናል።
የጆንሰን ኤንድ ጆንሰን የሕግ ጉዳዮች ኃላፊ ኤሪክ ሃስ፤ ስምምነቱ ኩባንያው ‹‹ይህን ጉዳይ በሰላም እንዲዘጋው›› ያስችለዋል ብለዋል።
ከሳሾችን የሚወክሉ ጠበቆችም ስምምነቱን ለአሥር ዓመታት ለዘለቀው የፍርድ ቤት ክርክር ጥሩ መፍትሔ ነው በማለት ተቀብለውታል።
በጥቅምት 2025 የቀረበው የእንግሊዙ ክስ፣ ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን ታልክ የማህፀን ካንሰርን እና ሜሶቴሊዮማን ሊያስከትል እንደሚችል እያወቀ ምርቱን መሸጡን ቀጥሏል ሲል ይከሳል።
ኩባንያው ግን ይህንን ክስ ይክዳል።
ጉዳዩ በአሁኑ ወቅት በእንግሊዝ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እየታየ ይገኛል።
እስከዳር ግርማ
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
18 514
የእስራኤል ጦር በበርካታ የዌስት ባንክ ከተሞች ላይ ጥቃት ሰነዘረ
በዌስት ባንክ ቢያንስ 20 ተጨማሪ ከተሞች ላይ ወረራ የተፈጸመ ሲሆን፣ ቤቶች ፈርሰዋል እንዲሁም በደርዘን የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ታስረዋል ነዉ የተባለዉ።
የእስራኤል ወታደሮች በተያዘችው ዌስት ባንክ እና ምስራቅ እየሩሳሌም የሚያደርጉትን ጥቃት አጠናክረው ቀጥለዋል።
ቢያንስ 20 ከተሞችን እና መንደሮችን በመውረር፣ ቤቶችን በማፍረስ እና በደርዘን የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያንን በቁጥጥር ስር አውለዋል ነዉ የተባለዉ።
የአልጀዚራ ዘጋቢዎች እንደዘገቡት፤ የእስራኤል ጦር ከናብሉስ በስተደቡብ በምትገኘው ቤይታ ከተማ የሚገኘውን የጀባል ሳልማን አካባቢ የወረረ ሲሆን፣ ከራማላ በስተምዕራብ በምትገኘው ኒሊን ከተማም የማፍረስ ስራዎችን አከናውኗል።
አምስት ፍልስጤማውያንም በቁጥጥር ስር ውለዋል።
‹‹የእስራኤል ሰፋሪዎች በፍልስጤማውያን ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት በአብዛኛው በቤቶቻቸው፣ በምሽት በማስፈራራት ይቀጥላሉ›› አልጀዚራ ዘግቧል፡፡
ሳራ ዮሐንስ
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም
18 514
+1
እጽዋትን በመትከል እና በመንከባከብ አከባቢን ከመጠበቅ ባለፈ የተፈጥሮ አደጋን አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል ተገለጸ
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ እና ንብ ኢንሹራንስ በጋራ በመሆን በእንጦጦ ተራራ በሚገኘው እና በባንኩ ስም በተከለለው የሀገር በቀል ችግኝ መትከያ ስፍራ ባዘጋጁት የአረንጓዴ አሻራ አካል በሆነው አመታዊ የሀገር በቀል ችግኝ መትከል መርሀ ግብር ላይ እጽዋትን በመትከል እና በመንከባከብ አከባቢን ከመጠበቅ ባለፈ የተፈጥሮ አደጋን አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል የንብ ኢንሹራንስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዙፋን አበበ ተናግረዋል፡፡
ስራ አስፈጻሚዋ እንደገለፁት፤ ንብ ኢንሹራንስ በዋናነት አደጋ ከተከሰተ በኋላ ዋስትና የመስጠት ስራ የሚሰራ ሲሆን፤እንደ ችግኝ ተከላ ያሉ ማህበራዊ ሀላፊነቶችን መወጣት አና አስቀድሞ አከባቢን መጠበቅ ደግሞ የተፈጥሮ አደጋን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
መርሀ ግብሩን አስመልክቶ የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሄኖክ ከበደ ባስተላለፋት መልዕክት፤ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገት ከአከባቢ ጥበቃ ጋር የተሳሰረ ሲሆን፤ በቀደሙት አመታት የተተከሉት ችግኞች በተደረገላቸው እንክብካቤ በተሳካ ሁኔታ መጽደቅ መቻላቸውን አንስተዋል፡፡
አቶ ሄኖክ አክለውም ባንኩ ይህንን እና መሰል የአከባቢ ጥበቃ ተግባራትን በቀጣይ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
በመርሀ ግብሩ ላይ የተሳተፉት የባንኩ ሰራተኞች ለኢትዮ ኤፍኤም እንደተናገሩት፤ እንደ ባህር ዛፍ ያሉ ችግኞችን በመቀነስ አገር በቀል የሆኑ ችግኞችን መትከል መቻሉ የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ ረገድ ሚናው የላቀ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡
ሰላማዊት ዲታ
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም
18 514
ባለፉት 12 ወራት ከ1ሺ 6መቶ ኪሎ ሜትር በላይ የግንባታና የጥገና ስራዎች ተከናውነዋል ተባለ
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን በ2018 በጀት ዓመት 1 ሺህ 6መቶ 66 ኪሎ ሜትር ርቀት የሚሸፍኑ ልዩ ልዩ የመንገድ ግንባታና ጥገና ስራዎች ማከናወኑን ገልጿል፡፡
ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ በበጀት ዓመቱ 1ሺ3መቶ3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የግንባታና የጥገና ስራዎች ለማከናወን አቅዶ፤በዕቅድ ከተያዙ ሥራዎች በተጨማሪ በርካታ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን መስራቱን አስታዉቋል፡፡
ከዚህም ውስጥ ከ3መቶ46 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት የሚሸፍነው ልዩ ልዩ የመንገድ ግንባታ ስራ ሲሆን፤በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ የተገነቡ መንገዶችን ጨምሮ 69 ኪሎ ሜትር የአስፋልት፣ 61 ኪሎ ሜትር የጠጠር እና 108 ኪሎ ሜትር የኮብል ንጣፍ መንገድ ስራ ይገኝበታል ተብሏል፡፡
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም
18 514
የኢትዮጵያ ደም እና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት በተያዘው የክረምት ወቅት 1መቶ50 ሺህ ዩኒት ደም ለማሰባሰብ ማቀዱን አስታወቀ።
ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የተቋሙ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ኡመን ሀይር እንደገለጹት፥ከተያዘው እቅድ ውስጥ 40 ሺህ ዩኒት ደም በአዲስ አበባ፣ ቀሪው 1መቶ10 ሺህ ዩኒት ደም ደግሞ በክልሎች ደረጃ የሚሰበሰብ ይሆናል።
ባለፈው ዓመት የክረምት ወቅት 1መቶ40 ሺህ ዩኒት ደም መሰብሰቡን ያስታወሱት ወ/ሮ ኡመን፤ ዘንድሮ የተያዘው እቅድ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ10 ሺህ ዩኒት ጭማሪ እንዳለው አስገንዝበዋል።
ልዩ የክረምት የበጎ ፈቃድ የደም ልገሳ ንቅናቄው ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን፥ እስከ መስከረም 30 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ እንደሚቀጥልም ስራ አስፈፃሚዋ ጠቁመዋል።
ሳራ ዮሐንስ
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም
18 514
የጦርነትና የግጭት ሁኔታዎች ለጤና አገልግሎት አሰጣጥ ትልቅ ፈተና መሆናቸው ተጠቆመ
በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶች እና ጦርነቶች ለጤና አገልግሎቱ ችግር መሆናቸውን ጤና ሚኒስቴር ነው ያስታወቀው።
በተለይም የእናቶች እና ህፃናት ጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ እንቅፋት መፍጠራቸውን በጤና ሚኒስቴር የስነ-ተዋልዶ ጤና ቤተሰብ ዕቅድና የአፍላ ወጣቶች ፕሮግራም ኃላፊ ዶ/ር አለማየሁ ሁንዱማ ገልፀዋል።
በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የነበረው ጦርነትና አሁን ላይ በተለያዩ አካባቢዎች የሚታዩ ግጭቶች የጤና ባለሙያዎች በነፃነት ተንቀሳቅሰው አገልግሎት እንዳይሰጡ ከማድረጋቸውም በላይ የግብዓትና የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት ምክንያት መሆናቸውን አንስተዋል።
ዶክተር አለማየሁ እንዳሉት፥ ግጭቶች ባሉባቸው አካባቢዎች እናቶች ለሞትና ለከፍተኛ ስቃይ የሚዳረጉበት ዕድል ሰፊ በመሆኑ፥መንግስት ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን በተንቀሳቃሽ የጤና ቡድኖች አማካኝነት ችግሩን ለመቅረፍ ጥረት እያደረገ ይገኛል።
በቀጣይም አገልግሎቱ ባልደረሰባቸው አካባቢዎች ተደራሽ ለማድረግ ከአካባቢው አስተዳደሮች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
ሊዲያ ደሳለኝ
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም
18 514
"የኢትዮጵያ የንግድ ተቋማት በቴክኖሎጂ ድክመት ምክንያት የዓለም አቀፍ ገበያን እምነት እያጡ መሆኑ ተገለጸ"
በኢትዮጵያ 43 ሺህ የውጭ ንግድ ፍቃድ ያላቸው ነጋዴዎች ቢኖሩም፣ አብዛኞቹ መሠረታዊ የሆነ የቴክኖሎጂ ኮሙኒኬሽን ሲስተም የሌላቸው በመሆኑ የዓለም አቀፍ ገዢዎችን እምነት ለማግኘት መቸገራቸው ተነገረ።
በአሎሃ ቪስታ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ በተካሄደ የቢዝነስ ጉባኤ መድረክ ላይ እንደተጠቆመው፤ የሀገር ውስጥ የንግድ ተቋማት "በግለሰብ ስልክና ጥረት" ብቻ
ከመመራት ወጥተው ዘመናዊ አደረጃጀት ካልገነቡ የኤክስፖርት ዘርፉ ስኬታማ ሊሆን አይችልም።
የስትራቴጂ እና የቢዝነስ አማካሪው አቶ ሰለሞን ሲሳይ በመድረኩ ላይ፤ የኢትዮጵያ ነጋዴዎች ንግዳቸውን ተቋማዊ የማድረግ እና የረጅም ጊዜ ራዕይ ሰንቆ የመንቀሳቀስ ሰፊ ክፍተት እንዳለባቸው አመልክተዋል።
እንደ አማካሪው ገለጻ፣ 43 ሺህ የኢምፖርትና ኤክስፖርት ነጋዴዎች ባሉባት ሀገር አብዛኞቹ ድርጅቶች የራሳቸው ዌብሳይትና የድርጅት ኢሜይል የሌላቸው መሆኑ፣ ከዓለም አቀፍ ገዢዎች ጋር ዘላቂ የንግድ ግንኙነት ለመፍጠር ትልቅ እንቅፋት ሆኗል።
ይህ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ድክመት በኢትዮጵያ ላኪዎችና በውጭ ሀገር ገዢዎች መካከል "የእምነት ቀውስ" እንዲፈጠር ማድረጉም ተገልጿል።
አቶ ሰለሞን አክለውም፣ የሀገር ውስጥ አምራቾች እንደ ቡና እና ሌዘር ያሉ ምርቶችን በጥሬነታቸው ብቻ ለመላክ ከመቸኮል ይልቅ፣እሴት በመጨመር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚሆን "ብራንድ" መገንባት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
ንግዶች ከግለሰብ ባለቤትነት ወጥተው ጠንካራ የሰው ሀብትና ግልጽ አደረጃጀት በመፍጠር ለትውልድ የሚሻገር ተቋም እንዲገነቡም ጥሪ ቀርቧል።
የሀገር ውስጥ ቢዝነሶች የጋራ አጋርነትን (Partnership Mindset) ካላዳበሩና ራሳቸውን በቴክኖሎጂ ካላዘመኑ፣ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ መሆን እንደማይችሉ በዚሁ የአሎሃ ቪስታ የቢዝነስ መድረክ ላይ አጽንኦት ተሰጥቶበታል።
ልዑል ወልዴ
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም.
18 514
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለቀጣይ 25 ዓመታት የሚዘልቅ የኃይል ዲስትሪቢዩሽን ማስተር ፕላን ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ዘመናዊና ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችልና እ.ኤ.አ እስከ 2049 የሚዘልቅ የ25 ዓመታት የኃይል ማከፋፈያ ሥርዓት ማስፋፊያና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ይፋ አደረገ።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው በማስተር ፕላኑ የምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ኤሌክትሪክ ለኢንዱስትሪ፣ ለዲጂታል ሽግግር፣ ለግብርናና ለሌሎች ማህበራዊ ዘርፎች እድገት መሠረት በመሆኑ ይህ ፍኖተ ካርታ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ ሚና ይጫወታል ብለዋል።
እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለጻ፣ በአሁኑ ወቅት 5,453 ሜጋ ዋት አካባቢ የደረሰው የሀገሪቱ ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት እ.ኤ.አ እስከ 2049 ድረስ በሰባት እጥፍ በማደግ 40,000 ሜጋ ዋት ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህን ፍላጎት ለማሟላትም የማከፋፈያ ኔትዎርኩን በቴክኖሎጂ ማዘመን የግድ መሆኑን ገልጸዋል።
ማስተር ፕላኑ የአገልግሎት አሰጣጡን ከባህላዊ አሠራር ወደ ስማርት ግሪድ ወይም ዘመናዊ ኔትዎርክ ለመቀየር ያለመ ነው ተብሏል።
ይህም በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)፣ በዘመናዊ የኃይል ቆጣሪዎች (Smart Meters) እና አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ላይ የተመሠረተ እንደሚሆን ተጠቁሟል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።
ለዚህ ግዙፍ የ25 ዓመታት ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ 30.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ኢንቨስትመንት እንደሚያስፈልግ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም 84 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ለሀገሪቱ እንደሚያስገኝ ተጠቁሟል።
"ለእያንዳንዱ ለሚወጣ 1 ዶላር፣ 3 ዶላር የሚሆን የኢኮኖሚ ጥቅም ይገኛል" ያሉት ኢንጂነር ጌቱ፣ ኢንቨስትመንቱ ከፍተኛ የሥራ ዕድልና ብልጽግናን እንደሚያመጣ አስረድተዋል።
ከማስተር ፕላኑ ዝግጅት ጎን ለጎን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መሐንዲሶች የዕውቀት ሽግግርና ሥልጠና መሰጠቱ እንደ ትልቅ ስኬት ተጠቅሷል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው ለዓለም ባንክና ለኢራኑ ሞኔንኮ (Monenco Iran) አማካሪ ድርጅት ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
"ዛሬ ማቀድ፣ ነገን ማብቃት" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ይህ ማስተር ፕላን፣ የኢትዮጵያን የኃይል ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግርና ለዜጎች ፍትሃዊ የኃይል ተደራሽነትን እንደሚያረጋግጥ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ገልፀዋል።
አዲስዓለም አበበ
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም
18 514
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ከጠዋቱ 2፡00-10፡00
👉አያት፣ አይ ሲ ኤም ሲ ሆስፒታል፣ ስኩል ኦፍ ቱሞሮ፣ መሪ መስኪድ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-12፡00
👉መቀሌ፣ኤስ ኦ ኤስ፣ ቀበሌ 14፣15፣16 እና 17፣ ዓይን ዓለም እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-10፡00
👉አዋሽ መልኬሳ መግቢያ እና ከተማ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-7፡00
👉መቀሌ ቬተርነሪ ካምፓሰ፣ ኤልሻዳይ፣ ሻፋት፣ ዳጋይ እና ገብረ ሰገን ውሃ ግድብ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡30-11፡00
👉ባህርዳር ጊዮን ት/ቤት፣ሞላልኝ ግሮሰሪ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦትይቋረጣል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም
