Dn Mekuria Murashe || ዲ/ን መኩሪያ ሙራሼ
እንኳን ወደዚህ መንፈሳዊ ማደርያ በሰላም መጡ! 🕊️ ሕይወት ሰጪ አዳዲስ ሐሳቦች፣ ልብን የሚነኩ ጥልቅ መንፈሳዊ ጽሑፎች፣ እንዲሁም ነፍስን የሚያረኩ እውነቶች በዚህ ቻናል ይጋራሉ። ከዕለት ተዕለት ኑሯችን ጋር የሚጣጣሙ አነቃቂ መልዕክቶችን፣ እምነትን የሚያጸኑ አጫጭር ሐሳቦች እና ቆንጆ ስንኞች እዚህ ያገኛሉ። መልካም ቆይታ!✨
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel Dn Mekuria Murashe || ዲ/ን መኩሪያ ሙራሼ
Channel Dn Mekuria Murashe || ዲ/ን መኩሪያ ሙራሼ (@mekuriyam) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 178 subscribers, ranking 3 641 in the Religion & Spirituality category and 1 631 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 178 subscribers.
According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -358 over the last 30 days and by -34 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 4.27%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 2.61% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 905 views. Within the first day, a publication typically gains 554 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 13.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“እንኳን ወደዚህ መንፈሳዊ ማደርያ በሰላም መጡ! 🕊️
ሕይወት ሰጪ አዳዲስ ሐሳቦች፣ ልብን የሚነኩ ጥልቅ መንፈሳዊ ጽሑፎች፣ እንዲሁም ነፍስን የሚያረኩ እውነቶች በዚህ ቻናል ይጋራሉ። ከዕለት ተዕለት ኑሯችን ጋር የሚጣጣሙ አነቃቂ መልዕክቶችን፣ እምነትን የሚያጸኑ አጫጭር ሐሳቦች እና ቆንጆ ስንኞች እዚህ ያገኛሉ።
መልካም ቆይታ!✨”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | 0 | |||
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | 0 |
| 2 | እኔ የምልህ ጌታ ሆይ!
«ጠላቶቻችሁን ውደዱ»
ብለኸን የለምን? ስለዚህ አንተም “ኃጥአንን ወደ ሲኦል መጨመር አትችልማ” 😞
እርግጥ ነው ጠላቴን አልወደድኩም። ያ ኃጢአተኛውም እኔ ነኝ። ቃልህን የምከስስ "ጠላትህም" እኔ ነኝ። እናማ እኔም ጠላትህ ስለሆንኩ ውደደኝና መንግሥትህን አሳየኝ።
በእርግጥ ወደ ሲኦል የምትጨምረው የምትጠላውን ሰው እንዳልሆነና መጥላትም እንደማትችል አውቃለኹ። ሥራዬን ጠልተህ ከሥራዬ የተነሳ ወደ ጥልቁ ከምትወረውረኝ ሥራዬንም እንድትወድልኝ እኔነቴንና ማንነቴን ቀይር🙏
ዲ/ን መኩሪያ (ዘኖርቻ) ጽዮን
30/11/2018
ወልቂጤ፣ ኢትዮጵያ
#ንነጽር_207 #እኔነቴንና #ማንነቴን #ቀይር
✨የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ✨ | 2 012 |
| 3 | ለዛለው ክንዱን ይልካል፤
ጥቂቱን በብዙ ይባርካል።
ኃጥኡን ንጹሕ፣ ዘማዊውን ድንግል፤
ያደርጋል ጌታ ይሰጠናል ዕድል።
ተመስገን😞🙏 | 1 167 |
| 4 | በበደል ውስጥ ያለ ነጻነት!
በውስጣችን ተንኮል አስበን፣ በር ዘግተን ኃጢአት ሠርተን፣ ተደብቀን ዘርፈን፣ ነፍስ አጥፍተን፣... ይሄ ሁሉ ነገር አድርገን ወደ ውጭ ከሰው ለመቀላቀል ስንወጣ ግን ምን ያላደረግን ንጹሐን መስለን ቁጭ!
ክርስቶስ የሰጠንን የነጻነት ጥግ እያስተዋላችሁት ነው?
ቂመኛ ሆነን ሳለ ቂማችንን አላሳየብንም፤ እዚው እቤት ሁኑ ወደ ውጭ ከወጣችሁ አጋልጣችኋለኹ አላለንም።
በጣም የምንወደው ሰው ለ2ኛ ጊዜ ጥፋት ከሠራብን፤ እህ! እሱ ማን ስለሆነ ነው ብለን ዝም ዝም እንለዋለን። ይሄ ክርስቶስ የተባለው ንጉሥ ግን እልፍ ጊዜ በድለነው በእልፍ እርምጃ ቀርቦናል። ታዲያ ለምንድነው በጥቂቱ እንኳ እሱን መውደድ ያልቻልነው?
እኔ ግን እንዲህ እልሃለኹ... ፍቅርህን አለማየቴን ወይም ፍቅርህን አለመረዳቴንና አንተን አለመውደዴን አውቃለኹና፣ ልወድህ በማሰቤ ብቻ ማረኝ🙏
አሜን
#ንነጽር_206 #በበደል #ውስጥ #ያለ #ነጻነት
✨የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ✨ | 3 483 |
| 5 | ✨ሰዎች ሰላምን ከሩቅ አገር ይፈልጋሉ፤ ነገር ግን ሰላም የሚገኘው በዝምታና በለሰለሰ ልብ ውስጥ ነው። አላስፈላጊ ክርክርንና ወሬን መተው ስትጀምር፣ የውስጥህ ሰላም እንደ ጧት ጸሐይ መብራት ይጀምራል። አፍህ ዝም ሲል የፈጣሪ ድምፅ በልብህ ውስጥ በግልጽ ይሰማል🤌
ቅዱስ አውግስጢኖስ❤️
| 308 |
| 6 | ✨እምነት ማለት ምንድነው?
1ኛ እግዚአብሔር እንዳለ ማመን እግዚአብሔርን ባይታይም እውነተኛ መሆኑን ማመን ነው።
2ኛ በእግዚአብሔር መታመን“ነገሩ እንደፈለግኩት ባይሆንም፣ እግዚአብሔር ያውቃል፣ እኔንም አይተወኝም” ብሎ ልብን በእርሱ ላይ ማሳረፍ ነው።
3ኛ ቃሉን ማመን እግዚአብሔር የተናገረውን እውነት አድርጎ መቀበል ነው።
4ኛ በሥራ መግለጥ እውነተኛ እምነት በተግባርም ይታያል። ለምሳሌ እግዚአብሔርን እንደምታምን ከተናገርህ፣ በሕይወትህ ፍቅርን፣ ይቅርታን፣ ትሕትናን እና ቅንነትን ለመኖር ትጥራለህ
🌱
አንድ ሰው ወንዝ ላይ ያለ ድልድይ ጠንካራ መሆኑን ቢነግርህ፣ “አዎ፣ አምናለሁ” ማለት አንድ ነገር ነው።
እምነት ግን ድልድዩ ላይ እግርህን አድርገህ መሻገር ነው።
ስለዚህ እምነት = ማመን + መታመን + በዚያ እምነት መኖር ማለት ነው። ❤️
መጽሐፍ ቅዱስም፦ “እምነትም ተስፋ በሚደረግባቸው ነገሮች መረጋገጥ፥ በማይታዩትም ነገሮች መረዳት ነው” ይላል (ዕብራውያን 11፥1)
🔷ሰማያዊ ኅብረት🔷 | 418 |
| 7 | ✨ብዙዎች “አብቅቷል” ብለው በተዉት ነገር ላይ፣
አንተ ግን መጥተህ ሕይወትን ስትዘራበት፣
የተሰበሩትን ስትጠግን፣
ነገሮችንም ሁሉ እንደገና ውብ ስታደርጋቸው አይቼሃለሁ። 🥺🤍
✨ስለዚህ አልፈራም… እጠብቅሃለሁ🗣✝️
ለሁሉም ጊዜ አለው።
🔹ሰማያዊ ኅብረት 🔹 | 255 |
| 8 | ጓደኛህ/ሽ ማን ነው?
1. ጓደኛ ባሕርይህን ይቀይራል
“ክፉ ባልንጀራነት መልካም ጠባይን ያጠፋል።” — 1ኛ ቆሮ15፥33
በየቀኑ አብረሃቸው የምትውላቸውን ሰዎች ጠባይ ፣ ንግግር፣ ልምድና አስተሳሰብ ሳታውቀው መውሰድ ትጀምራለህ፤ በዚህ ውስጥም እንድትቀየር ትገደዳለህ።
2. ጥሩ ጓደኛ ወደ ክርስቶስ ያቀርብሃል
ጥሩ ጓደኛ፦ “ዛሬ ቤተ ክርስቲያን እንሂድ፣
እንጸልይ፣ ይህ ነገር አይጠቅምህም፣ ከዚህ ኃጢአት እንራቅ” የሚልህ ነው ፤ እገሰዚአብሔር የሚያውቅ ከሆነ ሰውነትህን በመልካም እንድትገነባ የሚያግዝህ መልካም ረዳት ይሆንሃል ።
3. መጥፎ ጓደኛ ኃጢአትን መደበኛ ያደርግልሃል
መጀመሪያ የምትፈራውን ነገር “ምን ችግረ አለው ፣ምንም አይደለም፣ ሁሉም ያደርገዋል” እያለ ሊያለማምድህ ይችላል። ኃጢአትን የሚያቀልልህ ሰው መንፈሳዊ ጓደኛህ አይደለም ፤ ሳታውቀው እያሳሳቀ ገደል የሚከትህ ስጋህን ብቻ ሳይሆን ነፍስህንም የሚገድል ነው ።
4. ራስህን ስለ ጓደኛህ እንዲህ ብለህ ጠይቅ-
“ከዚህ ሰው ጋር ከተዋወቅሁ በኋላ፦ ጸሎቴ ጨምሯል ወይስ ቀንሷል? ቤተ ክርስቲያን ቀርቤአለሁ ወይስ ርቄአለሁ? ንጽሕናዬ ተጠብቋል ወይስ ተበላሽቷል? ትምህርቴና ዓላማዬ ተሻሽሏል ወይስ ወደኋላ ሄዷል?”
5. ጥሩ ጓደኛ ተሳስተህ እያየ የሚያጨበጭብልህ አይደለም
“ብረት ብረትን እንደሚስል፣ ሰውም ሌላውን ሰው እንደዚሁ ይስለዋል” ምሳሌ 27፥17
እውነተኛ ጓደኛ “ይህ አይጠቅምህም” ብሎ ሊያስቆምህ ይችላል። ሁሉን የሚያጸድቅልህ ሳይሆን ለመዳንህ የሚጨነቅ ነው ።
🔹 ሰማያዊ ኅብረት 🔹
https://t.me/Orthodox12S
https://t.me/Orthodox12S | 309 |
| 9 | https://t.me/Orthodox12S | 377 |
| 10 | አልዋሸኹም!
አዳምንና ሔዋንን ከመክሰሳችን በፊት የዲያብሎስን ውሸት ማውገዝ ይኖርብናል። ምንም እንኳ የአዳም መሳሳት ተጠያቂው ራሱ አዳም ቢሆንም፣ የሔዋን መሳሳት ተጠያቂዋ ሯሷ ብትሆንም፣ የዚህ መሳሳት መንስኤው ግን የዲያብሎስ ዲስኩር(ውሸት) እንደነበረ አትዘንጉ።
✨ ውሸት ወዳጅን ከወዳጅ የመለያየት ኃይል አለው!
✨ ውሸት ባል ከሚስቱ ጋር የመለያየት አቅም አለው!
✨ ውሸት ፍቅረኛሞችን የመለያየት ጕልበት አለው!
✨ ውሸት ሰዎችን ከእግዚአብሔር የመለያየት ብርቱ ጥንካሬ አለው!
✔️ ስለዚህ በጥቅሉ፥ ወዳጃችሁ የሆነ ነገር ቢጠይቃችኹና እናንተ ደግሞ ያንን ነገር ለማድረግ ባትፈልጉ "አልፈልግም!" በሉት እንጂ ላለመፈለጋችኹ የሚሆን የፈጠራ ውሸት አትዋሹት!
ዲ/ን መኩሪያ (ዘኖርቻ) ጽዮን
17/11/2018
ወልቂጤ፣ ኢትዮጵያ
#ንነጽር_205 #ውሸት #ባል #ከሚስቱ #ጋር #ይለየዋል
✨የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ!✨ | 3 107 |
| 11 | ለሠራተኞቻችሁ የሚገባቸውን የደካም ዋጋ ክፍሉ።
ንግድ በራሱ መጥፎ አይደለም፤ በእርግጥም ይህ የእግዚአብሔር ሥርዓት አካል ነውና። ዋናው ነገር የንግድ ሥራችንን እንዴት መምራት እንዳለብን ማወቅችን ነው። ንግድ አስፈላጊ የሆነበት ምክንያት እግዚአብሔር የሰው ልጆችን ፈጥሮ በተለያየ ምኞትና በተለያየ ችሎታ በመሆኑ ነው።
አንድ ሰው ጥሩ አናጺ ነው፤ ሌላው ጥሩ ሰባኪ ነው። አንድ ሰው በጣም ደካማ በሆነው አፈር ውስጥ ሰብሎችን ማምረት ይችላል፤ ሌላው ደግሞ በጣም አስከፊ በሽታዎችን መፈወስ ይችላል።
ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው እግዚአብሔር ለሾመው ሥራ ልዩ ያደርገዋል፤ እናም ችሎታውን በመሸጥ የዕለት ጉርሱን ይገኛል።
ችግሮቹ የሚፈጠሩት አንዳንድ ሰዎች ለሥራቸው ከሌሎች እጅግ የላቀ ዋጋ ማግኘት ፈልገው፤ የሌሎችን የድካም ዋጋ ስላማይከፍሉ ነው። በዚህም የተነሣ አንዳንዶቹ ሀብታም እና ሌሎች ድሃ ይሆናሉ።
ነገር ግን በእግዚአብሔር ዓይን አንድ ችሎታ ከሌላው አይበልጥም። ማንኛውም ዓይነት ታማኝነት ያለበት ንጹሕ ሥራ ሁሉ እኩል ነው። ስለዚህ ሰዎች ለድካማቸው የሚቀበሉት ያነሰ ዋጋ ይህንን መለኮታዊ ስጦታን እንደመናቅ ያስቆጥራልና፤ የተገባቸውን የላብ ዋጋ እንክፈል።
የነፍስ ምግብ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው።) ገጽ 59
✨የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ✨ | 1 257 |
| 12 | 💁♂ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል ማንኛውም ኦርቶዶክስ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል።
ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል ቻናሉን ለመቀላቀል ከስር👇👇
✅JOIN ✅ የሚለውን
በመጫን ይ🀄️ላ🀄️ሉ👇👇👇 | 57 |
| 13 | በዚህ መሆን ለእኔ መልካም አይደለም!
ጴጥሮስ ግን እንዴት የታደለ ሰው ነው? "ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው!" አለ!
እኔ ግን የምልህ ጴጥሮስ ከተናገረው ንግግር የሚቃረነውን ነው። እሱስ የነበረበትን ቦታ እንዲህ ያናግረው ዘንድ አስችሎት ይሆናል። ግን እኔስ? በየትኛው መንገድ ቆሜ እንደቀረኹ ትመለከታለኽን?
ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኔ መልካም አይደለም!
ጴጥርስን ላክልኝ ብዬ ጴጥሮስን አልዳፈርም፣ ሙሴንም እንዲሁ፣ ኤልያስንም ቢሆን ላክልኝ አልልህም። እንደ ታላቅ ቃለ እምነቱ ሰውዬም "ቃልህን ብቻ ላክ" አልልህም።
ልልህ የምችለው አንድ ነገር ብቻ ነው...
በዚህ መሆን ለእኔ መልካም አይደለም ብዬ በተናገርኩበት አፍ፤ አሁንስ በዚህ መሞት ለእኔ መልካም ነው ብዬ እናገር ዘንድ አስችለኝ!
ዲ/ን መኩሪያ (ዘከተፋ) ጽዮን
11/11/2018
ወልቂጤ፣ ኢትዮጵያ
#ንነጽር_204 #በዚህ #መሆን #ለእኔ #መልካም #አይደለም | 4 568 |
| 14 | ✣ ባለ ማኅተቦች ብቻ play ይበሉ ✣
💒 💒
💒 #የተዋህዶ_ፍሬዎች 💒
💒◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈💒
💒 ከ፩ኛ ዓመት ጀምሮ 💒
💒 መንፈሳዊ ኮርሶችን መማር 💒
💒 ለምትፈልጉ፦ 💒
💒 እሄን ጹህፍ ነክተው 💒
💒 ወደ እግዚአብሔር ቤት 💒
💒 መግባት ይችላሉ 💒
💒 💠መልካም ትምህርት💠 💒
💒◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈💒
💒 💒
💒💒💒💒💒💒💒💒💒💒💒
ባለ ማኅተቦች ብቻ play ይበሉ
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️
⬜️⬜️⬜️ play▶️ ⬜️⬜️⬜️
⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️ | 93 |
| 15 | #አጋፋሪ_ይደግሳል
፩ኛ ትርጕም አጋፋሪ፤ አሁን በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ደረጃ የማኅሌቱን ሥርዐት ፥ የዝክር ሁኔታን የሚያስተባብር አጋፋሪ ሲባል፤ ምክትሉ መጨኔ ይባላል፡፡
፪ኛ ትርጕሙ፤ አጋፋሪ፤ በቀድሞ ዘመን በሃገራችን በተለይም በቤተ መንግሥት ያለ ሹመት ሲሆን፤ (በጎንደር ፥ በሸዋ ፥ በወሎ ፥ በኢሉአባቦር፥ በሐረርጌ፥ በትግሬ ፥ አጋፋሪ ተብሎ ሲጠራ በጎጃም መጨኔ ይባላል/
ሁለቱንም በቀድሞ ዘመንም ሆነ አሁን ባለው ሁኔታ ትርጕሙን እናያለን ፤
፠፠፩ኛ ፠፠ አሁን ካለው የቤ/ክን አገልግሎት አንጻር፤ አጋፋሪ ማለት የማኅሌቱን ሥርዐት ፥ የዝክር ሁኔታን የሚያስተባብር ሲሆን ምክትሉ መጨኔ ይባላል፡፡ ይህ አጋፋሪ በደብረ ታቦር በዓል ላይም በቅዱስ ሚካኤል ተመስሎ፤ ‹‹ሆያ ሆዬ›› ይባላል፡፡ ይኸውም
‹‹#ሆያ_ሆዬ_ሆ_››፤ ማለት ጌታው ሆዬ ፥ እሜቴ ሆዬ ለማለት ነው፡፡
‹‹#እዚያ_ማዶ_ጢስ_ይጤሳል_›› የተባለው፤ እስራኤላውያን በበረሃ ለ40 ዓመታት ሲጓዙ ደመና እየጋረዳቸው (እየጤሰ) ስለመራቸው ነው፡፡
‹‹#አጋፋሪ_ይደግሳል_››፤ የተባለው አጋፋሪው /አለቃው/ ቅዱስ ሚካኤል ሲሆን፤ ይደግሳል መባሉ እስራኤላውያንን ‹‹በዕደ መልአኩ ይዕቀበነ ፥ ሰላመ ዚአሁ የኀበነ›› እንዲል፤ በአምላክ ትዕዛዝ ቅዱስ ሚካኤል መናን ከደመናን ፥ ውኃን ከጭንጫ ዓለት እያፈለቀ (እየደገሰ) መርቷቸዋልና ነው፡፡
****እንዲሁም የአብነት (የቆሎ) ተማሪዎች በክረምት ሲለምኑ የቆዩትን አጠራቅመው፤ የደብረ ታቦር ዕለት ብርሃነ መለኮቱን የገለጠ ጌታ ለኛም እንዲገልጥልን ብለው፤ ደግሰው ለሕዝቡ ያበላሉ ፥ ያጠጣሉ፡፡ /ይህ ሥርዐት በደብራችንም የሚከናወን ድርጊት ነው፡፡/
‹‹#ያችን_ድግስ_ውጬ_ውጬ_››፤ የተባለውና በድግስ የተመሰለው መና ሲሆን፤ በደጋሹ ቅዱስ ሚካኤል አማካይነት እስራኤል 40 ዓመታት መመገባቸውን (መና መዋጣቸውን) መናገር ነው፡፡
‹‹#ከድንክ_አልጋ_ተገልብጬ_›› ፤ ድንክ አልጋ የምትመች እንደሆነች ሁሉ ፥ በድንክ የምትመሰለውንና የምትመቻቸውን ተስፋዪቱ ምድር ኢየሩሳሌምን መውረሳቸው መናገር ነው፡፡
‹‹#ያቺ_ድንክ_አልጋ_አመለኛ_፥ #ያለአንድ_ሰው_አታስተኛ_››፤ መባሉ እስራኤል ከግብጽ ሲወጡ 600,000 ሆነው ሲሆን፤ ሁሉም በምድረ በዳ አልቀው ኢየሩሳሌምን የወረሳት ሴትና ሕፃናት ሳይቈጠሩ፤ አንድ ኢያሱና አንድ ካሌብ ናቸው ለማለት ነው፡፡
፠፠፪ኛ ፠፠ #አጋፈረ፤ግስ ሲሆን በቤተ መንግሥት ፥ በግብዣ ቦታ፥ …. በር ላይ ቆሞ የሚገባውንና የሚወጣውን ሰው አስተናበረ አስተናገደ፡፡
*አጋፋሪ፤ ቅጽል ሲሆን፤ ቃሉ የቀድሞ አማርኛ ሲሆን አስተናባሪ (ብዙውን ጊዜ በግብዣ ወይም በቤተ መንግሥት በር ላይ በመቆም ሥርዐት የሚያስከብር ማለት ነው፡፡
*አጋፋሪ፤ የድግስ አለቃ ፥ አስተናጋጅ ነገሥታት ግብር ሲያገቡ (ግብዣ ሲጋብዙ ፥ ድግስ ሲደግሱ) ወደ አዳራሹ (ወደ ድግሱ) እንዲገቡ የሚፈቅድ ፥ የማይገባቸውንም የሚከለክል፤ ከገቡም በኋላ እንደ የክብራቸውና እንደየማዕርጋቸው አንተ በዚህ ሁን ፥ አንተ በዚህ ተቀመጥ እያለ የሚያስቀምጥ፤ ኋላ የድግሱ ምግብና መጠጥ መታደል ሲጀምርም፤ እንጀራና ጠጅ አሳላፊዎችን የሚያዝና የሚቈጣጠር ትልቅ ሹም ነው፡፡
*አጋፋሪ፤ የሚለው መጠሪያ በ17ኛወና በ18ኛው ክፍለ ዘመን የታወቀ የቤተ መንግሥት ሹም መጠሪያ ነው፡፡ ‹‹ህዱግ ራስ›› በመባል የሚታወቅም ነው፤ በቤተመንግሥት የሚካሄዱ ሥራዎችንና የፍርድ ሂደቶች ያስተባብራል፤ አንዳንዴ ደግሞ የክፍላተ ሃገር የፍርድ ሰጪ ሰዎች ስም ሆኖም ያገለግላል፤ የስሜን (ከጎንደር በስተሰሜን የሚገኝ ግዛት ነው) አስተዳደር የሚገዛ ሰው ደግሞ የሰሜን አጋፋሪ እየተባለም ይጠራል፤ (ለምሳሌም አፄ ሱስንዮስ ልጃቸውን ፋሲለደስን የስሜን አጋፋሪ ብለው ሹመወት ነበር፤ ይህ የስሜን አጋፋሪ የሚለው ሹመትም እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ቆይቶ ነበር፡፡
#ቡሄ_፤
ቡሄ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጸበት የነሐሴ 13 ቀን መጠሪያ ስሙ ነው የሚሉ ሊቃውንት እንዳሉ ሁሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ፤
ቡሄ የሚባለው፤ ከነሐሴ 13 በኋላ እስከ መስከረም 17 መስቀል ድረስ ሲሆን፤ በተለይም ይህ በዓል የሚታወቀው በሸዋና ወሎ /እስከ ጋይንት ጫፍ መጋጠሚያ) ድረስ ሲሆን፤ በዚህ ወቅትም ክርስትና አባት ለክርስትና ልጁ ተማሪ ከሆነ መጻሕፍትን (ዳዊት፣ …)፣ እንዲሁም አልባሳትን፣ በግና ሙክት ፍየልን የሚሰጥበት ነው፡፡ ሕፃናትና ወጣቱም ‹‹ቡሄ ፥ ሆ ….. ›› እያለ ይጨፍራል ፤ የሚሰጠውንም ሙክትና በግ እስከ መሰቅል ድረስ ሲያጠራቅም ከርሞ ለመስቀል ዕለት አርዶ ይበላል ፥ ደስታን ያደርጋል፡፡
ምንጭ፤ የቃል ትምህርት
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ | 387 |
| 16 | ⛰️[ደብረ ታቦር] ⛰️
⛰️
✍ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
♥❖ ይኽ በዓል ከጌታችን 9ኙ ዐበይት በዓላት አንደኛው ሲኾን በዓሉ በየዓመቱ ነሐሴ 13 ላይ በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡ ታሪኩ በ3ቱ ወንጌላት ላይ የተጻፈ ሲኾን ጌታችን አምላችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሌሎቹን ሐዋርያትን ከእግረ ደብር (ከተራራው ሥር) ትቶ የምስጢር ደቀ መዛሙርት የሚባሉት ሦስቱን (ጴጥሮን፣ ያዕቆብን፣ ዮሐንስን) ይዟቸው ወደ ታቦር ተራራ በመውጣት የሞተውን ሙሴን ከ1644 ዓመታት በኋላ አስነሥቶ፤ የተሰወረውን ኤልያስንም ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ የሕያዋን አምላክና የሙታን አሥነሺያቸው ርሱ መኾኑን የገለጸበት ታላቅ ምስጢር የተከናወነበት ነው፡፡ (ማቴ 17፡1-9)።
♥❖ ጌታ 8ቱን ሐዋርያት ይዟቸው ያልወጣበት በይሁዳ ምክንያት ነው ምክያቱም ከምሥጢረ መንግሥቱ ቢለየኝ ከሞቱ ገባኹበት ባለ ነበርና ነው፤ ነገር ግን በተራራው ላይ ለ3ቱ የተገለጸው ምስጢር ከተራራው ሥር ላሉት ከይሁዳ በስተቀር ተገልጾላቸዋል፤ ለእኛም እንደ ሐዋርያት ምስጢሩን ጥበቡን ይግለጽልን፡፡
♥❖ ብዙ ተራሮች ሳሉ የታቦር ተራራን የመረጠበት
1)አስቀድሞ የጌትነት ክብሩ በዚያ ተራራ ላይ እንደሚገልጽ ነቢዩ ዳዊት በመዝ 88፡12 ላይ “ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚኣከ ይትፌሥሑ” (ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ይደሰታሉ) በማለት ጌታ በዚያ ተራራ ላይ ብርሃኑን ሲገልጽ የብርሃኑ ነጸብራቅ እስከ አርሞንኤም ተራራ ድረስ እንደሚታይ የተናገረውን ትንቢት ለመፈጸም ነው፡፡
♥❖ ሌላው ታቦር በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ 12 ጊዜያት ሲጠቀስ በተለይ በመሳ 4 እና 5 ላይ እንደተጻፈው አስቀድሞ በብሉይ ኪዳን የእስራኤል ጠላት የነበረው ሲሳራን መስፍኑ ባርቅ በተራራው ላይ ድል ነሥቶበት ነቢይቱ ዲቦራም በተራራው ላይ በደስታ አመስግናበታለች ዘምራበታለች፤ በተመሳሳይ መልኩ የእስራኤል ዘነፍስ የክርስቲያኖችን ጠላት የኾነውን ዲያብሎስን የኹላችን ፈጣሪ ንጉሠ ነገሥት ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነቱን ገልጦ ድል ስለነሣው ነቢያት ሐዋርያት ምእመናን የሚያመሰግኑት ስለኾነ ለምሳሌነቱ ተስማሚነት ያለውን የታቦርን ተራራን መርጦታል፡፡
♥❖ ለምን ሙሴንና ኤልያስን ከነቢያት መኻከል መረጠ? ቢሉ
ሀ) በማቴ 16፡13 ላይ ሐዋርያትን ስለማንነቱ እንደጠያቃቸው እንደመለሱለት ኹሉ በእውነት ጌታችን የሙሴና የኤልያስ ፈጣሪ መኾኑን ሲገልጽላቸው ነው።
ለ) በዘፀ 33፡17-23 ላይ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ካለው ጥልቅ ግንኙነት የተነሣ “እባክኽ ክብርኽን አሳየኝ” ብሎ ልመናን አቀረበ፤ እግዚአብሔርም "ወአነብረከ ውስተ ስቊረተ ኰኲሕ ወእከድን እዴየ በላዕሌከ እስከ አኃልፍ" (በሰንጣቃው ዐለት አኖርሃለኍ፤ እስካልፍ ድረስ እጄን በላይኽ እጋርዳለኍ፤ ካለፍኍ በኋላ እጄን አንሥቼልኽ ጀርባዬን ታያለኽ፤ ፊቴ ግን አይታይም) ብሎታል (ዘፀ ፴፫፥፲፯-፳፫)፡፡
♥❖ ይኸውም ጀርባ በስተኋላ እንደሚገኝ ኹሉ በኋላ ዘመን አካላዊ ቃል ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በታቦር ተራራ ላይ እንደሚገለጽለት ሲያመለክተው ነው።
♥❖ ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብም ስለ ታቦር በሚተነትነው መጽሐፉ ሙሴ በቃዴስ ባለው በመሪባ ውሃ ከእስራኤል ጋር በበደለው በደል ምክንያት ምድረ ርስት ኢየሩሳሌም እንዳይገባ አይቷት ብቻ በናባው ተራራ ላይ እንዲያርፍ ኾኗል (ዘፀ ፴፪፥፶፪፤
ዘፀ ፴፬፥፩-፰)፡፡
♥❖ ይኽ ለሙሴ አሳዛኝ ቢኾንም በኋላ ዘመን አካላዊ ቃል ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ሙሴ በፊት በሩቁ ያያት ግን ያልገባባት በምድረ ርስት በኢየሩሳሌም ያለች ታቦር ተራራ ላይ አምጥቶት በዘመነ ብሉይ በአካለ ሥጋ ያልገባባትን ርስት እንዲገባባት አድርጎታል፤ ይኸውም አዳምና ልጆቹ በአካለ ሥጋ ያጡትን ርስታቸው ገነትን በአካለ ነፍሳቸው ዳግመኛ ሊያገባቸው እንደመጣ የሚያመለክት መኾኑን በስፋት አስተምሯል፡፡
♥❖ ጌታችን በብሉይ ኪዳን ከነበሩት ከነቢያት ሙሴንና ኤልያስን በሐዲስ ኪዳን ከነበሩት ከሐዋርያት ሦስቱን በታቦር ተራራ ላይ ማውጣቱ፦
⛰️1) የታቦር ተራራ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ በመኾኗ ሲኾን በቤተ ክርስቲያናችን ብሉይ ኪዳንና ሐዲስ ኪዳን እንደሚነገሩ ለማመልከት
⛰️2) በተራራ በተመሰለች በጉባኤ ቤት ብሉይና ሐዲስ እንደሚነገሩ ለመግለጽ፡፡
⛰️3) ሌላው የታቦር ተራራ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ስትኾን ይኸውም ጌታ ነቢያትንና ሐዋርያትን በተራራዋ ላይ መሰብሰቡ መንግሥተ ሰማያትን ነቢያትም ሐዋርያትም እንደሚወርሷን ለማመልከት
⛰️4) ሙሴ ያገባ ሲኾን ኤልያስ ድንግል ነውና መንግሥተ ሰማያትን ደናግልም ያገቡም እንደሚወርሷት ለማጠየቅ ነው፡፡
⛰️5) እንደ ያዕቆብ ዘሥሩግ ትርጓሜ ሙሴ ኦሪት ዘፍጥረትን ሲጽፍ “በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ” (ዘፍ 1፡1) እንዳለ፤ ዮሐንስም “በመጀመሪያ ቃል ነበር” (ዮሐ 1፡1) ብሎ እንደ ሙሴ አምላክነቱን የሚመሰክር ነውና ሙሴ አስቀድሞ የጻፈልኝ፤ አኹንም ዮሐንስ አምላክነቴን የሚጽፍልኝ እኔ ነኝ ሲል ነው፡፡
⛰️6) ሙሴና ኤልያስ ይመሳሰላሉ፤ ይኸውም በሲና ተራራ 40 ቀንና ሌሊት እንደጾመ ኤልያስም በደብረ ኮሬብ 40 ቀንና ሌሊት የጾመ ነውና፨
⛰️7) ሙሴ ንጉሡ ፈርዖንን የገሠፀ እንደነበር ኤልያስም ንጉሡ አክዐብን የገሠፀ ነውና፨
⛰️8) ሙሴ ከንጉሡ ፈርዖን ፊት ሸሽቶ እንደሄደ ኤልያስም ከንግሥቲቱ ኤልዛቤል ፊት ሸሽቶ ሄዶ ነበር።
⛰️9) ዳግመኛም ሰማይኑን ዝናብ እንዳያዘንም በተሰጠው ሥልጣን ባሰረውና ከ3 ዓመት ከ6ወር ቆይታ በኋላ እንዲዘንብ በፈታው ኤልያስን እንዳመጣ ኹሉ የማሰር የመፍታት ሥልጣን ሥልጣነ ተሰጥቶት “እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል” (ማቴ 16፡18-19) ላለው ለጴጥሮስን ታላቅ ሰማያዊ ሥልጣን መስጠቱን ለማመልከት አምጥቷቸዋል፡፡
♥❖ በቤተ ክርስቲያንና በሀገራችን ያለው መንፈሳዊ አከባበር ደማቅ ነው፤ ይኽ በዓል በቤተ ክርስቲያን በማሕሌት በቅዳሴ በትምህርት የሚከበር በዓል ሲኾን በሀገርኛ የቡሄ በዓል ይባላል፤ ቡሔ ማለት ሊቁ ደስታ ተክለ ወልድ በመዝገበ ቃላት ላይ ሲገልጹት ቧ ብሎ በደብረ ታቦር የተገለጠው የጌታችንን የፊቱን ብርሃን ጸዳል የልብሱን እንደ በረዶ ነጭ መኾን ያስረዳል ስለዚኽ የብርሃን፣ ብርሃናዊ ማለት ነው፡፡
♥❖ በዚህ በዓል በታቦር የታየው የብርሃኑ ምሳሌ የሚሆን ችቦ ይበራል፤ ሌላው በዚኽ በዓል ሰሞን በገጠር ከተራራ ላይ እረኞች ሕጻናት ዥራፍ እየገመዱ ማስጮኻቸው ጌታ በተራራ ላይ ብርሃኑን በገለጸ ጊዜ አብ በደመና ኾኖ “እርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት” ባለ ጊዜ ሐዋርያት በድምፁ ደንግጸው መውደቃቸውን ለማመለክት ነው፡፡
♥❖ ሌላው ሙሉሙሉ ዳቦ መጋገሩ በትውፊት እንደምንረዳው ጌታ ብርሃኑን ሲገልጽ ብርሃኑ እስከ አርሞንኤም ተራራ ድረስ ያበራ ስለነበር እረኞች ሌሊቱ ኹሉ ቀን መስሏቸው እዛው ስለዋሉ ቤተሰቦቻቸው “ኅብስት” ይዘውላቸው ሄደዋልና የዚያ ምሳሌ እንደኾነ ይነገራል፡፡
⛰️[በደብረ ታቦር ላይ ብርሃኑን የገለጠው አምላካችን ክርስቶስ ምስጋና ይግባው]፡፡ 🙏🏻
[መልካም በዓል]
✍ መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
@MekuriyaM | 347 |
| 17 | 💍ከጋብቻ በፊት ሩካቤ (sex) መፈጸም ምን ችግር አለው⁉️
💁♂ከትዳር በፊት መሳም (ከንፈር ወዳጅ /kiss) ይቻላልን⁉️
👨🦱🧑🦳ፍቅረኛሞቹ እጅግ በጣም ስለሚውዋደዱ (ሩካቤ/sex) ቢፈጽሙ ምን ችግር አለው⁉️
⛪️በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ከተዋደዱ በኋላ ስሜታቸው ይገደባል⁉️
🤵♂የስሜት መግለጫዎች መፈጸም ይቻላል⁉️
በነዚህ ትምህርቶች ዙሪያ እየተማርን እንገኛለን
እርሶም እውቀቱ እዲኖርዎ ከፈለጉ ይህን ማስፈንጠሪያ Link ጠቅ ያድርጉት
👇👇👇
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
| 22 |
| 18 | ❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
መልካም ዕድል!!! | 49 |
| 19 | 📓#አንድጥያቄ
✟ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለአብርሃም ድንኳን ለኖህ መርከብ ለያዕቆብ መሰላል ለአዳም ምኑ ናት? ✟ | 16 |
| 20 | 🤴1. ያዕቆብ በሕልሙ ከምድር እስከ ሰማይ የተዘረጋች የወርቅ መሰላል ያየበት ቦታ_ነው? | 34 |
