MINSTERY OF EDUCATION ©
For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام MINSTERY OF EDUCATION ©
تُعد قناة MINSTERY OF EDUCATION © (@minster_of_education) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 47 140 مشتركاً، محتلاً المرتبة 3 733 في فئة التعليم والمرتبة 719 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 47 140 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 04 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 1 476، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 16، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 14.22%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 7.42% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 6 702 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 3 496 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 12.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“For more information!
It’s all about education
Official minstry of education telegram channel join and get more info About us
✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ
Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 05 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 05 سبتمبر | 0 | |||
| 04 سبتمبر | +18 | |||
| 03 سبتمبر | +1 | |||
| 02 سبتمبر | +28 | |||
| 01 سبتمبر | +25 |
| 2 | ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሰባት የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤታቸው በስህተት Disqualified እንደተባለባቸው በመግለፅ፣ የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ጽ/ቤት ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማሳወቁን ገልጿል።
ሰባቱም ተማሪዎች ለአገልግሎቱ ማመልከት ስለሚገባቸው፣ ተማሪዎቹ ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ መረጃው እንዲደርሳቸው ጠይቋል፡፡
ተማሪዎቹ (3 የማኅበራዊ ሳይንስ እና 4 የተፈጥሮ ሳይንስ) ፈተናቸውን በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የወሰዱ ናቸው።
(ጥር 11, 2022 የተከፈተና 18,853 ተከታዮች ያሉት የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር የቴሌግራም ገጽ ትናንት ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ያጋራው መረጃ ከላይ ተያይዟል።)
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናቸውን የወሰዱና ውጤታቸው Disqualified የተባለባቸው እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ። በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የተገለፀው አይነት መሠል ግድፈት ሊኖር ስለሚችል ዩኒቨርሲቲዎች በድጋሜ የሪሚዲያል ተፈታኞችን ውጤት እንዲያዩ ይጠየቃሉ። | 3 209 |
| 3 | #ጥናት
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተካሔደ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚያገኙት አገልግሎት የሚሰማቸው እርካታ ዝቅተኛ መሆኑን አሳየ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት ከተለያዩ ተቋማት በተውጣጡ አጥኚዎች የተሠራው ጥናቱ፤ በ2017 እና በ2018 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሚሰጡ አገልግሎቶች መምህራን፣ ተማሪዎች፣ የአስተዳደር ሠራተኞች እና ማህበረሰቡ ምን ያህል ደስተኛ ናቸው የሚለውን ለማወቅ ነው፡፡
በጥናቱ በ2017 ዓ..ም የተሻለ ደረጃ ላይ የነበሩ፣ በ2018 ዝቅ ማለታቸው የታየ ሲሆን፣ በተቃራኒው ባለፈው ዓመት ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የነበሩት በዚህ ዓመት መሻሻል ማሳየታቸውን ጥናቱ ጠቁሟል፡፡
በጥናቱ 47ቱም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተካተቱ ሲሆን፣ ከ16 ሺህ በላይ ተማሪዎች፣ ከ16 ሺህ በላይ መምህራን፣ ከ4 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሠራተኞች እና 4 ሺህ የሚሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች (በአጠቃላይ 61,431 ሰዎች) በጥናቱ ውስጥ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የጥናቱ ዋና ዋና ትኩረቶች
● የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአገልግሎት እርካታ
● የዩኒቨርሲቲ መምህራን አገልግሎት አሰጣጥ
● በዩኒቨርሲቲዎች የአስተዳደር ሠራተኞች እርካታ
● ዩኒቨርሲቲዎች በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ በሚሰጡት አገልግሎት እርካታ
ከ47ቱ ዩኒቨርሲቲዎች በተማሪዎች የአገልግሎት እርካታ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ፣ ኦዳ ቡልቱም እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች አጊኝተዋል፡፡
በተቃራኒው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች አገልግሎት ደስተኛ አለመሆን ቀዳሚ ሲሆን፣ መቐለ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
ሸገር ኤፍኤም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንትን ስለጥናቱ ግኝት የጠየቀ ሲሆን፣ "ለጊዜው መልስ መስጠት እንደማይችሉ" ነግረውታል፡፡
ከ47ቱ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል በመምህራን "የተሻለ አገልግሎት ይሰጣል" ተብሎ በጥናቱ በቀዳሚነት የተለየው ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚው ሲሆን፣ ቀብሪደሃር እና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
በእነዚህ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚያስተምሩ መምህራን ለመምህራን በሚሰጠው አገልግሎት ጥሩ እርካታ እንዳላቸው ጥናቱ ጠቅሷል፡፡
መቐለ ዩኒቨርሲቲ ዝቅተኛ የመምህራን እርካታ ያለበት ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ጥናቱ ያሳየ ሲሆን፣ ዋቸሞ እና ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይይዛሉ፡፡
በዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሠራተኞች እርካታ ኦዳ ቡልቱም፣ ቀብሪደሃር እና ሰላሌ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ እርካታ የተመዘገበባቸው ሲሆኑ፤ መቐለ፣ ደብረ ማርቆስ እና መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ ዝቅተኛ የአስተዳደር ሠራተኞች እርካታ የተጠቀሰባቸው ናቸው፡፡
ሐራማያ፣ ዓዲግራት እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ በሚሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ እርካታ ከተመዘገበባቸው መካከል ሲሆኑ፤ ዲላ፣ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በአካባቢው ማኅበረሰብ ዝቅተኛ የእርካታ ደረጃ ከተመዘገበባቸው መካከል ቀዳሚዎቹ መሆናቸውን ጥናቱ ጠቅሷል፡፡
ተማሪዎች በማደሪያ እና በመመገቢያ ስፍራዎች ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳላቸው የሚገልፀው ጥናቱ፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንም በደሞዝና ጥቅማ ጥቅም ደስተኛ እንዳልሆኑ ጥናቱ አመላክቷል፡፡ #ShegerFM | 2 938 |
| 4 | የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር በመጠናቀቁ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የውድድር ማስታወቂያ በቅርቡ ይወጣል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር ጊዜው በማብቃቱ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የሚያስችለውን የውድድር ማስታወቂያ ለማውጣት የመጨረሻ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል፡፡
የውድድር ማስታወቂያው በቅርብ ቀናት እንደሚወጣ ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀዋል።
ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡
በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ውሳኔ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የሆነው ሐምሌ 28/ 2015 ዓ.ም እንደነበር አይዘነጋም፡፡
@minster_of_education | 3 599 |
| 5 | በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ለአስር ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ አመራር ለመመደብ የሚያስችል የውድድር ማስታወቂያ ይፋ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች አመራር ምደባ ከተጠናቀቀ በኋላ ደግሞ ለ17 ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ አመራር ለመመደብ የውድድር ማስታወቂያ እንደሚወጣ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል።
ከዚህ በኋላ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች የሚመደቡት በውድድር ብቻ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ውድድሩ ብቃትና ስብዕና ላይ መሰረት ያደረገ ትክክለኛ ውድድር እንደሚሆን ገልፀዋል።
የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከዚህ በኋላ ግዴታ ሦስተኛ ዲግሪ የማይጠየቅ ሲሆን፣ ኢንዱስትሪዎችን ጨምሮ በየትኛውም ተቋም የሚገኙ ባለሙያዎች ለኃላፊነቱ መወዳደር ይችላሉ ብለዋል።
@minster_of_education | 3 155 |
| 6 | ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባን ለማዘመን ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ጋር ባደረጉት የምክክር መድረክ እንደገለፁት፣ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስብጥር ብዝሃነትን ባካተተ፣ መቻቻልንና ሀገራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ሊሆን ይገባል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪዎች ምደባና ዝውውር ጋር ተያይዘው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚዘረጋ ገልፀዋል።
ከበጀት አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደበላቸውን በጀት ለታቀደለት ዓላማ ብቻ በቁጠባና በተጠያቂነት መንፈስ መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገብረህይወት (ፕ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርስቲዎቹ በስምምነት ተማሪዎችን ሲያዘዋውሩ ለትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
@minster_of_education | 2 531 |
| 7 | #ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ
የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️
BSc Fields of Study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing
TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography
⭐️ የ CPD ማዕከል አገልግሎት!
☎️ 0913398780 / 0911596059
አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ
📍 Addis Ababa, CMC Square, Behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital
Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege
Tiktok: https://www.tiktok.com/@lorcan.medical.co | 2 826 |
| 8 | የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ያድርጉ!
በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሐግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ 👇
ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ የሚያደርጉበት ሊንክ 👇
https://student.ethernet.edu.et/
የሕክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከስድስት ወር በታች ህጻን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል ተብሏል።
| 3 514 |
| 9 | በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚሰጠው ዛሬ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ከሰዓት ከ9:00 ጀምሮ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ለሙከራ ፈተናው የተመረጡ የፈተና መስጫ ማዕከላት፦
➻ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (6 ኪሎ ዋናው ግቢ)
➻ ዳግማዊ ምኒልክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
➻ የእቴጌ መነን የልጃገረዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
Username እና Password በመፈተኛ ማዕከላቱ ስትደርሱ በጣቢያው ከሚመደቡ የፈተና ጣቢያ አስተባባሪዎች ታገኛላችሁ ተብሏል። | 3 286 |
| 10 | ቶኩማ ሀርቨስቲንግ የተባለ የግብርና ማሽን የሠራው ወጣት 👏
ሰለሞን ቡታ ከፍቼ ከተማ የተገኘ የክህሎት ኢትዮጵያ ውድድር ቴክኖሎጂ ፈጣሪ ወጣት ነው፡፡
"ቶኩማ ሀርቨስቲንግ" የተሰኘ በውስጡ ሦስት አገልግሎቶችን የሚሰጥ ዘመናዊ የግብርና ማሽን ፈጥሯል፡፡ ማሽኑ መሬት ማረስ፣ ምርት መሰብሰብ እና ውሃ ፓምፕ ማድረግ የሚችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ይህ ፈጠራ የጊር ቦክስ ስርዓቱን በመቀየር በጋዝ፣ በሶላር እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል መስራት የሚያስችል አማራጭ አለው፡፡ ከመሬት ያለው ከፍታ ለየትኛውም የሀገሪቱ የመሬት አቀማመጥ ምቹ እንዲሆን ተደርጎ የተሠራ ነው፡፡
አጠቃላይ የማሽኑ ክብደት 150 ኪሎ ግራም ቢሆንም፣ ሲነቃቀል እያንዳንዱ ክፍል 25 ኪሎ ግራም ብቻ ስለሚመዝን በቀላሉ ተነቃቅሎ እንዲጓጓዝና እንዲገጣጠም አስችሎታል፡፡ ከኢንጂኑ በስተቀር ሁሉም የማሽኑ ክፍሎች በሀገር ውስጥ የተሠራ እንደሆነ ተመላክቷል፡፡
ይህ ቴክኖሎጂ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ ያሉ ችግሮችን የመፍታት አቅም ያለው ሲሆን፣ በምርት መሰብሰብ ሒደት ጣለን ብክነት ከ30 ፐርሰንት ወደ 5 ፐርሰንት ዝቅ ያደርገዋል ተብሏል፡፡ 👏 | 2 676 |
| 11 | በተልዕኮ የተለዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጧቸውን የትምህርት አይነቶች ክለሳ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር
ዩኒቨርሲቲዎች ራሳቸውን በተልዕኮ ሲለዩ በአካባቢያቸው ካለው ፀጋ ጋር በማስተሳሰር ትኩረታቸውን ይበልጥ እንዲያጠቡ ወይም በልዩ ሁኔታ እንዲለዩ እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች በሚገኙበት አካባቢ ባሉ ሀብቶች ላይ በመመስረት በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በግብርና እና በመሳሰሉት ዘርፎች ተልዕኳቸውን እንዲለዩ እየተደረገ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት ከሚሰጡ 297 ፕሮግራሞች ውስጥ 111 ያህሉ መከለሳቸውን በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሜጀና (ዶ/ር) ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል።
ዩኒቨርሲቲዎቹ የትምህርት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ የአፕላይድ ሳይንስ፣ የምርምር እና የአጠቃላይ ትምህርት ተብለው የተከፈሉ መሆኑን ያስታወሱት ኃላፊው፣ ተቋማቱ የሚሰጧቸው የትምህርት አይነቶችም በተመደቡበት ተልዕኮ መሰረት እንዲከልሱ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
ይህ ክለሳ ተቋማቱ የበለጠ ተወዳዳሪ እንዲሆኑና ብቃት ያለው ተማሪ እንዲያፈሩ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ከዚህ በኋላ ከመረጡት ተልዕኮ ውጪ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጡት ትምህርት እንደማይኖር ያስረዱት ኃላፊው፤ ተማሪዎች በአዲሱ የትምህርት ዘመን በሚገባ መረጃ ኖሯቸው እንዲመጡ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲዎች ራሳቸውን በአግባቡ ማስተዋወቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል። #ShegerFM | 2 338 |
| 12 | 🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻
8ኛ ዙር የእንግሊዘኛ ቋንቋ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!
ስልጠናዎቹ በሦስት ደረጃ ተከፍለው መሰረታዊ (A1 and A2)፣ ማዕከላዊ (B1 and B2) እና በከፍተኛ ደረጃ (C1 and C2) ተብለው የሚሰጥ ይሆናል።
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute | 2 843 |
| 13 | https://youtu.be/rNqQgwZHZhE?si=ECfwY6crU7Cf8wtB | 3 429 |
| 14 | https://youtu.be/rNqQgwZHZhE | 1 |
| 15 | በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች የሙከራ ፈተና ነገ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ጀምሮ የሚሰጥ በመሆኑ፤ በሚቀርባችሁ የፈተና መስጫ ማዕከል ከጠዋቱ 2:30 ተገኝታች የሙከራ ፈተናውን እድትወስዱ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።
Username እና Password መፈተኛ ማዕከሉ ስትደርሱ በጣቢያው ከሚመደቡ የፈተና ጣቢያ አስተባባሪዎች በኩል የምታገኙ መሆኑ ተገልጿል።
@minster_of_education | 4 115 |
| 16 | #ጥቆማ
በትምህርት ሚኒስቴር የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት አስያየም መመሪያ ቁጥር 1146/2018 መሰረት፤ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን አወዳድሮ መመደብ ይፈልጋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ለውድድር ክፍት ያደረጋቸው የሥራ መደቦች፦
1. የአካዳሚክ ምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት
2. የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት
3. ቺፍ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር ለጤና ሳይንስ ኮሌጅ (በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ)
ለተጠቀሱት ክፍት የአመራር ቦታዎች ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲሁም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውጪ ባለ በመንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ መስሪያ ቤቶች እና ድርጅቶች ውስጥ የሚገኙ ተወዳዳሪዎችን መወዳደር ይችላሉ ተብሏል፡፡
(ለእያንዳንዱ የአመራር የሥራ መደብ የተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶችን ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመለልከቱ፡፡)
የምዝገባ ሁኔታ፦
ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ፣ የብቃትና የሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ ህንፃ ቁ. 139፣ ቢሮ ቁ. 107 ወይም በኢሜይል አድራሻ፡ dtuhr2026@gmail.com ሰነዶችን በ PDF ፋይል በመላክ ወይም በፖ.ሳ.ቁ. 272 (ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ) መመዝገብ ይቻላል፡፡
@minster_of_education | 3 779 |
| 17 | #EthiopianPoliceUniversity
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ለ2019 የትምህርት ዘመን አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የመግቢያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጿል።
ይህ ማስታወቂያ በሁሉም የማስተርስ ዲግሪ፣ የቅድመ-ምረቃ ዲግሪ፣ የፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ (ለሲቪል ተመልማዮች)፣ በደረጃ 4 (ክሊኒካል ነርሲንግ፣ ሜዲካል ላቦራቶሪ እና ፋርማሲ) እንዲሁም በሁሉም ዲፕሎማ (ፖሊስ ሳይንስ፣ ፖሊስ ኢንተለጀንስ እና አቪዬሽን ፖሊስ) ፕሮግራሞች የተመዘገባችሁ አመልካቾችን በሙሉ የሚመለከት መሆኑ ተገልጿል፡፡
የተፈታኞች የትምህርት ማስረጃ ማጣራትና ኦሬንቴሽን መስከረም 04 እና 05/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 እስከ 6:00 እንዲሁም ከሰዓት ከ8:00 እስከ 11:00 ሰዓት በየተመደቡበት ማዕከል የሚከናወን መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የመግቢያ ፈተና መስከረም 06/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 እስከ 5:00 ሰዓት በሁሉም የፈተና ማዕከላት ይሰጣል ተብሏል።
አመልካቾች አስፈላጊ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውና ኮፒውን በመያዝ በተጠቀሱት ቀናት በፈተና ማዕከላት እንድትገኙ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
@minster_of_education | 2 797 |
| 18 | #Pioneer_College
🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ
የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️
ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦
► የሕክምና ዶክትሬት
► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት
► ፋርማሲ
► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ
🔔 ምዝገባ ጀምረናል!
በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ!
አድራሻ
ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ
☎️ 0902442244 / 0902443344
www.pioneercollege.edu.et | 2 379 |
| 19 | የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፉ የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ዕውቅና ሰጪ ቦርድ (ABET) ተጨማሪ ሁለት ፕሮግራሞቹ ሙሉ የጊዜ-ዑደት ዕውቅና አጊኝተዋል።
ዩኒቨርሲቲው የኬሚካል ኢንጂነሪንግ እና የኢንቫይሮንመንታል ኢንጂነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞቹ እስከ መስከረም 19/2025 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሙሉ የጊዜ-ዑደት ዕውቅና ማግኘታቸውን አሳውቋል።
ከዚህ ቀደም የዩኒቨርሲቲው የባዮቴክኖሎጂ፣ የምግብ ሳይንስና አፕላይድ ኑትሪሽን፣ የጂኦሎጂ እና የኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞቹ እስከ መስከረም 20/2024 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ዕውቅና ማግኘታቸው ይታወሳል።
ዕውቅናዎቹ የዩኒቨርሲቲውን ዓለም አቀፍ የትምህርት ጥራት የሚያረጋግጥ መሆኑ ተገልጿል።
@minster_of_education | 2 419 |
| 20 | #ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ
የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️
BSc Fields of Study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing
TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography
⭐️ የ CPD ማዕከል አገልግሎት!
☎️ 0913398780 / 0911596059
አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ
📍 Addis Ababa, CMC Square, Behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital
Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege
Tiktok: https://www.tiktok.com/@lorcan.medical.co | 2 628 |
