MINSTERY OF EDUCATION ©
For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ ለማግኘት እኛን ይከተሉ!! https://www.youtube.com/@minster_of_education Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام MINSTERY OF EDUCATION ©
کانال MINSTERY OF EDUCATION © (@minster_of_education) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 43 029 مشترک است و جایگاه 4 254 را در دسته آموزش و رتبه 750 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 43 029 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 16 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 77 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 13 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 10.42% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 4.99% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 4 485 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 2 148 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 7 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“For more information!
It’s all about education
Official minstry of education telegram channel join and get more info About us
✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ
ለማግኘት እኛን ይከተሉ!!
https://www.youtube.com/@minster_of_education
Ad:https://telega.io/c/minsterofeduca...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 17 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 17 ژوئن | +4 | |||
| 16 ژوئن | +23 | |||
| 15 ژوئن | +11 | |||
| 14 ژوئن | +10 | |||
| 13 ژوئن | +11 | |||
| 12 ژوئن | +6 | |||
| 11 ژوئن | +57 | |||
| 10 ژوئن | +55 | |||
| 09 ژوئن | +52 | |||
| 08 ژوئن | +29 | |||
| 07 ژوئن | +18 | |||
| 06 ژوئن | +23 | |||
| 05 ژوئن | +5 | |||
| 04 ژوئن | +25 | |||
| 03 ژوئن | +23 | |||
| 02 ژوئن | +3 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
| 2 | ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ መስክ የሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ትምህርት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡
ዩኒቨርሲቲው በኢኮኖሚክስ የትምህርት መስክ አዲስ የዶክትሬት መርሐግብር ለመጀመር የስርዓተ-ትምህርት ግምገማ አካሒዷል።
በግምገማ መድረኩ ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ባለስልጣን እና ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የተወከሉ ባለሙያዎች በአካል እና በዌቢናር ተሳትፈዋል።
በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በኢኮኖሚክስ የትምህርት መስክ በዶክትሬት ደረጃ ትምህርት የሚሰጥ ተቋም ባለመኖሩ ፕሮግራሙን በአካባቢው የመጀመሪያ ያደርገዋል ተብሏል።
ግምገማውን ተከትሎ የፀደቀው ስርዓተ-ትምህርት፣ የልማት ኢኮኖሚክስ፣ ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚክስና ንግድ እንዲሁም የፋይናንስ ኢኮኖሚክስ መስኮችን በዶክትሬት ዲግሪ ለማስተማር የተዘጋጁ መሆኑ ተገልጿል። | 1 111 |
| 3 | በ Lomi Study ፈተናዎች 10 ሺህ ብር ያሸንፉ!
ብቃትን የሚመዝኑ ፈተናዎችን በመውሰድ እውቀታችሁን አሳድጉ፤ ሳምንታዊ ተሸላሚ ሁኑ! ዛሬውኑ ይቀላቀሉ!
በ Lomi Study ምን ያገኛሉ?
● የፈተና ልምምድ
● ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ጋር ውድድር
● ሳምንታዊ ፈተናዎች ላይ በመሳተፍ የ 10,000 ብር ልዩ ሽልማት
Website:
https://lomistudy.com/r/lomi28
Telegram Bot:
https://t.me/Lomistudybot?start=lomi28 | 1 043 |
| 4 | የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የሥራ አመራር ቦርድ ለሁለት የተቋሙ መምህራን፣ ተመራማሪዎች እና የሕክምና ባለሙያዎች የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።
ቦርዱ የሁለቱን ባለሙያዎች የአካዳሚክ፣ የምርምር፣ የሕክምና አገልግሎት እና ተቋማዊ አበርክቶ ከገመገመ በኋላ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አፅድቋል፡፡
በዚህም ዶ/ር ሰለሞን አሊ እና ዶ/ር በረከት ፋንታሁን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት አጊኝተዋል፡፡
ዶ/ር ሰለሞን አሊ ማይክሮባዮሎጅስትና የሕክምና ምርምር ስፔሻሊስት ሲሆኑ፤ ከ20 ዓመታት በላይ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ እና በጅማ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት፣ በምርምር እና በሕክምና አገልግሎት እያገለገሉ የሚገኙ ባለሙያ ናቸው።
በተመሳሳይ ዶ/ር በረከት ፋንታሁን በኮሌጁ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሮፌሰር ሲሆኑ፤ በሙያቸው የህጻናት ሕክምና ስፔሻሊስት ናቸው፡፡ በሕጻናት ኢንዶክራይኖሎጂ ሕክምና ደግሞ የሰብ ስፔሻሊስት ስልጠና አላቸው፡፡ በሕክምና ትምህርት፣ በምርምር እና በጤና ሥርዓት ማጠናከር ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቶ ያላቸውና በአሁኑ ጊዜ በኮሌጅ በማገልገል ላይ የሚገኙ መሆኑ ከኮሌጁ የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡
| 2 156 |
| 5 | የመውጫ ፈተና እየወሰዱ የሚገኙ እናቶች
በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂ የሆኑ ሴት ተማሪዎች ልጆቻቸውን ከወለዱ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። እነዚህ ተማሪዎች የእናትነትን ኃላፊነት ከትምህርታዊ ግዴታቸው ጋር በማስታረቅ የመውጫ ፈተና በብርታት እየወሰዱ ይገኛሉ።
በተመሳሳይ ልጇን አዝላ የመውጫ ፈተና በመውሰድ ላይ የምትገኝ ብርቱ እናት በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተመልክትናል፡፡
የፅናት ምሳሌ ለሆኑ ለእነዚህ ተፈታኝ እናቶች መልካም ዕድል እንመኛለን።
| 1 938 |
| 6 | #ጥቆማ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን መቀበል ጀምሯል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ለ Masters ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች እንዲሁም ለ PhD ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች አመልካቾችን ይቀበላል፡፡
የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞቹን ዝርዝር በ https://admission.aau.edu.et/GraduatePrograms መመልከት ይችላሉ፡፡
አመልካቾች በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መውሰድና ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡
የ GAT ማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም | 2 573 |
| 7 | የ4ኛ ቀን የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተናዎች እየተሰጡ ነው፡፡ በዛሬው ውሎ የ24 ትምህርት አይነት ፈተናዎች ይሰጣሉ፡፡
የመውጫ ፈተና የ4ኛ ቀን መርሐግብር (ሰኔ 09/2018 ዓ.ም)
✅ ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:00-4:30 ሰዓት
✅ ፈረቃ 2: ጠዋት ከ5፡00-7:30 ሰዓት
✅ ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ08:30-11:00 ሰዓት
የመውጫ ፈተና እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም በኦንላይን ይሰጣል፡፡ ምስል፦ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ | 2 248 |
| 8 | #ጥቆማ
በ2018 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሬዚደንሲ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁና በተለያዩ ተቋማት የተመደባችሁ፤ ነገር ግን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ School of Medicine, General Surgery ትምህርት ዘርፍ ለመማር የምትፈልጉ ሐኪሞች እንድታመለክቱ ዩኒቨርሲቲው ጋብዟል፡፡
የምዝገባ ጊዜ፦ ከሰኔ 08-12/2018 ዓ.ም
የማመልከቻ አማራጮች፦
● Email: registrar@wku.edu.et
● በአካል በዩኒቨርሲቲው ዋና ሬጅስትራር ጽ/ቤት
ለተጨማሪ መረጃ፦ 0920204770
| 1 952 |
| 9 | 💥 የክረምት ስልጠና (ከ40% እስከ 60% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ለምትመዘገቡ) 💥
የጋዜጠኝነት ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!
በስልጠናው የተካተቱ፦
👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች፣ የሚዲያ እና የጋዜጠኝነት ዓይነቶች
👉 የዜና አሰራር እና የቃለመጠይቅ አደራረግ
👉 የመዝናኛ ፕሮግራም ጋዜጠኝነት፣ የፕሮግራም ዝግጅት፣ የማስታወቂያ አሰራር እና ዶክመንተሪ ዝግጅት
👉 የሞባይል እና የዩቲዩብ ጋዜጠኝነት
ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል!
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute | 2 093 |
| 10 | #HawassaUniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለዘጠኝ የተቋሙ መምህራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ሰጠ።
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ የዘጠኙ መምህራንን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት አፅድቋል።
የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ያገኙ፦
1. ዶ/ር አቻምየለሽ ገብረፃዲቅ ተክሌ - በ Public Health
2. ዶ/ር አለማየሁ ሙሉነህ ቢተው - በ Climate Change and Environmental Science
3. ዶ/ር አውደነገስት ሞገስ ባንጃው - በ Soil and Water Conservation
4. ዶ/ር ምህረት ዳናንቶ ዑልሲዶ - በ Water Supply and Environmental Engineering
5. ዶ/ር ሙሉጌታ ዳዲ በለጠ - በ Hydrology
6. ዶ/ር አንዳርጋቸው ገዴቦ አቢተአ - በ Plant Breeding
7. ዶ/ር ዘሪሁነ ግርማ ወ/ገብርኤል - በ Wildlife Ecology and Management
8. ዶ/ር ሁሴን ሞሐመድ በሽር- በ Horticultural Sciences
9. ዶ/ር ታረቀኝ ዮሴፍ ሳማጎ- በ Agronomy
https://t.me/minster_of_education | 3 202 |
| 11 | #ጥቆማ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በ 2019 ዓ.ም በ Human Rights የትምህርት መስክ የ2ኛ ዲግሪ እና የ3ኛ ዲግሪ (PhD) ፕሮግራሞች ለመማር ያመለክቱ!
ፍላጎት ያላቸውና ብቁ የሆኑ አመልካቾች እንዲያመለክቱ ማዕከሉ ጥሪ አድርጓል፡፡
ለዝርዝር መረጃ፣ መስፈርቶችን ለማየት እና የማመልከቻ መመሪያ ለማግኘት 👇
https://www.aau.edu.et/announcements/detail?title=Call~for~applications~for~admission~to~graduate~programs~for~the~First~Semester~of~2026/27~(2019~E.C.)~Academic~Year
አመልካቾች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ወስደው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡
https://t.me/minster_of_education | 2 780 |
| 12 | የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል/ከተማ አቀፍ ፈተና በተለያዩ ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሰጠት ጀምሯል።
ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል፡፡
https://t.me/minster_of_education | 2 548 |
| 13 | በኢንተርኔት የታገዘ የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም (IoT Smart Irrigation System) የሠሩ ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት የመጀመሪያው የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊዎች ሆነዋል፡፡
ኢንስቲትዩቱ ያዘጋጀው የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ምርምር ኮንፈረንስና የቴክኖሎጂ ውድድር ተጠናቋል።
በቴክኖሎጂ ውድድሩ ከ10 ሀገራት የተውጣጡ 35 ፈጠራዎች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን፤ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃን ሲይዙ፣ ናይጄሪያዊው ወጣት የፈጠራ ባለሙያ ሦስተኛ ደረጃን በማግኘት የነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።
የቴክኖሎጂ ውድድሩ አሸናፊዎች የሆኑት IoT Smart Irrigation System አንደኛ፣ የCerebro Logic ሁለተኛ እንዲሁም የናይጄሪያው Eco-Bin Revenue Intelligence and Traceability System ሦስተኛ ደረጃን አግኝተዋል።
የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም ቴክኖሎጂው እስከ 10ኪሜ ርቀት ላይ ያሉ የመስኖ እርሻዎችን ለመከታተልና አስፈጊውን ግባዓት ለማቅረብ የሚረዳ ነው።
https://t.me/minster_of_education | 2 424 |
| 14 | ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቁጥር ሦስት በአዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ላይ ትናንት ሰኔ 07/2018 ዓ.ም ተመርቋል።
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute | 2 716 |
| 15 | #ጥቆማ
ነጻ የክረምት ስልጠና ይከታተሉ!
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ-12ኛ ክፍል ለሆነ ተማሪዎች የክረምት ስልጠና አዘጋጅቷል።
የክረምት ስልጠና መስኮች፦
● ፋንዳሜንታልስ ኦፍ ኤ.አይ.
● ፕሮግራሚንግ
● ማሽን ለርኒንግ
● ሮቦቲክስ እና IOT
● ዳታ ሳይንስ
የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ሰኔ 30/2018 ዓ.ም
በተከታዩ የጉግል ፎርም ይመዝገቡ 👇
https://forms.gle/uDGPmQsiZcWWeNuRA | 3 785 |
| 16 | #HawassaUniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2.8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተሠሩ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል።
ዩኒቨርሲቲው በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል።
በዩኒቨርሲቲው የተመረቁ ስድስት ፕሮጀክቶች፦
● ልዩ የቀዶ ሕክምናና የወሊድ ፅኑ ህሙማን ክፍል
● የክሊኒካል ሙከራ ማዕከል (Clinical Trial Unit)
● የሕፃናት ቀዶ ሕክምና የልህቀት ማዕከል
● የጡት ወተት ባንክ (በኢትዮጵያ የመጀመሪያው)
● የኦክሲጅን ማምረቻና የሕክምና ጋዝ ሥርዓት
● የሕክምና ቆሻሻ ማቃጠያ (Incinerator)
ፕሮጀክቶቹ የጤና አገልግሎትን ለማስፋፋት፣ የኅብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ እና ጥራት ያለው ሕክምና ለማቅረብ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል ተብሏል። | 4 793 |
| 17 | በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተናዎች ከሰኔ 09-12/2018 ዓ.ም ይሰጣሉ። - የክልሉ ትምህርት ቢሮ
የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና
➫ ሰኔ 09 እና 10/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
የ8ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና
➫ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ | 3 704 |
| 18 | #ጥቆማ
የነርሲንግ አመራርና ሙያዊ አቅም ማጠናከሪያ ፕሮግራም ስልጠና ይውሰዱ!
ፍላጎት ያላችሁ የነርሲንግ ባለሙያዎች ምዝገባ እንድታደርጉ ጤና ሚኒስቴር ጋብዟል።
ብቃትን መሠረት ያደረገ ምልመላ ተከትሎ ሰልጣኞች አድቫንስድ ክሊኒካል የተግባር ዝግጁነት ስልጠና ይወስዳሉ። ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ የተረጋገጠ ዲጂታል ሰርተፊኬት የሚያገኙ ይሆናል።
የምዝገባ ጊዜ 👇
ከሰኔ 04-10/2018 ዓ.ም
ለማመልከት 👇
https://ncep.mohdigitalhealth.gov.et | 3 717 |
| 19 | #ጥቆማ
የሞሮኮ መንግሥት በ2026/27 የትምህርት ዘመን መስፈርቱን ለሚያሟሉ 50 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል።
በመሆኑም መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች ለዚሁ ዓላማ ተብሎ በተከፈተው ድረ-ገፅ www.marccalumni.ma በማመልከት የትምህርት ዕድሉ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር በቀን 26/09/2018 ዓ.ም ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ ገልጿል።
ለማመልከት 👇
www.marccalumni.ma
የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ሰኞ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም | 3 330 |
| 20 | በሚገኙበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ወይም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ያልተሰጣቸው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ስም ዝርዝርን እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉንም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች ጠይቋል።
በቀን 04/10/2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ኮራ ጡሹ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች የተጻፈ ደብዳቤ፣ ከሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ የመምህራኑ ዝርዝር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲላክ አዟል። | 3 093 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
