ግጥም ብቻ 📘
前往频道在 Telegram
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1
显示更多📈 Telegram 频道 ግጥም ብቻ 📘 的分析概览
频道 ግጥም ብቻ 📘 (@getem) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 63 100 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 784,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 522 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 63 100 名订阅者。
根据 16 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -241,过去 24 小时变化为 -17,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 14.16%。内容发布后 24 小时内通常能获得 3.95% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 8 939 次浏览,首日通常累积 2 492 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 76。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
@leul_mekonnen1”
凭借高频更新(最新数据采集于 17 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
63 100
订阅者
-1724 小时
-507 天
-24130 天
帖子存档
63 100
A SPARKLER
Even if that sun never rises,
I'm already bright with your lights.
The night becomes darker and darker,
but can't destroy your smile, a sparkler.
No way!
The black fog centered me like a core?
oh, I'm safer than ever before.
And if it's not going to end,
I'll choose to stay dead.
smelling your fragrance instead.
If this night finally decides to go away,
I still won't miss the sun anyway!
[ዓለም]
@mypoems396
@getem
@getem
@getem
63 100
ግዜ ደጉ
.
.
.
ልክ ለመሆን ላለመሳሳት
ወርቅ ዘመኔን መፈተን በ'ሳት
በፍጡር ይዘት በሰው ትከሻ
ፍፁም ካልሆንኩ ይሉት ንክሻ
ገጥሜ ትግል ውድቀት ሳላምጥ
ሰውንኳ መሆን ሲያቅተኝ በቅጥ...
ጊዜ ደግ አይደል...?
ካጓጉል ቅዠት ነክቶ ያባንናል
ወደቀ ያሉት በድሜ ይቃናል
ነብር ነኝ ባዩም ግልገል ይሆናል
ከሆዴ አራግፎ የጅል ኩራቴን
ፆም አስገድፎ ሰጠኝ እራቴን
የውስጤን ርሀብ በጉርሻ ዋጀው
አልጋ ትራሴን ከ'ረፍት አበጀው
ተመስገን አልኩ ልቤን ሳሳርፍ
መንፏቀቅ ትቼ በተሳቢ ረድፍ
መቆም ስጀምር ታየኝ መንገዱም
ለካስ ጉዞ ነው መንገዳገዱም
By Tadios Alemayehu
@getem
@getem
@paappii
63 100
ሳይፀልዩ ማደር
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የተራበ ነብር ከሩቅ ተመልክታ
ሚዳቆ ፀለየች "አውጣኝ አውጣኝ" አለች ለፈጠራት ጌታ
ነብሩም ተርቦ
ወደ አምላኩ ቀርቦ
አንጀቱ ከሆዱ እንደተጣበቀ
ፈቅዶ እንዲሰጠው አምላኩን ጠየቀ
የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውንም ሰማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምጹ ሚዳቆዋን አላት
"እሩጠሽ አምልጪ ከበረታው ጠላት።"
ነብሩንም አለው "እሩጥ ተከተላት
ምግብ አድርገህም ብላት"
ሚዳቆዋ ስትሮጥ
ከነብር ለማምለጥ
ነብሩም ሲከተላት
ሆዱን ሊሞላባት
ቋጥኙን ስትዘል እግሯ ተስፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛ ከርከሮ
ከእንቅልፉ ሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየው ነብር
አውጣኝ ያለው ወጥቶ አብላኝ ያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው ከርከሮ ተበላ።
By በረከት በላይነህ
@getem
@getem
@paappii
63 100
ደርሷል ትዕዛዛችን ፣ እንብላ ከእህሉ
አዘን አዘን የተቀመጥን ፣ ዳስዳስ ያለን ሁሉ
እንደአበሻ ገበሬ ፣ አርሶ እንዳጨደ
ነዶን ከምረን ፣ እጃችን ሰብል ያዘ
የመብቃትን ማዕረግ ፣ የመድረስን ከፍታ
እጃችን ጨብጦ ፣ ክንዳችን ባይገታ
ግና
ግና ሆዳችን ፣ አልጠገበም ሞልቶ
ሰው ሰው ተርቧል ፣ ወዳጁን አጥቶ
የእራሱ ራስ ከዳ ፣ የሆዱን ሆድ ፈጀ
ፍቅር እየዘራ ፣ አሜከላ አጨደ
ሰውን ሰው ራበው ፣ ሰውን ሰው ተጠማ
አበሻ በታሪኩ ፣ ዛሬ ብቸኝነት ደማ።
By ናትናኤል_አበበ
@getem
@getem
@getem
63 100
ትዝ ይልሻል?
የዛሬው ዋዜማ በጳጉሜ 5 አምና
ከበርሽ ነበርኩኝ
የሀሳቤን ልኖር ደጅሽን ስጠና
አይገርምም?
ድሮ ልንል በቃን እኒያ ቀናት አልፈው
ትዝብት ሊሆኑን በፊደል ተጽፈው
ይሄውልሽ አለሜ ይሄንን እወቂ
፡
እንዳለፈው ዘመን
ለእኔ ኑሪ እያለ
ደጅ ይጠናል ብለሽ እንዳትጠብቂ።
፡
ባይሆን
እኔ የምፈልገው
ይሄን አዲስ ዘመን ንጹህ እንቁ'ጣ'ጣሽ
ለሚመጣው ዓመት
:
ከሀሳቤ አሻግሮ
:
ከስኬቴ ጀርባ አምላክ አንችን ያምጣሽ።
ጳጉሜ ፭ ፳፻፲፰ እኩለ ሌሊት
By ይክበር ፀጋዬ
@getem
@getem
@paappii
63 100
አዲስ አመት
.
.
ያ...ጠቢብ ሰለሞን..........
ያማረ ቀለበት ከእጅሽ ያጠለቀዉ፤
ምን ያክል ዉበትሽ ልቡን ቢገዛዉ ነው?
ከአደይቷ ይልቅ ደምቀሽ ብትታይዉ፤
ሽንፈት የማያዉቀዉ ፍቅርሽ አሸነፈው።
ትዋቢበት ዘንዳ ዉብ እንቁን ለጣትሽ፤
ችግር ሲያገኝሽ ማለፊያ ለጣጣሽ፤
አንድም ለልብሽ ነዉ ማሰሪያ ለቃልሽ፤
ለቅድስቷ ምድር አንድም ለሀገርሽ።
የካም እድል ፈንታ እንቁ ዕጣ ለወጣች፤
ጸሎቷን ለማድረስ እጇን ለዘረጋች፤
ህመምሽ ለሆነች ፈዋሽሽም እሷዉ፤
ለቅድስቷ ምድር አንድም ለሀገርሽ ነው።
ዛሬም ለሀገሬ........
መከራ እንደ ሀምሌ ፀንቶ ላጨገጋት፤
ዉሽንፍር መባርቅት አብሮ ለሚንጣት፤
ቀለበትሽን አዉሻትና........
መከራዋ ያብቃ ነጭ ልብስ ትልበስ፤
ተስፋዋ ይለምልም በፍቅር ትታደስ፤
እንባዋ ታብሶ ብርሃን ይታያት፤
በዚ በአዲስ አመት ደግ ቀን ይዉጣላት።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
✍✍ዔደን
@topazionnn
@getem
@getem
63 100
"እኔ
ባዲስ ቀን አላምንም
ቀን ከቀን አልለይም
አሮጌ መሆን ነው የቀረኝ አንድ አቅም!"
የሚል ድባቴያም ሰምተህ ግን አታውቅም?!
ካደፈ ልብሱ አልፎ ከርሞ ልቡናውን እያስተባበረ
መስኮት ግድግዳውን እያሰማመረ
ድባብ የሚጨምር ደርሶ ባያየውም
እንዲህ ያለውንስ አላስተዋልኸውም?!
ግን
ከዚ ሁሉ ረቅቀን መጠቅ ነጠቅ ብለን፣
ከአይደለም እና አዎ መሃል ወጥተን፣
ካዲስነት ጀርባ ምን ታምር ታይቶሃል?፣
እውነትም ብርሃን ያለው ይመስልሃል?!
...
መልስ ያበጀህ እንደው ያጣህም እንደሆን
ወዴት ትሸሻለህ ተቀባይ ከመሆን?!
ሰው ፍጡር ነውና የለም የሚዘልለው፣
ከሚሆነው መሃል እንዳይሆን ሚነቅለው!
መቼም አለመቻል አስካቆረመደው
ሰውነት አንድ እርሙ መቀበል ብቻ ነው!
እናም..
ከመፈለግና ከመመኘት በስቲያ
እንደፈቃዳችን ከመናፈቅ ወዲያ
አዲስ ቀን ያው ቀን ነው መምጣቱን አይተውም፧
ተአምር ቢያመጣልን ወይ
አንዳች ባይፈጥርም፣
ከመኖር አይበልጥም።
አደይ ታብባለች ጠሃይ ትወጣለች
ህይወትም አትቀልልም፣
...
(ወደሚቀጥለው ብናልፍ አይሻልም?)
ለምኑም ለምኑም:(
@mypoems396
@getem
@getem
@getem
63 100
«ናፈቅሽኝ አቦ !» ብዬ የፃፍኩት
ኩራት ሲሰማኝ - ቀድጄ ጣልኩት ።
«ናፈቅከኝ በጣም» ብለሽ የፃፍሽው
ልምምጥ መስሎሽ
ወርውረሽ ጣልሽው ።
የፍቅር ብርሃን እንዳልተሰማን
ቅር እንዳላለን እንዳልናፈቅን
በአዲስ ወረቀት - ፀብ ተላላክን ።
እንበልና ...
እኒያ ወረቀቶች ...
ቀደን የጣልናቸው
የክረምት ጎርፍ አገናኛቸው ።
እስኪ አስቢያቸው ...
ደራሽ ተሳፍረው
ሆነው ጎን ለጎን
እርስ በርሳቸው ተያይተው ቢሆን ?
ምን ይሉ ይሆን ?
By Habtamu Hadera
@getem
@getem
@paappii
63 100
๘
ቃና አልባ ህይወቴ
የፈሰሰ ሀሞቴ
ጣዕም ፣
መልኩ ጠፍቶ ፡ የጠቆረ ወተቴ
ያ ‛መት ሙት አመቴ 𓏸 𓏸 𓏸
ተሰርዮልኛል ! !
....ተሰርዞልኛል...
እናትነት ፍቅርሽ ፡ ያለፍኩትን አይቶ
፤ አዝኖ ራርቶልኛል
ከአዘቅት እመቃት ፡ከባርያነት ግዞት
ለይቶ አንስቶኛል ⨳
ఎ
ማህፀንሽ ሳለሁ ኪዳን ገብተሽልኝ ያንቺን መልከ ስጋ ˔ ከእግዜር ገዝተሽልኝ . . . አገልግለሽኛል ተርበሽ ተጠምተሽ አሳድገሽኛል ꨄ𓏲 አፈር ግፈሽ ቅመሽ ርኩስ ፍጡር ወንድን በስራሽ አስንቀሽ ‟ቅድሚያ ላንተ” ብለሽ ከሰው እኩል አርገሽ አሁን ያለሁትን ፣ ነገ ምሆነውን . . . ሰውነቴን ሰራሽ ! { አበጀሽ ! አበጀሽ ! } 𓏲 እናት ሴት እናቴ ኅቡዕ ቃለ~ጥበብ ˔ የፀሎት ቅናቴ ከፈራረስኩበት ፣ ከወለገድኩበት ፣ ደርሰሽ አንከብክበሽ ፥ በፍቅርሽ መቅናቴ ⨳ 𖥔 [ ምን ትባል ፅዕዱቴ ? . . . በምን ስም ትጠራ ምድራዊ የሆነች የሰማያት ጣራ ] 𓏲 ስላንቺ ማንሳቱን ˔ ላልፈፅም ሰደርኩት ላላከትም ካደምኩት ቢሆንም ቢሆንም እንኳንም ጀመርኩት... < ግዴም ሆኖ ቢገኝ አበጀሁ > እሺ by ሰምረ የሽዋስ @getem @getem @getem
63 100
🔔 ውድ የቻናላችን አባላት፣ አዲስ የምስራች አለን!
የተመረጡ ግጥሞችን እና ሀሳቦችን, ወጎችን የምናጋራበትን ጉዞአችንን የበለጠ ለማሳደግ እና ጽሁፎቻችንን ባማረ ሁኔታ ለማቅረብ አዲስ Substack ገጽ ከፍተናል!
📌 ግጥሞች ለማንበብ እና አዳዲስ ጽሁፎቻችን በኢሜይል እንዲደርሷችሁ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው Substack ገጻችንን Subscribe ያድርጉ፡
https://substack.com/@getembicha
@getem
63 100
ትናንትን በዛሬ_!
ያቺ ትናንቴ ሀ--ሁ-- ዬ የነበረች፣
የሆነ ቀን ዛሬ ነበረች።
እንድያው ሳላስብ ዘንግቻት፣
ይሄው ዛሬ አስታወስኳት።
ቁጭ ብዬ በዛሬ ፊት ስታዘባት፣
የኳተነች ጎስቋላ ፊት የነበራት፣
በደስታ እና በፈተና የረሳዃት፣
ይሄው አሁን በዛሬ ፊት አነሳዃት።
ከፊቴ ፊት ቁጭ ብላ ስትስቅብኝ፣
ስጠብቃት ብን ብላ እንዳጠፋኝ።
ባትሆን ኖሮ የኔ ትናንት፣
ይችን ዛሬ-- አሁን ባልል ታምኜባት።
መምህሬ የኔ ትናንት፣
መቆሚያዬ የዛሬ እናት፣
የጉዞዬ እርሾ የነገዬ ርስት፣
የጉልበቴ ሰደፍ የዘመኔ ሽበት።
በ መ/ር ሰይድ: ነሐሴ 6, 2018
@getem
@getem
@getem
63 100
ውደቅ እስቲ ላንዴ
እንደ ጥልያን ጦር፣
ገላህ ይሸለታል
በጦር በጎራዴ።
፡
አንተ ባለ ክብር !
ላንዴ እስቲ አቀርቅር
መታሸት ያወዛው …
ጀርባህ ይነረታል ፣
በዱላ ና በትር።
:
ተገልጠህ ብታየው
ትከ’ሻህ ተከፍቶ
አናትህ አይተርፍም
በኮናኝ ተሞልቶ።
.
ፅጌረዳ የሰጠህ
በዘመንህ ወራት
እሾሁን ያስቀራል
ቅጠሏን አራግፏት።
:
ከፊት ስትቀርብ አይደል?
(እንደ ለቅሶ ንፍሮ)
ተዘግነህ ‘ምታልቀው
ልኬትህ ተሽሮ ?
:
ተሞልቷል ከተማው
በድንጋይ ፣ በምሳር
ዘንበል ያልህ ጊዜ
ተቋጥሮ ያመሻል
የፈካልህ ግንባር ።
:
ብቻ!
ወንዝ እንደወረደች
የገጠር ኮረዳ ፣
ላስቲክ ጫማዋ ስር
አዳልጧት በነበር
ረጢብ እንግጫ ፣
-
ሚዛን ስተህ ውደቅ
በቋጥኝ ፣ በጭንጫ ፤
፡
ያጨበጨቡ እጆች
ጉያህ ይሰርጋሉ፣
ደግሞ ለቁንጥጫ ።
(ሚካኤል አ)
@getem
@getem
@paappii
63 100
ተኳረፍኩኝ ካገሬ ጋር
ተሳቅቄ ሆኜ ከዳር
ጀርባየን አላምነውም
ጠላቴንም አላውቀውም
ማውቀውንም አላውቀውም
ባውቀውም አልንቀውም
መተንፈሻ አጣ አገሩ
ኩፍ በዛ በየዳሩ
ሰቀቀን በርዞታል
አይጥምም አየሩ
ዘር በዛ ባገሩ
አዲስ ጠፋች በአበባ
ሚሰቴ አሏት ባለቤቴን
ቀለበቴን አይቶ አገባ
አገሯ ዳር ናት
ሰውም ወድቋል ጥጉጥጉ
ሬሳው ሳይነሳ
ዘሩን ዘሩን እየፈለጉ
አዲስ አመት ባክህ ና
አታብቅል አበባ
ኢትዬጵያን ሚሏት ሀገር
ባይሆን ይዘህ ግባ
.
.
ግዕዝ ሙላት
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem
