en
Feedback
🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

Open in Telegram

ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

Channel 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 12 196 subscribers, ranking 7 397 in the Religion & Spirituality category and 2 756 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 12 196 subscribers.

According to the latest data from 05 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 68 over the last 30 days and by 9 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.34%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 13.70% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 089 views. Within the first day, a publication typically gains 1 670 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 40.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

12 196
Subscribers
+924 hours
+317 days
+6830 days
Posts Archive
✍ እንደዛሬ ትራቭልም ይሁን ፕሌን በሌለበት ዘመን ነው....... አንዱ ሐጅ ለማድረግ ከሀገሩ ቀደም ብሎ ጉዞ ይጀምራል። ጋራ ሸንተረሩን አልፎ፣ ድንበር ተሻግሮ በቶሎ ወደ ሐረም ይደርሳል። የደረሰው
እንደዛሬ ትራቭልም ይሁን ፕሌን በሌለበት ዘመን ነው.......   አንዱ ሐጅ ለማድረግ ከሀገሩ ቀደም ብሎ ጉዞ ይጀምራል። ጋራ ሸንተረሩን አልፎ፣ ድንበር ተሻግሮ በቶሎ ወደ ሐረም ይደርሳል። የደረሰው የሐጅ ስርዓት ከመጀመሩና ሑጃጆችም ከመግባታቸው በፊት ነበርና ወደ ሐረም ክልል ሲገባ ነፃነት ተሰማው። ወደ 🕋ካዕባ በመጠጋት እጆቹ ወደላይ አነሳና    🤲አላህ ሆይ! ሰዎች ሳያጨናንቁህ በፊት ሐጃዬን ፈፅምልኝ🤲 አለ /ይባላል/።   አላህ እንኳንስ ሑጃጆች... የምድር ኸልቆች በአጠቃላይ በአንድ ቅፅበት ቢጣሩት እንኳ የሚጨናነቅ (ቢዚ) የሚሆን ጌታ አይደለም። ✈️የለምለም ትራቭል ግን.......     ቀድማችሁ ካልተመዘገባችሁ በስተቀር በኋላ ላይ ብትመጡ "ሞልቷል" ተብላችሁ ልትመለሱ ትችላላችሁ። እናም........    ያለው ውስን ቦታ ሞልቶ ከመጨናነቁ በፊት አሁኑኑ ቀድማችሁ ተመዝገቡ።    እናተን ያለ እንግልት አስተናግዶ ለማስደሰት ሲባል ልዩ የክረምት የዑምራ ፓኬጅ ተዘጋጅቷል። ጊዜው እየደረሰ ነው ከሐምሌ_16 እስከ ሐምሌ_26 መካና መዲና መንሸራሸር የፈለገ አሁኑኑ ይደውል። 🤳 0911674580 🤳 0922448888 🤳 0911683917   ሁሌም ክፍት ናቸው።   በአካል መዘየርና መተዋወቅ ለፈለገ ቤተል ሚና_ሞል ሁለተኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን። ✈️የለምለም ትራቭል የትውልዱ ተስፋ!!

ኒቃብ ለብሳችሁ ጃኬት የምትደርቡ እና    ኒቃብ ለብሳችሁ 👡ሂል የምትጫሙ እህቶች;   "ከስጋው ጾም ነው ከመረቁ ስጭኝ" አይሆንባችሁም ወይ???

ሰለምቴዎችን ማሳቀቁም ማስቸኮሉም እብደት ነው!!    ብዙ ሰሓብዮች እስልምና በተቀበሉበት ቅፅበት ወድያው ተነስተው እስልምናቸው ግልፅ በማድረግ ሌሎችን ወደ እስልምና የመጥራት ዳዕዋ ይጀምሩ ነበር። ሰልመው ወደ እስልምና ለመጣራት "አንድ ጁዝ መሓፈዝ አለብህ ወይም ይህን ያህል ጊዜ መቆየት አለብህ" አይባሉም ነበር። «ከእኔ የሰማችኋት አንዲትም አንቀጽ ብትሆን አስተላልፉ» በሚለው መርህ ከረሱልﷺ የሰሙትን የተመለከቱትን ለማስተላለፍ ይቻኮላሉ። በዚህም የሚያነውራቸው አንድም አልነበረም። ምክንያቱም፦     ከረሱልየሰሙትን የተመለከቱትን ነውና የሚያስተላልፉት።     የሰማትን አንዲትም አንቀጽ ብትሆን ማስተላለፍ የሁሉም ሙስሊም ግዴታና ሀላፍትና ነው። ይህ ለማድረግ በእስልምና ተወልዶ በእስልምና ማደጉ መስፈርት አይደለም። ዛሬ ሰልሞ ዛሬ ሰምቶ ዛሬውኑ ማስተላለፍ ይችላል።    ወደ እስልምና ለመጠራት ሰለምቴም ላይ ይሁን በእስልምና ላረጀ ሰው የተቀመጠው መስፈርት ተመሳሳይ ነው;     «ከእኔ የሰማችኋት»  የረሱልﷺ አስተምህሮ መሆኑ መረጋገጡ ብቻ ነው። ንግግሩም ይሁን ተግባሩ ከቁርኣን ወይም ከሐዲስ መሠረት የሌለው ቀጠፋ ወይም ጥመት ከሆነ ግን; ተናጋሪው የራሱንና የተከታዮቹ ወንጀል ተሸክሞ ወደ እሳት የሚጓዝበት አደገኛ መንገድ ነው። «በእኔ ላይ የዋሸ መቀመጫው ከእሳት ያዘጋጅ» ብለው ከባድ 🚨ማስጠንቀቂያ አስቀምጠዋልና "ሰልሜያለሁ" በሚል ወኔ ብቻ ያልተረጋገጡና መሠረት የሌላቸው መፈክሮች በዳዕዋ ስም ለማስተላለፍ የሚሞክር ሰለምቴ ካለ ሸሽቶት የመጣው እሳት የማረፊያ ስፍራው ለማድረግ መንገድ እየጠረገ ነውና ሊቆጠብ ይገባዋል። የዳሰሳው ጭብጥ ሁለት ነጥቦች ናቸው፦ 1ኛው, የሰለመበት መቼት ሳይታይ ወደ እስልምና መጣራት የሁሉም ሙስሊም ሀላፍትና ነውና; አዳዲስ ሰለምቴዎች ይህንን በሚያደርጉ ጊዜ ስህተት ቢሰሩ እንደማንኛውም ሙስሊም ዳዒ መምከር ወይም ማውገዝ እንጂ;    ነውር የሰሩ ይመስል በሰለምቴነታቸው አሸማቅቆ ረድ ማድረግ አርቆ ካለ ማየት የሚመጣ ጠባብነት ነውና ይታረም፤ 2ኛው, የትኛውም ወደ እስልምና መጣራት የሚፈልግ አካል ጥሪው በዕውቀትና በመረጃ የተረጋገጠ መሆኑ ቀዳሚ መስፈርት ነውና ማንኛውም አካል ወደ ዳዕዋ ከመግባቱ በፊት የፀና እውቀት መያዝ አለበት። የጃሂል ዒባዳ ተመልሶ እዳ ነውና ያለ ዕውቀት መድረክ ላይ መውጣት ራስን ባልሰላ ሰይፍ ማረድ ነውና ከሁሉም ዕውቀት ይቅደም!!

🕋 ቢደጋገም የማይሰለች ሰበር!! የሁል ጊዜ ተወዳጅ እና ተመራጭ የሆነው የለምለም ትራቭል ልዩ የክረምት የዑምራ ፓኬጅ አዘጋጅቶ ምዝገባው ተጀምሯል። የአላህ ዕዝነት ይበልጥ በሚከጀልበት በክረምቱ ወ
🕋      ቢደጋገም የማይሰለች ሰበር!!   የሁል ጊዜ ተወዳጅ እና ተመራጭ የሆነው የለምለም ትራቭል ልዩ የክረምት የዑምራ ፓኬጅ አዘጋጅቶ ምዝገባው ተጀምሯል። አላህ ዕዝነት ይበልጥ በሚከጀልበት በክረምቱ ወቅት; ከሚወርደው በረካ እና ዕዝነት የተሻለውን ለመውሰድ የክረምቱ መግቢያ በአላህ ቤት ትቀበሉ ዘንዳ ዕድሉን ተጠቀሙበት።    የዑምራ ጉዞው የሚሆነው በአላህ ፍቃድ 👉 ከሐምሌ16 እስከ ሐምሌ26 👈 ወይም ከJuly23 እስከ August2 ይሆናል።   ረሱልሕያው ሆነው የተሰደዱባትና ሲሞቱም የተቀበሩባት መዲነቱል ሙነወራ ጨምሮ የተለያዩ ታሪካዊ ቦታዎች ዝያራ ያካተተው ፓኬጃችን ላይ ፈጥነው በመመዝገብ የማይረሳና ትክክለኛ ዑምራ ታደርጉ ዘንድ ትራቭላችን በአክብሮት ይጋብዛችኋል። 👉ፓኬጁ የሚያካትተው፦የተረጋገጠ የዑምራ ቪዛ፤የደርሶ መልስ የአየር ትኬት፤እስከ መመለሻው ቀን ሆቴል፤የተለያዩ ታሪካዊ ቦታዎች ዝያራ፤የመንቀሳቀሻ የባስ ትራንስፖርት ይገኙበታል። ✈️የለምለም ትራቭል.... የትውልዱ ተስፋ!! 🤳 0911674580 🤳 0922448888 🤳 0911683917        🏢 ቤተል ሚና ሞል 2ኛ ፎቅ ላይ  እንገኛለን። 👇   👇   👇   👇   👇   👇   👇 https://t.me/Yelemlem_travel

🕋 ቢደጋገም የማይሰለች ሰበር ዜና!!   የሁል ጊዜ ተወዳጅ እና ተመራጭ የሆነው የለምለም ትራቭል ልዩ የክረምት የዑምራ ፓኬጅ አዘጋጅቶ ምዝገባው ተጀምሯል። አላህ ዕዝነት ይበልጥ በሚከጀልበት በክረምቱ ወቅት; ከሚወርደው በረካ እና ዕዝነት የተሻለውን ለመውሰድ የክረምቱ መግቢያ በአላህ ቤት ትቀበሉ ዘንዳ ዕድሉን ተጠቀሙበት።    የዑምራ ጉዞው የሚሆነው በአላህ ፍቃድ ከሐምሌ16 እስከ ሐምሌ26 ወይም ከJuly23 እስከ August2 ይሆናል።   ረሱልሕያው ሆነው የተሰደዱባትና ሲሞቱም የተቀበሩባት መዲነቱል ሙነወራ ጨምሮ የተለያዩ ታሪካዊ ቦታዎች ዝያራ ያካተተው ፓኬጃችን ላይ ፈጥነው በመመዝገብ የማይረሳና ትክክለኛ ዑምራ ታደርጉ ዘንድ ትራቭላችን በአክብሮት ይጋብዛችኋል። ፓኬጁ የሚያካትተው፦ የተረጋገጠ የዑምራ ቪዛ፤ የደርሶ መልስ የአየር ትኬት፤ እስከ መመለሻው ቀን ሆቴል፤ የተለያዩ ታሪካዊ ቦታዎች ዝያራ፤ የመንቀሳቀሻ የባስ ትራንስፖርት ይገኙበታል። ✈️የለምለም ትራቭል.... የትውልዱ ተስፋ!! 🤳 0911674580     🤳 0922448888     🤳 0911683917        🏢ቤተል ሚና ሞል 2ኛ ፎቅ ላይ  እንገኛለን። 👇 👇 👇 👇 👇 👇 👇 https://t.me/Yelemlem_travel

ሁለተኛ እንዳገቡ ብዙ ወንድሞች ነግረውህ ሊሆን ይችላል;    ሦሥተኛ ወይም አራተኛ እንዳገባ የነገረህ ግን አንድም ሰው የለም። ካለም በጣም ጥቂት ነው። ምክንያቱም፦     ሐበሻ መከራ መከራውን እንጂ ሲደላው መንገር አይወድም።

ያልቸኮለ ብቻ ያንብበው!! በበፊቱ ጊዜ.......     አንድ ሰው ንግዱ ቢከስርበት; ዘመድ አዝማድ: ተሰብስቦ ሁሉም የየአቅሙን በማድረግ የከሰረው አካል በቶሎ እንዲያገግም እርዳታ ይደረግለት ነበር።    አንድ ሰው ሙሲባ ደርሶበት ቢጎዳ; ጎረቤቶቹ ተሰባስበው ከማፅናናት በተጨማሪ ለሙሲባው መካሻ የሚሆን ነገር በማቅረብ ቁስሉን አክመው ቀዳዳውን ይሸፍኑለት ነበር።    አንድ ሰው ከባድ ጉዳይ ቢገጥመው; ወዳጆቹና ጓደኞቹ ተጠራርተው ጉዳዩን እንደጉዳያቸው በማየት ሁሉም የድርሻው ተካፍሎ ሸክሙን ያቀሉለት ነበር። አሁን ላይ ግን......     አንዱ ችግር ደርሶበት ወደ ዘመዶቹ ቢመለከት; እነርሱ ላይ የደረሰው ችግር ከእሱው የከፋ ሆኖ ያገኘዋል፤      ደክሞ አቅም አጥቶ የጎረቤቶቹ እገዛ ፍለጋ ቢወጣ; ከእሱ ብሰው የደከሙ ሆነው ያገኛቸዋል፤    ሀሳቡን የሚጋራው: አድምጦ አቅጣጫ የሚያሳየው ጓደኛው ቢፈልግ; ጓደኛው ካለበት ውጥረት አንፃር የእሱው ቀላል እንደሆነ አምኖ ይመለሳል።     ይህ ብቻም አይደለም፨ በበፊቱ ጊዜ........     የሆነ ከበድ ያለ ህመም ታመህ ከሆነ; ሌላ ከባድ ህመም የሚገጥምህ ከብዙ ዓመታት በኋላ ነበር፤    ኪሳራ ቢደርስብህም; ቀጣይ ዓመታቶች በተሻለ ትበለፅጋለህ እንጂ ዳግም ሌላ ኪሳራ ማየትህ የተለመደ አልነበረም።    እንደውም "እከሌ ከሰረ" ማለት እንደ ሰበር ዜና ከስንት አንዴ የሚሰማ ዐረፍተነገር ነበር። አሁን ላይ ግን.......     ከታመምክ; ቀድሞ የጀመረህ የቱ እንደነበር እስከምትረሳው ድረስ ህመሞቹ ይደራረቡብሃል፤    አንዴ መስመር ስተህ ኪሳራ ከቀመስክ; መኖር እስክትጠላ ድረስ ይከታተልብብሃል። ዋሸሁ እንዴ?????? ያለነው ኣኺሩ ዘማን ላይ አይደለ??......    እንደ ጨለማ የተደራረቡ ፈተናዎች የሚመጡት "ዳዕዋ" ላይ ብቻ ሳይሆን: ፐርሰናል ላይፍ ላይም መሆኑን ተገንዝባችሁ ሸሪዓዊ መጠበቂያዎች እንድቲዙ ነው። አላህ በግዴታነት የደነገጋቸው ዒባዳዎች ከመፈፀም በተጨማሪ;     የጠዋትና የማታ አዝካር በቋሚነት መያዝ ከሁሉም ፈተና ለመጠበቅ ሰበብ ከሚሆኑ ትላልቅ ምሽጎች አንዱ ነው። 🤲ድብቅም ይሁን ግልፅ ከሆኑ ፊትናዎች ሁሉ አላህ ይጠብቀን!!

የበፊቶቹ.....   ለወር ለሁለት ወር ሳይገናኙ ቆይተው ሲገናኙ; "እንዴት ነህ? ቤተሰብ እንዴት ነው?" ከማለት ሌላ ዝርዝር አይጠያየቁም ነበር። ሆኖም አንዱ ለሌላው ግማሽ ሀብቱ ቢጠይቀው ሳያመነታ ይሰጠዋል። አሁን ላይ ግን......     ለአንድ ቀን ለሁለት ቀን ሳይገናኙ ቆይተው ሲገናኙ; ቤታቸው ውስጥ ስላለችዋ ዶሮ ሳይቀር ይጠያየቃሉ። አንደኛው ለሌላው የሳንቲም ስባሪ ቢጠይቀው ግን ሞቱን ይመርጣል እንጂ አውጥቶ አይሰጠውም።

ጥቂት ቀናቶች ናቸው የቀሩት; ቀጠሯችን ጀነት ነው!! እያሉ ይፅናኑ ነበር።

ለመኖር ስንደክም: መኖራችን ያበቃል!!

✍ ቢያለቅስ ዓይኔ በናፍቆት ቢቆራረጥሎት አንጀቴ: ልቤ ጠቋቁሯል በወንጀል እንጃልኝ እርሶን ማየቴ!! ካልደረሰልኝ ረሕማን የዕዝነት በሩን ከፋፍቶ የለኝም እኔስ መዳኛ ተከምሯል ወንጀሌ በዝቶ!!
✍     ቢያለቅስ ዓይኔ በናፍቆት             ቢቆራረጥሎት አንጀቴ: ልቤ ጠቋቁሯል በወንጀል          እንጃልኝ እርሶን ማየቴ!! ካልደረሰልኝ ረሕማን       የዕዝነት በሩን ከፋፍቶ የለኝም እኔስ መዳኛ   ተከምሯል ወንጀሌ በዝቶ!!

✍ እሷ ራሷ እሷን አትፈልጋትም: እንዴት አንተ ትፈልጋታለህ??? እሷ.... የራሷን መልክ ስለማትፈልገው በሜካፕ ትሸፍነዋለች፤ እሷ.... የራሷን ፀጉር ስለማትፈልገው ፈረስ_hair ትተክልበታለች፤ እ
እሷ ራሷ እሷን አትፈልጋትም: እንዴት አንተ ትፈልጋታለህ??? እሷ.... የራሷን መልክ ስለማትፈልገው በሜካፕ ትሸፍነዋለች፤ እሷ.... የራሷን ፀጉር ስለማትፈልገው ፈረስ_hair ትተክልበታለች፤ እሷ.... የራሷን ቅንድብ ስለማትፈልገው ቀብታ ትደብቀዋለች፤ እሷ.... የራሷን ጥፍር ስለማትፈልገው ሌላ ቁስ ትቀጥልበታለች፤ እሷ.... የራሷን (ስሙን የማልጠቅሰው ነገሯ) ስለማትፈልገው ስፖንጅ ወጥራ ትቀይረዋለች። እሷ ማለት እኮ፦    በሁለቱም እጆችህ ከፍ አርገህ እንደ አንሶላ ብታራግፋት.... የተቀጣጠሉ ነገሮቿ ሁሉ ይረግፉና ሌላ ፍጥረት መስላ የምትታይህ ስውር ሰው ናት!!    በራሷ አፍራ... ራሷን ደብቃ... በዚህ ልክ ራሷን ጠልታ የምትኖር ሴት ላይ;    ልቡ ተማርኮ... ራሱን ስቶ... እየተቁለጨለጨ የሚጃጃል ወንድ "ወንድ" ይባላል ወይ???

በአሁን ሰዓት "ወቅቱን ያልጠበቀ ወንጀል" ማለት ኩራት ነው፦ ኩራት (በራስ መደነቅ)፦     ሊመጣ የሚችለው አንድ ሰው ከሌሎቹ የተሻለ ሲሰራ፤ ከሌሎቹ የተሻለ ሲጥራራ፤ ከሌሎቹ የበለጠ.... እና በተለያዩ ነገሮች ከሌሎቹ ተሽሎ ሲገኝ ነበር። አሁን ላይ ያለው ተጨባጭ ያስተዋለ ግን;    አንዱ ከሌላው የበለጠ ሲሳነፍ፤ ከሌላው የበለጠ ሲግማማ፤ ከሌላው የበለጠ ሲወርድና ሲወድቅ እንጂ የተሻለ ሆኖ የሚገኝ ማየት ብርቅ ሆኗል። አንተ ከእሱ የሻልክ  እንደሆንክ የምታየው አካል;     እሱ ከአንተ ስለ ባሰ እንጂ አንተ ከእሱ ተሽለህ አይደለም። አንተ ከእሱ የበለጠ ጥንቁቅ እንደሆንክ የምታየው አካል;    እሱ ከአንተ የበለጠ ስለተጃጃለና ስለደከረተ እንጂ አንተ ጥንቁቅ ሆነህ አይደለም።    በቀን አንድ ገፅ እንኳ ዊርድ የለህም; የጀምዐ ሰላት መስገድ ያቃተው ስታይ ከእሱ እንደተሻልክ ይሰማሃል። እውታው ግን፦     እሱ ከአንተ ብሶ እንጂ አንተ ከእሱ ተሽለህ አይደለም።    ዓይንህ እንኳ መቆጣጠር አቅቶህ ከሄደች ከመጣችዋ ጋ ይኳትናል; ከአጅነብይ ጋ ተጨባብጦ የሚያወራ ስታይ ከእሱ እንደተሻልክ የሰማሃል። እውነታው ግን፦     እሱ ከአንተ ብሶ እንጂ አንተ ከእሱ ተሽለህ አይደለም።    ከጌታህ ጋ በሚስጥር ያስቀመጥካት አንዲትም የተደበቀች መልካም ስራ የለህም; ሱሪው እየጎተተ ጺሙን የሚልጭ ሰው ስታይ ከእሱ የተሻልክ ይመስልሃል። እውነታው ግን፦    እሱ ከአንተ ብሶ እንጂ አንተ ከእሱ ተሽለህ አይደለም።    ስድስት ሰባት ዓመታት ሁሉ ከአንዲት ሚስት ጋ ብቻ እየኖርክ ነው; ትራሱን ታቅፎ የሚተኛው ላጤ ስታይ ከእሱ የተሻልክ ይመስልሃል። እውነታው ግን፦    እሱ ከአንተ ብሶ ነው እንጂ አንተም እንደ እኩዮችህ "ሁለት... ሦሥት... አራት" መደርደር ነበረብህ። ሲጠቃለል......    በዚህ ዘመን አንዱ ከሌላው የሚብስ እንጂ: አንዱ ከሌላው የሚሻል ማግኘት ሩቅ ነገር ሆኗል። ደካማ ሆነህ ሳለ;     ጭራሽ የዘቀጡትን እያየህ ራስህን የምታጥራራ ከሆነ =>ከድክመትህ ባሻገር ጅህልናህም እያሳየህ ነውና ተቆጠብ!!   

"ሞትህን.... ሞተህ አትጠብቀው" /ከታክሲ ጥቅሶች/ የወደዳችሁት ካለ አካፍሉን👇

✍ በየቤቱ ገብተህ መከራውን ብታይ፣ ብሶቱን ብትሰማ ያለበትን ስቃይ፤ ይገባህ ነበረ ያለህበት ፀጋ፣ ታመሰግን ነበር ሲመሽም ሲነጋ!! በየቤቱ ሕይወት ከብዷቸው: ሞት አስፈርቷቸው: በመኖርና ባለ መኖር
በየቤቱ ገብተህ  መከራውን ብታይ፣ ብሶቱን ብትሰማ  ያለበትን ስቃይ፤   ይገባህ ነበረ   ያለህበት ፀጋ፣ ታመሰግን ነበር  ሲመሽም ሲነጋ!!   በየቤቱ ሕይወት ከብዷቸው: ሞት አስፈርቷቸው: በመኖርና ባለ መኖር መሃል ሆነው በስቃይ ላይ ያሉት ሁሉ 🤲አላህ ፈረጃውን ያቅርብላቸው።

"ሁለት ጊዜ ሐጅ አድርጌያለሁ" እንደማይባለው ሁሉ;   "ሁለት ሚስት ነው ያለኝ" ተብሎ አይነገርም፤ ሁለቱም ትላልቅ ዒባዳዎች ናቸው!!

ዓሊም ይኑር!!    አንዱ ለኢማሙ አሕመድ "በህልሜ ጀነት ውስጥ አይቼሃለሁ" አለው። ኢማሙ ሲመልሱለት፦    "ህልም ለሙእሚን ታስደስተዋለች እንጂ አታስተኛውም። አንተ ለእኔ ያልከኝ ነገር ለእንትናም ይታይለት ነበር: እሱ ግን አሁን ላይ የኸዋሪጆች አመለካከት አራማጅ ሆኗል።" አለው።

ይህ ከባድ ነው!!    "አንድም ባሪያ ከወንጀሉ ወደ አላህ ተውበት አያደርግም....   ☝️አላህ የተውበቱን እውነተኛነት ሊፈትነው የወንጀሉ መንገድ ቢያመቻችለት ቢያገራለት እንጂ።"             /ኢማሙ ሺንቂጢ/

👆 የልሙጦች መከራ ቀላል ነው ኣ የሚመስላችሁ!!
👆     የልሙጦች መከራ ቀላል ነው ኣ የሚመስላችሁ!!

✍     የጠመሙ ሰዎች ቢሆኑ እንኳ; ሲዋረዱ ብታይ ለነገው ራስህ ፈርተህ ልትተናነስ እንጂ ልትሳለቅ አይገባህም!! ጁበይር ኢብኑ ኑፈይር ይባላል የሚነግረን👇    "ቁብሩስ የተባለችዋ ግዛት ድል አድርገን በከፈትናት ጊዜ የቀጠናዋ ነዋሪዎች ከፊሉ ከከፊሉ ጋ ሆነው በደረሰባቸው ሽንፈት ይላቀሳሉ።  አቡ ደርዳዠም ለብቻው ተነጥሎ ተቀምጦ ሲያለቅስ አየሁት። ወደሱ ሄጄ……   "አቡ ደርዳ ሆይ! ዛሬ አላህ ኢስላምና ሙስሊሞችን የበላይ ባደረገበት በደስታችን ቀን ምንድን ነው ያስለቀሰህ? " አልኩት ሲመልስልኝ………   "ጁበይር ሆይ! እንደው ፍጥረታት የአላህን ትዕዛዝ በሚተዉ ጊዜ ምን ያህል አላህ ዘንድ የተዋረዱ ናቸው?" ይኸውልህ ተመልከት……   "እነዚህ እኮ ንግስና የነበራቸው ሀያል እና አሸናፊ ህዝቦች ነበሩ: የአላህን ትዕዛዝ በተዉ ጊዜ እንዲህ እንደ ምታያቸው ሆኑ። አለኝ" ይላል።                  ማስተዋሉን ይስጠን!!