en
Feedback
🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

Open in Telegram

ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

Channel 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 12 187 subscribers, ranking 7 244 in the Religion & Spirituality category and 2 754 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 12 187 subscribers.

According to the latest data from 29 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -32 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.01%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 11.95% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 559 views. Within the first day, a publication typically gains 1 456 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 29.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 30 August, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

12 187
Subscribers
-724 hours
-77 days
-3230 days
Posts Archive
ማርጀት እንጂ መሸምገል የጠፋበት ዘመን!!    ለዚህ አባባል ቋሚ ምሳሌ "ኢብራሂም ቱፋ" ነው። ይህ ሰው እውነቱ ለማውራት ከአፉ የወጡ ቃላቶች ግማት ከመቀመጫው ከሚወጣው ንጥረ ነገር የከረፉ ናቸው። ያልተማረ መሃይም ሊሆን ይችላል: ግን እንዴት ዕድሜው አይገስፀውም። ለነገሩ ከላይ እንዳየነው ነው የሚያረጅ የሚሸብት እንጂ የሚሸመግል ሰው የጠፋበት ዘመን ነው። ባይሆንማ ፀጉሩ በሽበት የነጣ ሰው ምላሱ እንዲህ ጠቁሮ ከተናጋሪው በፊት አድማጭ የሚያስደነግጥ ንግግር ባልተናገረ ነበር። ያለውን ሰምታችኋል???……………     "ከነብዩ ሙሐመድ በኋላ የሚላክ ነብይ የለም እንጂ ዐብይ አሕመድ “ነብይ” እንለው ነበር፤ የሚላክ ነብይ ስለሌለ “ወልይ” ብለነዋል"    ይህ ንግግር ምድር ተሰንጥቃ ተናጋሪው ልትውጠው በቂ አይደለም ነው የምትሉኝ?? እንዳለመታደል ሆኖ ዑመርና የዑመር በትር የሉም እንጂ: ይህንን ምላስ ለተሸከመ ጭንቅላት መድሃኒቱ እሱ ነበር። የኢብራሂም ቱፋ ንግግር ትርጉሙ ምን መሰላችሁ፦   "ዐብይ አሕመድ ነብይ ለመሆን ሁሉም መስፈርት አሟልቶ ነበር: ነገር ግን ከሙሐመድ በኋላ የሚላክ ነብይ ስለሌለ ብቻ ነው ነብይ ያልሆነው።" ማለት ነው። ዐብይ አሕመድ ማን ነው????     አላህ በሁሉም ሙከለፎች ላይ ግዴታ ያደረገው, ወደ አላህ መድረሻ ብቸኛው መንገድ የሆነው እስልምና ትቶ ወደ ኩፍር የሄደ ሰው ነው። በግልፅ ሸሪዐ የዚህ ዓይነቱ "ሙርተድ" ተብሎ ይሰየማል። [ኢብራሂም ቱፋ ጋ ግን ነብይ ወይም ወልይ] ለቱፋ ልጅ የሚጠየቀው ብቸኛው ጥያቄ;     ምንም እንኳ ከነብዩ ሙሐመድﷺ በኋላ የሚላክ ነብይ ባይኖርም ከእሳቸው በፊት ግን ብዙ ነብያቶች ተልከዋል፤ ከእነርሱ መሃል "ካፊር" ሆኖ የተላከ አንድ ነብይ ጥቀስልን??!! ምክንያቱም: በአንተ አነጋገር መሠረት ዐብይ አሕመድ ኩፍሩም ላይ ሆኖ ነብይ ሊሆን በቂ ነበርና¡¡    እንደው ምን ብትበላ ምን ብትሰበስብ ምን ቃል ቢገባልህ ነው እንዲህ ከካካህ የከረፋ ቆሻሻ በአፍህ መትፋት የቻልከው?? እንደው ምላስህ እንዴት ታዘዘልህ?? ቃላቶቹ እንዴት ችለህ ተናገርካቸው?? አይገርመንም!! የአላህ ነብይ ቀድመው ነግረውናልና፦ «مَا ذِئْبَانِ جَائِعَانِ أُرْسِلَا فِي غَنَمٍ، بِأَفْسَدَ لَهَا مِنْ حِرْصِ الْمَرْءِ عَلَى الْمَالِ وَالشَّرَفِ لِدِينِهِ»    «ሁለት የተራቡ ተኩላዎች በበግ መንጋ ላይ ገብተው የሚያደርሱት ውድመት:   አንድ ሰው ለገንዘብና ለስልጣን ብሎ ዲኑ ላይ ከሚያደርሰው ውድመት የከፋ አይሆንም።» እንደው ስለዚህ ካወራን አይቀር……………    ዐብይ አሕመድ ምንም ሳይል እንዲህ የሆኑለት ሰ_ዎች ነገ ደፈር ብሎ "ነብይ ነኝ" ቢል አቋማቸው ምን ይሁን የሚሆነው?????

ወደ አላህ ተጓዦች ሁሉም የተስማሙበት ነጥብ ነው፦        ልቦች ጌታቸው ጋ እስኪደርሱ ድረስ የልባቸውን መሻት አያገኙም፤     ጤናማና ሰላማዊ ልብ እስካልሆኑ ድረስም ጌታቸው ጋ መድረስ አይችሉም፤     እንዲሁም ህመማቸው ራሱ ወደ መድኃኒት እስኪቀየር ድረስ ጤናማና ሰላማዊ ሊሆኑ አይችሉም!!    ይህ ሊሳካ የሚችለው ደግሞ የነፍስን ፍላጎት በመቃረን ብቻ ነው። ምክንያቱም፦    የነፍስ ፍላጎት ለልብ ህመሙ ነው: እሱን መቃወም ደግሞ መድኃኒቱ ነው!!      [ሸይኹል ኢስላም ኢብኑል ቀይም]

የህሊና ረፍት……… ምላስህ ስለ አንተ ማሳመን ሲያቅተው: አላህ አንተን ወክሎ ይከላከልልሃል!!    መርየም ዓለይሃ ሰላም በውሸት ተወነጀለች፤ ልጅዋን ይዛ በሕዝቧ ፊት ስትቆም የተከሰተውን ነገር ለእነሱ ለማስረዳት አቅም አልነበራትም። 📖﴿يَا أُخْتَ هَارُونَ مَا كَانَ أَبُوكِ امْرَأَ سَوْءٍ وَمَا كَانَتْ أُمُّكِ بَغِيًّا﴾.   {አንቺ የሀሩን እህት ሆይ! አባትሽ ክፉ ሰው አልነበረም፤ እናትሽም ዝሙተኛ አልነበረችም።} አሏት   ሆኖም; እሷ ግን ክርክር ውስጥ አልገባችም። ረጅም ማብራሪያም አልሰጠችም። ብቻ ግን፦ 📖﴿فَأَشَارَتْ إِلَيْهِ﴾. {ወደ እሱ (ሕፃኑ) ጠቆመች።}    አላህ ማንንም ባልጠበቀው መንገድ ተከላካይ ሆነላት፤ አንቀልባ ላይ የነበረውን ሕፃን እንዲናገር አደረገው። 📖﴿إِنِّي عَبْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَابَ وَجَعَلَنِي نَبِيًّا﴾.    {እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፤ መጽሐፍን ሰጥቶኛል፤ ነብይም አድርጎኛል።}      ሰዎች እንዲረዱህ አትቸኩል፤ ስለ አንተ ለተባለው ሁሉ መልስ ለመስጠት በመሞከርም ራስህን አታድክም። ምላስህ እውነትን ለማስረዳት አቅም ሊያጣ ይችላል፤ ነገር ግን እውነትን ለመግለጥ አላህ የሚሳነው ምንም ነገር የለም።   ለራስህ ለመከላከልም አትቸኩል፤ አላህ ፈጽሞ ባላሰብከው መንገድ ይከላከልልሃል።

👆 🤝
👆 🤝

✍     ለሊት የጠየቅነው ነገር ጠዋት ፊት ለፊታችን ሆኖ እናገኘዋለን!!        [ይሉ ነበር ከፊል ሰለፎች] 👇 👉የሙእሚን ጉዳይ ማስፈፀሚያው የለይል ሰላት ናት!!

✍      አንዳንድ ጊዜ ደግሞ እንዲህ ይሆናል; ብቸኛ ባሪያው  የሆንክ እስኪመስልህ ይንከባከብሃል!!

✍      ከአላህ በስተቀር ምንም ነገር ባልቀረልህ ጊዜ... ተስፋ አትቁረጥ!! 📖{فَنَادَى فِي الظُّلُمَاتِ أَن لَّا إِلَهَ إِلَّا أَنتَ سُبْحَانَكَ إِنِّي كُنتُ مِنَ الظَّالِمِينَ ★ فَاسْتَجَبْنَا لَهُ وَنَجَّيْنَاهُ مِنَ الْغَمِّ وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُؤْمِنِينَ}   {በጨለማዎችም ውስጥ ሆኖ  "ከአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፤ ​​አንተ ጥራት ይገባህ፤ እኔ ከበደለኞቹ ነበርኩ" ሲል ጠራ። ★ እኛም ለርሱ ተቀበልነው፤ ከጭንቀትም አዳነው፤ እንዲሁም አማኞችን እናድናለን።}   ተስፋ ለማጣት የሚያነሳሱ ምክንያቶች በተከማቹበት፣ በሰው ልጅ አስተሳሰብ መፍትሔ ማግኘት የማይቻል በሚመስልበት እና ጥፋት ከየአቅጣጫው በተጋረጠበት ወቅት… በአላህ ላይ ያለው ተስፋ ያልጠፋበት አንድ ልብ ነበር።    የባሕር ጨለማ፣ የሌሊቱ ጨለማ እና የአሳ ነባሪው ሆድ ውስጥ ባለው ጨለማ በተከበበበት ሁኔታ ውስጥ የነበረ ልብ……   ሆኖም፧ ያንን ጨለማ ከአላህ የበለጠ አድርጎ አላየውም። ስለዚህ እንዲህ ሲል ጥሪውን አቀረበ፦ {ከአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፤ ​​አንተ ጥራት ይገባህ።}   ከዚያም: የሰው ልጅ ሊያደርግለት በማይችለው መንገድ መፍትሄ መጣለት።   {እኛም ለርሱ ተቀበልነው፤ ከጭንቀትም አዳነው።}   በመቀጠልም……  ይህ አንቀጽ ከዩኑስﷺ ታሪክ ባሻገር ለአንተም የሚሆን መልካም ብስራት ያስተላልፋል፦ 📖{وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُؤْمِنِينَ} {እኛም አማኞችን እንደዚሁ እናድናለን።} ይህንን አስተንትን………    የዩኑስ መዳን የአንድ ታሪክ ማብቂያ ብቻ አልነበረም፤ ይልቁንም በራሳቸው የጨለማ ጊዜ ውስጥ ለሚያልፉ አማኞች ሁሉ የተሰጠ የተስፋ ቃል ነበር።   ምናልባት አማራጮችህ እየጠበቡ፣ ሰዎች ሊታደጉህ የማይችሉበት ሁኔታ ላይ ሆነህ እንዲሁም በምድራዊ ስሌት መፍትሄ ማግኘት የማይቻል መስሎ ሊታይህ ይችላል።  ሆኖም፧ በወቅቱ ሁኔታህ ላይ ያለው አስቸጋሪ መሰናክል የአላህን ኃይል ታላቅነት እንድትረሳ አያድርግህ። 🤲ዱዐ ለማድረግ ጨለማው እስኪገፈፍ ድረስ አትጠብቅ፤ ይልቁንም በዚያው ጨለማ ውስጥ ሆነህ አላህን ጥራው!! ምክንያቱም፦    ዩኑስን ከአሳ ነባሪው ሆድ ያወጣው ጌታ አንተንም እጅግ አስቸጋሪና ጠባብ ከሆነ ሁኔታህ ውስጥ ለማውጣት ሙሉ ኃይል አለው!! 📖{وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُؤْمِنِينَ}

✍      ከአላህ በስተቀር ምንም ነገር ባልቀረልህ ጊዜ... ተስፋ አትቁረጥ!! 📖{فَنَادَى فِي الظُّلُمَاتِ أَن لَّا إِلَهَ إِلَّا أَنتَ سُبْحَانَكَ إِنِّي كُنتُ مِنَ الظَّالِمِينَ ★ فَاسْتَجَبْنَا لَهُ وَنَجَّيْنَاهُ مِنَ الْغَمِّ وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُؤْمِنِينَ}   {በጨለማዎችም ውስጥ ሆኖ  "ከአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፤ ​​አንተ ጥራት ይገባህ፤ እኔ ከበደለኞቹ ነበርኩ" ሲል ጠራ። ★ እኛም ለርሱ ተቀበልነው፤ ከጭንቀትም አዳነው፤ እንዲሁም አማኞችን እናድናለን።}   ተስፋ ለማጣት የሚያነሳሱ ምክንያቶች በተከማቹበት፣ በሰው ልጅ አስተሳሰብ መፍትሔ ማግኘት የማይቻል በሚመስልበት እና ጥፋት ከየአቅጣጫው በተጋረጠበት ወቅት… በአላህ ላይ ያለው ተስፋ ያልጠፋበት አንድ ልብ ነበር።    የባሕር ጨለማ፣ የሌሊቱ ጨለማ እና የአሳ ነባሪው ሆድ ውስጥ ባለው ጨለማ በተከበበበት ሁኔታ ውስጥ የነበረ ልብ……   ሆኖም፧ ያንን ጨለማ ከአላህ የበለጠ አድርጎ አላየውም። ስለዚህ እንዲህ ሲል ጥሪውን አቀረበ፦ {ከአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፤ ​​አንተ ጥራት ይገባህ።}   ከዚያም: የሰው ልጅ ሊያደርግለት በማይችለው መንገድ መፍትሄ መጣለት።   {እኛም ለርሱ ተቀበልነው፤ ከጭንቀትም አዳነው።}   በመቀጠልም……  ይህ አንቀጽ ከዩኑስﷺ ታሪክ ባሻገር ለአንተም የሚሆን መልካም ብስራት ያስተላልፋል፦ 📖{وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُؤْمِنِينَ} {እኛም አማኞችን እንደዚሁ እናድናለን።} ይህንን አስተንትን………    የዩኑስ መዳን የአንድ ታሪክ ማብቂያ ብቻ አልነበረም፤ ይልቁንም በራሳቸው የጨለማ ጊዜ ውስጥ ለሚያልፉ አማኞች ሁሉ የተሰጠ የተስፋ ቃል ነበር።   ምናልባት አማራጮችህ እየጠበቡ፣ ሰዎች ሊታደጉህ የማይችሉበት ሁኔታ ላይ ሆነህ እንዲሁም በምድራዊ ስሌት መፍትሄ ማግኘት የማይቻል መስሎ ሊታይህ ይችላል።  ሆኖም፧ በወቅቱ ሁኔታህ ላይ ያለው አስቸጋሪ መሰናክል የአላህን ኃይል ታላቅነት እንድትረሳ አያድርግህ። 🤲ዱዐ ለማድረግ ጨለማው እስኪገፈፍ ድረስ አትጠብቅ፤ ይልቁንም በዚያው ጨለማ ውስጥ ሆነህ አላህን ጥራው!! ምክንያቱም፦    ዩኑስን ከአሳ ነባሪው ሆድ ያወጣው ጌታ አንተንም እጅግ አስቸጋሪና ጠባብ ከሆነ ሁኔታህ ውስጥ ለማውጣት ሙሉ ኃይል አለው!! 📖{وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُؤْمِنِينَ}

መንገድ ላይ ስትገጣጠም ባላየ የሚያልፍህ ሁላ;     ወደ መቅበራ ስትወሰድ ጀናዛህ ለመሸከም ይጋፋል ይሻማል።    ጀናዛ በሚሸኝበት ጊዜ ለመሸከም የሚደረገው ሽሚያ ስታይ;     በሕይወት ሳለ የረሱትን የተዉትን ቀዷ እያወጡ እኮ ነው የሚመስለው።

ለብቻህ በተነጠልክ ጊዜ የሰውነት ክፍሎችህ ፀጥታ እንዳይሸውድህ። ሁሉም ድምፅ አውጥተው የሚናገሩባት የሆነች አንዲት ቀን ትመጣለችና!! 📖{ٱلْيَوْمَ نَخْتِمُ عَلَىٰٓ أَفْوَٰهِهِمْ وَتُكَلِّمُنَآ أَيْدِيهِمْ وَتَشْهَدُ أَرْجُلُهُم بِمَا كَانُوا۟ يَكْسِبُونَ}

ለአንድ ሰው ሙሉ ዱንያ ከመጀመሪያዋ እስከ መጨረሻዋ ቢሰጠውና ከዚያም ሞት ቢመጣበት;    ሁኔታው ​​ልክ በመናሙ የሚያስደስት ነገር አይቶ ከእንቅልፉ ሲነቃ በእጁ ምንም ነገር እንደማያገኝ ሰው ይሆናል።         [ዑመር ኢብኑል ኸጣብ]

✍ ሰብስቦ ሲሰጥ እንዲህ ነው!! ራሱ ሰሓብይ፤ አባቱ ሰሓብይ፤ እናቱ ሰሓብይ፤ አያቶቹ ሰሓብይ፤ ቅድመ አያቱ ሰሓብይ የሆኑለት ሰሓብይ!! ትልቁ ሰሓብይ ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር፦ ከሂጅራ በኋላ በእስል
ሰብስቦ ሲሰጥ እንዲህ ነው!! ራሱ ሰሓብይ፤   አባቱ ሰሓብይ፤    እናቱ ሰሓብይ፤     አያቶቹ ሰሓብይ፤      ቅድመ አያቱ ሰሓብይ የሆኑለት ሰሓብይ!! ትልቁ ሰሓብይ ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር፦      ከሂጅራ በኋላ በእስልምና የተወለደ የመጀመሪያው ሰሓብይ ነው። አባቱ => ዙበይር ኢብኑ ዐዋም። እናቱ => አስማእ ቢንት አቢበክር። አያቶቹ => አቡበክር ሲዲቅ እና ሰፍያ ቢንት ዐብዱል ሙጦሊብ። ቅድመ አያቱ => አቡ ቁሓፋ ዑስማን ቢን ዓሚር አል_ቁረይሺ። ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር፦      ገና በአስራ አራት ዓመቱ ታዋቂው የየርሙክ ዘመቻ ተካፍሏል። እንዲሁም ኸሊፋ ዑስማን ቢን ዓፋን ወደ አፍሪካ ለሚገኘው የሙስሊም ጦር ከላኳቸው የድጋፍ ኃይሎች መካከል አንዱ ነበር፤ በዚያም ለጦሩ ድልን ያስገኘ ወታደራዊ ክህሎትና ብቃት አሳይቷል። 120,000 ቁጥር የነበረውን የሮማውያን ጦር ሰራዊት መስመር ሰብሮ በመግባት አዛዣቸውን መግደል ችሏል። ይህ ድርጊት የሮማውያንን ኃይል በመበታተን ለሙስሊሞች ድል ምክንያት ሆኗል። ከዚያም በኋላ ኢብኑ ዙበይር የአፍሪካን ድል የመክፈቻ ዘመቻ ላይ ተሳትፏል።

የሕይወት ስንቅ!! {وَعَدَ ٱللَّهُ ٱلْمُؤْمِنِينَ وَٱلْمُؤْمِنَـٰتِ جَنَّـٰتٍ تَجْرِى مِن تَحْتِهَا ٱلْأَنْهَـٰرُ خَـٰلِدِينَ فِيهَا وَمَسَـٰكِنَ طَيِّبَةً فِى جَنَّـٰتِ عَدْنٍ ۚ وَرِضْوَٰنٌ مِّنَ ٱللَّهِ أَكْبَرُ ۚ ذَٰلِكَ هُوَ ٱلْفَوْزُ ٱلْعَظِيمُ}    {አላህ ምእመናንና ምእምናትን ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸውን ጀነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲሆኑ በመዘውተሪያ ጀነቶችም ውስጥ መልካም መኖሪያ ቤቶችን ቃል ገብቶላቸዋል፡፡ ከአላህም የሆነው ውዴታ ከሁሉ የበለጠ ነው፡፡ ይህ እርሱ ታላቅ እድል ነው፡፡}    እቺን ሀረግ አስተውላት {አላህ ቃል ገብቷል} ቃል ኪዳኑ ከአላህ ሲሆን: ስለ ውጤቱ መጨነቅ አያስፈልግም። ይህ አንቀጽ ስለ ወደፊቱ ጊዜ ደስታ ብቻ አይናገርም፤ ይልቁንም በጉዞህ ላይ ልብህን የሚያረጋጋ መልእክትም ጭምር ነው።   ልትሰናከል ትችላለህ... እርምጃህ ሊያመነታ ይችላል... መንገዱ ሊከብድህ ይችላል... እንዲሁም የጥረትህን ፍሬ አሁን ላይታይህ ይችላል። ሆኖም፧ በልብህ ውስጥ እምነት እስካለ ድረስና በሕይወትህ ውስጥ መልካም ሥራዎች እስካሉ ድረስ መንገድህን አልሳትክም።   አላህ ፍፁም እንከን-አልባ እንድትሆን አይጠይቅህም፤ ይልቁንስ ከስህተትህ በኋላ ሁሌ ወደ እሱ መመለስህን እንድትቀጥል፤ ከራስህ ጋር እንድትታገል፤ በመልካም ነገር ላይ እንድትጸና እና መሰናከል ተስፋ ለመቁረጥ ምክንያት እንዳይሆን እንድታደርግ ይጠይቅሃል። ለዚህም ነው ገና እዚያ ሳትደርስ የምስራቹ የሚመጣው፦ {አላህ ቃል ገብቷል}    ፍሬውን ለማየት አትቸኩል؛ የጉዞው ገሚስ ተጉዘህም አትፍረድበት።    አሁን እንደ ድካም ብቻ የምታየው ነገር؛ አላህ ዘንድ የተወደደ ጥረት ነው።    እፎይታው የዘገየ የሚመስለውም ነገር;  የገባው ቃል ኪዳን ከመፈጸም አንጻር የዘገየ አይደለም። ልብህን አረጋጋ!! ምክንያቱም፦    ቃል የገባው ቃሉን የማያፈርስ አካል ነው።   ቃል ኪዳኑ እውነት ነው። ጉዞውም ምንም ያህል ረጅም ቢሆን መጨረሻ አለው። ﴿رَبَّنَا لَا تُزِغْ قُلُوبَنَا بَعْدَ إِذْ هَدَيْتَنَا وَهَبْ لَنَا مِن لَّدُنكَ رَحْمَةً ۚ إِنَّكَ أَنتَ الْوَهَّابُ}

✈️     ልዩ የዑምራ ፓኬጅ!!     ሁለት ጁሙዐዎች በሁለቱ ሐረሞች በመስገድ: 3ቀናት ለረሱልየስደት ማረፊያ በሆነችው መዲነቱል ሙነወራ እና    7 ቀናቶች ነብያችንተወልደው ባደጉባት፤ ከምድር ገፅ ሁሉ በላጭና ዱንያ ላይ ያሉ ምእመናን በአጠቃላይ ተቀጣጭተው በሚሰግዱባት መከተል ሙከረማህ ቆይተው፤     የረሱልእና የምርጥ ባልደረቦቻቸው ቀብር ዘይረውና ሰልመው፤    መስጂድ አል_ቁባዕ ዘይረውና ረከዐተይን ሰግደው፤    ረውደቱል ሸሪፋ ዘይረው: ረከዐተይን ሰግደው: ጌታዎትን ተመሳጥረው፤    ወደ አላህ ይበልጥ ቀርበው ዱንያና አኼራዎትን የሚያሳምርሎት ከሙኻለፋ የጠራ: ሱናውና አዳቡን የጠበቀ 🕋ዑምራ🕋 መፈፀም የሚያስችሎት ልዩ የዑምራ ፓኬጅ አዘጋጅተናል።    በሀገራችን በተለያዩ ምክንያቶች በተከታታይ ስራ ዝግ በሚሆንባቸው የወከባና የግርግር ቀናቶች;      ከመስከረም 14  _  መስከረም 24 የሚቆይ 10ኛ ዙር ልዩ የዑምራ ፓኬጅ ተዘጋጅቷል።    ከፈለጋችሁ በVIP  ከፈለጋችሁም በNORMAL መመዝገብ ትችላላችሁ።   ለሁለቱም ሐረሞች ቅርብ የሆኑ ምቹና ዘመናዊ ሆቴሎች በማዘጋጀት በቤተሰባዊ እንክብካቤ ልንኻድማችሁ ተዘጋጅተናል። የሁል ጊዜ ምርጡና ተመረጭ ትራቭል =>የለምለም የጉዞ ወኪል!! ፓኬጁ የሚያካትተው…… 📨ዓመታዊ የዑምራ ቪዛ፤ ✈️ደርሶ መልስ የአየር ትኬት፤ 🏨በሁለቱም ሐረሞች የሆቴል ክፍያ፤ 🚌በሁለቱም ሐረሞች ዘመናዊ የባስ ትራንስፖርት፤ 🛣በሁለቱም ሐረሞች የተለያዩ ቦታዎች ዝያራ፤ ያስተውሉ…   አብረው ለሚመጡ ጥንዶች ልዩ መስተንግዶ ይደረጋል!! አሁኑኑ ይደውሉ  🤳  0911674580                        🤳  0911683917                       🤳  0922448888 ቤተል "ሚና_ሞል"  2ኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን። ✈️የለምለም ትራቭል የትውልዱ ተስፋ!! https://t.me/Yelemlem_travel

⚫️ በሰው ልጆች ታሪክ የተሰማው ክፉ መርዶ!!   ዐብዱረሕማን ቢን ዑሰይላ አል_ሰናቢሒ የሕይወቱ መራራ ገጠመኝ እንዲህ ይተርከዋል፦    "ረሱልለመገናኘትና የሱሕባ ክብር ለማግኘት ከየመን ተሰደን ወጣን። ልክ ጁሕፋ① የተባለው ቦታ ስንደርስ አንድ ጋላቢ ወደኛ ሲመጣ ተመለከትን። እኔም “መዲና ውስጥ ምን አዲስ ነገር አለ?” ብዬ ጠየኩት; ”دفنا رسول الله ﷺ منذ خمس ليالٍ“   “የአላህ መልእክተኛﷺ ከቀበርናቸው አምስት ቀን ሆኖናል።” አለኝ።" ይላል።   ከየመን ሀገር ተነስቶ፤ ጋራና ሸንተረር አቋርጦ፤ ኮረብታው ወጥቶ ቁልቁለቱን እየወረደ በአላህ ነብይ ናፍቆት የነደደው ልቡ ፊታቸውን በማየት ለማስታገስና ዕድሜ ልኩን ከሚሰራው ዒባዳ ሁሉ በላጭ የሚሆንለት የሱሕባ ማዕረግ ለማግኘት ጓጉቶ የመጣን ናፋቂ;    "ረሱልﷺ ከቀናት በፊት ቀብረናቸዋል" የሚሉ ተራራ የመናድ ክብደት ያላቸው ቃላቶች ሲሰማ እግሮቹ እንዴት ችለው ተሸክመውት ይሆን????

✍     ቁርኣን ውስጥ ከተጠቀሱ ከንቱ ምኞቶች ውስጥ……… 📖{يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي} {"ዋ ምኞቴ! ምነው ለሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡}    [አል_ፈጅር:24] 📖{وَيَقُولُ الْكَافِرُ يَا لَيْتَنِي كُنتُ تُرَابًا} {ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምን ነው ዐፈር በሆንኩ ይላል።}     [አል_ነባእ:40] 📖{وَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ بِشِمَالِهِ فَيَقُولُ يَا لَيْتَنِي لَمْ أُوتَ كِتَابِيَهْ} {መጽሐፉንም በግራው የተሰጠውማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡}     [አል_ሓቃ:69] 📖{وَيَوْمَ يَعَضُّ الظَّالِمُ عَلَىٰ يَدَيْهِ يَقُولُ يَا لَيْتَنِي اتَّخَذْتُ مَعَ الرَّسُولِ سَبِيلًا} {በዳይም «ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በሆነ ዋ ምኞቴ!» እያለ (በጸጸት) ሁለት እጆቹን የሚነክስበትን ቀን (አስታውስ)፡፡}     [አል_ፉርቃን:27] እነርዚህ ሁሉ………    አንድ ሟች ምንም ነገር መስራትና መቀየር  በማይችልበት ቀን በቁጭት ከሚያሰማቸው ከንቱ ምኞቶቹ ውስጥ ከፊሎቹ ናቸው። እኔና አንተ ግን………     ዛሬ ላይ በተሰጠን ዕድል ሁሉም ነገር ሰርተን ነፍሳችን ከዚህ ከንቱ ምኞት እና ቁጭት መታደግ እንችላለን!! ዋናው ጥያቄ………     የሚነቃ የሚያስተውል አለ ወይ??? ነው። 🖊ሐምዱ ቋንጤ ከፉርቃን ሰማይ ስር!!

በሕይወት ውዝግብ ግራ ለተጋባ ሁሉ……የመንገድህ ግማሽ ተጉዘህ በሕይወትህ ተስፋ አትቁረጥ!!    ሁኔታዎች ሲወሳሰቡ፤ በሮች ከፊትህ ሲዘጉ፤ መንገዱ በጭጋግ ሲሸፈን እና በልብህ ውስጥ ያሉ ጥያቄዎች ከምታገኘው ውጤት ሲበዙ; ስለ ሕይወትህ ታሪክ ለመፍረድ አትቸኩል!! ምክንያቱም፦   አሁን ላይ ያልተገለፀልህ ነገር ሁሉ ክፉ አይደለም እንዲሁም ህመም የፈጠረብህ ነገር ሁሉ መጨረሻህ አይደለም። አላህ ያወሳልን ታሪኮች ተመልከት……... ኑሕ ዐለይሂ ሰላም፦     በአላህ ትዕዛዝ መርከብ ሲሠራ: ህዝቦቹ የብስ ላይ መርከብ እየሰራ የሚጃጃል ሰው አርገውት ያፌዙበት ነበር። ኑሕም ነገ ምን እንደሚከሰት ዝርዝር ሁኔታውን አያውቅም ነበር; የሚያውቀው አንድ ነገር ብቻ ነበር => መርከብ እንዲሰራ አላህ እንዳዘዘው። 📖 {وَاصْنَعِ الْفُلْكَ بِأَعْيُنِنَا وَوَحْيِنَا} ኢብራሂም ዐለይሂ ሰላም፦     በመናሙ ልጁን ሲያርድ ተመለከተ። የጌታውን ትዕዛዝ ለመፈፀም እስከ መጨረሻው ቅጽበት ድረስ ተጓዘ። ከዝያም የአላህ ፈረጅ መጣለት; 📖 {وَفَدَيْنَاهُ بِذِبْحٍ عَظِيمٍ} የሙሳ እናት፦      የትኛዋ እናት ልቧ እሺ ብሏት ጨቅላ ህፃኗ ወንዝ ውስጥ የምትወረውር ይመስልሃል?? ግና የአላህ ትዕዛዝ ነበር; 📖 {وَأَوْحَيْنَا إِلَى أُمِّ مُوسَى أَنْ أَرْضِعِيهِ فَإِذَا خِفْتِ عَلَيْهِ فَأَلْقِيهِ فِي الْيَمِّ وَلَا تَخَافِي وَلَا تَحْزَنِي إِنَّا رَادُّوهُ إِلَيْكِ}   ከዝያም የአላህ ቃል_ኪዳን እውን መሆኑን ታምን ዘንዳ አላህ ልጇን ወደሷ መለሰላት። ኡሙ ኢስማኢል ሀጀር፦      አላህ እንደማይተዋት እርግጠኛ ከመሆኗም ጋ ቁጭ ብላ ተኣምር እስኪመጣላት አልጠበቀችም። ይልቁንስ ሰፋ እና መርዋ መሃል ተመላልሳ እየሮጠች መፍትሔ ፍለጋ ታገለች። በመጨረሻም ጭራሽኑ ባልገመተችው ቦታ አላህ በዘምዘም ፈረጃት።   በእያንዳንዱ ታሪክ ውስጥ አስፈሪ የሚመስሉ ክስተቶች ነበሩ። ነገር ግን መጨረሻቸው አላህ ወደ ስኬት የሚያደርስ መንገድን እያዘጋጀባቸው እንደነበር አሳየ። ስለዚህ፦   በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ያለው መሰናክል ጌታህ ላይ መጥፎ እንድታስብ ምክንያት አይሁንብህ። አንተ የምታየው አሁን ያለውን ነው; አላህ ግን ከዚያ በኋላ ያለውን ያውቃል።   አንተ የተዘጋውን በር ነው የሚታይህ; ነገር ግን ለምን እንደተዘጋ አይታይህም።   አንተ መዘግየቱን ነው የሚታይህ; ነገር ግን ጉዳዩ ቀደም ብሎ ቢፈጸም ኖሮ ሊጎዳህ የሚችለውን ነገር አይታይህም። አንተ የመንገዱን መጥበብ ነው የሚታይህ; ነገር ግን አላህ በዚያ ጠባብ መንገድ በኩል ወዴት እየመራህ እንደሆነ አታውቅም።   ሁሌም ድብቅ ምስጥሩን ማወቅ አይጠበቅብህም; ይልቁንም የማይታየውን በሚያውቀው አምላክ እንድታምን ነው የሚጠበቅብህ። ልክ እንደ ኢብራሂም ታገስ!! ልክ እንደ ሀጀር ጥረት አድርግ!! ልክ እንደ ኑሕ አስፈላጊውን እርምጃ ውሰድ!! ልክ ለሙሳ እናት የነበራት ዓይነት የቂን ይኑርህ!! ከአንተ ችሎታ ውጪ የሆነውን ሁሉ ለአላህ አደራ ስጥ!! 📖 {وَمَن يَتَّقِ اللَّهَ يَجْعَل لَّهُ مَخْرَجًا ★ وَيَرْزُقْهُ مِنْ حَيْثُ لَا يَحْتَسِبُ وَمَن يَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ فَهُوَ حَسْبُهُ} እንግዲያውስ;     የመንገድህ ግማሽ ተጉዘህ በሕይወትህ ተስፋ አትቁረጥ!!    አሁን እያሳመመህ ያለው ክስተት; ምን አልባትም ለነገው ስኬትህ አንዱ ድልድይ ሊሆን ይችላል!!    አሁን ላይ ተዘግቶብህ ያስለቀሰህ በር; ምን አልባትም ሊያጠፋህ የነበረው ሙሲባ ከዚህ በር ጀርባ የነበረ ሊሆን ይችላል!!    የምኞትህ መዘግየት; ምን አልባትም አላህ የተሻለው እያዘጋጀልህ ስለሆነ ሊሆን ይችላል!! ሁል ጊዜ አላህ የሚሰራውን ማወቅ አይጠበቅብህም;      አላህ አዛኝና ጥበበኛ መሆኑ ማወቅህ በቂ ነው!! ይህንንም ዕወቅ 👇    በዚህ መንገድ እየተጓዝክ ያለኸው ብቻህን አይደለህም!! ሕይወት ተወሳስቦ ግራ በሚገባህ ጊዜ: ልብህ በፅኑ ይመንና እንዲህ በል;    "አላህዋ ምን እንደሚከሰት አላውቅም: እንደማትተወኝ ግን አውቃለሁ!!" ለኑሕ በመርከብ ከማዕበል ያዳነው አላህ፤ ለሙሳ እናት ህፃኗን መልሶ ያሳቀፈው አላህ፤ ለኢብራሂም ከትልቅ ፈተና በኋላ ቅያሪ ያደረገው አላህ፤ ለሀጀር ከበረሀ እምብርት ዘምዘም ያፈለቀው አላህ፤   ለአንተም ባላሰብከው መልኩ ሊፈርጅህ ቻይ ነው!! 📖{إِنَّ اللَّهَ بَالِغُ أَمْرِهِ قَدْ جَعَلَ اللَّهُ لِكُلِّ شَيْءٍ قَدْرًا} 🖊ሐምዱ ቋንጤ ከፉርቃን ሰማይ ስር!!

✍ ውዴታቸው ካለህ ለሰው ልጅ አለቃ መንዙማህን ትተህ በሐዲስ ተብቃቃ። ብትወዳቸውማ ሰይዱል አንቢያ ሱናቸው ለያዘ ባላልክ ወሀቢያ። አፍህ ይሞግታል የረሱል ውዴታ ስራህ ተቃራኒ የሚያስቆጣ ጌታ። ወንድ
✍    ውዴታቸው ካለህ  ለሰው ልጅ አለቃ መንዙማህን ትተህ  በሐዲስ ተብቃቃ። ብትወዳቸውማ   ሰይዱል አንቢያ   ሱናቸው ለያዘ   ባላልክ ወሀቢያ። አፍህ ይሞግታል  የረሱል ውዴታ ስራህ ተቃራኒ  የሚያስቆጣ ጌታ።   ወንድና ሴት አብሮ  ሆኖ በአንድ ቤት መውሊዳቸው ብሎ  ይላል ሰለዋት ምን ዓይነት ሰለዋት  ምን ዓይነት ውዴታ      ረሱል በጀነት   አንተ ሌላ ቦታ?? ወዳጅ ለወደደው  ይታዘዛል እንጅ ክልከላው ተላልፎ  አያነሳም ፈንጅ። በልብህ ውስጥ ካለ  የነብዩ ፍቅር ልደታቸው ሳይሆን   ትዕዛዛቸው አክብር።      🖌ሐምዱ ቋንጤ

💵 የሰው ልጅ ተፈጥሮ ከገንዘብ ጋ ጥብቅ ቁርኝት አለው። አንድ ሰው ገንዘብ በሚያገኝ ጊዜ ነፍሱ የአካል ብቃትና የአእምሮ መነሳሳት ታገኛለች!! [ይህ ሀኪሞችም ዘንድ የተረጋገጠ ምርምር ነው።]
💵      የሰው ልጅ ተፈጥሮ ከገንዘብ ጋ ጥብቅ ቁርኝት አለው። አንድ ሰው ገንዘብ በሚያገኝ ጊዜ ነፍሱ የአካል ብቃትና የአእምሮ መነሳሳት ታገኛለች!!       [ይህ ሀኪሞችም ዘንድ የተረጋገጠ ምርምር ነው።]

     የሰው ልጅ ተፈጥሮ ከገንዘብ ጋ ጥብቅ ቁርኝት አለው። አንድ ሰው ገንዘብ በሚያገኝ ጊዜ ነፍሱ የአካል ብቃትና የአእምሮ መነሳሳት ታገኛለች!!       [ይህ ሀኪሞችም ዘንድ የተረጋገጠ ምርምር ነው።]