uz
Feedback
🇞🇊ሐምዱ ቋንጀ🇵🇞

🇞🇊ሐምዱ ቋንጀ🇵🇞

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰሚት በማድሚግ ዚመልካም ቀደምቶቻቜን ፋና በመኹተል ስለ እስልምናቜን ዚምንማማርበት እና ዚምንመካኚርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ ዹሌለው መፍትሔ ነው‌ 👇🏟👇🏟👇🏟 @hamdquante አስተያዚትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali 🇞🇊ሐምዱ ቋንጀ🇵🇞 analitikasi

🇞🇊ሐምዱ ቋንጀ🇵🇞 (@hamdquante) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 12 180 obunachidan iborat bo'lib, Din & MaÊŒnaviyat toifasida 7 244-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 754-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

МевіЎПЌП sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 12 180 obunachiga ega bo‘ldi.

29 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -32 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 21.01% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 11.95% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 559 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 456 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 29 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰሚት በማድሚግ ዚመልካም ቀደምቶቻቜን ፋና በመኹተል ስለ እስልምናቜን ዚምንማማርበት እና ዚምንመካኚርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ ዹሌለው መፍትሔ ነው‌ 👇🏟👇🏟👇🏟 @hamdquante አስተያዚትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 30 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & MaÊŒnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

12 180
Obunachilar
-724 soatlar
-77 kunlar
-3230 kunlar
Postlar arxiv
✍ ዹህሊና ሚፍት    ምላስህ ስለ አንተ ማሳመን ሲያቅተው: አላህ አንተን ወክሎ ይኹላኹልልሃል!!    መርዹም ዓለይሃ ሰላም በውሞት ተወነጀለቜፀ ልጅዋን ይዛ በሕዝቧ ፊት ስትቆም ዹተኹሰተውን ነገር ለእነሱ ለማስሚዳት አቅም አልነበራትም። 📖يَا أُخْتَ هَارُونَ مَا كَانَ أَُؚوكِ امْرَأَ سَوْءٍ وَمَا كَانَتْ أُمُّكِ َؚغِيًّا.   {አንቺ ዚሀሩን እህት ሆይ! አባትሜ ክፉ ሰው አልነበሚምፀ እናትሜም ዝሙተኛ አልነበሚቜም።} አሏት   ሆኖም; እሷ ግን ክርክር ውስጥ አልገባቜም። ሹጅም ማብራሪያም አልሰጠቜም። ብቻ ግን፩ 📖فَأَ؎َارَتْ إِلَيْهِ. {ወደ እሱ (ሕፃኑ) ጠቆመቜ።}    አላህ ማንንም ባልጠበቀው መንገድ ተኚላካይ ሆነላትፀ አንቀልባ ላይ ዹነበሹውን ሕፃን እንዲናገር አደሚገው። 📖إِنِّي عَؚْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَاَؚ وَجَعَلَنِي نَؚِيًّا.    {እኔ ዹአላህ ባሪያ ነኝፀ መጜሐፍን ሰጥቶኛልፀ ነብይም አድርጎኛል።}      ሰዎቜ እንዲሚዱህ አት቞ኩልፀ ስለ አንተ ለተባለው ሁሉ መልስ ለመስጠት በመሞኹርም ራስህን አታድክም። ምላስህ እውነትን ለማስሚዳት አቅም ሊያጣ ይቜላልፀ ነገር ግን እውነትን ለመግለጥ አላህ ዚሚሳነው ምንም ነገር ዚለም።   ለራስህ ለመኹላኹልም አት቞ኩልፀ አላህ ፈጜሞ ባላሰብኚው መንገድ ይኚላኚልልሃል።

✍     ለሊት ዹጠዹቅነው ነገር ጠዋት ፊት ለፊታቜን ሆኖ እናገኘዋለን!!        [ይሉ ነበር ኹፊል ሰለፎቜ] 👇 👉ዚሙእሚን ጉዳይ ማስፈፀሚያው ዹለይል ሰላት ናት!!

✍      አንዳንድ ጊዜ ደግሞ እንዲህ ይሆናል; ብ቞ኛ ባሪያው  ዹሆንክ እስኪመስልህ ይንኚባኚብሃል!!

✍      ኹአላህ በስተቀር ምንም ነገር ባልቀሚልህ ጊዜ... ተስፋ አትቁሚጥ!! 📖{فَنَادَى فِي ال؞ُّلُمَاتِ أَن لَّا إِلَهَ إِلَّا أَنتَ سُؚْحَانَكَ إِنِّي كُنتُ مِنَ ال؞َّالِمِينَ ★ فَاسْتَجَؚْنَا لَهُ وَنَجَّيْنَاهُ مِنَ الْغَمِّ وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُ؀ْمِنِينَ}   {በጚለማዎቜም ውስጥ ሆኖ  "ኹአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ ዚለምፀ ​​አንተ ጥራት ይገባህፀ እኔ ኚበደለኞቹ ነበርኩ" ሲል ጠራ። ★ እኛም ለርሱ ተቀበልነውፀ ኚጭንቀትም አዳነውፀ እንዲሁም አማኞቜን እናድናለን።}   ተስፋ ለማጣት ዚሚያነሳሱ ምክንያቶቜ በተኚማቹበት፣ በሰው ልጅ አስተሳሰብ መፍትሔ ማግኘት ዚማይቻል በሚመስልበት እና ጥፋት ኚዚአቅጣጫው በተጋሚጠበት ወቅት  በአላህ ላይ ያለው ተስፋ ያልጠፋበት አንድ ልብ ነበር።    ዚባሕር ጚለማ፣ ዚሌሊቱ ጹለማ እና ዚአሳ ነባሪው ሆድ ውስጥ ባለው ጹለማ በተኚበበበት ሁኔታ ውስጥ ዹነበሹ ልብ     ሆኖም፧ ያንን ጹለማ ኹአላህ ዹበለጠ አድርጎ አላዚውም። ስለዚህ እንዲህ ሲል ጥሪውን አቀሹበ፩ {ኹአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ ዚለምፀ ​​አንተ ጥራት ይገባህ።}   ኚዚያም: ዹሰው ልጅ ሊያደርግለት በማይቜለው መንገድ መፍትሄ መጣለት።   {እኛም ለርሱ ተቀበልነውፀ ኚጭንቀትም አዳነው።}   በመቀጠልም

  ይህ አንቀጜ ኚዩኑስﷺ ታሪክ ባሻገር ለአንተም ዹሚሆን መልካም ብስራት ያስተላልፋልፊ 📖{وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُ؀ْمِنِينَ} {እኛም አማኞቜን እንደዚሁ እናድናለን።} ይህንን አስተንትን       ዚዩኑስ መዳን ዚአንድ ታሪክ ማብቂያ ብቻ አልነበሚምፀ ይልቁንም በራሳ቞ው ዹጹለማ ጊዜ ውስጥ ለሚያልፉ አማኞቜ ሁሉ ዹተሰጠ ዚተስፋ ቃል ነበር።   ምናልባት አማራጮቜህ እዚጠበቡ፣ ሰዎቜ ሊታደጉህ ዚማይቜሉበት ሁኔታ ላይ ሆነህ እንዲሁም በምድራዊ ስሌት መፍትሄ ማግኘት ዚማይቻል መስሎ ሊታይህ ይቜላል።  ሆኖም፧ በወቅቱ ሁኔታህ ላይ ያለው አስ቞ጋሪ መሰናክል ዹአላህን ኃይል ታላቅነት እንድትሚሳ አያድርግህ። 🀲ዱዐ ለማድሚግ ጹለማው እስኪገፈፍ ድሚስ አትጠብቅፀ ይልቁንም በዚያው ጹለማ ውስጥ ሆነህ አላህን ጥራው!! ምክንያቱምፊ    ዩኑስን ኚአሳ ነባሪው ሆድ ያወጣው ጌታ አንተንም እጅግ አስ቞ጋሪና ጠባብ ኹሆነ ሁኔታህ ውስጥ ለማውጣት ሙሉ ኃይል አለው!! 📖{وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُ؀ْمِنِينَ}

✍      ኹአላህ በስተቀር ምንም ነገር ባልቀሚልህ ጊዜ... ተስፋ አትቁሚጥ!! 📖{فَنَادَى فِي ال؞ُّلُمَاتِ أَن لَّا إِلَهَ إِلَّا أَنتَ سُؚْحَانَكَ إِنِّي كُنتُ مِنَ ال؞َّالِمِينَ ★ فَاسْتَجَؚْنَا لَهُ وَنَجَّيْنَاهُ مِنَ الْغَمِّ وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُ؀ْمِنِينَ}   {በጚለማዎቜም ውስጥ ሆኖ  "ኹአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ ዚለምፀ ​​አንተ ጥራት ይገባህፀ እኔ ኚበደለኞቹ ነበርኩ" ሲል ጠራ። ★ እኛም ለርሱ ተቀበልነውፀ ኚጭንቀትም አዳነውፀ እንዲሁም አማኞቜን እናድናለን።}   ተስፋ ለማጣት ዚሚያነሳሱ ምክንያቶቜ በተኚማቹበት፣ በሰው ልጅ አስተሳሰብ መፍትሔ ማግኘት ዚማይቻል በሚመስልበት እና ጥፋት ኚዚአቅጣጫው በተጋሚጠበት ወቅት  በአላህ ላይ ያለው ተስፋ ያልጠፋበት አንድ ልብ ነበር።    ዚባሕር ጚለማ፣ ዚሌሊቱ ጹለማ እና ዚአሳ ነባሪው ሆድ ውስጥ ባለው ጹለማ በተኚበበበት ሁኔታ ውስጥ ዹነበሹ ልብ     ሆኖም፧ ያንን ጹለማ ኹአላህ ዹበለጠ አድርጎ አላዚውም። ስለዚህ እንዲህ ሲል ጥሪውን አቀሹበ፩ {ኹአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ ዚለምፀ ​​አንተ ጥራት ይገባህ።}   ኚዚያም: ዹሰው ልጅ ሊያደርግለት በማይቜለው መንገድ መፍትሄ መጣለት።   {እኛም ለርሱ ተቀበልነውፀ ኚጭንቀትም አዳነው።}   በመቀጠልም

  ይህ አንቀጜ ኚዩኑስﷺ ታሪክ ባሻገር ለአንተም ዹሚሆን መልካም ብስራት ያስተላልፋልፊ 📖{وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُ؀ْمِنِينَ} {እኛም አማኞቜን እንደዚሁ እናድናለን።} ይህንን አስተንትን       ዚዩኑስ መዳን ዚአንድ ታሪክ ማብቂያ ብቻ አልነበሚምፀ ይልቁንም በራሳ቞ው ዹጹለማ ጊዜ ውስጥ ለሚያልፉ አማኞቜ ሁሉ ዹተሰጠ ዚተስፋ ቃል ነበር።   ምናልባት አማራጮቜህ እዚጠበቡ፣ ሰዎቜ ሊታደጉህ ዚማይቜሉበት ሁኔታ ላይ ሆነህ እንዲሁም በምድራዊ ስሌት መፍትሄ ማግኘት ዚማይቻል መስሎ ሊታይህ ይቜላል።  ሆኖም፧ በወቅቱ ሁኔታህ ላይ ያለው አስ቞ጋሪ መሰናክል ዹአላህን ኃይል ታላቅነት እንድትሚሳ አያድርግህ። 🀲ዱዐ ለማድሚግ ጹለማው እስኪገፈፍ ድሚስ አትጠብቅፀ ይልቁንም በዚያው ጹለማ ውስጥ ሆነህ አላህን ጥራው!! ምክንያቱምፊ    ዩኑስን ኚአሳ ነባሪው ሆድ ያወጣው ጌታ አንተንም እጅግ አስ቞ጋሪና ጠባብ ኹሆነ ሁኔታህ ውስጥ ለማውጣት ሙሉ ኃይል አለው!! 📖{وَكَذَلِكَ نُنجِي الْمُ؀ْمِنِينَ}

✍ መንገድ ላይ ስትገጣጠም ባላዚ ዚሚያልፍህ ሁላ;     ወደ መቅበራ ስትወሰድ ጀናዛህ ለመሾኹም ይጋፋል ይሻማል።    ጀናዛ በሚሞኝበት ጊዜ ለመሾኹም ዹሚደሹገው ሜሚያ ስታይ;     በሕይወት ሳለ ዚሚሱትን ዚተዉትን ቀዷ እያወጡ እኮ ነው ዚሚመስለው።

✍ ለብቻህ በተነጠልክ ጊዜ ዚሰውነት ክፍሎቜህ ፀጥታ እንዳይሞውድህ። ሁሉም ድምፅ አውጥተው ዚሚናገሩባት ዚሆነቜ አንዲት ቀን ትመጣለቜና!! 📖{ٱلْيَوْمَ نَخْتِمُ عَلَىٰٓ أَفْوَٰهِهِمْ وَتُكَلِّمُنَآ أَيْدِيهِمْ وَتَ؎ْهَدُ أَرْجُلُهُم ؚِمَا كَانُوا۟ يَكْسُِؚونَ}

✍ ለአንድ ሰው ሙሉ ዱንያ ኚመጀመሪያዋ እስኚ መጚሚሻዋ ቢሰጠውና ኚዚያም ሞት ቢመጣበት;    ሁኔታው ​​ልክ በመናሙ ዚሚያስደስት ነገር አይቶ ኚእንቅልፉ ሲነቃ በእጁ ምንም ነገር እንደማያገኝ ሰው ይሆናል።         [ዑመር ኢብኑል ኞጣብ]

✍ ሰብስቊ ሲሰጥ እንዲህ ነው!! ራሱ ሰሓብይፀ አባቱ ሰሓብይፀ እናቱ ሰሓብይፀ አያቶቹ ሰሓብይፀ ቅድመ አያቱ ሰሓብይ ዚሆኑለት ሰሓብይ!! ትልቁ ሰሓብይ ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር፩ ኚሂጅራ በኋላ በእስል
✍ ሰብስቊ ሲሰጥ እንዲህ ነው!! ራሱ ሰሓብይፀ   አባቱ ሰሓብይፀ    እናቱ ሰሓብይፀ     አያቶቹ ሰሓብይፀ      ቅድመ አያቱ ሰሓብይ ዚሆኑለት ሰሓብይ!! ትልቁ ሰሓብይ ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር፩      ኚሂጅራ በኋላ በእስልምና ዹተወለደ ዚመጀመሪያው ሰሓብይ ነው። አባቱ => ዙበይር ኢብኑ ዐዋም። እናቱ => አስማእ ቢንት አቢበክር። አያቶቹ => አቡበክር ሲዲቅ እና ሰፍያ ቢንት ዐብዱል ሙጊሊብ። ቅድመ አያቱ => አቡ ቁሓፋ ዑስማን ቢን ዓሚር አል_ቁሚይሺ። ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር፩      ገና በአስራ አራት ዓመቱ ታዋቂው ዹዹርሙክ ዘመቻ ተካፍሏል። እንዲሁም ኾሊፋ ዑስማን ቢን ዓፋን ወደ አፍሪካ ለሚገኘው ዚሙስሊም ጩር ኚላኳ቞ው ዚድጋፍ ኃይሎቜ መካኚል አንዱ ነበርፀ በዚያም ለጊሩ ድልን ያስገኘ ወታደራዊ ክህሎትና ብቃት አሳይቷል። 120,000 ቁጥር ዹነበሹውን ዚሮማውያን ጩር ሰራዊት መስመር ሰብሮ በመግባት አዛዣ቞ውን መግደል ቜሏል። ይህ ድርጊት ዚሮማውያንን ኃይል በመበታተን ለሙስሊሞቜ ድል ምክንያት ሆኗል። ኚዚያም በኋላ ኢብኑ ዙበይር ዚአፍሪካን ድል ዚመክፈቻ ዘመቻ ላይ ተሳትፏል።

✍ ዚሕይወት ስንቅ!! {وَعَدَ ٱللَّهُ ٱلْمُ؀ْمِنِينَ وَٱلْمُ؀ْمِنَـٰتِ جَنَّـٰتٍ تَجْرِى مِن تَحْتِهَا ٱلْأَنْهَـٰرُ خَـٰلِدِينَ فِيهَا وَمَسَـٰكِنَ طَيَِؚّةً فِى جَنَّـٰتِ عَدْنٍ ۚ وَرِضْوَٰنٌ مِّنَ ٱللَّهِ أَكَؚْرُ ۚ ذَٰلِكَ هُوَ ٱلْفَوْزُ ٱلْعَ؞ِيمُ}    {አላህ ምእመናንና ምእምናትን ኚሥሮቻ቞ው ወንዞቜ ዚሚፈሱባ቞ውን ጀነቶቜ በውስጣ቞ው ዘውታሪዎቜ ሲሆኑ በመዘውተሪያ ጀነቶቜም ውስጥ መልካም መኖሪያ ቀቶቜን ቃል ገብቶላ቞ዋል፡፡ ኹአላህም ዹሆነው ውዎታ ኹሁሉ ዹበለጠ ነው፡፡ ይህ እርሱ ታላቅ እድል ነው፡፡}    እቺን ሀሹግ አስተውላት {አላህ ቃል ገብቷል} ቃል ኪዳኑ ኹአላህ ሲሆን: ስለ ውጀቱ መጹነቅ አያስፈልግም። ይህ አንቀጜ ስለ ወደፊቱ ጊዜ ደስታ ብቻ አይናገርምፀ ይልቁንም በጉዞህ ላይ ልብህን ዚሚያሚጋጋ መልእክትም ጭምር ነው።   ልትሰናኚል ትቜላለህ... እርምጃህ ሊያመነታ ይቜላል... መንገዱ ሊኚብድህ ይቜላል... እንዲሁም ዚጥሚትህን ፍሬ አሁን ላይታይህ ይቜላል። ሆኖም፧ በልብህ ውስጥ እምነት እስካለ ድሚስና በሕይወትህ ውስጥ መልካም ሥራዎቜ እስካሉ ድሚስ መንገድህን አልሳትክም።   አላህ ፍፁም እንኚን-አልባ እንድትሆን አይጠይቅህምፀ ይልቁንስ ኚስህተትህ በኋላ ሁሌ ወደ እሱ መመለስህን እንድትቀጥልፀ ኚራስህ ጋር እንድትታገልፀ በመልካም ነገር ላይ እንድትጞና እና መሰናኹል ተስፋ ለመቁሚጥ ምክንያት እንዳይሆን እንድታደርግ ይጠይቅሃል። ለዚህም ነው ገና እዚያ ሳትደርስ ዚምስራቹ ዚሚመጣውፊ {አላህ ቃል ገብቷል}    ፍሬውን ለማዚት አት቞ኩል؛ ዹጉዞው ገሚስ ተጉዘህም አትፍሚድበት።    አሁን እንደ ድካም ብቻ ዚምታዚው ነገር؛ አላህ ዘንድ ዹተወደደ ጥሚት ነው።    እፎይታው ዹዘገዹ ዚሚመስለውም ነገር;  ዚገባው ቃል ኪዳን ኹመፈጾም አንጻር ዹዘገዹ አይደለም። ልብህን አሹጋጋ!! ምክንያቱምፊ    ቃል ዚገባው ቃሉን ዚማያፈርስ አካል ነው።   ቃል ኪዳኑ እውነት ነው። ጉዞውም ምንም ያህል ሹጅም ቢሆን መጚሚሻ አለው። رََؚّنَا لَا تُزِغْ قُلُوَؚنَا َؚعْدَ إِذْ هَدَيْتَنَا ÙˆÙŽÙ‡ÙŽØšÙ’ لَنَا مِن لَّدُنكَ رَحْمَةً ۚ إِنَّكَ أَنتَ الْوَهَّاُؚ}

✈     ልዩ ዚዑምራ ፓኬጅ!!     ሁለት ጁሙዐዎቜ በሁለቱ ሐሚሞቜ በመስገድ: 3ቀናት ለሚሱልﷺ ዚስደት ማሚፊያ በሆነቜው መዲነቱል ሙነወራ እና    7 ቀናቶቜ ነብያቜንﷺ ተወልደው ባደጉባትፀ ኚምድር ገፅ ሁሉ በላጭና ዱንያ ላይ ያሉ ምእመናን በአጠቃላይ ተቀጣጭተው በሚሰግዱባት መኹተል ሙኹሹማህ ቆይተውፀ     ዚሚሱልﷺ እና ዚምርጥ ባልደሚቊቻ቞ው ቀብር ዘይሹውና ሰልመውፀ    መስጂድ አል_ቁባዕ ዘይሹውና ሹኹዐተይን ሰግደውፀ    ሚውደቱል ሞሪፋ ዘይሹው: ሹኹዐተይን ሰግደው: ጌታዎትን ተመሳጥሚውፀ    ወደ አላህ ይበልጥ ቀርበው ዱንያና አኌራዎትን ዚሚያሳምርሎት ኚሙኻለፋ ዚጠራ: ሱናውና አዳቡን ዹጠበቀ 🕋ዑምራ🕋 መፈፀም ዚሚያስቜሎት ልዩ ዚዑምራ ፓኬጅ አዘጋጅተናል።    በሀገራቜን በተለያዩ ምክንያቶቜ በተኚታታይ ስራ ዝግ በሚሆንባ቞ው ዚወኚባና ዹግርግር ቀናቶቜ;      ኚመስኚሚም 14  _  መስኚሚም 24 ዹሚቆይ 10ኛ ዙር ልዩ ዚዑምራ ፓኬጅ ተዘጋጅቷል።    ኚፈለጋቜሁ በVIP  ኚፈለጋቜሁም በNORMAL መመዝገብ ትቜላላቜሁ።   ለሁለቱም ሐሚሞቜ ቅርብ ዹሆኑ ምቹና ዘመናዊ ሆ቎ሎቜ በማዘጋጀት በቀተሰባዊ እንክብካቀ ልንኻድማቜሁ ተዘጋጅተናል። ዹሁል ጊዜ ምርጡና ተመሹጭ ትራቭል =>ዹለምለም ዹጉዞ ወኪል!! ፓኬጁ ዚሚያካትተው   📚ዓመታዊ ዚዑምራ ቪዛፀ ✈ደርሶ መልስ ዹአዹር ትኬትፀ 🏚በሁለቱም ሐሚሞቜ ዹሆቮል ክፍያፀ 🚌በሁለቱም ሐሚሞቜ ዘመናዊ ዚባስ ትራንስፖርትፀ 🛣በሁለቱም ሐሚሞቜ ዚተለያዩ ቊታዎቜ ዝያራፀ ያስተውሉ    አብሚው ለሚመጡ ጥንዶቜ ልዩ መስተንግዶ ይደሹጋል!! አሁኑኑ ይደውሉ  🀳  0911674580                        🀳  0911683917                       ðŸ€³  0922448888 ቀተል "ሚና_ሞል"  2ኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን። ✈ዚለምለም ትራቭል ዚትውልዱ ተስፋ!! https://t.me/Yelemlem_travel

⚫ በሰው ልጆቜ ታሪክ ዹተሰማው ክፉ መርዶ!!   ዐብዱሚሕማን ቢን ዑሰይላ አል_ሰናቢሒ ዚሕይወቱ መራራ ገጠመኝ እንዲህ ይተርኹዋል፩    "ሚሱልﷺ ለመገናኘትና ዚሱሕባ ክብር ለማግኘት ኹዹመን ተሰደን ወጣን። ልክ ጁሕፋ① ዚተባለው ቊታ ስንደርስ አንድ ጋላቢ ወደኛ ሲመጣ ተመለኚትን። እኔም “መዲና ውስጥ ምን አዲስ ነገር አለ?” ብዬ ጠዚኩት; ”دفنا رسول الله ï·º منذ خمس ليالٍ“   “ዹአላህ መልእክተኛﷺ ኹቀበርናቾው አምስት ቀን ሆኖናል።” አለኝ።" ይላል።   ኹዹመን ሀገር ተነስቶፀ ጋራና ሾንተሹር አቋርጊፀ ኮሚብታው ወጥቶ ቁልቁለቱን እዚወሚደ በአላህ ነብይ ናፍቆት ዹነደደው ልቡ ፊታ቞ውን በማዚት ለማስታገስና ዕድሜ ልኩን ኚሚሰራው ዒባዳ ሁሉ በላጭ ዚሚሆንለት ዚሱሕባ ማዕሹግ ለማግኘት ጓጉቶ ዚመጣን ናፋቂ;    "ሚሱልﷺ ኚቀናት በፊት ቀብሚና቞ዋል" ዹሚሉ ተራራ ዚመናድ ክብደት ያላ቞ው ቃላቶቜ ሲሰማ እግሮቹ እንዎት ቜለው ተሞክመውት ይሆን????

✍     ቁርኣን ውስጥ ኚተጠቀሱ ኚንቱ ምኞቶቜ ውስጥ    📖{يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي} {"ዋ ምኞቮ! ምነው ለሕይወቮ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡}    [አል_ፈጅር:24] 📖{وَيَقُولُ الْكَافِرُ يَا لَيْتَنِي كُنتُ تُرَاًؚا} {ኚሓዲውም ዋ ምኞቮ! ምን ነው ዐፈር በሆንኩ ይላል።}     [አል_ነባእ:40] 📖{وَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَاَؚهُ ؚِ؎ِمَالِهِ فَيَقُولُ يَا لَيْتَنِي لَمْ أُوتَ كِتَاؚِيَهْ} {መጜሐፉንም በግራው ዹተሰጠውማ «ዋ ጥፋ቎! ምነው መጜሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡}     [አል_ሓቃ:69] 📖{وَيَوْمَ يَعَضُّ ال؞َّالِمُ عَلَىٰ يَدَيْهِ يَقُولُ يَا لَيْتَنِي اتَّخَذْتُ مَعَ الرَّسُولِ سَؚِيلًا} {በዳይም «ኚመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ á‹­á‹€ በሆነ ዋ ምኞቮ!» እያለ (በጞጞት) ሁለት እጆቹን ዚሚነክስበትን ቀን (አስታውስ)፡፡}     [አል_ፉርቃን:27] እነርዚህ ሁሉ


    አንድ ሟቜ ምንም ነገር መስራትና መቀዹር  በማይቜልበት ቀን በቁጭት ኚሚያሰማ቞ው ኚንቱ ምኞቶቹ ውስጥ ኚፊሎቹ ና቞ው። እኔና አንተ ግን


     ዛሬ ላይ በተሰጠን ዕድል ሁሉም ነገር ሰርተን ነፍሳቜን ኹዚህ ኚንቱ ምኞት እና ቁጭት መታደግ እንቜላለን!! ዋናው ጥያቄ        ዹሚነቃ ዚሚያስተውል አለ ወይ??? ነው። 🖊ሐምዱ ቋንጀ ኹፉርቃን ሰማይ ስር!!

✍ በሕይወት ውዝግብ ግራ ለተጋባ ሁሉ


 ዚመንገድህ ግማሜ ተጉዘህ በሕይወትህ ተስፋ አትቁሚጥ!!    ሁኔታዎቜ ሲወሳሰቡፀ በሮቜ ኚፊትህ ሲዘጉፀ መንገዱ በጭጋግ ሲሞፈን እና በልብህ ውስጥ ያሉ ጥያቄዎቜ ኚምታገኘው ውጀት ሲበዙ; ስለ ሕይወትህ ታሪክ ለመፍሚድ አት቞ኩል!! ምክንያቱምፊ   አሁን ላይ ያልተገለፀልህ ነገር ሁሉ ክፉ አይደለም እንዲሁም ህመም ዚፈጠሚብህ ነገር ሁሉ መጚሚሻህ አይደለም። አላህ ያወሳልን ታሪኮቜ ተመልኚት  ... ኑሕ ዐለይሂ ሰላም፩     በአላህ ትዕዛዝ መርኚብ ሲሠራ: ህዝቊቹ ዚብስ ላይ መርኚብ እዚሰራ ዹሚጃጃል ሰው አርገውት ያፌዙበት ነበር። ኑሕም ነገ ምን እንደሚኚሰት ዝርዝር ሁኔታውን አያውቅም ነበር; ዚሚያውቀው አንድ ነገር ብቻ ነበር => መርኚብ እንዲሰራ አላህ እንዳዘዘው። 📖 {وَاصْنَعِ الْفُلْكَ ؚِأَعْيُنِنَا وَوَحْيِنَا} ኢብራሂም ዐለይሂ ሰላም፩     በመናሙ ልጁን ሲያርድ ተመለኚተ። ዚጌታውን ትዕዛዝ ለመፈፀም እስኚ መጚሚሻው ቅጜበት ድሚስ ተጓዘ። ኚዝያም ዹአላህ ፈሹጅ መጣለት; 📖 {وَفَدَيْنَاهُ ؚِذِؚْحٍ عَ؞ِيمٍ} ዚሙሳ እናትፊ      ዚትኛዋ እናት ልቧ እሺ ብሏት ጹቅላ ህፃኗ ወንዝ ውስጥ ዚምትወሚውር ይመስልሃል?? ግና ዹአላህ ትዕዛዝ ነበር; 📖 {وَأَوْحَيْنَا إِلَى أُمِّ مُوسَى أَنْ أَرْضِعِيهِ فَإِذَا خِفْتِ عَلَيْهِ فَأَلْقِيهِ فِي الْيَمِّ وَلَا تَخَافِي وَلَا تَحْزَنِي إِنَّا رَادُّوهُ إِلَيْكِ}   ኚዝያም ዹአላህ ቃል_ኪዳን እውን መሆኑን ታምን ዘንዳ አላህ ልጇን ወደሷ መለሰላት። ኡሙ ኢስማኢል ሀጀር፩      አላህ እንደማይተዋት እርግጠኛ ኹመሆኗም ጋ ቁጭ ብላ ተኣምር እስኪመጣላት አልጠበቀቜም። ይልቁንስ ሰፋ እና መርዋ መሃል ተመላልሳ እዚሮጠቜ መፍትሔ ፍለጋ ታገለቜ። በመጚሚሻም ጭራሜኑ ባልገመተቜው ቊታ አላህ በዘምዘም ፈሚጃት።   በእያንዳንዱ ታሪክ ውስጥ አስፈሪ ዚሚመስሉ ክስተቶቜ ነበሩ። ነገር ግን መጚሚሻ቞ው አላህ ወደ ስኬት ዚሚያደርስ መንገድን እያዘጋጀባ቞ው እንደነበር አሳዚ። ስለዚህፊ   በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ያለው መሰናክል ጌታህ ላይ መጥፎ እንድታስብ ምክንያት አይሁንብህ። አንተ ዚምታዚው አሁን ያለውን ነው; አላህ ግን ኚዚያ በኋላ ያለውን ያውቃል።   አንተ ዹተዘጋውን በር ነው ዚሚታይህ; ነገር ግን ለምን እንደተዘጋ አይታይህም።   አንተ መዘግዚቱን ነው ዚሚታይህ; ነገር ግን ጉዳዩ ቀደም ብሎ ቢፈጞም ኖሮ ሊጎዳህ ዚሚቜለውን ነገር አይታይህም። አንተ ዚመንገዱን መጥበብ ነው ዚሚታይህ; ነገር ግን አላህ በዚያ ጠባብ መንገድ በኩል ወዎት እዚመራህ እንደሆነ አታውቅም።   ሁሌም ድብቅ ምስጥሩን ማወቅ አይጠበቅብህም; ይልቁንም ዚማይታዚውን በሚያውቀው አምላክ እንድታምን ነው ዚሚጠበቅብህ። ልክ እንደ ኢብራሂም ታገስ!! ልክ እንደ ሀጀር ጥሚት አድርግ!! ልክ እንደ ኑሕ አስፈላጊውን እርምጃ ውሰድ!! ልክ ለሙሳ እናት ዚነበራት ዓይነት ዹቂን ይኑርህ!! ኹአንተ ቜሎታ ውጪ ዹሆነውን ሁሉ ለአላህ አደራ ስጥ!! 📖 {وَمَن يَتَّقِ اللَّهَ يَجْعَل لَّهُ مَخْرَجًا ★ وَيَرْزُقْهُ مِنْ حَيْثُ لَا يَحْتَسُِؚ وَمَن يَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ فَهُوَ حَسُؚْهُ} እንግዲያውስ;     ዚመንገድህ ግማሜ ተጉዘህ በሕይወትህ ተስፋ አትቁሚጥ!!    አሁን እያሳመመህ ያለው ክስተት; ምን አልባትም ለነገው ስኬትህ አንዱ ድልድይ ሊሆን ይቜላል!!    አሁን ላይ ተዘግቶብህ ያስለቀሰህ በር; ምን አልባትም ሊያጠፋህ ዹነበሹው ሙሲባ ኹዚህ በር ጀርባ ዹነበሹ ሊሆን ይቜላል!!    ዚምኞትህ መዘግዚት; ምን አልባትም አላህ ዚተሻለው እያዘጋጀልህ ስለሆነ ሊሆን ይቜላል!! ሁል ጊዜ አላህ ዚሚሰራውን ማወቅ አይጠበቅብህም;      አላህ አዛኝና ጥበበኛ መሆኑ ማወቅህ በቂ ነው!! ይህንንም ዕወቅ 👇    በዚህ መንገድ እዚተጓዝክ ያለኞው ብቻህን አይደለህም!! ሕይወት ተወሳስቊ ግራ በሚገባህ ጊዜ: ልብህ በፅኑ ይመንና እንዲህ በል;    "አላህዋ ምን እንደሚኚሰት አላውቅም: እንደማትተወኝ ግን አውቃለሁ!!" ለኑሕ በመርኚብ ኹማዕበል ያዳነው አላህፀ ለሙሳ እናት ህፃኗን መልሶ ያሳቀፈው አላህፀ ለኢብራሂም ኚትልቅ ፈተና በኋላ ቅያሪ ያደሚገው አላህፀ ለሀጀር ኹበሹሀ እምብርት ዘምዘም ያፈለቀው አላህፀ   ለአንተም ባላሰብኚው መልኩ ሊፈርጅህ ቻይ ነው!! 📖{إِنَّ اللَّهَ َؚالِغُ أَمْرِهِ قَدْ جَعَلَ اللَّهُ لِكُلِّ ؎َيْءٍ قَدْرًا} 🖊ሐምዱ ቋንጀ ኹፉርቃን ሰማይ ስር!!

✍ ውዎታ቞ው ካለህ ለሰው ልጅ አለቃ መንዙማህን ትተህ በሐዲስ ተብቃቃ። ብትወዳ቞ውማ ሰይዱል አንቢያ ሱና቞ው ለያዘ ባላልክ ወሀቢያ። አፍህ ይሞግታል ዚሚሱል ውዎታ ስራህ ተቃራኒ ዚሚያስቆጣ ጌታ። ወንድ
✍    á‹á‹Žá‰³á‰žá‹ ካለህ  ለሰው ልጅ አለቃ መንዙማህን ትተህ  በሐዲስ ተብቃቃ። ብትወዳ቞ውማ   ሰይዱል አንቢያ   ሱና቞ው ለያዘ   ባላልክ ወሀቢያ። አፍህ ይሞግታል  ዚሚሱል ውዎታ ስራህ ተቃራኒ  ዚሚያስቆጣ ጌታ።   ወንድና ሎት አብሮ  ሆኖ በአንድ ቀት መውሊዳ቞ው ብሎ  ይላል ሰለዋት። ምን ዓይነት ሰለዋት  ምን ዓይነት ውዎታ      ሚሱል በጀነት   አንተ ሌላ ቊታ?? ወዳጅ ለወደደው  ይታዘዛል እንጅ ክልኹላው ተላልፎ  አያነሳም ፈንጅ። በልብህ ውስጥ ካለ  ዚነብዩ ፍቅር ልደታ቞ው ሳይሆን   ትዕዛዛ቞ው አክብር።      🖌ሐምዱ ቋንጀ

💵 ዹሰው ልጅ ተፈጥሮ ኚገንዘብ ጋ ጥብቅ ቁርኝት አለው። አንድ ሰው ገንዘብ በሚያገኝ ጊዜ ነፍሱ ዚአካል ብቃትና ዚአእምሮ መነሳሳት ታገኛለቜ!! [ይህ ሀኪሞቜም ዘንድ ዹተሹጋገጠ ምርምር ነው።]
💵      ዹሰው ልጅ ተፈጥሮ ኚገንዘብ ጋ ጥብቅ ቁርኝት አለው። አንድ ሰው ገንዘብ በሚያገኝ ጊዜ ነፍሱ ዚአካል ብቃትና ዚአእምሮ መነሳሳት ታገኛለቜ!!       [ይህ ሀኪሞቜም ዘንድ ዹተሹጋገጠ ምርምር ነው።]

✍      ዹሰው ልጅ ተፈጥሮ ኚገንዘብ ጋ ጥብቅ ቁርኝት አለው። አንድ ሰው ገንዘብ በሚያገኝ ጊዜ ነፍሱ ዚአካል ብቃትና ዚአእምሮ መነሳሳት ታገኛለቜ!!       [ይህ ሀኪሞቜም ዘንድ ዹተሹጋገጠ ምርምር ነው።]

✍ ዛሬ ቢያዩስ    መዲና ውስጥ ዹነበሹ አንድ ሙኣዚን ዹፈጅር አዛን ሊል ሲል ሁሌም ተነሕኑሕ① ያደርግ ነበር። ይህንን ነገር ያስተዋሉት ኢማሙ ማሊክ ሙኣዚኑን አስጠሩትና; "በሀገራቜን ያልነበሚ ፈጠ
✍     ዛሬ ቢያዩስ       መዲና ውስጥ ዹነበሹ አንድ ሙኣዚን ዹፈጅር አዛን ሊል ሲል ሁሌም ተነሕኑሕ① ያደርግ ነበር። ይህንን ነገር ያስተዋሉት ኢማሙ ማሊክ ሙኣዚኑን አስጠሩትና;    "በሀገራቜን ያልነበሚ ፈጠራ አትፍጠርብንፀ ኹዚህ ተግባርህ ተቆጠብ። ሁለተኛ እንዳደግም!!" ብለው ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጡት። በሌላ ዘገባፊ     "ይህ ሙብተዲዕ ዹሆነ ሙኣዚን በፍጥነት አስወግዱት!!" ብለው አዘዙ።   [①ተነሕኑሕ ማለትፊ አንድ ሰው ጉሮሮውን ለማፅዳት ሲፈልግ ምናምን ዚሚያሰማው እህህ ዹሚለው ዓይነት ድምፅ ነው።]