cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

🇵🇸ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Show more
Advertising posts
10 952
Subscribers
+3524 hours
+1867 days
+35930 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
✍      ስስታሙ ሰወዬ ወደ ገበያ ወጥቶ ማንቆርቆሪያ እና ሳህን ገዛ አሉ።    የገዛቸው ዕቃዎች ይዞ ወደ ማተሚያ ቤት በመሄድ "እባክህ እላያቸው ላይ የሆነ ነገር ብለህ ፃፍልኝ" አለው።   "ምን ብየ ልፃፍልህ?" ሲለው; 🫖ማንቆርቆሪያው ላይ:  {فَمَن شَرِبَ مِنْهُ فَلَيْسَ مِنِّي}   {ከእሱ የጠጣ ከእኔ አይደለም።} 🍽ሳህኑ ላይ ደግሞ:      {وَمَن لَّمْ يَطْعَمْهُ فَإِنَّهُ مِنِّي}   {ያልቀመሰው ሰው እሱ ከእኔ ነው።} ብለህ ፃፍባቸው አለው። https://t.me/hamdquante
6559Loading...
02
✍ አንዳንድ ጊዜ………  {يَا لَيْتَنِي مِتُّ قَبْلَ هَذَا وَكُنتُ نَسْيًا مَّنسِيًّا} የምትልበት ቻሌንጅ ይገጥምህና መልሶ ደግሞ……… {لَعَلَّ اللَّهَ يُحْدِثُ بَعْدَ ذَلِكَ أَمْرًا} የሚል ተስፋ መንፈስህን ይጠግንልሃል!! https://t.me/hamdquante
9012Loading...
03
✍ የጉዳዩ መፈፀሚያ ጊዜ ሲደርስ አላህ በሮቹ ይከፍታቸውና ሰበቦቹ ያገራቸዋል!! በሰብር ጠብቅ https://t.me/hamdquante
1 2824Loading...
04
✍      ኡስታዝ……… ኡስታዝህ ከዐይን ብሌንህ የበለጠ ልትወደው, ልትንከባከበው, ልትጠብቀው ይገባሃል። አላህ……… አባት እናትህ ለመፈጠርህ ሰበብ ካደረጋቸው በኋላ ተጨንቀው, ተጠበው እና ተቸጋግረው ከጥሩው, ከጣፋጩ እያበሉ እንዲህ  የተዋበ ሰውነት ገንብተውልሃል። ዳሩ ግን ይህ ውብ ግንባታ የጀሀነም እሳት ማቀጣጠያ ብቻ ሁኖ ሊቀር ይችላል።   ከዚህ መጨረሻ እና ዕረፍት ከሌለው ዕሳት ድነህ, በምእናብህ አስበህ ልትደርስበት እንኳ በማትችል ፀጋ የተሞላው ዘላለማዊው ጀነት እንድትገባ ከተፃፈልህ: ለዚህ ስኬት ሰበብ በመሆን   የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው ኡስታዝህ ነው!! ምን ይህ ብቻ………    ዛሬ ላይ ኡስታዝህን ጨምረህ ታላቁም ታናሹም የምትመዝንበት ሚጥጥዬ ዕውቀትህ እንኳ ከኡስታዝህ ምንጭ የተቀዳ ነው። አላህ እሱ ሰበብ ባያደርግልህ ዛሬ ላይ "ተራ" ከምትላቸው ሰዎች የባስክ "ተራ" ነበርክ። ከዚህ ሁሉ ውለታ………    ጥቂቱን እንኳ መመለስ ቢሳንህ: ውለታውን ዐውቀህ ማክበሩ እንዴት ይሳንሃል?? ነገር ግን ዕወቅ………    ኡስታዝህ ማለት ኡስታዝህ እንጂ ነብይህ አይደለም!! ከእሱ………    ሐቅ የሆነውን ትወስዳለህ; ውድቅ የሆነውን ትተወዋለህ!!   እንዲህ ስትል ቅር የሚለው ከሆነ……    እሱንም ተ ወ ው!! https://t.me/hamdquante
2 11412Loading...
05
✍ ድሮ መድረሳ ላይ ቀድሞ አፍንጫውን የሚዘው ልጅ ነበር ፈስ እንደፈሳ ይጠረጠር የነበረው። በእርግጥም ብዙ ጊዜ የፈሱ ባለቤት ነበር ቀድሞ "ፈስ ፈስ" ብሎ አፍንጫውን የሚይዘው። ዛሬም ላይ በየ መድረኩ "ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ" የሚሉ ብሄርተኞች ኢትዮጵያን እያፈረሷት እንደሆነው ሁሉ በየጉራንጉሩ……… "ዘረኝነት ዘረኝነት" እያሉ ሰዎች ላይ ውዥንብር የሚፈጥሩ ዘረኞች ናቸው እያግማሙን ያሉት። https://t.me/hamdquante
2 39011Loading...
06
✍ ሴት ልጅ የሚያዋርድ ወንድ ካየህ…… እሱ ወንዶች መሃል የተዋረደ መሆኑን እወቅ!! https://t.me/hamdquante
2 3358Loading...
07
🧿 ተጠንቀቅ!! እየተዋጋኸው ያለው ሰውየ ምን አልባትም መሳሪያው {حَسْبيَ الله وَنِعْمَ الوَكِيل} ሊሆን ይችላል። https://t.me/hamdquante
2 2628Loading...
08
✍     ወንዳወንድነቱ ላይ ጉድለት ያለበት ባል ነው    በሆነው ባልሆነው  ሁለተኛ ሚስት እና ፍቺ ለሚስቱ ማስፈራሪያ አድርጎ መጠቀም የሚፈልገው። https://t.me/hamdquante
2 47517Loading...
09
✍ አንድ ሰው ላይ ትልቅ ሙሲባ ማለት፦    ራሱ ላይ ጉድለት እንዳለበት ያውቅና: ይህንን ጉድለት ምንም ሳያስጨንቀው እና ቦታ ሳይሰጠው መቅረቱ ነው።         /ኢብኑ ሙባረክ/ https://t.me/hamdquante
2 50713Loading...
10
አንድ ሰው ላይ ትልቅ ሙሲባ ማለት፦    ራሱ ላይ ጉድለት እንዳለበት ያውቅና: ይህንን ጉድለት ምንም ሳያስጨንቀው እና ቦታ ሳይሰጠው መቅረቱ ነው።         /ኢብኑ ሙባረክ/ https://t.me/hamdquante
00Loading...
11
✍ አይባልም እንጂ    ለእኔ ያርገው  ተብሎ አልችለውም እንጂ  ሸክምህን ከቶ; አንተን ከሚያምህ   ከማይህ አልጋ ላይ መሆን እመርጥ ነበር  እኔ በቦታህ ላይ!! ይሁን ችግር የለም   በጌታዬ መሻት መታመም መቸገር  የሷሊሕ ድርሻ ናት!! ቢወድህ ነው እንጅ  ቢመርጥህ አልቆ እሱ ምን ሊጠቀም  አንተን አስጨንቆ?! ደረጃህ ከፍ ይበል   ዐፊያህ ይመለስ ፈገግታማው ፊትህ  በደስታህ ይታደስ!!    አንተን አሳጥቶ  አላህ አይፈትነን በጤና መልሶህ  ሰላም ያገናኘን!!    የሐበሻ ዕንቁ; የዳዕዋችን ፋና ወጊ; የሁላችን ባለ ውለታ የሆነው;   ታላቁ አባታችን እና መካሪው አስተማሪያችን አቡ ዐብዱረሕማን አብራር   በህመም ምክንያት ሆስፒታል ተኝቷል። የሩቅ ወንድም ዱዐ ፈጥኖ ደራሽ ነውና    ሁላችንም አላህ ዱዐችን ሊቀበል ቅርብ ነው በምንለው ሁኔታ ላይ ሆነን አላህን አብዝተን እንማፀንለት። https://t.me/hamdquante
3 14025Loading...
12
✍ ወይ ዐዝነው አልሄዱ ሸክምህን ዐይተው ወይ መጥተው አልሰሩ ቦታህን ሸፍነው። ስታቆም ተቆጥተው ስትሰራ ኮንነው አንተን መምከር ትተው ከሌላው ጋ አምተው። እንዲህ ነው ስራቸው ስራ መች አላቸው ሰሪዎች መተቸት ይህ ነው ችሎታቸው። አትጠብቅ ከእነሱ ውዳሴ በጭራሽ ለለውጥ ያልታደሉ ሁሌም አመድ አፋሽ። ከፊት አይቀርቡህም አይችሉም መጋፈጥ ዞሮ መንጨት እንጂ ክብርህን መዘርጠጥ። ውሾቹ ይጩሁ ድሮም ስራቸው ነው ግመሎች ይሂዱ አደራውን ይዘው!! እኛ እንሄዳለን መጮህ ያልሰለቸው ይጩህ!! ✍ሐምዱ ቋንጤ ከፉርቃን ሰማይ ስር!! https://t.me/hamdquante
2 59316Loading...
13
🗞 ሁለት መቶ ብር ከተዘረዘረ ሹፌር ከሰከረ ዋጋ የላቸውም። በቃ ሳትዘረዝሩ ተገበያዩበት https://t.me/hamdquante
2 4045Loading...
14
🗞 የሆነ ነገር እንዳወዛገበው ፊቱ ያስታውቃል; ጠጋ ብየ "ምን ሆነህ ነው?" አልኩት; : : "ሁለት መቶ ብሩ ከዘረዘርኩት በኋላ……… "መቶ ብሩ እኔ ሳጠፋው: መቶ ብሩ ራሱ ሚጠፋው ነገር ሊገባኝ አልቻለም።" አለኝ ገጥሟችሁ ያቃል ወይ??? https://t.me/hamdquante
2 42711Loading...
15
"በረከቱ ይስፈንብን" ብሎ የሚሰቀል ኦርቶ የለም ወይ??
310Loading...
16
✍     አንድ ክርስቲያን የሆነ ሰው ለየቲሞች መርጃ ማዕከል 10 ሚልየን ብር ገቢ ቢያደርግ ፍርዱ ምንድን ነው?      ብሎ ጠየቀ; መላሹ………    ትምህርት ቤቱ ውስጥ ስሙ ያልተመዘገበ ተማሪ በትምህርት ቤቱ የሚፈለጉ የተማሪ መማሪያ ቁሳቁሶች እና የመፈተኛ መሳሪያዎች አሟልቶ ገዝቶ ቢመጣ ጥቅሙ ምንድን ነው?    ብሎ መለሰለት።   የትኛውንም ሰው በሚሰራው መልካም ስራ ምንዳው ማግኘት ይችል ዘንድ መጀመሪያ ሙስሊም መሆን አለበት። ወደ እስልምና ሳይገባ የትኛው መልካም ስራ ቢሰራ ወደ ቀጣዩ ዐለም የሚሸጋገርለት ምንም ዐይነት ምንዳ የለውም። 📖{وَمَن يَبْتَغِ غَيْرَ الْإِسْلَامِ دِينًا فَلَن يُقْبَلَ مِنْهُ وَهُوَ فِي الْآخِرَةِ مِنَ الْخَاسِرِينَ} {ከኢስላም ሌላ ሃይማኖት የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከእሱ ተቀባይ የለውም። እሱም በመጨረሻው ዐለም ከከሳሪዎች ነው።}      [አል_ዒምራን:85] https://t.me/hamdquante
2 74414Loading...
17
🧿Life……… ብትኮሳተርብህ እንኳ ኮርኩረህም ቢሆን አስቃት እንጅ; በፍጹም እጅ እንዳትሰጥ!! https://t.me/hamdquante
2 26616Loading...
18
✍ ያኔ ድሮ……ድሮ……… የድምፅ ማጉያ አልነበረም; የማንቂያ ሰዓት የሚሞላበት አላርምም አልነበረም; ከመሆኑም ጋ……… አንድም ቀን የፈጅር ላት ጀምዐ አምልጧቸው አያውቁም። ምክንያቱም……… እነርሱን የሚያነቃው ልባቸው ውስጥ የነበረው ኢማን ነበር!! https://t.me/hamdquante
2 46511Loading...
19
✍      ለሰዎች ስትነግራቸው……… ቢሰሙህ እንኳ የንግግራቸው መጨረሻ የሚሆነው "አላህ ይርዳህ" ነው። እንግዲያውስ………     ከጅምሩም ንግግርህ አሳጥርና ☝️የሚረዳህ ለሆነው ብቻ ንገረው!! https://t.me/hamdquante
2 40619Loading...
20
📖      በቁርኣን ታሪኮች ለምን ይወሱልናል??!! ከብዙ ጥበቦቹ ውስጥ አንዱ……    ታሪኮቹ በምታነብ ጊዜ ከምታውቀው ጠባቡ ዐለም ወደ የረሳኸው ሰፊው ዐለም ይዘውህ ይሻገራሉ። ያ………    የረሳኸው ሰፊው ዐለም ላይ የአንተው ዐይነት ሰዎች ነበሩ; እንደቆሰልከው የቆሰሉ; እንደታመምከው የታመሙ; እንደተበደልከው የተበደሉ።    ታግሰው; ተሸክመው; ችለው… አልፈዋል!! 🧿ብትዋሽ………     ከአንተ በፊት ኑሕ ተዋሽቷል። 🧿ብትታመጽ………      ከአንተ በፊት ሙሳ ታምጿል። 🧿ብትበደል………      ከአንተ በፊት ዩሱፍ ተበድሏል። 🧿ብትቸገር………      ከአንተ በፊት ዒሳ ተቸጋግሯል። 🧿ብትባረር………     ከአንተ በፊት ሙሐመድ ተባሯል። 🧿እምቢተኛ ልጅ ቢኖርብህ………     የኑሕ ልጅ ከአንተ ልጅ ቀድሞ እምቢ ብሏል። 🧿አመጸኛ ሚስት ብትኖርብህ………      የሉጥ ሚስት ከአንተዋ ቀድማ አምጻለች። 🧿አመጸኛ ባል ቢኖርብሽ………     የዐሲያ ባል ከአንቺ ባል ቀድሞ አምጿል። 🧿አጓጉል ዘመዶች ቢገጥሙህ………     የሙሐመድ ዘመዶች በዚህ ተግባር ቀድመዋል። ብቻህን አይደለህምና <> ቀለል አርገው!! እነርዚህ ታላላቆች መከራውን ለማለፍ በተሳፈሩበት መርከብ ከተሳፈርክ;    የደረሱበት ደረጃ ትደርሳለህ!! ታገስ……ታገስ……ታገስ ወንድሜ!! ✏️አቡ ሙስሊም          ከፉርቃን ሰማይ ስር!! https://t.me/hamdquante
3 09359Loading...
21
✍ በጭራሽ አትመቃኝ!! ልብህ ውስጥ የቅናት መንፈስ ከነገሰ…… ሌሎች ላይ የሚዋለው ውለታ: አንተ ላይ የተጣለ ሙሲባ ሁኖ እየታየህ: ውስጥህ ሰላም አጥቶ ትኖራለህ። https://t.me/hamdquante
2 72613Loading...
22
🤲አልሃምዱ ሊላህ!!         አልሃምዱ ሊላህ!!             አልሃምዱ ሊላህ!!   ትልቅ ስጦታ እጅግ በጣም ገራሚ ከሆነ ገጠመኝ ጋ!! በእኛ አቆጣጠር………     ልክ የዛሬ ዐመት በዛሬዋ ቀን (ሸዋል25) ነበር ከውዷ ባለቤቴ ጋ ጋብቻችን የፈፀምነው። እነሆ ዘንድሮም………    ሸዋል25 በታጋባንበት ልክ በዐመቱ በራሱ በቀኑ አላህ የመጀመሪያው ልጃችን ለግሶናል!! ልጃችንም………    አላህ ኢስላም እና ሙስሊሞች የሚረዳ ያደርገው ዘንዳ "ሙስሊም" ብለን ሰይመነዋል።        📖{وَأَمَّا بِنِعْمَةِ رَبِّكَ فَحَدِّثْ} https://t.me/hamdquante
3 47423Loading...
23
🤲 አላሁመ……… ሁሉም "ይጠቅመኛል" ወደ ሚለው ሲጠጋ; ☝️አንተ መርጠን ወደ አንተ ተጠግተናል!! 🤲اللهم يسر لنا🤲 https://t.me/hamdquante
3 16011Loading...
24
✍      ማብራሪያው……… {وَقَوْلِهِمْ إِنَّا قَتَلْنَا الْمَسِيحَ عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ رَسُولَ اللَّهِ وَمَا قَتَلُوهُ وَمَا صَلَبُوهُ وَلَٰكِن شُبِّهَ لَهُمْ ۚ وَإِنَّ الَّذِينَ اخْتَلَفُوا فِيهِ لَفِي شَكٍّ مِّنْهُ ۚ مَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ إِلَّا اتِّبَاعَ الظَّنِّ ۚ وَمَا قَتَلُوهُ يَقِينًا} {እኛ የአላህን መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን ገደልን» በማለታቸውም (ረገምናቸው)፡፡ አልገደሉትም አልሰቀሉትምም፡፡ ግን ለእነሱ (የተገደለው ሰው በዒሳ) ተመሰለ፡፡ እነዚያም በእርሱ ነገር የተለያዩት ከእርሱ (መገደል) በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም፡፡}    [አል_ኒሳእ:157] https://t.me/islmina_min_ale
3 67025Loading...
25
✍      ማብራሪያው……… {وَقَوْلِهِمْ إِنَّا قَتَلْنَا الْمَسِيحَ عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ رَسُولَ اللَّهِ وَمَا قَتَلُوهُ وَمَا صَلَبُوهُ وَلَٰكِن شُبِّهَ لَهُمْ ۚ وَإِنَّ الَّذِينَ اخْتَلَفُوا فِيهِ لَفِي شَكٍّ مِّنْهُ ۚ مَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ إِلَّا اتِّبَاعَ الظَّنِّ ۚ وَمَا قَتَلُوهُ يَقِينًا} {እኛ የአላህን መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን ገደልን» በማለታቸውም (ረገምናቸው)፡፡ አልገደሉትም አልሰቀሉትምም፡፡ ግን ለእነሱ (የተገደለው ሰው በዒሳ) ተመሰለ፡፡ እነዚያም በእርሱ ነገር የተለያዩት ከእርሱ (መገደል) በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም፡፡}    [አል_ኒሳእ:157] https://t.me/islmina_min_ale
10Loading...
26
“ተሰቅሏል” ለሚሉት…… ተሰቅሎ ከሆነ   ጌታ በውዴታው በጠላቶቹ ላይ   ምንድን ነው ወቀሳው? ሳይፈልግ ከሆነ   ሰቅለው የገደሉት ጌታቸው በጉልበት  እንዴት አሸነፉት? 🫵እነርሱ እንደ ሚሉት "ጌታቸው ሲሰቀል" ✍ፈቅዶና ወዶ ከሆነ የተሰቀለው; ፈቅዶላቸው የሰቀሉት ጠላቶቹ በወንጀል መውቀስ የጌታን ፍትህ የሚቃረን ነው። [ፈቅዶና ወዶ ስለ ሰቀሉት ለምን ይወቀሳሉ❓] ✍መሰቀልና መገደል ሳይፈልግ ጠላቶቹ ሰቅለው የገደሉት እንደ ሆነ; የጠላቶቹ ጉልበት ከጌታ ጉልበት በለጠ ማለት ነው። [በጠላቱ የሚሸነፍ አካል እንዴት ጌታ ሊሆን ይችላል❓] ✍እውነታው ግን 👇ይህ ነው 👇 👉የመርየም ልጅ ዒሳ «ጌታ» አይደለም። አላህ "ሁን" በሚለው የትእዛዝ ቃሉ ያስገኘው (የፈጠረው) የአላህ ባሪያ ነው። አላህም መርጦት መልእክተኛ አድርጎ ላከው። ጠላቶቹ ሊገሉት በፈለጉ ጊዜ አላህ ወደ ሰማይ ከፍ አደረገው። አላህ እንዲወርድ በፈለገው ጊዜ ወደ ምድር ይወርድና በእስልምና ሀይማኖት ይፈርዳል። አለምን ብቻውን የፈጠረው ጌታ ግን  አምሳያም ይሁን ቢጤ የሌለው ብቸኛው ☝️አላህ ነው። የሚያሸንፈውም ይሁን የሚጋፈጠው ጠላት የለውም ነገሮች እንዲሆኑ በፈለገ ጊዜ "ሁን!" ብሎ ያዛቸዋል ይሆናሉም‼️ በዚህኛውም ይሁን በዘላለማዊው ዓለም መዳኛው መንገድ እስልምና ብቻ ነው‼️ https://t.me/islmina_min_ale
3 41447Loading...
27
🟢 አንዳንድ ወንዶች ደሞ አሉ……… ሀያ ምናምን ዐመት እናቱ ቤት ቁጭ ብሎ ሲበላ የወደቀ ሳህን እንኳ ማንሳት አይፈልግም; ልክ ትዳር ሲመሰርት……… "በቤት ውስጥ ስራ ሚስት ማገዝ ሱና ነው" ይላል። አዎን ሚስትህን ማገዝ ሱና ነው; እናትህ ማገዝ ግን ግዴታ እንደነበር ለምን ዘነጋህ?? https://t.me/hamdquante
3 00824Loading...
28
✍ ከቀደምቶች አንዱ እንዲህ ይላል፦ በሕይወቴ አንድ ቀን እንኳ ቢሆን ልሰራበት ፈልጌ ልሰራበት ያልቻልኩት የቁርኣን አንቀፅ ይህ ነው………  {وَإِن قِيلَ لَكُمُ ارْجِعُوا فَارْجِعُوا} {ተመለሱ ከተባላችሁ ተመለሱ።} መመለስ ፈልጌ ሳስፈቅድ አንድም "ተመለስ" የሚለኝ ማግኘት አልቻልኩም። ይላል በእነርሱ ዘመን…… በእነርሱ ወንድማማችነት…… በእነርሱ መተዛዘን; አንደኛቸው የወንድሙን ቤት አንኳኩቶ እንዴት "ተመለስ" ሊባል። በእኛ ዘመን ግን, ስልክ የሚዘጋው… መብራት የሚያጠፋው… አድራሻ የሚቀይረው…… ቤት ይቁጠረው https://t.me/hamdquante
3 58812Loading...
29
🟢 ስራዎች በገፅታቸው ወይም በብዛታቸው አይደለም የሚበላለጡት። የስራ መበላለጥ የሚከሰተው; ልብ ውስጥ ባለው ኢኽላስ ነው። ሰዎቹ ተመሳሳይ የሆነ ዒባዳ ይሰራሉ: በሁለቱ ሰዎች ዒባዳ መሃል ግን የሰማይ እና የምድር ያህል ርቀት ይኖራቸዋል። [ኢማም ኢብኑል ወይም] [إبطال التنديد - حمد بن علي/٢٤] https://t.me/hamdquante
3 59917Loading...
30
📖{لِّلَّهِ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ يَهَبُ لِمَن يَشَاءُ إِنَاثًا وَيَهَبُ لِمَن يَشَاءُ الذُّكُورَ} {የሰማያትና የምድር ንግሥና ለአላህ ነው፡፡ የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ ለሚሻው ሰው ሴቶችን ይሰጣል፡፡ ለሚሻው ሰው ወንዶችን ይሰጣል፡፡} ኢማም ኢብኑል ይቀም አላህ ይዘንለት እንዲህ ይላል፦ ‏"وكفى بالعبد تعرُّضًا لمقته ؛ ‏أن يتسخط ما وهبه " "አንድ ባሪያ አላህ በሰጠው ነገር መቆጣቱ; ራሱን ለአላህ ቁጣ ለመጋበዙ በቂው ነው።" https://t.me/hamdquante
3 35716Loading...
31
يا نور السموات والأرض ومن فيهن، يا حق، 🤲ارحم ضعفي🤲 يا الله يا رؤوف يا رحيم يا أهل الحمد وأهل العبادة سبحانك ما أكرمك، 🤲أرفع البلاء عني🤲 يا أول ليس قبله شيء وأخر ليس بعده شيء أنت ربنا لا إله إلا أنت 🤲نعوذ بك من شر ما صنعنا🤲 https://t.me/hamdquante
3 0458Loading...
32
🤲اللهم ……… أنت عضدي، ونصيري، وبك أحول، وبك أصول، https://t.me/hamdquante
3 0032Loading...
33
🟢     አስደሳች ዜና                                 ታላቅ የዳዕዋ እና የዝያራ ፕሮግራም!! 🧲ጉራጌ ዞን ጌቶ ወረዳ እና አካባቢው ላላቹ ወንድም እህቶች    🕌መስጂደል-ሱና ቆረፍቻ ጁማዐ ከጁማዐ ኹጥባ ጀምሮ መስጂዳችን ታላቅ እንግዳን ታስተናግዳለች    👉  ኡስታዝ አቡ የህያ ኢሊያስ አወል.  አሏህ ይጠብቀዉ      ወደ መስጂዳችን መስጂደል-ሱና(ቆረፍቻ) የሚያቀና መሆኑን እያበሰርናችሁ ከጣፋጭ ምክሮቹ ሰምታችሁ እንድትጠቀሙ እና ላልሰሙ ወዳጅ ዘመዶች እንድታስተላልፉ ከወዲሁ እንጋብዛለን። የፊታችን ጁምዐ ከጁምዐ ኹጥባ ጀምሮ በአሏህ ፈቃድ  ሙሀደራና, አጠር ያለ ሪሳላ,  የፈትዋ ጥያቄዎች እና የመሳሰሉ ፕሮግራሞች ይደረጋሉ። ለሴቾችም በቂ ቦታ ተዘጋጅቷል         የመስጂዳችን አጠቃላይ ፕሮግራሞች ለመከታተል       👇  👇  👇  👇  👇 https://t.me/mesjdesunakorefcha
3 7326Loading...
34
🟢 አንተስ?? 📖{حَتَّىٰ إِذَا أَتَوْا عَلَىٰ وَادِ النَّمْلِ قَالَتْ نَمْلَةٌ يَا أَيُّهَا النَّمْلُ ادْخُلُوا مَسَاكِنَكُمْ لَا يَحْطِمَنَّكُمْ سُلَيْمَانُ وَجُنُودُهُ وَهُمْ لَا يَشْعُرُونَ} {በጉንዳን ሸለቆ በመጡ ጊዜ: አንዲት ጉንዳን "እናንተ ጉንዳኖች ሆይ! ወደ መኖሪያዎቻችሁ ግቡ፡፡ ሱለይማንና ሰራዊቱ እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ አይሰባብሩዋችሁ" አለች፡፡} ጉንዳን ናት……… ወገኖቿ በሱለይማን እና በሰራዊቱ እንዳይጨፈለቁ ካስጠነቀቀች በኋላ: ሱለይማንና ወታደሮቹ ይህንን ድርጊት ቢያስገኙ እንኳ "ሳያውቁ ነው" ብላ ዑዝር ትሰጣቸዋለች። 🧿አንተስ……… ወንድምህ ታሳስቶ ሲያጠፋ ስታየው ዑዝር ትሰጠዋለህ?? ወይስ……… አለማወቁም እያወክ ትፈርድበታለህ?? https://t.me/hamdquante
3 33018Loading...
35
🟢 በዚህም ምክንያት……… ዐምይ የሆኑ ሰዎች ከብዙ ጣሊበል ዒልሞች በዐቂዳቸው እና በኢኽላሳቸው የተሻሉ ሆነው ታገኛቸዋለህ። እነዝያ ጣሊበል ዒልሞች………     ሀሳብ ጭንቀታቸው ሁሉ መፈላፈል እና መተቸት ነው። "አሉ" ተባለ ነው። ስለ እከሌ ምን ትላለህ? ስለ እከሌ ኪታብ ምን ትላለህ? እከሌ ስለ ፃፈው ነገር ምን ትላለህ? ማለት እንጂ ሌላ ሀሳብ የላቸውም። ይህ ነው………     አንድ ባሪያ ልቡን ከአላህ አዘናግቶ በ"አሉ" ተባለ ተጠምዶ እንዲባክን የሚያደርገው ነገር። 🧿ለሁሉም ሰው የማስተላልፈው ነሲሀ………    ሰዎች እና ንትርካቸው ትቷቸው ወደ አላህ እንዲቀጣጭ ነው። ይህ ነው የተሻለው ነገር።      /ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን/     [ لقاء الباب المفتوح 232/7] https://t.me/hamdquante
3 45913Loading...
36
✍       የደጋጎች ጀርባ የሚቆርጥ ሙሲባ!! ሓዲሱ አስፈሪ ከሆኑ የነብዩﷺ ሓዲሶች ተርታ ሊመደብ ይችላል።    ኢብኑ ማጃህ ከሰውባን ባስተላለፈው የአላህ መልእክተኛﷺ እንዲህ ይላሉ፦   «لأعلمن أقواما من أمتي يأتون يوم القيامة بحسنات أمثال جبال تهامة بيضا، فيجعلها الله -عز وجل- هباء منثورا» «የቂያማ ቀን ከህዝቦቼ ውስጥ እንደ ትላልቅ ተራራዎች የገዘፈ ምንዳ ይዘው ይመጡና አላህ የተበተነ አቧራ የሚያደርግባቸው ሰዎች አውቃለሁ» አሉ። قال ثوبان:     "يا رسول الله، صِفْهم لنا، جلِّهم لنا، أن لا نكون منهم، ونحن لا نعلم" ሰውባን:   "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ሳናውቅ ከእነርሱ  እንዳንሆን ለእኛ ግለፃቸው አብራርተህ ንግረን" አላቸው። قال:   أما إنهم إخوانكم، ومن جلدتكم، ويأخذون من الليل كما تأخذون، «እነርሱማ ወንድሞቻችሁ ናቸው, ከእናንተው ጎራ ናቸው, ከለይል እንደ ምትሰግዱት ሁላ የሚሰግዱ ናቸው» አሉ። «ولكنهم ………» «ነገር ግን…………» አሉ የአላህ መልእክተኛﷺ : : : : : :    «أقوام إذا خلوا ‌بمحارم ‌الله انتهكوها» «ብቻቸው በሚነጠሉ ጊዜ አላህ ዕርም ያደረጋቸው ነገሮች የሚዳፈሩ ሰዎች ናቸው» አሉ። ላ ኢላሃ ኢለሏህ!!      ወላሂ በጣም እጅግ በጣም አስፈሪ የሆነ ሓዲስ ነው። አላህ ያገራልህ………     ትሰግዳለህ… ትጾማለህ… ትቀራለህ… ሰዎችን ትመክራለህ… የቻልከው ዒበዳ ታስገኛለህ። ማሻ አላህ!! 🫵ወንድሜ…………      ማንም ሳይኖር… ብቻህን ስትሆን… ለብቻህ ስትነጠል… ማንም የሌለበት… ማንም የማያይህ ቦታ ላይ ስትሆን………        ምን ዐይነት ሰው ነህ?? 🫵ወንድሜ…………    የሚያውቅህ ሰው የሌለበት ሀገር ስትሄድ…… የማትታወቅበት ከተማ ስታርፍ…… ከስልክህጋ ብቻህን ስትሆን…… ትራንስፖርት ውስጥ ብቻህን ስትሆን………     ምን ዐይነት ሰው ነህ?? እዚህጋ ነው የብዙኃን ደጋጎች ጀርባ የሚቆረጠው!!      🤲አላህ ይጠብቀን🤲 إذا خلوت بريبة في ظلمة      👈والنفس داعية إلى العصيان فاستحي من نظر الإله وقل لها       👈 إن الذي خلق الظلام يراني https://t.me/hamdquante
4 33859Loading...
37
✍ ከአቡ ሁረይራ በተላለፈው የአላህ መልእክተኛﷺ እንዲህ ይላሉ፦ «من لم يسأل الله غضب الله عليه» «አላህ የማይለምን የሆነ ሰው አላህ ይቆጣበታል።» https://t.me/hamdquante
3 11015Loading...
38
✍ ከአንዱ አጫሽ ጋ እያወሩ ነው………… "የሲጋራው እሳት በልብስህ አጥፋውና እናውራ" ሲለው "ልብሴን እስከ ማቃጥል ድረስ እብድ መሰልኩህ እንዴ?" አለው "አሀ! ልብስህ ከሳንባህ በላይ ውድ ሆኖ ነው?? https://t.me/hamdquante
3 60024Loading...
39
🔊 አማራጭ ከሌለው እስልምና መሸሽ እስከመቼ??!! 🟣እስልምና  ከጌታችን ዘንድ የመጣ ታላቁ ፀጋ ነው!! 🟣እስልምና ወደ አንድ አምላክ የሚጣራ ብቸኛው ሃይማኖት ነው!! 🟣እስልምና ሁሉም ነብያቶች የተጣሩበት ሃይማኖት ነው!! 🎤 በታላቁ ወንድማችን አቡ ሰልማን ዐብዱልመጂድ ወርቁ አላህ ይጠብቀው። 🕌 በሱና መስጂድ (ወልቂጤ) 📅 ዕለተ ቅዳሜ, 19/08/2016 EC (ከመግሪብ በኋላ) በእስልምና ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ትምህርቶች ለመከታተል 👇 👇 👇 ይቀላቀሉን!! https://t.me/islmina_min_ale
3 09216Loading...
40
Media files
2 95018Loading...
✍      ስስታሙ ሰወዬ ወደ ገበያ ወጥቶ ማንቆርቆሪያ እና ሳህን ገዛ አሉ።    የገዛቸው ዕቃዎች ይዞ ወደ ማተሚያ ቤት በመሄድ "እባክህ እላያቸው ላይ የሆነ ነገር ብለህ ፃፍልኝ" አለው።   "ምን ብየ ልፃፍልህ?" ሲለው; 🫖ማንቆርቆሪያው ላይ:  {فَمَن شَرِبَ مِنْهُ فَلَيْسَ مِنِّي}   {ከእሱ የጠጣ ከእኔ አይደለም።} 🍽ሳህኑ ላይ ደግሞ:      {وَمَن لَّمْ يَطْعَمْهُ فَإِنَّهُ مِنِّي}   {ያልቀመሰው ሰው እሱ ከእኔ ነው።} ብለህ ፃፍባቸው አለው። https://t.me/hamdquante
Show all...
🇵🇸ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

👍 11
አንዳንድ ጊዜ………  {يَا لَيْتَنِي مِتُّ قَبْلَ هَذَا وَكُنتُ نَسْيًا مَّنسِيًّا} የምትልበት ቻሌንጅ ይገጥምህና መልሶ ደግሞ……… {لَعَلَّ اللَّهَ يُحْدِثُ بَعْدَ ذَلِكَ أَمْرًا} የሚል ተስፋ መንፈስህን ይጠግንልሃል!! https://t.me/hamdquante
Show all...
👍 18👌 2💯 1
የጉዳዩ መፈፀሚያ ጊዜ ሲደርስ አላህ በሮቹ ይከፍታቸውና ሰበቦቹ ያገራቸዋል!! በሰብር ጠብቅ https://t.me/hamdquante
Show all...
👍 35💯 5
✍      ኡስታዝ……… ኡስታዝህ ከዐይን ብሌንህ የበለጠ ልትወደው, ልትንከባከበው, ልትጠብቀው ይገባሃል። አላህ……… አባት እናትህ ለመፈጠርህ ሰበብ ካደረጋቸው በኋላ ተጨንቀው, ተጠበው እና ተቸጋግረው ከጥሩው, ከጣፋጩ እያበሉ እንዲህ  የተዋበ ሰውነት ገንብተውልሃል። ዳሩ ግን ይህ ውብ ግንባታ የጀሀነም እሳት ማቀጣጠያ ብቻ ሁኖ ሊቀር ይችላል።   ከዚህ መጨረሻ እና ዕረፍት ከሌለው ዕሳት ድነህ, በምእናብህ አስበህ ልትደርስበት እንኳ በማትችል ፀጋ የተሞላው ዘላለማዊው ጀነት እንድትገባ ከተፃፈልህ: ለዚህ ስኬት ሰበብ በመሆን   የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው ኡስታዝህ ነው!! ምን ይህ ብቻ………    ዛሬ ላይ ኡስታዝህን ጨምረህ ታላቁም ታናሹም የምትመዝንበት ሚጥጥዬ ዕውቀትህ እንኳ ከኡስታዝህ ምንጭ የተቀዳ ነው። አላህ እሱ ሰበብ ባያደርግልህ ዛሬ ላይ "ተራ" ከምትላቸው ሰዎች የባስክ "ተራ" ነበርክ። ከዚህ ሁሉ ውለታ………    ጥቂቱን እንኳ መመለስ ቢሳንህ: ውለታውን ዐውቀህ ማክበሩ እንዴት ይሳንሃል?? ነገር ግን ዕወቅ………    ኡስታዝህ ማለት ኡስታዝህ እንጂ ነብይህ አይደለም!! ከእሱ………    ሐቅ የሆነውን ትወስዳለህ; ውድቅ የሆነውን ትተወዋለህ!!   እንዲህ ስትል ቅር የሚለው ከሆነ……    እሱንም ተ ወ ው!! https://t.me/hamdquante
Show all...
🇵🇸ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

👍 27 5💯 4
Photo unavailableShow in Telegram
✍ ድሮ መድረሳ ላይ ቀድሞ አፍንጫውን የሚዘው ልጅ ነበር ፈስ እንደፈሳ ይጠረጠር የነበረው። በእርግጥም ብዙ ጊዜ የፈሱ ባለቤት ነበር ቀድሞ "ፈስ ፈስ" ብሎ አፍንጫውን የሚይዘው። ዛሬም ላይ በየ መድረኩ "ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ" የሚሉ ብሄርተኞች ኢትዮጵያን እያፈረሷት እንደሆነው ሁሉ በየጉራንጉሩ……… "ዘረኝነት ዘረኝነት" እያሉ ሰዎች ላይ ውዥንብር የሚፈጥሩ ዘረኞች ናቸው እያግማሙን ያሉት። https://t.me/hamdquante
Show all...
👍 42💯 11 3
ሴት ልጅ የሚያዋርድ ወንድ ካየህ…… እሱ ወንዶች መሃል የተዋረደ መሆኑን እወቅ!! https://t.me/hamdquante
Show all...
👍 35💯 12
🧿 ተጠንቀቅ!! እየተዋጋኸው ያለው ሰውየ ምን አልባትም መሳሪያው {حَسْبيَ الله وَنِعْمَ الوَكِيل} ሊሆን ይችላል። https://t.me/hamdquante
Show all...
👍 36👌 5
✍     ወንዳወንድነቱ ላይ ጉድለት ያለበት ባል ነው    በሆነው ባልሆነው  ሁለተኛ ሚስት እና ፍቺ ለሚስቱ ማስፈራሪያ አድርጎ መጠቀም የሚፈልገው። https://t.me/hamdquante
Show all...
💯 37👍 24🤝 1
አንድ ሰው ላይ ትልቅ ሙሲባ ማለት፦    ራሱ ላይ ጉድለት እንዳለበት ያውቅና: ይህንን ጉድለት ምንም ሳያስጨንቀው እና ቦታ ሳይሰጠው መቅረቱ ነው።         /ኢብኑ ሙባረክ/ https://t.me/hamdquante
Show all...
👍 28
አንድ ሰው ላይ ትልቅ ሙሲባ ማለት፦    ራሱ ላይ ጉድለት እንዳለበት ያውቅና: ይህንን ጉድለት ምንም ሳያስጨንቀው እና ቦታ ሳይሰጠው መቅረቱ ነው።         /ኢብኑ ሙባረክ/ https://t.me/hamdquante
Show all...