uk
Feedback
🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

Відкрити в Telegram

ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

Канал 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 12 188 підписників, посідаючи 7 209 місце в категорії Релігія і духовність та 2 770 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 12 188 підписників.

За останніми даними від 19 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -12, а за останні 24 години на 4, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 22.87%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 12.72% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 2 788 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 550 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 30.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 20 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

12 188
Підписники
+424 години
+87 днів
-1230 днів
Архів дописів
✏️ ክፉ ጓደኛ 🥰የእሳት ቁራጭ ነው‼️

☝️🦻 አእምሮህ ቢጠፋ ራሱ…… ከአእምሮህ የማይጠፋ ድምፅ!!

✏️ ሺዐ እና የአቅሷ ፖለቲካ……………   የሺዐ ስብስብ ከምስረታቸው ጀምሮ በሙስሊም ደም በመታጠብና የሙስሊሞች ግዛት በማውደም እስልምና ውስጥ ጥቁር ታሪክ ከመፃፍ ውጪ;    አንድም ድል ያደረጉት የኩፍር ሀገር ወይም የደመሰሱት የሙስሊም ጠላት የለም።    ይህንን በደም የጨቀየ ታሪክና በኩፍር የተበረዘ ዐቂዳ ይዘው [በተለይ በዚህ ዘመን] በሀገራችን እንኳ ሳይቀር ይህንን ሁሉ ደጋፊ እንዴት ሊኖራቸው ቻለ?? ከተባለ መልሱ ግልፅና ግልፅ ነው   አቅሷን በተመለከተ የቆመሩት ሀይለኛ ፖለቲካ ነው!!    እንደሚታወቀው እያንዳንዱ ሙስሊም አኼራ ላይ ጀነትን እንደሚመኘው ሁሉ: ዱንያ ላይም ሦሥቱ ቅዱሳን ስፍራዎች ጋ ለመድረስ ይጓጓል። ሆኖም; ሐረመይን አላህ በአለ_ሱዑድ ሰበብ ደህንነታቸው አስጠብቆ ሲያኖራቸው፧ አቅሷ ግን አላህ ለሚፈልገው ጥበብ ከጊዜ ወደ ጊዜ በጠላት እጅ እየወደቀች እየተፈተነች ትገኛለች።   በዓለም ላይ ያሉ ሙስሊሞችም በየጎራው በተፈጠረው ክፍፍል ምክንያት ህብረት አጥተው ለቅዱሷ መስጂዳቸውን የሚገባትን ከለላ መስጠት አልቻሉም። በዚህም ልባቸው ተሰብሮ እንደ ዓለም አቀፍ ደረጃ በአሁን ሰዓት የሙስሊሞች ደካማው ጎን መስጂድ አል_አቅሷ ሆናለች።   ይባስ ብሎ ሐማሶች በጀመሩት ዕቅድ አልባ የደንባራ ውጊያ ሰበብ ሙሉ ጋዛ ለውድመት ሲዳርጋት የሙስሊሞች ቁጭትና ህመም ይበልጥ ተባባሰ።   የሐማሶች ዘመቻ ጥቅምና ጉዳት ያላመዛዘነ፤ በቂ ዝግጅት ያልተደረገበትና ምንም ዓይነት ድፕሎማሲ ያልታከለበት በመሆኑ ሌሎች የሙስሊም ሀገራቶች ጦርነቱ ላይ ቀጥታ ለመግባት ምቹ አልሆነላቸው። በዚህም የተበሳጩ ሙስሊሞች በተለይም ሳዑዲ ላይ ቁጣቸው በማጠንከር "አቅሷን ለምን ትተዋለች" የሚል አብዮት በውስጣቸው ተቀጣጠለ።    ይህንን የሙስሊሞች እልህና ቁጣ የተመለከቱ ሺዐዎች በሙስሊሞች በደካማ ጎናቸው ገብተው ልባቸው ለመማረክ በሚል ጭራሽኑ ዕውቅና ለማይሰጧት አቅሷ "እኛ ነን ነፃ አውጪዎቿ" በማለት ግርግር ፈጥረው ማስታወቂያ ሰሩ። በእልህና በቁጭት ተቃጥሎ የነበረው የዓለም ሙስሊም ወከባቸው በተመለከተ ጊዜ ተሸወደላቸው። እንጂማ…………    ዑመርን የሚሳደብ፤ ከመሳደብ አልፎም የሚያከፍር ስብስብ፧ ዑመር የከፈታትን ሀገር የሚከፍት ይመስልሃል???    ቢከፍትስ: በዑመር ዐቂዳ የሚያስተዳድራት ይመስልሃል???              በጭራሽ!!

👇
👇

✉️ ቆርጠህ ላክለት!!   🇮🇷"ሺዐዎች ከሌሎች ሙስሊሞች በተለየ መልኩ መስጂድ አል_አቅሷን ነፃ ለማውጣት ስለሚታገሉ ነው የምወዳቸው" ለሚለው…………    ሲጀመር በሺዐ መዝሀብ "በቁርኣን ውስጥ የተጠቀሰው መስጂድ አል_አቅሷ ምድር ላይ የለም፤ ረሱልﷺ ሚዕራጅ ያደረጉበት መስጂድ አል_አቅሷ ሰማይ ላይ (በአራተኛው ሰማይ) የሚገኝ እንጂ ፈለስጢን ሀገር የሚገኘው መስጂድ አይደለም።" ብለው ያምናሉ። ይህ ብቻም አይደለም;     በፈለስጢን ምድር የሚገኘው መስጂድ አል_አቅሷ እንኳንስ በላጭነት ሊኖረው ይቅርና: "ኩፋ ውስጥ የሚገኘው መስጂድ በፈድል ከአቅሷ ይበልጣል" ብለው ያምናሉ።   ⁉️"ምድር ላይ የለም!!" ብለው ለሚያምኑት አቅሷ በምን ሂሳብ ነው እሱን ነፃ ለማድረግ የሚታገሉት?????ይህ የዋሁ ሙስሊም ላይ የተጫወቱት ፖለቲካ ብቻ ነው።

⚽️ ለምሳሌ እኛ ሰፈር “ሰለፍይ ነኝ” የሚሉ አሉ¡¡   ኳስ ባለ ቀን አምይ መሰሎቻቸውና ካፊሮች ጭምር ተሰብስበው ኳሱን የሚያዩት እነዚህ ሰለፍይ ልጆች ሱቅ ነው። ሲመስለኝ፦    እነዚህ ጀለሶች ኳስ ሳትደግፍና ቲክ_ቶክ ሳታይ ሰለፍይ ሆነህ መኖር ኋላ ቀርነት ስለሚመስላቸው፧ ዕርድናቸው ለማሳየት ሲሉ ስለ ኳስ ከሌላው የበለጠ ይተነትናሉ ምናምን።    ኳስ በሚኖር ጊዜም ሌላው ቦታ ባይሰጠው እንኳ እነሱ ግን ቶሎ ከፍተው ይቀመጣሉ። ሌላውም እነሱጋ እየመጣ ማየት ይጀምራል። በየቦታው የዚህ ዓይነቱ ነው ያስቸገረው።

የኳስ ደጋፊዎች የገቡበት ሙሲባ!!    ፊትናው ላይ የወደቁትም ይሁን አላህ የጠበቃቸው ወጣቶች ሊያዳምጡት የሚገባ ወሳኝ ነሲሀ!! አቡ ቀታዳ ዐብደላህ ቢን ሙዘሚል    መርከዝ አስ_ሱናህ ቂልጦ https://t.me/merkezassunnah https://t.me/Al_Furqan_Islamic_Studio/21015

✏️ ሦሥት ዓይነት ሰዎች ዕድለ_ቢስ አይሆኑም መከራ አያገኛቸውም!! 🥰ኛ, ወላጆቹን የሚንከባከብ ሰው፦ 📖﴿وَبَرًّا بِوَالِدَتِي وَلَمْ يَجْعَلْنِي جَبَّارًا شَقِي
✏️ ሦሥት ዓይነት ሰዎች ዕድለ_ቢስ አይሆኑም መከራ አያገኛቸውም!! 🥰ኛ, ወላጆቹን የሚንከባከብ ሰው፦ 📖﴿وَبَرًّا بِوَالِدَتِي وَلَمْ يَجْعَلْنِي جَبَّارًا شَقِيًّا﴾ {ለእናቴም ታዛዥ አድርጎኛል፤ ትዕቢተኛና ዕድለ_ቢስ አላደረገኝም።}       [መርየም:³²] 🥰ኛ, ዱዐ የሚያዘወትር ሰው፦ 📖﴿وَلَمْ أَكُن بِدُعَائِكَ رَبِّ شَقِيًّا﴾ {ጌታዬ ሆይ! አንተን በመለመኔ ዕድለ_ቢስ አልሆንኩም}      [መርየም:⁴] 🥰ኛ, ቁርኣን አዘውትሮ የሚቀራ ሰው፦ 📖﴿مَا أَنزَلْنَا عَلَيْكَ الْقُرْآنَ لِتَشْقَى﴾ {ቁርኣን በአንተ ላይ እንድትቸገር አላወረድነውም።}     [ጣሀ:²] 🔵

✏️     "የሚጨቃጨቁ ሰዎች አብረው ሆነው ሳሉ ድምፃቸው ከፍ አድርገው ለምን ይጯጯሃሉ?"   ብሎ ሲጠይቅ…………   "በአካል ቢቀራረቡም በዝያች ቅፅበት ልባቸው ስለ ተራራቀች የተራራቁ ይመስላቸውና አንደኛው ሌላኛው ለማሰማት ሲል ይጮሃሉ።" 📱

`⚔️مقتطف بعنوان……… 🫵يـــــــارجـــال العقـــــــيدة      أنسيـــــــتم إجــــــرام الحوثــي؟ للشيخ الفاضل: أبي معاذ حسين الحطيبي حفظه الله

🗡     ከራፊዳ ጋ በሰይፍ ካልሆነ ምንም ዓይነት የሚደረግ ድርድር የለው!! 🗡الرافضة ليس لهم محاولة إلا السيف!! የኖራቸው ያወቃቸው ያያቸው    🪑ኢማሙ ሸውካኒ

↗️ ምላስህ አላህን ከማውሳት እስካልተቆጠበ ድረስ; መላኢካዎች ጀነት ውስጥ ቤትህን ከመገንባት አይቆጠቡም❗️ 📱
↗️     ምላስህ አላህን ከማውሳት እስካልተቆጠበ ድረስ;   መላኢካዎች ጀነት ውስጥ ቤትህን ከመገንባት አይቆጠቡም❗️ 📱

📱 የማትገመት ሁን‼️ "እሱማ ሀሳቡ እንኳ አይቀይርም" ብለው ሲያሙህ; 👇👇👇👇👇👇👇 👉ይህንን ቀይረህ አስገርማቸው!! 🔵Telegeram የሚለውን ተጭናችሁ ግቡ።

✏️ የባለማዕረጎች እስልምናን መቀበል ለዳዕዋው መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ ሊኖረው ቢችልም…… አንቀጿ የወረደችው ከፊል የቁረይሽ መኳንንቶች ለነብዩﷺ ደሀ ምእመናኖችን ከእሳቸው እንዲያርቁ ወይም ለእነ
✏️ የባለማዕረጎች እስልምናን መቀበል ለዳዕዋው መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ ሊኖረው ቢችልም……    አንቀጿ የወረደችው ከፊል የቁረይሽ መኳንንቶች ለነብዩﷺ ደሀ ምእመናኖችን ከእሳቸው እንዲያርቁ ወይም ለእነሱ ብቻ የሚሆን ልዩ ሸንጎ እንዲያዘጋጁላቸው በጠየቁ ጊዜ ነበር።     እነዚህ የቁረይሽ መኳንንቶች ሊሰልሙ ወይም ላይሰልሙ፧ ብቻ ግን ነብዩﷺ የሚሉትን ለማድመጥ ከአነዝያ ደሀዎች ጋ አንድ ቦታ ላይ አብረው መቀማመጥ አይፈልጉም ነበር።   በዚህ ጊዜ  ለነቢዩﷺ ታማኝ ምእመናንን ከመሰብሰብና ከእነሱ ጋር ከመሆን እንዳይገለሉ የሚመክር መለኮታዊ መመሪያ መጣ፦ ﴿وَاصْبِرْ نَفْسَكَ﴾ {ነፍስህን አስታግስ} ማለትም፦     ምንም እንኳን የሀብትና የሥልጣን ባለቤቶች ባይሆኑም ነፍስህን ከእነርሱ ጋር በማድረግ ላይ ያዛት። ከእነሱም አትለይ። እዚህ ላይ “አስታግስ” ማለት ነፍስን የታዛዦች (የአላህ ባሮች) ጓደኛ አድርጎ ማጽናትና ከእነሱ አለማራቅ ለማለት ነው። የተፈለገውም በውጫዊ አካል ብቻ አብሮ መቀመጥ ሳይሆን: በነፍስ፣ በልብና በትኩረትም ጭምር ከእነሱ ጋር መሆንን ነው። ​   በመቀጠል መመሪያው በዝርዝር ይበልጥ ግልጽ ተደረገ፦ ﴿وَلَا تَعْدُ عَيْنَاكَ عَنْهُمْ﴾ {ዓይኖችህም ከእነሱ (ወደሌላ) አይለፉ።} ማለትም፦     የዱንያ ጌጥና ማዕረግ ያላቸውን ሰዎች በመፈለግ እንዲሁም ወደ እሰልምና ለማስገባት በማሰብ ዓይኖችህ ከእነሱ አልፈው ወደ ሌሎች አይመልከቱ። ባለሥልጣናትንና ባለሃብቶች ጋ የመድረስ ፍላጎት እነዚህን ታማኝ ምእመናን ቸላ ለማለት ምክንያት አይሁንህ። ​   የባለማዕረጎች እስልምናን መቀበል ለዳዕዋው መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ ሊኖረው ቢችልም፧ አላህ የሰው ልጅ ዋጋ በያዘው ሀብት ወይም በሰዎች ዘንድ ባለው ቦታ ሳይሆን፧ ልቡ በያዘው እውነትና ኢኽላስ መሆኑን መሠረታዊ መመሪያ አድርጎ ሊተክል ወደደ። ​  በዚህ አንቀጽ ውስጥ ለዘመናችን ዱዐቶችም ትልቅ መመሪያ አለው፦    ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎችን ማግኘት ዳዕዋውን ሊጠቅም ይችላል; ነገር ግን አላህን ፈልጎና ሐይማኖቱን ሊማር በእውነት የመጣውን ሰው በመተው ወይም ቸላ በማለት ሙሉ ትኩረት ወደ ታዋቂዎች መዘንበል  የለበትም። የሰው ልጅ ዋጋ በሥልጣኑ፣ በሀብቱ ወይም በተከታዮቹ ብዛት አይለካም። ዳዕዋውም ወደ follower ቆጠራ፣ view ንፅፅር እና Like ብዛት መለወጥ የለበትም!! 🔵🔵🔵🔵🔵

✏️ ​የተሰበረው ስሜት የተጠገነባት አንቀጽ‼️ አንቀጿ የወረደችው ነብዩﷺ ለልባቸው እጅግ ተወዳጅ የሆነችውን መካን ተሰናብተው በመውጣት ወደ መዲና በሚሰደዱበት ወቅት መንገድ ላይ ሳሉ ነበር። በዚያ
✏️ ​የተሰበረው ስሜት የተጠገነባት አንቀጽ‼️    አንቀጿ የወረደችው ነብዩﷺ ለልባቸው እጅግ ተወዳጅ የሆነችውን መካን ተሰናብተው በመውጣት ወደ መዲና በሚሰደዱበት ወቅት መንገድ ላይ ሳሉ ነበር። በዚያ የስንብት ስሜት እጅግ ከብዶ በነበረበት ቅጽበት ይህች አንቀጽ ለልባቸው ማረጋጊያና የመመለሻ ቃል ኪዳን ልትሆናቸው፤ መንፈሳቸውንም ልታድስና ይህ ስደት የመንገዱ መጨረሻ እንዳልሆነ፧ ከስደቱም ጀርባ ተመልሶ መግባት እንዳለ ብስራት ልትነግራቸው ወረደች።    ይህም አንቀጿን እጅግ የተለየች ያደርጋታል። ከመካ በሚወጡበት ያችሁ ቅጽበት የመመለስ ቃል ኪዳን ተሰጣቸው። 📖​﴿إِنَّ الَّذِي فَرَضَ عَلَيْكَ الْقُرْآنَ} (ያ……  በአንተ ላይ ቁርኣንን ግዴታ ያደረገው አካል} ማለትም፦      ይህንን ቁርኣን በአንተ ላይ ያወረደልህ፣ ከፍጥረታቱም ሁሉ መርጦ እንድትሸከመውና እንድታደርስ ያደረገህ አካል፧ እርሱ ራሱ; {لَرَادُّكَ إِلَى مَعَادٍ} {በእርግጥ ወደ መመለሻህ ይመልስሃል።} ማለትም፦     አላህ ከእሷ ካወጣህ በኋላ መልሶ ያስገባሃል። ​  ስደቱ የታሪኩ ማጠቃለያ አልነበረም። የነብዩም ከመካ መውጣት ያለ መመለስ የቀረ ስደት አልነበረም። ይልቁንም በመንገዱ መጨረሻ ላይ የሚጠብቃቸው ቃል ኪዳን ነበረ።   ነብዩﷺ ከዓመታት በኋላ መካን በድል አድራጊነት ተቆጣጥረው ወደ እሷ ተመለሱ። የአላህም ቃል ኪዳን እውነት ሆነ፤ አላህ ቃል ኪዳኑን አያጥፍምና።በዚህች አንቀጽ ውስጥ ለእኛም ትልቅ መልእክት አለ; ይህ የምንጓዝበት እያንዳንዱ መሰናክል መመለሻ አለው።   ቁርኣንን ተሸክመን በዚህች አጭር ሕይወት ውስጥ እንጓዛለን፤ ከዚያም መመለሻችን ወደዚያ ቁርኣኑን ወደ አወረደው አላህ ነው!!

📺    ከጁሙዐ በኋላ ዘወር ዘወር እያላችሁ አንዳንድ ነገሮች ማየት ከፈለጋችሁ። 👇👇የኮከብ ምስሉን ተጭናችሁ ግቡ!!         ★★★★★★★★★

✏️ ሙጅሪሞች የሚሾሙት በሷሊሖች አመፅ ነው!! 📖ኢብን አቢ ዱንያ ከፉደይል ኢብኑ ዒያድ ባስተላለፈው፦ አላህ ወደ ከፊል ነብያቶች እንዲህ ስል አስተላልፏል;   "እኔን ያወቁኝ ሰዎች ባመፁኝ ጊዜ: እኔን የማያውቁ ሰዎች እሾምባቸዋለሁ"       [الداء والدواء  ص١١٧]

🇮🇷 ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለች አደገኛ ካምሰር ናት!!
🇮🇷 ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለች አደገኛ ካምሰር ናት!!

📖﴿إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلّونَ عَلَى النَّبِيِّ يا أَيُّهَا الَّذينَ آمَنوا صَلّوا عَلَيهِ وَسَلِّموا تَسليمًا} {አ
📖﴿إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلّونَ عَلَى النَّبِيِّ يا أَيُّهَا الَّذينَ آمَنوا صَلّوا عَلَيهِ وَسَلِّموا تَسليمًا} {አላህና መላኢካዎቹ በነቢዩ ላይ ሰለዋት (የአክብሮት ውዳሴና ዱዐ) ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት ዱዐን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡} 💫ነብዩﷺ እንዲህ ይላሉ፦ «أكثروا الصلاة علي يوم الجمعة وليلة الجمعة فمن صلى علي صلاة صلى الله عليه عشرا » «ጁሙዐ ቀንና ጁሙዐ ሌሊት በእኔ ላይ ሰለዋት አብዙ። በእኔ ላይ አንድ ጊዜ ሰለዋት ያወረደ ሰው በእሱ ላይ አላህ ዐስር ጊዜ ሰለዋት ያወርድበታል።» «من صلى علي مرة كتب الله له بها عشر حسنات» «በእኔ ላይ አንድ ጊዜ ሰለዋት ያወረደ ሰው አላህ ለእሱ በዚህ ምክንያት ዐስር ምንዳ ይፅፍለታል።» « من صلى علي من أمتي صلاة مخلصا من قلبه صلى الله عليه بها عشر صلوات ورفعه بها عشر درجات وكتب له بها عشر حسنات ومحا عنه عشر سيئات » «ከኡመቶቼ ውስጥ ከቀልቡ ጥርት አድርጎ በእኔ ላይ ሰለዋት ያወረደ የሆነ ሰው; አላህ በእሷ ምክንያት ዐስር ሰለዋት ያወርድበታል፣ ዐስር ደረጃም ከፍ ያደርግለታል፣ ዐስር ምንዳም ይፅፍለታል፣ ዐስር ወንጀልም ያብስለታል።» « من صلى علي واحدة صلى الله عليه عشرا » «በእኔ ላይ አንድ ሰለዋት ያወረደ በእሱ ላይ አላህ ዐስር ያወርድበታል።»   🤲اللهم صل على محمد وعلى آل محمد    كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد، 🤲اللهم بارك على محمد وعلى آل محمد      كما باركت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد. ወደ መልካም ያመላከተ የሰሪው ምንዳ ያገኛል!! ⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️