es
Feedback
🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

Ir al canal en Telegram

ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸

El canal 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸 (@hamdquante) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 12 115 suscriptores, ocupando la posición 7 540 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 777 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 12 115 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 14 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de -24, y en las Ăşltimas 24 horas de -2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 27.07%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 13.17% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 3 280 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 1 596 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 38.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው። ✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼ 👇🏾👇🏾👇🏾 @hamdquante አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል 👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 15 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a ReligiĂłn y espiritualidad.

12 115
Suscriptores
-224 horas
+47 dĂ­as
-2430 dĂ­as
Archivo de publicaciones
🕋 መካ ውስጥ ሁሉም ዒባዳ ይባዛል? ወንጀልስ??   ሐረም ውስጥ ሁሉም ዒባዳዎች በመቶ ሺህ ይባዛሉን? ወይስ ሰላት ብቻ ነው በመቶ ሺህ የሚባዛው? የሚለው ጥያቄ ዑለሞች መሃል ኺላፍ ያለበት ርዕስ ሲሆን ሦሥት ዋና ዋና አቋሞች አሉ። 1ኛው, ሁሉም ዒባዳዎች እንደ ሰላት በመቶ ሺህ ይባዛሉ የሚል ነው። ለዚህም የሚጠቅሱት ሐዲስ አላቸው; ሐዲሱ ግን በርካቶቹ ደዒፍ መሆኑን ይገልፃሉ። 2ኛው, ሐረም ውስጥ የሚሰራ የትኛውም ዒባዳ በዚህ ያህል ባይባልም ሌላ ቦታ ከሚሰራ ዒባዳ ብልጫ አለው የሚል ነው። ለዚህ የሚጠቅሱት መረጃ በጥቅል የሐረምን በላጭነትና ቱሩፋት በመጥቀስ የመጡ መረጃዎችንና የሰለፎችን ተግባር ነው። 3ኛው, የኡሱልዮች  አቋም ሲሆን; ቀጥታ ጥቅሱ የመጣበትን ሰላት እንጂ ሌላ ዒባዳ ላይ የሚደረግ ጭማሪ አለ አንልም ይላሉ።   ወላሁ አዕለም የሁለተኛው አቋም አሳማኝ ይመስላል!! ወንጀል በተመለከተ......   አላህ ይጠብቀንና  ሐረም ውስጥ የሚፈጸም ወንጀል ሌላ ቦታ ከሚፈጸመው ይበልጥ የከፋ እንደሆነ ሁሉም ቢስማሙበትም ወንጀሉ የሚከፋው በምን መልኩ ነው? በሚል ግን ሁለት ዓይነት አቋሞች አሉ፦ 1ኛው, ልክ እንደሰላት ወንጀሉም ቁጥሩ ይበዛል የሚል ሲሆን; 2ኛው, የቁጥሩ ብዛት ሳይሆን የወንጀሉ ክብደት (ቅጣት)  ከፍ ይላል የሚል ነው።    ከሚጠቅሷቸው መረጃዎች አንጻር የወጀሉ ክብደት ይጨምራል የሚለው አሳማኝ ነው!!

ما_السبب_في_كثرة_الجنائز_في_المكة_1.mp32.31 MB

✍ የእስልምና ውበት!!..... «ለዐረቡ ዐረብ ካልሆነው: ለነጩም ከጥቁሩ በአላህ ፍራቻ ቢሆን እንጂ ምንም ብልጫ የለውም።» ይላሉ ረሱልﷺ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት፦ ለእስልምና በዋላቸው በጎ ተግባ
✍       የእስልምና ውበት!!.....   «ለዐረቡ ዐረብ ካልሆነው: ለነጩም ከጥቁሩ በአላህ ፍራቻ ቢሆን እንጂ ምንም ብልጫ የለውም።» ይላሉ ረሱልﷺ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት፦    ለእስልምና በዋላቸው በጎ ተግባሮቹ ሙስሊሞች ዘንድ ክብር የነበረውና እንደ ሀገርም በነበረው የከንቲባነት ስልጣን "አንቱታን" ያተረፈው ሰሞኑ ወደ አኼራ የሄደው የወንድማችን "ዓሊ ዐብዶ" ቀብር ነው [አላህ ይዘንለት]። በእስልምና አስተምህሮ፦     አንድ ሰው ከሞተ በኋላ የአኼራ ጉዳዩ የሚወሰነው ከመሞቱ በፊት በሰራቸው ስራዎቹ ልክ ነው። እንጂ ከሞተ በኋላ ቀብሩ ላይ የሚደረግ ግንባታም ይሁን ማስዋብ ለሟቹ ቅንጣት ያህል እንኳ የሚጠቅመው ነገር የለም። ይህ ለሁሉም ባለፀጋዎች እና ደሀዎች ትልቅ ትምህርት ይሰጣል። ከፍተኛ ስልጣንና ሰፊ ሀብት ኖሮት በድሎት የኖረውም ይሁን; ከስልጣንም ይሁን ከሀብት ቅንጣት ሳይደርሰው በችግር የኖረው ሁለቱም በተመሳሳይ ጨርቅ ተከፍነው በተመሳሳይ ጉድጓድ ይቀበራሉ። አኼራ ላይ የሚኖራቸው ሕይወት የሚመዘነው ሁለቱም ከመሞታቸው በፊት ከሞቱ በኋላ ለሚኖራቸው ሕይወት ሰርተው ባስቀደሙት ልክ ነው። لا داع Ů„لمعإ بؚد الموت يسكنها     إلا التي كان قبل الموت ŮŠŘ¨Ů†ŮŠŮ‡Ř§ فان بناها Ř¨ŘŽŮŠŘą ءاب مسكنها      وان بناها بشع, ؎اب Ř¨Ř§Ů†ŮŠŮ‡Ř§

✍ የእስልምና ውበት!!..... «ለዐረቡ ዐረብ ካልሆነው: ለነጩም ከጥቁሩ በአላህ ፍራቻ ቢሆን እንጂ ምንም ብልጫ የለውም።» ይላሉ ረሱልﷺ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት፦ ለእስልምና በዋላቸው በጎ ተግባ
✍       የእስልምና ውበት!!.....   «ለዐረቡ ዐረብ ካልሆነው: ለነጩም ከጥቁሩ በአላህ ፍራቻ ቢሆን እንጂ ምንም ብልጫ የለውም።» ይላሉ ረሱልﷺ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት፦    ለእስልምና በዋላቸው በጎ ተግባሮቹ ሙስሊሞች ዘንድ ክብር የነበረውና እንደ ሀገርም በነበረው የከንቲባነት ስልጣን "አንቱታን" ያተረፈው ሰሞኑ ወደ አኼራ የሄደው የወንድማችን "ዓሊ ዐብዶ" ቀብር ነው [አላህ ይዘንለት]። በእስልምና አስተምህሮ፦     አንድ ሰው ከሞተ በኋላ የአኼራ ጉዳዩ የሚወሰነው ከመሞቱ በፊት በሰራቸው ስራዎቹ ልክ ነው። እንጂ ከሞተ በኋላ ቀብሩ ላይ የሚደረግ ግንባታም ይሁን ማስዋብ ለሟቹ ቅንጣት ያህል እንኳ የሚጠቅመው ነገር የለም። ይህ ለሁሉም ባለፀጋዎች እና ደሀዎች ትልቅ ትምህርት ይሰጣል። ከፍተኛ ስልጣንና ሰፊ ሀብት ኖሮት በድሎት የኖረውም ይሁን; ከስልጣንም ይሁን ከሀብት ቅንጣት ሳይደርሰው በችግር የኖረው ሁለቱም በተመሳሳይ ጨርቅ ተከፍነው በተመሳሳይ ጉድጓድ ይቀበራሉ። አኼራ ላይ የሚኖራቸው ሕይወት የሚመዘነው ሁለቱም ከመሞታቸው በፊት ከሞቱ በኋላ ለሚኖራቸው ሕይወት ሰርተው ባስቀደሙት ልክ ነው። لا داع Ů„لمعإ بؚد الموت يسكنها     إلا التي كان قبل الموت ŮŠŘ¨Ů†ŮŠŮ‡Ř§ فان بناها Ř¨ŘŽŮŠŘą ءاب مسكنها      وان بناها بشع, ؎اب Ř¨Ř§Ů†ŮŠŮ‡Ř§

✍ ሁሉም ሰው ሊባል ይችላል (አላህ የጠበቀው ሲቀር)   የሆነች እንድትነሳ የማይፈልጋት ርዕስ አለችው። ወንጀል መሆኑ ልቡ ያውቃል፤ ግን ደግሞ የለመደው ነገር ስላለ መተው ማቆም አይፈልግም። የሚያውቁት ሰዎች ሲገናኝም ሁሌ እንደተሳቀቀ ነው። ወንጀል መሆኑን እያወቀ: መተውም ስላልፈለገ ነውና የሚሰራው ማንም በዚህ ዙሪያ እንዲናገረው አይፈልግም። ድምፁ አይሰማም እንጂ በውስጡ፦    "ወንጀል መሆኑን የማላውቅ መስሎህ ነው እንዴ? በቃ ተወኝ አትነዝንዘኝ። ፋራ!!" ይልሃል። ለእሱ ሸውራራ ስሜት ቦታ ሳይሰጡ ነጥቡን እያነሱ የሚያወግዙ ሰዎች ሲገጥመው;    የማይገባቸው፣ ኋላቀሮች፣ ያልነቁ፣ ንግግር የማይችሉ አርጎ ይስላቸዋል። ይህ ድክመት ብቻ ሳይሆን ከባድ አመጽ ነው!! ሙእሚንማ      ኢማኑ ደክሞ ወንጀል ላይ ቢወድቅ እንኳ: ጥረትና ፍላጎቱ ሁሌም ከወንጀሉ ወጥቶ ተውበት ለማድረግ ነው። በዚህ ዙሪያ ለሚመክሩትም ክብር ይሰጣል።   ለዚህም ነው ዑለማዎች ሲመክሩ "ሁለት ሰዎች አብረው ኸምር እየጠጡ ቢሆን እንኳ አንዱ ሌላው ላይ ማውገዝ አለበት" የሚሉት።

✍ ኢማም ለተከታዮቹ የሚሸፍንላቸው ስድስት ነጥቦች!! 1ኛ, ከፋቲሓ በኋላ ያለው ቂርኣት; የትኛውም ሰላት ላይ ፋቲሓ መቅራት በሁሉም ሰጋጅ ላይ ግዴታ ነው። ከፋቲሓ በኋላ ያለው ቂርኣት ግን ጀህር ላ
✍      ኢማም ለተከታዮቹ የሚሸፍንላቸው ስድስት ነጥቦች!! 1ኛ, ከፋቲሓ በኋላ ያለው ቂርኣት;    የትኛውም ሰላት ላይ ፋቲሓ መቅራት በሁሉም ሰጋጅ ላይ ግዴታ ነው። ከፋቲሓ በኋላ ያለው ቂርኣት ግን ጀህር ላይ ከሆነ ማእሙም የኢማሙን ቂርኣት ያዳምጣል እንጂ በራሱ አይቀራም። 2ኛ, የማሟያ ሱጁድ;     ከኋላ የሚሰግደው ማእሙም ሰላቱ ላይ ሰላትን የማያፈርስ ስህተት ወይም መርሳት ቢያስገኝ ለብቻው የማሟያ ሱጁድ አያደርግም: የኢማሙ ሰላት ለእሱ ስህተት ያሟላለታል። ኢማሙ በራሱ የተሳሳተው ነገር ኖሮ ሱጁድ ከወረደ ግን ተከታዩ ምክንያቱ ባያውቅም ኢማሙን ተከትሎ ሱጁድ ያደርጋል። 3ኛ, የቲላዋ ሱጁድ;    ኢማሙ ሱጁድ የሚወረድበት አንቀጽ ቀርቶ ሱጁድ ከወረደ ማእሙም ተከትሎ ይወርዳል፤ ሳይወርድ ካለፈውም ተከታዩ ተነጥሎ ሱጁድ አያደርግም። እንዲሁም; ድምፅ ሳይወጣ በሚሰገድባቸው ሰላቶች ማእሙም ሱጁድ የሚወረድበት አንቀጽ ቢቀራ እንኳ ኢማሙን ትቶ ሱጁድ አያደርግም። 4ኛ, ሱትራ;    ኢማም ያደረገው ሱትራ ለሁሉም ማእሙሞች ይሆናል። ኢማም ተከትለህ እየሰገድክ አንዱ ከፊትህ ማለፍ ቢፈልግ መከልከል የለብህም: ምክንያቱም አንተ የምትወከለው በኢማምህ ሱትራ ነው። 5ኛ, የቁኑት ዱዐ;     የቁኑት ዱዐ በሚደረግባቸው ሰላቶች ላይ ማእሙም የኢማሙን ዱዐ እየሰማ "ኣሚን" ይላል እንጂ እሱ የራሱ ዱዐ አያደርግም። 6ኛ, "سمع الله لمن حمده " ማለት;     ከሩኩዕ በኋላ ኢማም "سمع الله لمن حمده" ሲል ማእሙም "ربنا ولك الحمد" ወይም መሰሎቹ ይላል እንጂ: ለብቻው እንደሚሰግድ ዓይነት "سمع الله لمن حمده" አይልም።

✍ የመፈመስ ጉጉት ያለው ሰው የአኼራ ጥፍጥና ሊያገኝ አይችልም!!

✍ ሾል ቦታ ሴት ቀጥሮ ቀኑን ሙሉ ከእሷ ጋ የልብልቡን ሲያወራ ይውልና: ማታ መጥቶ ድካሙን ሲያራግፍብሽ;      የምር የሚስትነት ክብር ይሰማሻል ወይ??

✍ ልጄ አንባቢ እንዲሆን ምን ላድርግ? ሲለው; 📖መጽሐፉ ለእሱ ከማስያዝህ በፊት ቀድመህ አንተ ያዘው። ልጆች የሚያንፀው ምክር ሳይሆን ተግባር ነው!! አለው።

✍ ከዝያ በኋላስ???? ثم ماذا؟؟؟؟؟؟؟؟   በሕይወታችን አንድ ቀን እንኳ ከራሳችን ጋ አውርተን ይህንን ጥያቄ እኛው ለእኛው ጠይቀን እናውቅ ይሆን? "ከዝያ በኋላስ???" "ثم ماذا؟؟؟"       ነብዩ ሙሳﷺ አጀላቸው በደረሰ ጊዜ መለከል መውት ሩሓቸው ከጀሰዳቸው ሊለየው ሲመጣ እንደ ሌሎች ነብያቶች "በመኖርና በመሞት መሃል" አላስመረጣቸውም ነበር። በሰው ተመስሎ ሩሓቸው ሊነጥቃቸው ሰተት ብሎ ገባ። እሳቸውም ያንን ቂብጥይ እንኳ በአንድ ቡጢ መግደል የቻሉ ፈርጣማ እንጂ የዋዛ አልነበሩምና ሩሓቸው ሊወስድ የመጣውን መለክ በሞቀ ጥፊ አጮሉት። የጥፊው ክብደት የታወቀው መለከል መውት ዓይኑን እንደጠፋ ሲነገር ነበር።    የሙሳ ጥፊ ዓይኑን ያጠፋው መለከል መውት ወደ ጌታው በመመለስ «አላህዬ! ሞት ወደ ማይወድ ባሪያህ ልከኸኝ ይኸው ዓይኔን አጥፍቶልኝ ተመለስኩ» አለ።    ልዕለ ሀያሉ አላህ መለከል መውትና ሙሳ መሃል ስለሚከሰተው ነገር ገና መለኩ ወደ ሙሳ ከመላኩ በፊት አስቀድሞ ያውቃል። ይህንን ያደረገበትም ይሁን: ለሌሎች ነብያቶች በሚያስመርጠው መልኩ ለመሳ ሳያስመርጥ መላኩ የላከበት ትልቅ ጥበብና ምክንያት አለው።   አዎ.... ይህንን ክስተት የሰማ ያነበበ ሁሉ ሁል_ጊዜ ከራሱ ጋ "ከዝያ በኋላስ?? ثم ماذا؟؟" እያለ እንዲጠያየቅ አላህ ይፈልጋል። ወደ ክስተቱ ስንመለስ......     መለከል መውት ወደ አላህ ሄዶ ሙሳ በጥፊ ብሎ ዓይኑን እንዳጠፋበት ሲነግረው: ተመልሶ እንዲሄድና ለሙሳ ሌላ አማራጭ እንዲያቀርብለት ነገረው።    «ወደ ሙሳ ተመለስና ዱንያ ላይ መቆየት የሚፈልግ ከሆነ መዳፉን በበሬ ቆዳ ላይ እንዲያሳርፍ ንገረው፤ መዳፉን ባረፈበት ፀጉር ልክ በያንዳንዱ ፀጉር አንድ አንድ ዓመት ይሰጠዋል» አለው። መለከል መውት ይህንን ተልዕኮ ይዞ ወደ ሙሳ በመመለስ ጌታው ያቀረበለትን ነገረው። በዚህ ጊዜ ሙሳ «ثم ماذا يا عب?ÂŤ «ጌታዬ ሆይ ከዝያ በኋላስ?Âť አለ።   "እጄን ከበሬ ቆዳ ላይ አሳርፌ በነካሁት የፀጉር ብዛት ልክ የሆኑ ዓመታቶች ተጨምረውልኝ ከኖርኩ በኋላስ ምንድን ነው የሚጠብቀኝ??" ማለቱ ነው።    ጌታው ሲመልስለት «ثم الموت» «ከዝያማ ሞት ነው» አለው። ሙሳ «فالآن» «እንግዲያውስ አሁኑኑ ይሁንልኝ» አለ።    ሰው ነንና ብዙ እናስባለን: ብዙ እናቅዳለን። ያላገባው ስለወደፊት ትዳሩ፤ ያገባው ስለልጆቹ አስተዳደግና አያያዝ፤ የሚማረው ሾለ ቀጣይ ሕይወቱ፤ ነጋዴው ቀጣይ ስለሚሰራው ቤትና ስለሚነዳው መኪና......፤ በጣም ብዙ ብዙ ነገሮች እናስባለን። ሀሳባችን ሲጎለብት ዕቅድ አውጥተን ጉዞ እንጀምራለን። ግና....... "ከዝያ በኋላስ???  የሚለው ጥያቄ ለምን እንረሳዋለን።   ዕቅድህ ሙሉ ባይሆን እንኳ በከፊል ተሳካ እንበል; ደረስክ... አገባህ... ወለድክ... ዳርክ... ቤት ሰራህ... መኪና ገዛህ... ምናምን... ምናምን;     ከዝያ በኋላ የሚጠብቅህ ምንድን ነው?????? ዕቅድህ ላይ ሞት ጨምርበት!!

خطبة الجمعة للشيخ حسين آل الشيخ 26 ذو الحجة 1447هـ https://youtu.be/I8DuBgrsmUA

خطبة الجمعة للشيخ فيصل غزاوي 26 ذو الحجة 1447هـ https://youtu.be/0NKy0jjPhg8

✍ መንግስት ለታርጋ ቅያሪ ያወጣው የዋጋ ተመን ስሰማ "መንግስት ጤና የለውም እንዴ?" ብዬ አብዮት ላስነሳ አስቤ ነበር፤ በኋላ ግን ባለ መኪናዎቹ ምንም ሳይመስላቸው እየከፈሉ: ተቃውሞ የምናሰማው ታ
✍ መንግስት ለታርጋ ቅያሪ ያወጣው የዋጋ ተመን ስሰማ "መንግስት ጤና የለውም እንዴ?" ብዬ አብዮት ላስነሳ አስቤ ነበር፤    በኋላ ግን ባለ መኪናዎቹ ምንም ሳይመስላቸው እየከፈሉ: ተቃውሞ የምናሰማው ታክሲ ውስጥ በትርፍ የተቀመጥነው መሆናችን ስመለከት ነው እዚህ ሀገር ጤና ያለው ህዝብም ይሁን መንግስት እንደሌለ የተገለጠልኝ!!

✍      «ከቀናቶቻችሁ በላጩ ቀን የጁሙዐ ቀን ነው፤    በእሱ ኣደም ተፈጥሮበታል, በዚሁ ቀን ሞቷል፤   በዚሁ ቀን ጥሩንባ ይነፋል, በዚሁ ቀን (ለቂያማ) ሁሉም ራሱን ስቶ ይወድቃል፤    በዚህ ቀን በእኔ ላይ ሰላት (ሰለዋት) ማውረድን አብዙ የእናንት ሰላት (ሰለዋት) ወደ እኔ ይቀርብልኛል።»           /ረሱልﷺ/

✍ የዕዝነት የፍትህ የሰላም ተምሳሌት፣ ከሰው ልጅ የላቁ የክብር ባልተቤት፤ ዛፉ እንደ ህፃን ያለቀሰላቸው፣ ግመል ስሞታውን የሚያሰማቸው፤ ድንጋይ ሰላምታውን ያቀረበላቸው፣ ስሞትን ሳወሳ ልቤ ይፈወሳል
✍   የዕዝነት የፍትህ  የሰላም ተምሳሌት፣   ከሰው ልጅ የላቁ  የክብር ባልተቤት፤    ዛፉ እንደ ህፃን    ያለቀሰላቸው፣ ግመል ስሞታውን  የሚያሰማቸው፤ ድንጋይ ሰላምታውን  ያቀረበላቸው፣    ስሞትን ሳወሳ   ልቤ ይፈወሳል፤ ሀሳብ ጭንቁ ረስቶ  ሰኪናን ይወርሳል!!   አላህ ይወፍቀኝ  የእርሶን ጉርብትና፤  á‰ á‰°á‹áˆ’ዾ አኑሮ  ይውሰደኝ በሱና። ሸፍዓዎት ያድለኝ         አላህ በዕዝነቱ ከሐውዶም ያጠጣኝ  ያስገባኝ ጀነቱ። ሰላትና ሰላም  ይውረድ በሙሐመድ በተከተላቸው   ሱናቸውን በመውደድ‼️   🌙ﷺ🌙ﷺ🌙ﷺ🌙ﷺ🌙 📖{إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا}   🌙ﷺ🌙ﷺ🌙ﷺ🌙ﷺ🌙  

✍ ጥበብና ዕውቀት ሲያብሩ!!.... ደሓክ ኢብኑ ሙዛሂም የተባለው ጋ የሚመላለስ አንድ ነሷራ ነበር። "ወደ እስልምና ለምን አትገባም?" ብሎ ሲጠይቀው; "ለኸምር ያለኝ ፍቅር ነው ከመስለም የከለከለኝ
✍ ጥበብና ዕውቀት ሲያብሩ!!....   ደሓክ ኢብኑ ሙዛሂም የተባለው ጋ የሚመላለስ አንድ ነሷራ ነበር። "ወደ እስልምና ለምን አትገባም?" ብሎ ሲጠይቀው;    "ለኸምር ያለኝ ፍቅር ነው ከመስለም የከለከለኝ" አለው።   "እሱማ አያሳስብህ: ሰልመህም ትጠጣለህ" አለው።    ነስራኒው ሰለመ። ከሰለመ በኋላ ደሓክ "አሁን ሰልመሃል: ኸምር ከጠጣህ ሓድ እናቆምብሃለን፤ ከተመለስክ ደግሞ በሙርተድ ሑክም እንገድልሃለን!!" አለው።    ሰውየው ግን ከሰለመ በኋላ እስልምናው አምሮለት ሷሊሕ ሰው ሆኖ ኖረ።

✍ በዱንያም ይሁን በአኼራው መንገድ ላይ ክፉ እንቅፋት ማለት፦ አስተካካይ መስለው አጥፊዎች ናቸው!!

✍      ሙሳﷺ በሕይወት ቢኖር; ከሙሐመድﷺ መንሓጅ ሌላ መከተል አይሰፋለትም ነበር።      ዒሳﷺ መጨረሻው ዘመን ላይ ወደ ምድር ሲወርድ; በሙሐመድﷺ መንሓጅ ነው የሚፈርደው። አንድ ሰው ከረሱልﷺ መንሓጅ ውጪ ተከትሎ እንዴት ሊድን ይችላል?? ምክንያቱም፦   ከአላህ ጋ መገናኛ ብቸኛው መንገድ የነብዩ ሙሐመድﷺ መንገድ ነው!!     

👆 ላጤያንስ እያነበባችሁ።
👆 ላጤያንስ እያነበባችሁ።

✍      "ከማን ጋ ነህ?" ስትባል     የምታፍርበት ጓደኛ አትያዝ!!