EB Media
前往频道在 Telegram
👉መዝናኛ 👉ዜና 🗣 Our YouTube Channel https://youtube.com/@ebmedia123?si=3Zgov2sCJcx1Qla4
显示更多1 782
订阅者
-224 小时
+447 天
+28430 天
数据加载中...
吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+69
在0个频道中
六月 '26
+346
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+109
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+202
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+39
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+9
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+31
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+33
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+30
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+88
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+121
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+167
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+79
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+20
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+35
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+83
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+183
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+217
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+341
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+161
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+220
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+197
在0个频道中
Get PRO
九月 '240
在0个频道中
Get PRO
八月 '240
在0个频道中
Get PRO
七月 '240
在0个频道中
Get PRO
六月 '240
在0个频道中
Get PRO
五月 '240
在0个频道中
Get PRO
四月 '240
在0个频道中
Get PRO
三月 '240
在0个频道中
Get PRO
二月 '240
在0个频道中
Get PRO
一月 '240
在0个频道中
Get PRO
十二月 '230
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+1
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+274
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 11 七月 | +1 | |||
| 10 七月 | +2 | |||
| 09 七月 | +4 | |||
| 08 七月 | +6 | |||
| 07 七月 | +3 | |||
| 06 七月 | +47 | |||
| 05 七月 | 0 | |||
| 04 七月 | +2 | |||
| 03 七月 | +1 | |||
| 02 七月 | +2 | |||
| 01 七月 | +1 |
频道帖子
ህዝቤ ሆይ! እስኪ ቆም ብለን እናስተውል።
ሰሞኑን በቲክቶክ መንደር የምንሰማው የእናትና የልጅ ታሪክ ልብ ሰባሪ ብቻ ሳይሆን፣ በየግል ሁላችንንም መስተዋት ፊት የሚያቆም ትልቅ ማህበራዊ ትምህርት ነው። ታሪኩን በአጭሩ ስናየው፦
.****
በአንድ ወቅት በመረጠችው ትዳር ምክንያት ከእናቷ ጋር የተጣላች ሴት ልጅ፣ ትዳሯን መርጣ ወደ ወደደችው ወንድ ሄዳለች። በዚህም ምክንያት ከእናቷ ጋር በመካከላቸው ያለው ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ይቋረጣል። በየሚዲያው መሰዳደቡ እና መወራረዱ ግን ቀጥሎ ነበር።
.****
ነገር ግን ጉዳዩ የቤተሰብ ገመና ሆኖ መቅረት ሲገባው፣ የሚዲያ ተጠቃሚዎች ሁሉ እየገቡ ሀሳብ የሚሰጡበት ጎራ ለይተው የሚነታረኩበት እጅግ አስቀያሚ የእናት እና ልጅ ጭቅጭቅ ወደ ሶሻል ሚዲያ አደባባይ ወጣ። መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ አጀንዳ ሆኖ ተባባሰ። እናት እና ልጅም በአደባባይ ተዘላለፉ ተረጋገሙ ፍፁም ጠላት ሆኑ!
.****
ከብዙ መለያየት በኋላ፣ ያቺ እናት "ልጄ ናፈቀችኝ" ብላ በግልፅ አደባባይ ብታለቅስም፣ ልጅቱ ነገሩን በዝምታ አለፈችው። ይባስ ብላ አሁን ማን ያርዘኛል መውለድ ፈራሁ ብላ በአደባባይ እናት እንደሌለው ሆና ቪዲዮ ሰራች። እናትም ይሄን ቪዲዮ የሰማች ጊዜ ካለችበት ሀገር መጥታ ኢትዮጵያ ነበረች አሉ። ይሄኔ ድንገት እስትሮክ መትቷት ሆስፒታል ገባች።
.*
አሁን ግን የሚሰማው መርዶ ይረብሻል። ያቺ ልጇን የናፈቀች ምስኪን እናት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች እየተባለ ነው። ልጅቱ እድሜ ልክ የማትፋቀው ፀፀት ታቅፋ ልትኖር ነው! እግዚአብሔር የሚወራውን ውሸት ያደርግላት እንዳልል ነገሩ እውነት ነው። ነገር ግን ከዚህ ታሪክ ጀርባ እኛስ ልንመረምራቸው የሚገቡ እውነታዎች አሉ።
.****
ባሻዪ! እውነቱን እንነጋገር ከተባለ፣ ወንዶችም ሆኑ ሴቶች በወጣትነት (በቲኔጀር) እድሜያቸው ማንንም መስማት አይፈልጉም። በተለይ በዚህ የዕድሜ ክልል ውስጥ ቤተሰብ ትልቁ ጠላት እንደሆነ አድርገው ያስባሉ።
.****
ከዚህም በላይ ደግሞ "አፈቀርኩ" ሲሉ ሙሉ ህሊናቸው ይደፈናል፤ ፍቅር አይናቸውን ያውረዋል። ማስተዋልን አጥተው ማንንም አይሰሙም፤ ይባስ ብሎ የቤተሰብ ገበናቸውን አደባባይ ላይ አውጥተው ሲያሰጡት ምንም አይፈሩም፣ አያፍሩምም።
.****
ነገር ግን ይሄ ጊዜያዊ ስሜትና "እንጠጥ እንጠጥ ዝልል ዝልል" የሚለው የወጣትነት ግልብነት መጨረሻው የት እንደሆነ አያስተውሉትም። በህይወት ውስጥ እንዳታረፍዱ የሚባለው ለዚህ ነው። ማርፈድ ፀፀትን ያወርሳል፤ ፀፀት ደግሞ ከባድ የእግር እሳት የሆነ የእድሜ ልክ ስቃይ ነው!
.****
ሌላው የሚገርመኝና ልብ የሚሰብረው ነገር በዚሁ የሶሻል ሚዲያ መንደር የምናያቸው ሰዎች ባህሪ ነው። በእናትና በልጅ መካከል ገብተው ለእናት አግዘው ልጅቱን የሚሰድቡ፣ ወይም ለልጅቷ አግዘው እናትን የሚያንቋሽሹ ደጋፊዎች ነገር በእጅጉ ይገርማል። እዛጋ ይሰማል? በቤተሰብ መሃል ገብቶ እሳት መጫር ማንን ጠቀመ?
.****
በዚህ መሃል ግን ሞት ቀጠሮ የለውምና መጥቶ እናትን ሲነጥቅ ለልጅቷ ስነልቦና ምን እንደሚፈጠር መገመት አያቅትም።
"ልጅቷ አሁን ምንም ላይሰማት ይችላል። ነገር ግን አሁን እርጉዝ ነች። ነገ ስትወልድ ከወሊድ ጋር የሚመጣው ድብርት ወይም በእንግሊዘኛ Postpartum Stress የእናቷ ድንገተኛ ሞት፣ እና የባሏ በቅርብ እርቀት አለመኖር ተደማምሮ፣ የሚዲያውም ጫጫታ ተጨምሮበት ገና ብዙ የስነ-ልቦና ቀውስ እንደሚፈጠርባት መገመት አይከብድም።"
.****
ማጠቃለያ የእኔ ምክር!
ጎበዝ! በዚህ ዘመን መታወቅ እና ማወቅ የተለያዩ ነገሮች ሆነዋል። በቲክቶክ ላይ መታወቅን እንጂ ነገሮችን አርቆ ማወቅን አጥተናል። በስተመጨረሻ የምንገነዘበው ግን የጊዜን ክፉኛ ማርፈድ ብቻ ነው። እናቶች ሲኖሩ ክብር እንስጣቸው፤ ሚዲያ ላይ ገመናን መዘርገፍ ትርፉ የዕድሜ ልክ ጠባሳ ነው።
ይህ ታሪክ ለሁላችንም ትልቅ ማስጠንቀቂያ ይሁን። በህይወታችሁ እንዳታረፍዱ!
| 2 | 没有文字... | 62 |
| 3 | “ለሻዕቢያ ከምገረድ፣ ለብልጽግና ብንበረከክ እመርጣለሁ”‼️
የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም መጠይቅ፣ ከህወሓት ጋር ተድርጎ ለሻዕቢያ ከመገረድ በብልጽግና አንገት መድፋት ይሻለኛል ብለዋል፡፡ ኬሪያ ከፋና ቲቪ ጋር ባደረጉት ቃለ ትግራይን በበላይ የተቆጣጠሩትን እነ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን የትግራይን ሕዝብ ለሻዕቢያ አሳልፈው በመስጠት ወንጅለዋል፡፡
ኬሪያ የቀድሞ ድርጅታቸው ህወሓት ትግራይን ለማጥፋት ይመኛል ላሉት ሻዕቢያ “ተላላኪ ሆኖ እየተገረደ” ነው ብለዋል፡፡ ህወሓት “የብልጽግና ተንበርካኪ መሆን የለብንም ነው የሚለን” ያሉት ኬሪያ፣ “ለሻዕቢያ ከምገረድ እዚህ ብንበረከክ ነው የምመርጠው” ብለዋል፡፡
አንዳፍታ
💎⬇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
👉 https://t.me/EBMedia123 | 68 |
| 4 | ሰማሃል መለስ ዜናዊ በወቅታዊ የትግራይ ፖለቲካ እና የህወሃት አመራሮች ላይ ትችት ሰነዘረች‼
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ልጅ ሰማሃል መለስ፤ "ላንዳ ሪፖርት" ከተባለ የቪዲዮ ሚዲያ ጋር ባደረገችው የትግርኛ ቃለ-ምልልስ በወቅታዊው የትግራይ ክልል ፖለቲካ እና ከፍተኛ ተጽዕኖ ባላቸው የህወሃት አመራሮች ላይ ያላትን ጠንከር ያለ ትችት ሰንዝራለች።
ሰማሃል በንግግሯ በአሁኑ ሰዓት በትግራይ ክልል ውስጥ ያለውን ፖለቲካ እያሽከረከሩ ነው ያለቻቸውን የተወሰኑ አመራሮች ስም በይፋ ጠቅሳለች።
በዚህም መሰረት አቶ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ)፣ የቀድሞው የብሔራዊ ደህንነት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሰፋ እና አቶ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በአባቷ አቶ መለስ ዜናዊ እና በቤተሰቧ ላይ የቆየ የቂም በቀል ስሜት የነበራቸው ግለሰቦች መሆናቸውን ገልጻለች።
እነዚህ ሶስት አመራሮች በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል መዋቅር ውስጥ ቁልፍ ቦታዎችን እንደያዙ የጠቀሰችው ሰማሃል፤ ከአባቷ ህልፈት በፊትም ቢሆን በአመራርነት በነበሩበት ወቅት በስራቸው ላይ ክፍተቶች ይስተዋሉባቸው እንደነበር እና አባቷ በሚሰጣቸው ግምገማዎች ሳቢያ ከፍተኛ ቅሬታ ያሳድሩ እንደነበር በማብራሪያዋ አካታለች። | 144 |
| 5 | የፓኪስታን አየር መንገድ አቶ ተወልደ ገብረማርያምን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለመሾም ማጨቱ ተሰማ
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዘርፍ ያፈራቸው አንጋፋ መሪዎች በዓለም አቀፍ እና በአህጉራዊ መድረኮች ላይ ያላቸው ተፈላጊነት እና ተፅዕኖ ከመቼውም ጊዜ በላይ እየጎላ መጥቷል። ከቀናት በፊት የወጡ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት፣ የፓኪስታን ብሔራዊ አየር መንገድን ወደ ግል ይዞታነት ያዛወረው አዲሱ ጥምረት የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያምን አየር መንገዱን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት እንዲመሩለት በእጩነት መርጧቸዋል።
በጉዳዩ ላይ ቅርበት ያላቸውን ምንጮች ጠቅሶ ብሉምበርግ እንደዘገበው፣ በኪሳራ ውስጥ የቆየውንና በቅርቡ ወደ ግል ይዞታነት የተሸጋገረውን የፓኪስታን አየር መንገድ ሙሉ በሙሉ ለመረከብ የመጨረሻ ሂደቶችን እያጠናቀቀ የሚገኘው የአሪፍ ሀቢብ ኮንሰርቲየም፣ የአቶ ተወልደ ገብረማርያምን ሹመት በይፋ ለማሳወቅ ዝግጅቱን አጠናቋል።
አቶ ተወልደ የኢትዮጵያ አየር መንገድን በበላይነት በመሩባቸው 11 ዓመታት ውስጥ፣ አየር መንገዱ ከአዲስ አበባ ማዕከል በመነሳት አህጉሪቱን ከዓለም ጋር በማስተሳሰር ወደ አፍሪካ ትልቁና ትርፋማው አየር መንገድነት እንዲያድግ ያደረጉበት ስኬታማ የሥራ ታሪክ፣ ለፓኪስታን አየር መንገድ አዲስ ሕይወት ለመዝራት ለተነሳው አዲሱ ባለቤት ዋነኛ ምርጫ ሊያደርጋቸው ችሏል።
እ.ኤ.አ በ2022 ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት በዩናይትድ ስቴትስ ለሚያደርጉት የሕክምና ክትትል ትኩረት ለመስጠት ሲሉ በቅድሚያ ጡረታ መውጣታቸው የሚነገርላቸው አቶ ተወልደ፣ አሁንም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው የኢንዱስትሪ ተደማጭነት እና ተሰሚነት ከፍተኛ መሆኑን የሚያመለክት እንደሆነ ተጠቁሟል።
የአቶ ተወልደ ወደ ፓኪስታን አየር መንገድ መምራት መነጋገሪያ ከመሆኑ ወራቶች አስቀድሞ ፣ ሌላኛው የኢትዮጵያ አቪዬሽን ቁንጮና አንጋፋ መሪ አቶ ግርማ ዋቄ በተመሳሳይ መልኩ የኡጋንዳን ብሔራዊ አየር መንገድ ለመታደግ በኃላፊነት ላይ መሾማቸው ይታወሳል።
Via capital | 154 |
| 6 | 没有文字... | 136 |
| 7 | የአዲስ አበባ ታክሲዎች ዛሬ
በመደማመጥ፣ በመከባበር እንመካካር!
ሐምሌ 4/2018 ዓ.ም
የሰው ልጅ በተፈጥሮው መደመጥን ይሻል። ሰው ሲደመጥ የሚፈጠርበት ደስታ በሀገር ደረጃ ደግሞ ትርጉሙ የላቀ ነው። የሚደማመጡ ዜጎች ሀገራቸውን እፎይ ያሰኛሉ። በአንጻሩ የመደማመጥ ባሕል ከተሸረሸረ ጭቅጭቅ ይነግሳል።
ሀገራዊ ምክክር ልብ ለልብ የመደማመጥ ተግባር ነው። የተለያዩ አመለካከቶች በአንድ ጠረጴዛ ላይ ቀርበው ሲመጋገቡ የጋራ መፍትሔን ያፈልቃሉ። ዜጎች ስለሀገራቸው ያላቸውን አመለካከት፣ ተስፋና ስጋት ያለገደብ ሲገልጹ የሀገር ባለቤትነት ስሜታቸው ይዳብራል። በመደማመጥ መርሕ የሚከናወን ምክክር የአመለካከት ስብጥሩ ከፍተኛ ስለሚኾን ያለጥርጥር በማኅበረሰቡ ዘንድ ቅቡልነት ያለው መፍትሔን ያመነጫል። እርስ በእርስ ተደማምጠው የሚመካከሩ ዜጎች፤ ከመተዋወቅ የተሸመነ የአብሮነት ስሜትን ይቀዳጃሉ። የመደማመጥ የመጨረሻ ውጤቱ ደግሞ መከባበር ነው።
መከባበር ከጥልቅ መደማመጥ የሚፈጠር ሀገራዊ እሴት ነው። ለመከባበር በአመለካከት አንድ አይነት መኾን ግዴታ አይደለም። አንዱ ኢትዮጵያዊ የሌላዋን ኢትዮጵያዊት የተለየ አመለካከት ሲያዳምጥ፤ እርሷም በተራዋ ስታደምጠው አንድ ላይ ተቀምጦ በመወያየት የሚፈጠር መከባበር በእያንዳንዳቸው ልቡና ውስጥ ቦታ ይይዛል። የተለየ አመለካከትን ለማዳመጥ ልብን መክፈት በተመካካሪዎች ዘንድ የአክብሮት መንፈስን ያሰፍናል።
ተደማምጠው የሚከባበሩ ዜጎች በጊዜ ሂደት መተማመንን እንደሚፈጥሩ እሙን ነው። መተማመን አንዱ የሌላዋን ሀሳብ ያምንበታል ማለት አይደለም። ተደማምጦ በመከባበር ሂደት የአንድ ሀገር ልጅነት መቀራረብ ሲፈጠር፤ ጥርጣሬ ተሽሮ ወገናዊ የመተማመን እርሾ ይጠነሰሳል። እርስ በእርስ የሚተማመን ማኅበረሰብ ደግሞ ወደ ሀገራዊ መግባባት ይሸጋገራል።
ተደማምጠን እንመካከር፤ ተማምነን እንግባባ!
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
💎⬇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
👉 https://t.me/EBMedia123 | 139 |
| 8 | 没有文字... | 138 |
| 9 | " የሰሜኑ ጦርነት ኢትዮጵያን ለIMF ቅድመ ሁኔታዎች እንድትገዛ አስገድዷታል"ማሞ ምህረቱ
የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ «ቮክስዴቭ» ከተባለ የውጭ የበይነ መረብ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ውይይት፣ የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱን ገለጹ።
ቀደም ሲል በብድር ላይ የተመሠረተው የዕድገት ጉዞ ገደብ ላይ ደርሶ እንደነበር የጠቆሙት የቀድሞው ገዢ፣ ጦርነቱ አገሪቱን አማራጭ ወደሌለው ቀውስ ውስጥ በመክተት ለዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ቅድመ ሁኔታዎች እንድትገዛ አስገድዷታል ብለዋል።
አገሪቱ በከፍተኛ ጫና ውስጥ ሆና የብርን ዋጋ በገበያ እንዲወሰን (floating) ማድረግን ጨምሮ በIMF የሚመሩ የለውጥ እርምጃዎችን ለመተግበር መገደዷ ያስከተለውን ተጽዕኖ በማንሳትም ጥልቅ ፀፀት መፈጠሩን ጠቁመዋል።
ውሳኔው በሀገር ውስጥ የታቀዱ ማሻሻያዎችን መሠረት ያደረገ ቢሆንም፣ የጦርነቱ መዘዝ ግን አገሪቱ ለውጭ የገንዘብ ተቋማት እጅ እንድትሰጥ ማድረጉን አስገንዝበዋል።
💎⬇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
👉 https://t.me/EBMedia123 | 217 |
| 10 | ዳኛ ዑመር በጅግጅጋ ከተማ በታላቅ እና ደማቅ አቀባበል ተቀብለዋል።
በአቀባበሉ ላይ የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት፣ ከንቲባው፣ የወጣቶች ሚኒስትር፣ የባምቤዳ ኃይል፣ የባህልና የሙዚቃ ቡድኖች እንዲሁም የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
⚽️⚽️⚽️
📷Ahmed Shafi ከስፍራው | 193 |
| 11 | ታዋቂው ገጣሚ ይልማ ገብረአብ "ይረገም ይህ አይኔ" እና ለመስፍን አበበ የሰጠውን "እርግብ" የተሰኙትን ድንቅ ዘፈኖች እንዲፅፍ ያደረገውን እውነተኛ እና ልብ የሚነካ የህይወት ታሪክ ያውቁ ኖሯል? 👇 ሙሉ ታሪኩን በቪዲዮው ይመልከቱ፦
➡️ https://youtu.be/0cj6veZ5kqE?si=I5riZLhXUYsWJUmI | 178 |
| 12 | አዲስአበባ ዩኒቨርስቲ በጀት መድቦ የትግራይ ክልል ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው እንዲቆዩ አደረገ 🔥
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ ከትግራይ ክልል የመጡ ተማሪዎች፣ በክልሉ አለ ባሉት " አስገዳጅ የውትድርና ምልመላ " እና የጸጥታ ስጋት ምክንያት ወደ ቤተሰቦቻቸው መመለስ እንደማይችሉ ገልጸው፤ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር የክረምት ማደሪያ (ዶርሚተሪ) እንዲፈቅድላቸው ጥሪ አቅርበው ነበር።
ተማሪዎቹ ወደ ክልሉ መመለሳቸው ከአካላዊ ደህንነት ስጋት ባለፈ፣ የጀመሩትን የከፍተኛ ትምህርት ጉዞ ሙሉ በሙሉ ሊያቋርጥባቸው እንደሚችልም ስጋታቸውን ገልጸውም ነበር።
በአሁኑ ወቅት ተማሪዎች በግቢው ውስጥ ክረምቱን እንዲያሳልፉ የተፈቀደላቸው መሆኑን ተማሪዎች ተናግረዋል።የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኮምዩኔኬሽን ዳይሬክተር ኤልያስ ወርቁ (ዶ/ር) ይህንኑ አረጋግጠዋል።
ዳይሬክተሩ " አስፈላጊው በጀት እንዲመጣ ተደርጎ ተማሪዎቹ በግቢው እንዲቆዩ ተደርጓል" ነው ያሉት።የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄይሉ ኡመር (ዶ/ር) ተማሪዎቹ በግቢው ያሉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
💎⬇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
👉 https://t.me/EBMedia123 | 208 |
| 13 | በአከራዮች ላይ ጠንካራ ቅጣት ተደነገገ‼
በአዲስ አበባ ከተማ የቤት ኪራይ ውል ያላደሱ እና የተቀመጠውን የዋጋ ጣሪያ ያላከበሩ አከራዮች ላይ የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣል ተደነገገ።
📌የቤት ኪራይ ውል ሳያድሱ እስከ ሁለት ወር የቆዩ አከራዮች የአንድ ወር ሙሉ ኪራይ እንዲቀጡ ይደረጋል።
📌ከሦስት ወር በላይ ውሉን ሳያድሱ የቆዩ ደግሞ የሁለት ወር የኪራይ ክፍያ ያህል ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
በተጨማሪም አዲስ ተከራይ አጋብተው ያላስመዘገቡ አከራዮች የአንድ ወር ኪራይ የሚቀጡ ሲሆን፣
📌 ድርጊቱ በጥቆማ ወይም በክትትል ከተደረሰበት ግን ቅጣቱ እስከ ሦስት ወር የኪራይ ዋጋ ሊደርስ እንደሚችል ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሕጉ አከራዮች ውል የማደስና የማሳወቅ ግዴታ እንዳለባቸው በግልጽ ይደነግጋል ብሏል።
💎⬇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
👉 https://t.me/EBMedia123 | 197 |
| 14 | በሉ ደህና እደሩ🤔
🏆ይህን የፈረንሳይ ቡድን የሆነ ልዩ ሀይል ካልመጣ በስተቀር አያቆመውም 🔥🔥🔥🔥
#FIFAWorldCup | 195 |
| 15 | 🚨 ሁለተኛ ጎል! ፈረንሳይ 2-0 ሞሮኮ
🇫🇷 ፈረንሳይ በ67ኛው ደቂቃ በኡስማን ዴምቤሌ ጎል መሪነቷን ወደ 2-0 አስፍታለች። ጎሉን ያመቻቸው ደግሞ ኪሊያን ምባፔ ነው። ⚽ | 182 |
| 16 | 🚨 "ሿሿ" ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች ተያዙ!
በአዲስ አበባ የትራንስፖርት ተሳፋሪ በመምሰል በተለምዶ "ሿሿ" ተብሎ የሚጠራውን የስርቆት ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ተይዘዋል።
ተጠርጣሪዎቹ የአንዲትን ተሳፋሪ ትኩረት በማሳጣት 32 ሺህ ብር የሚገመት ሳምሰንግ ስልክ ሰርቀው ነበር። በፖሊስ በተደረገ ፍተሻም በተሽከርካሪው ውስጥ 7 የተለያዩ ስልኮች ተገኝተዋል።
ፖሊስ ሕብረተሰቡ የሕዝብ ማመላለሻ ሲጠቀም ከእንዲህ ዓይነት ማጭበርበር ለመጠበቅ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።
ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ (አዲስ ፖሊስ) | 193 |
| 17 | 🚨 እረፍት! ፈረንሳይ 0-0 ሞሮኮ
ፈረንሳይ በመጀመሪያው 45 ደቂቃ በኳስ ቁጥጥርና በጥቃት የበላይነት ብታሳይም፣ የሞሮኮው ግብ ጠባቂ ያሲን ቦኖ የፈረንሳይን ፔናልቲ ጨምሮ ወሳኝ ኳሶችን በማዳን ጨዋታውን 0-0 አድርጎ ወደ እረፍት አስገብቷል።
🔥 ሁለተኛው አጋማሽ ምን ያመጣል? ግምታችሁን በአስተያየት አጋሩ! 👇⚽ | 202 |
| 18 | 🚨 ቦኖ የፈረንሳይን ፔናልቲ አዳነ!
በ2026 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል በተካሄደው ጨዋታ፣ የሞሮኮው ግብ ጠባቂ ያሲን ቦኖ (Yassine Bounou) ለፈረንሳይ የተሰጠውን ፔናልቲ በጀግንነት በማዳን ቡድኑን ከጎል አድኗል። ይህ ወሳኝ ማዳን ጨዋታውን እጅግ አስደሳች እና ተወዳዳሪ አድርጎታል። � | 178 |
| 19 | 没有文字... | 191 |
| 20 | 🎭 ይህ ታዋቂ አርቲስት ማነው? 🤔 | 208 |
