uk
Feedback
EB Media

EB Media

Відкрити в Telegram

👉መዝናኛ 👉ዜና 🗣 Our YouTube Channel https://youtube.com/@ebmedia123?si=3Zgov2sCJcx1Qla4

Показати більше
1 784
Підписники
-224 години
-107 днів
+28930 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
липень '26
липень '26
+108
в 0 каналах
червень '26
+346
в 0 каналах
Get PRO
травень '26
+109
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+202
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+39
в 0 каналах
Get PRO
лютий '26
+9
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+31
в 0 каналах
Get PRO
грудень '25
+33
в 0 каналах
Get PRO
листопад '25
+30
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '25
+88
в 0 каналах
Get PRO
вересень '25
+121
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+167
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+79
в 0 каналах
Get PRO
червень '25
+20
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+35
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+83
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+183
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+217
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+341
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+161
в 0 каналах
Get PRO
листопад '24
+220
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+197
в 0 каналах
Get PRO
вересень '240
в 0 каналах
Get PRO
серпень '240
в 0 каналах
Get PRO
липень '240
в 0 каналах
Get PRO
червень '240
в 0 каналах
Get PRO
травень '240
в 0 каналах
Get PRO
квітень '240
в 0 каналах
Get PRO
березень '240
в 0 каналах
Get PRO
лютий '240
в 0 каналах
Get PRO
січень '240
в 0 каналах
Get PRO
грудень '230
в 0 каналах
Get PRO
листопад '23
+1
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '23
+274
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
22 липня+3
21 липня0
20 липня+2
19 липня+2
18 липня+1
17 липня+5
16 липня+1
15 липня+3
14 липня+6
13 липня+13
12 липня0
11 липня+4
10 липня+2
09 липня+4
08 липня+6
07 липня+3
06 липня+47
05 липня0
04 липня+2
03 липня+1
02 липня+2
01 липня+1
Дописи каналу
ጦርነት የመቀስቀስ እድሉ እየሰፋ ነው‼️ ፓርቲው ለ ጠ/ሚንስተር ዶ/ር አብይ አሕመድ ደብዳቤ ላከ‼️ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ በደብዳቤው 'ከፍተኛ መስዋዕትነት የተከፈለበትና የብዙዎችን ህይወት የቀጠፈው ያለፈው አስካፊ ጦርነት ካስከተለው መጠነ-ሰፊ ውድመትና ሰብአዊ ቀውስ ገና ሳያገግም፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ መንግስትና በህወሓት እንዲሁም የውጭ ሀይሎች የሚሳተፉበት ተብሎ በሚገመተው አዲስ የጦርነት ደመና እያንዣበበ መምጣቱና ጫፍ መንካቱ እጅግ አሳሳቢና አደገኛ ሁኔታ ላይ ደርሷል ብሏል'። ጦርነት ትርፉ ጥፋት፣ እልቂትና የኢኮኖሚ ውድመት ብቻ መሆኑ በተደጋጋሚ የታየ እውነታ ሲሆን አሁን ሊቀሰቀስ የሚችል ማንኛውም ጦርነት ውጤቱ የማይገመት፣ የጦርነቱ ባህሪም እጅግ አደገኛ፣ የአካባቢውና የዓለም ኃያላን መንግስታት አዳዲስ የጦር መሳሪያዎቻቸውን በሁሉም ተዋጊ ሃይሎች የሚፈትኑበት የውክልና ጦርነት በመሆኑ በጣም አደገኛ ያደርገዋል። ይህ ደግሞ በትግራይ ህዝብ ብቻ ሳይሆን የሀገሪቱን ህልውና እንዲሁም ምስራቅ ኣፍሪካ ሙሉ በሙሉ ወደለየለት ጥፋት የሚያመራ ነው። በተለይም ሀገሪቱና የትግራይ ህዝብ በከፍተኛ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ቀውስ ውስጥ ባሉበት በዚህ ደካማ ወቅት ውስጥ መገኘታችን አደጋውን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ጦርነትን ለማስቀረትና ሰላምን እንዲረጋገጥ ከተፈለገ፣ የትግራይ ህዝብ እውነተኛና ህዝባዊ የሆኑትን ሰብኣዊ ፣ ሕገ መንግስታዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎች ከተለያዩ አካላት ጋራ በማያያዝ ማጓተትና አለመመለስ በአስቸኳይ አስቁሞ የትግራይ ህገ-መንግስታዊ ግዛትና ከጦርነቱ ብኃላ የተተከሉ ህገወጥ መዋቅር በአስቸኳይ አፍርሶ ሕግ እንዲከበርና ወደ ነበረበት እንዲመለስ ማድረግ ፣ በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉና የተሰደዱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆችን ያለምንም መስተጓጎልና ስጋት ሰብአዊ መብቶቻቸዉ ተጠብቆ ወደ ቀድሞ ቀያቸው በአስቸኳይ መመለስና በዘላቂነት ማቋቋም ፣ ቀጥታ ለትግራይ ህዝብ የዕለት ተዕለት ኑሮ ወሳኝ የሆኑትን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረታዊ አገልግሎቶችን (ፍትሃዊ የባጀት ክፍፍልን ጨምሮ) ያለምንም ቅድመ ሁኔታና ገደብ ሙሉ በሙሉ ስራ ላይ እንዲውሉ ማድረግ ሲገባ እነዚህን እውነተኛ የህዝብ ጥያቄዎች ከተለያዩ የፖለቲካ ጥቅሞችና አካላት በተለይ ከህወሓት ጋር በማያያዝ (በማሽመድመድ) አለመመለስ፣ ለሌላ ጦርነት መቀስቀስ ትልቁን ምክንያት እየፈጠረ መሆኑን ታውቆ፣ መንግስት ከጦርነት አማራጭ ወጥቶ በሰላማዊ መንገድና በውይይት ለችግሮቹ እውነተኛ ምላሽ እንዲሰጥ የፀና የስላም ጥሪያችንን እናቀርባለን። ሳልሳይ ወያነ ትግራይ የጦርነትን አማራጭች በመተው በሰላማዊና በሰለጠነ መንገድ መፈታት አለበት ሲል በፌደራል መንግስት የተነፈጉ የትግራይ ህዝብ እውነተኛና ህዝባዊ የሆኑትን ሰብኣዊ ፣ ሕገ መንግስታዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎች እንዲሁም በህወሓት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ለጦርነት ከበቂ በላይ ምክንያት ስላልሆኑ ሳይሆን የትግራይ ህዝብም ሆነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ዳግም ወደ እልቂትና ውድመት የሚወስደውን የጦርነት መንገድ  አይቀበለውም ብቻ ሳይሆን የጦርነት አስቃቂ ዋጋ ተጨማሪ መክፈል የለበትም በማለት ፤ ይህ መንግስት የታሪክና የህግ ተጠያቂነትን በማሰብ ፣ በቀጥታም ሆነ በእጀዙር የጦርነት ነጋሪት መምታቱን በአስቸኳይ አቁሞ፣ የትግራይ ህዝብ ጥያቄዎችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በመመለስ ለሰላም ያለው ዝግጅነት ቅድሚያ እንዲሰጥ “የጦርነትን ቅስቀሳ ይቁም የሰላም ውይይቶችን አሁኑን ይጀመሩ” ሲል አሳስቧል።

2
Немає тексту...
124
3
🚨 ሰበር ዜና ንብረትነቱ የዮሴፍ ገብሬ (ጆሲ) የሆነው JFM 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለ6 ወራት ከስርጭት ታግዷል። ባለሥልጣኑ እንዳስታወቀው፣ ጣቢያው የብሮድካ+1
🚨 ሰበር ዜና ንብረትነቱ የዮሴፍ ገብሬ (ጆሲ) የሆነው JFM 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለ6 ወራት ከስርጭት ታግዷል። ባለሥልጣኑ እንዳስታወቀው፣ ጣቢያው የብሮድካስት አዋጅና የፈቃድ ውል ግዴታዎችን ባለማክበሩ እና ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎች ቢሰጡትም መሻሻል ባለማሳየቱ እርምጃው መወሰዱን ገልጿል። 📌 እግዱ በሚቆይበት ጊዜ 106.7 ፍሪኩዌንሲውን መጠቀምም አይፈቀድለትም። #Ethiopia #JFM1067 #ሬዲዮ #ሰበርዜና
129
4
የዳውድ የላሊበላ ጉዞና የ3 ሺህ ብር ጮርናቄ ጉድ! 🥹💔 አዘርባጃናዊው የጉዞ ዩቲዩበር ዳውድ አኹንድዛዳ ላሊበላን ሲጎበኝ፣ 20 ጮርናቄዎችን ለነዋሪዎች ለመግዛት ወሰነ። ነገር ግን 50 ብር የነበ
የዳውድ የላሊበላ ጉዞና የ3 ሺህ ብር ጮርናቄ ጉድ! 🥹💔 አዘርባጃናዊው የጉዞ ዩቲዩበር ዳውድ አኹንድዛዳ ላሊበላን ሲጎበኝ፣ 20 ጮርናቄዎችን ለነዋሪዎች ለመግዛት ወሰነ። ነገር ግን 50 ብር የነበረው የአንድ ጮርናቄ ዋጋ 150 ብር ተብሎ በ3,000 ብር ገደማ እንዲከፍል ተደረገ። የቁርስ ቤቷ ባለቤት እውነተኛው ዋጋ 50 ብር መሆኑን በመናገር ቢቃወሙም፣ ውዝግብ ላለመፍጠር ዳውድ ገንዘቡን ከፍሎ ወጣ። በኋላም እውነተኛውን ዋጋ በሌላ ቦታ አረጋገጠ። ይህ ክስተት በማህበራዊ ሚዲያ ብዙ ቁጣን ቀስቅሷል። የጥቂቶች ድርጊት የኢትዮጵያን መልካም ስምና የእንግዳ ተቀባይነት እንዳይጎዳ ተገቢ እርምጃ ሊወሰድ ይገባል። 📌 ተጨማሪ ወቅታዊ ዜናዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። 👉 https://t.me/EBMedia123
163
5
ተስፋ ከመቁረጥህ በፊት ይህንን አንብብ * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * በ17 ዓመቷ ከኮሌጅ ተባረረች በ25 ዓመቷ እናቷን በሞት አጣች በ26 ዓመቷ ጽንስ ወረደባት
ተስፋ ከመቁረጥህ በፊት ይህንን አንብብ * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * በ17 ዓመቷ ከኮሌጅ ተባረረች በ25 ዓመቷ እናቷን በሞት አጣች በ26 ዓመቷ ጽንስ ወረደባት በ28 ዓመቷ ትዳሯ ፈረሰ ብዙ ከመጨነቅ የተነሳ የተለያየ በሽታ ተገኘባት በ29 ዓመቷ በእርዳታ ትተዳደር ነበር በ30 ዓመቷ ሞትን ተመኝታ ራሷን ለማጥፋት አሰበች ይሁን እንጂ ሃሳቧን በመተው እራሷን ለመቀየር ወሰነች በ31 ዓመቷ የመጀመሪያ መጽሐፏን አሳተመች በ35 ዓመቷ 4 መጽሐፎችን በማሳተም የአመቱ ምርጥ ደራሲ ተባለች በ42 ዓመቷ በአንድ ቀን ውስጥ 11 ሚሊዮን ኮፒ መጽሐፎቿን ሸጠች ይህቺ ሴት እንግሊዛዊት ደራሲ J.K. Rowling ትባላለች በ30 አመቷ ራሷን ልታጠፋ የነበረችው ሴት የHarry Potter መጽሐፍ ደራሲ ከመጽሐፉ ብቻ በተገኘው ከ15 ቢሊዮን ዶላር በአለም አቀፍ ደረጃ በቱጃሮች ተርታ ተቀምጣለች! ተስፋ አትቁረጥ ፣ ትዕግስት ይኑርህ ፣ በዓላማ ኑር በእግዚአብሔር ታመን፣ ታሸንፋለህ! Never give up❗ባልተተያያዘ መረጃ የፈታት ባሏም አርግዤልሻለው ብሎ ተመልሷል አሉ🤰
239
6
ቢርበንም ዳቦ ስጡኝ የማንላቸው ሰዎች አሉ!💔 #maleda : የቱንም ያህል ቢርበን ዳቦ ስጡኝ የማንላቸው ሰዎች አሉ🙌💔 ያሰላም✌️አስጉ. Via:- አስጌ ደንዴሾ+2
ቢርበንም ዳቦ ስጡኝ የማንላቸው ሰዎች አሉ!💔 #maleda : የቱንም ያህል ቢርበን ዳቦ ስጡኝ የማንላቸው ሰዎች አሉ🙌💔 ያሰላም✌️አስጉ. Via:- አስጌ ደንዴሾ
207
7
የቴዲ አፍሮና የአምለሰት ዳጎስ ያለ ድጋፍ!❤️🙏 በብዙ መልካም እና የበጎ አድራጎት ስራዎቹ የሚታወቀው ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ፣ በቅርቡ በዶንኪ ቲዩብ (Donkey Tube) ላይ ያጋጠሙትን ፈተናዎችና+1
የቴዲ አፍሮና የአምለሰት ዳጎስ ያለ ድጋፍ!❤️🙏 በብዙ መልካም እና የበጎ አድራጎት ስራዎቹ የሚታወቀው ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ፣ በቅርቡ በዶንኪ ቲዩብ (Donkey Tube) ላይ ያጋጠሙትን ፈተናዎችና የፋይናንስ እቅዶችን ተከትሎ ለህዝብ ያቀረበውን የድጋፍ ጥሪ በማንሳት በርካታ አጋሮች ከጎኑ በመቆም ላይ ይገኛሉ። ከነዚህም መካከል ተወዳጁ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) እና ባለቤቱ አርቲስት አምለሰት ሙጨ ቀዳሚዎቹ በመሆን ለኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ድርጅት ዳጎስ ያለ የገንዘብ ስጦታ ማበርከታቸው ተረጋግጧል። አምለሰት ያደረጉት የገንዘብ ድጋፍ የተቋሙን እንቅስቃሴ ለማስቀጠል ትልቅ አቅም የሚፈጥር ሲሆን፣ በተለይም እሸቱ በማህበረሰብ አቀፍ የበጎ አድራጎት ስራዎች እና በ"ድንቅ ልጆች" ፕሮግራሙ የሚያደርጋቸውን በጎ ተፅዕኖዎች ለመደገፍ ታስቦ የተደረገ እንደሆነ ተገልጿል። የሁለቱ ዝነኛ ጥንዶች ቅን ስራቸው የጥበብ ባለሙያዎች በችግርና በፈተና ወቅት እርስ በእርስ መጠያየቅና መረዳዳት እንዳለባቸው ዳግም ያሳየ ትልቅ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል። Via:- Teddy Afro Real Fans page
211
8
🎤 የድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ ጤና ሁኔታ ላይ አዲስ መረጃ! 🙏 በለንደን ያካሄደውን ስኬታማ ኮንሰርት አጠናቆ ሲመለስ፣ በኤርፖርት ውስጥ በመንሸራተቱ በእግሩ ላይ ቀላል ጉዳት ደርሶበታል። በአሁኑ ወቅ+1
🎤 የድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ ጤና ሁኔታ ላይ አዲስ መረጃ! 🙏 በለንደን ያካሄደውን ስኬታማ ኮንሰርት አጠናቆ ሲመለስ፣ በኤርፖርት ውስጥ በመንሸራተቱ በእግሩ ላይ ቀላል ጉዳት ደርሶበታል። በአሁኑ ወቅት በላፍቶ አካባቢ በሚገኝ ክሊኒክ ህክምና እየተከታተለ ሲሆን፣ እንደ ሰይፉ ፋንታሁን ገለጻ ሁኔታው አሳሳቢ ወይም ለህይወቱ አደገኛ አይደለም። ጎሳዬም "ደህና ነኝ፣ አትጨነቁ" በማለት ለአድናቂዎቹ መልዕክት አስተላልፏል። ፈጥኖ ሙሉ በሙሉ እንዲያገግም እንመኝለታለን። ❤️🙏
231
9
“ሐሰተኛ ሪፖርት ማቅረብ ከሌብነት እኩል ያስጠይቃል” ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ2018 በጀት ዓመት የስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ባደረ
“ሐሰተኛ ሪፖርት ማቅረብ ከሌብነት እኩል ያስጠይቃል” ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ2018 በጀት ዓመት የስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ ማቅረብ ከሌብነት ጋር በተመሳሳይ የሚያስጠይቅ መሆኑን አስረግጠው ተናገሩ። ተመሳሳይ በጀትና የሰው ኃይል በተመደበላቸው ተቋማት መካከል ሰፊ የአፈጻጸም ልዩነት መታየቱ የሚያስጠይቅ መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባዋ፤ ወደፊት የሚቀርቡ ሪፖርቶች በሕዝብ ሕይወት ላይ ያመጡትን ለውጥ በግልጽ ማሳየት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በተጨማሪም ከንቲባ አዳነች፦ 📌 የፅዳት ሥራ የነዋሪው የዕለት ተዕለት ባህል ሊሆን እንደሚገባ፣ 📌 የኑሮ ውድነትን የመከላከል፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የቤት ልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ፣ 📌ለመሠረተ ልማቶች ከፍተኛ በጀት መመደቡን ገልጸው፣ ለተመዘገቡት ስኬቶች የሕዝብና የልማት አጋሮች ተሳትፎ የጎላ እንደነበር ጠቁመዋል።
232
10
አጥር አጥረው ለሚያስቀምጡ ተጨማሪ እድል የለም! የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ታጥረው ያለምንም አገልግሎት በተቀመጡ መሬቶች ላይ አስፈላጊውን ማጣራት በማካሄድ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ ጥብቅ
አጥር አጥረው ለሚያስቀምጡ ተጨማሪ እድል የለም! የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ታጥረው ያለምንም አገልግሎት በተቀመጡ መሬቶች ላይ አስፈላጊውን ማጣራት በማካሄድ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ። ከንቲባዋ ይህንን የገለጹት ለተከታታይ ሶስት ቀናት ሲካሄድ በነበረው የከተማ አስተዳደሩ የ5 ዓመታት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ እና የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት ነው። ከንቲባ አዳነች በገለጻቸው፣ አዲስ አበባ መሬት ታጥሮ የሚቀመጥባት ከተማ እንዳትሆን ከዚህ ቀደም መግባባት ላይ ደርሰናል ካሉ በኋላ፣ ይህንን ስምምነት ጥሰው ድጋሚ አጥር አጥረው የሚያስቀምጡ አካላት ምንም ዓይነት ተጨማሪ ዕድል ሊሰጣቸው እንደማይገባ በአፅንዖት ተናግረዋል። የወጡ ሕጎችና ደንቦች መሬት ላይ እንዲተገበሩ በማድረግ፣ የለሙ መሠረተ ልማቶችም በተገቢው ሁኔታ ለተፈለገው ዓላማ እንዲውሉ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በመድረኩ ላይ በከተማዋ የሰላምና ደህንነት ሁኔታ ዙሪያ ማብራሪያ የሰጡት ከንቲባዋ፣ በአዲስ አበባ ምንም ዓይነት የደህንነት ስጋት ሳይፈጠር በርካታ አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ኩነቶች በሰላም መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። ይህ የሕዝብን ሰላም የማስከበር ሥራ ማኅበረሰብ አቀፍ በሆነ መንገድ መከናወኑ ትልቅ ዕድገት የታየበት በመሆኑ፣ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል።
203
11
አቶ ሽመልስ አብዲሳ ትውልደ ኢትዮጲያዊውን ተጨዋች አሊ አህመድ በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ አሊ አህመድ በዓለም ዋንጫው ከካናዳ ብሔራዊ+1
አቶ ሽመልስ አብዲሳ ትውልደ ኢትዮጲያዊውን ተጨዋች አሊ አህመድ በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ አሊ አህመድ በዓለም ዋንጫው ከካናዳ ብሔራዊ ቡድን ጋር ለነበረው ቆይታ የእንኳን ደስ አለህ መልዕክት አስተላልፈዋል። ክቡር አቶ ሽመልስ በንግግራቸው አሊ በእግርኳሱ እያሳየ ባለው ነገር እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ክልል መኩራታቸውን ገልፀዋል። ትውልደ ኢትዮጲያዊው አሊ መሐመድ ለተደረገለት አቀባበል ምስጋናውን አቅርቦ መነሻዬ እዚህ ኢትዮጲያ ነው ያደግኩት በኦሮሞ ባህል ነው ስለዚህ መነሻዬን መርሳት አልችልም በማለት ሀሳቡን ሰጥቷል። እዚህ በመምጣቴ ደስተኛ ነው የሚለው አሊ ከዚህም በላይ የሀገሬን ስም ለማስጠራት ጥረቴን እቀጥላለው ብሏል። የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል ፕሬዝዳንት የተከበሩ አቶ ሽመልስ አብዲሳ አሊ አህመድ ለሁለት ወይ ሶስት ሳምንታት በኢትዮጲያ ቢቆይ እና ታዳጊዎችን ተዘዋውሮ ቢመለከት ደስተኛ እንደሚሆኑ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም አሊ በሀገራችን የእግርኳስ አካዳሚ ለመገንባት እቅድ ካለው አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን ብለዋል። ዘገባው የሀገሬ ቴሌቪዥን ነው።
239
12
💔😭የሰርጉ ደስታ በአንድ ቅጽበት ወደ ድንጋጤ ተቀየረ!😭😭 "በፍቅር የተጀመረ ታሪክ... በድንጋጤ ተጠናቀቀ! ለብዙ ዓመታት በፍቅር የቆዩ ጥንዶች የሰርግ ቀናቸውን በደስታ ሲጠባበቁ ነበር። ቤተ
💔😭የሰርጉ ደስታ በአንድ ቅጽበት ወደ ድንጋጤ ተቀየረ!😭😭 "በፍቅር የተጀመረ ታሪክ... በድንጋጤ ተጠናቀቀ! ለብዙ ዓመታት በፍቅር የቆዩ ጥንዶች የሰርግ ቀናቸውን በደስታ ሲጠባበቁ ነበር። ቤተሰቦች፣ ጓደኞችና እንግዶች በዓሉን ለማክበር ተሰብስበው ነበር። ነገር ግን ማንም ያልጠበቀው ነገር ሊከሰት ነበር። እንደሚነገረው፣ ሙሽራው ከሰርጉ በፊት ሙሽሪቱ ከሌላ ሰው ጋር ያላትን ግንኙነት የሚያሳይ ቪዲዮ ደርሶት ነበር። ሆኖም ነገሩን ለማንም ሳይናገር የሰርጉን ቀን ጠበቀ። በሥነ-ሥርዓቱ መካከል "ለሙሽሪቴ ልዩ ስጦታ አለኝ" ብሎ ወደ መድረኩ ወጣ። እንግዶቹ የፍቅር ፎቶዎችና ትዝታዎች ይታያሉ ብለው ሲጠብቁ፣ በስክሪኑ ላይ ያልተጠበቀ ቪዲዮ መታየት ጀመረ። አዳራሹ በድንጋጤ ተዋጠ። አንዳንዶች ዝም አሉ፣ ሌሎች በመደንገጥ ተመለከቱ። ከዚያም ሙሽራው ሰርጉን ማቋረጡን በማስታወቅ ከአዳራሹ ወጣ። ይሁን እንጂ፣ ይህ ታሪክ በሶሻል ሚዲያ በስፋት ቢሰራጭም፣ በእውነት የተከሰተ ስለመሆኑ የተረጋገጠ መረጃ አልተገኘለትም። ስለዚህ እንደ ያልተረጋገጠ ወሬ መመልከቱ ተገቢ ነው። እርስዎ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ያስባሉ? እውነት ቢሆን ኖሮ እንዲህ ዓይነት እርምጃ ተገቢ ነበር ወይስ ጉዳዩ በግል መፍታት ይሻል ነበር? ምስል ፣_Ai 📌 ተጨማሪ ወቅታዊ ዜናዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። 👉 https://t.me/EBMedia123
245
13
🙏 ወገኖቼ ታምሜ አለሁ፤ ፀልዩልኝ! ተወዳጁ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ኮከብ ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ፣ በለንደን ያደረገውን የሙዚቃ ኮንሰርት በተሳካ ሁኔታ ካጠናቀቀ በኋላ በድንገተኛ የጤና እክል ምክንያት ወደ+1
🙏 ወገኖቼ ታምሜ አለሁ፤ ፀልዩልኝ! ተወዳጁ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ኮከብ ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ፣ በለንደን ያደረገውን የሙዚቃ ኮንሰርት በተሳካ ሁኔታ ካጠናቀቀ በኋላ በድንገተኛ የጤና እክል ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን አስታውቋል። ድምጻዊው በማህበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ በዊልቸር ላይ ተቀምጦ የሚያሳይ ፎቶ በማጋራት፣ "ታምሜ ገባሁ፤ ስለሁሉ ግን እግዚአብሔር ይመስገን!!" ሲል መልእክት አስተላልፏል። 👉 https://t.me/EBMedia123 እስካሁን ድረስ የገጠመው የጤና እክል ምን እንደሆነ በይፋ የተገለጸ መረጃ የለም። ከዚህ በኋላም በርካታ አድናቂዎቹ፣ የሙዚቃ አፍቃሪዎች እና የጥበብ ባልደረቦቹ ፈጣን ማገገም እንዲያገኝ ምኞታቸውንና ጸሎታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ፈጣን ማገገም እንመኝለታለን። 🙏❤️ 📌 ተጨማሪ ወቅታዊ ዜናዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። 👉 https://t.me/EBMedia123
248
14
ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፌዬ ፈጣሪ ይማርህ!!
ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፌዬ ፈጣሪ ይማርህ!!
252
15
የነበራችሁ ( በተለይ ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጳጳሳት ፣ መነኮሳትና ካህናት ውጡና መስክሩ ። ዝም ማለት ያለማስረጃ የቀረበበትን ክስ መደገፍ ነው ። ስለ እውነት ስትሰብኩን እንደኖራችሁ ኑና ስለ እውነት መስክሩ ። ኢትዮጵያውያንም አንድ " እሸቱ መለሰ " የተባለ ትልቅ ተቋም እንዳይፈርስ ተባበሩ ። ` https://www.facebook.com/100000937441229/posts/7956389931068843/?app=fbl https://vt.tiktok.com/ZSXC95UwC/
245
16
📝 በቴዎድሮስ ተክለአረጋይ የተጻፈ መግቢያ፦ የኮሜዲያን እሸቱ መለሰን የዶንኪ ቲዩብ የፋይናንስ ችግርና 31 ሰራተኞችን ሊያሰናብት መቻሉን ተከትሎ፣ ጋዜጠኛ እና ደራሲ ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ ሰፊ አስተያየት አቅርበዋል። ጽሑፉ እሸቱ ለማህበረሰብ ያበረከተውን አስተዋፅኦ በማስታወስ፣ 31 ሰራተኞች ሥራቸውን እንዳያጡ እንዲተባበሩ ጥሪ ያቀርባል። " #እሸቱ_መለሰ " የተባለ አንድ ትልቅ ተቋም እንዳይፈርስ ። 👉 " ላሰናብታቸው ነው " ያላቸው 31 ሰራተኞች ያሉት ማን ነው ? ` ሰሞኑን የኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ዶንኪ ቲዩብ በበጀት እጥረት የሰራተኛ መቀነስ ፣ በዚያም ካልበቃ የመዘጋት አደጋ እንደገጠመው ሲገልጽ የተለያዩ ሙቅና ቀዝቃዛ ስሜቶች ተፈጥረዋል ። በዋንኛነት ከተለያዩ ገዳማትና የረድዔት ድርጅቶች ጋር ሲሰራ ስለተቀበለው ኮምሽን እዚህም እዚያም እርግጠኛ እየተሆነ ተነስቷል ። ይህ ጉዳይ የተነሳው ዛሬ አይደለም ። ቆየት ካለ ጊዜ ጀምሮ ተደጋግሞ ተነስቷል ። ይህ ሲደጋገምበትም ይመስላል የተሰራባቸውን ቦታዎች በስም እየጠራ " ለአሜሪካው ገዳም 6.1 ሚሊዮን ዶላር ( ከ950 ሚሊዮን ብር በላይ ) ፣ ለሰቆጣ 10 ሚሊዮን ብር ፣ 31 በሬ እና 1 መኪና ሙሉ ልብስ ፣ ቦረና 8 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ እህል " ሲያበረክት ኮምሽን እንዳልተቀበለ ጠቅሶ ሜቄዶኒያን ጨምሮ አብሯቸው የሰራባቸው ተቋማት ሁሉ ኮምሽን መቀበል አለመቀበሉን ጠቅሰው ቪዲዮ እንዲሰሩለት ጠይቋል ። በርካታ አቅመ ደካማ እናቶች ከዕለት ጉርስ ማጣት ተነስተው ዶንኪ ቲዩብ ላይ ቀርበው ቤት እስከመግዛት የደረሱ ሁሉ ባመቻቸው መንገድ ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ ተማጽኗል ። እኔ አንዱን የቅርብ እማኝ የሆንኩበትን ምስክርነት ላንሳ ። የ " ሰው ለሰው " እና " ዘመን " ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች ደራሲ ጸሐፊ ተውኔት መስፍን ጌታቸውን ኮቪድ 19 ሲነጥቀን እናቱ ወ/ሮ ሎሚናት ወ/መስቀል የሚገቡበት ቤት ፣ የሚበሉ የሚጠጡበት አልነበራቸውም ። ሌቱ ብቻ ሳይሆን ቀኑም ነበረ የጨለመባቸው ። መስፍኔ መከታቸው ልጃቸው ነበረ ፤ እግዚአብሔር አልፈቀደም ። ሎሚናት በአንዲት ቅጽበት ጥቂት በጎ አድራጊዎች እጅ ላይ ነው የወደቁት ። በዓል መዋያ ይሆናቸው ዘንድ ጥቂት ላግዛቸው ቤታቸው ( ለመጀመሪያ ጊዜ ) ሄጄ በዚያው ሌሎች እንዲያግዟቸው ፌስቡክ ገጼ ላይ ለጠፍኩ ። ብዙዎች የቻሉትን አገዟቸውና ተስፋቸው አንሰራራ ። በወቅቱ ለነበርን የተሻለ እንዲታገዙ ፣ የሚጠጉበት ደሳሳ ጎጆ እንዲያገኙ ፊትለፊት የመጣልን እሸቱ መለሰ ነበረ ። ምክንያቱም እሸቱ በአምላክ እገዛ ብዙ የጨለመ የምስኪኖች ተስፋን አብርቷል ። ወ/ሮ ሎሚናት ዶንኪ ቲዩብ ላይ ቀረቡ ። እሸቱ መለሰ የምስኪኖች ታሪክ በዶንኪ ቲዩብ ቀርቦ የሚሰበሰበው ገንዘብ ወደ እሱ ኪስ እንዳይገባና ሀሜት እንዳያስነሳ የበዛ ጥንቃቄ ያደርጋል ። ተረጂው አዲስና 0 ብር የሆነ የዳሽን ባንክ የሂሳብ ደብተር እንዲያወጣ ይደረጋል ። ከዚያ ብሩ ለታቀደለት ዓላማ ሳይውል ተረጂው አውጥቶ እንዳይጠቀምበት ከዶንኪ ቲዩብ ጋር ውለታ ይፈራረማል ። እሸቱ በራሱ ወጪ በወ/ሮ ሎሚናት ሕይወት ዙሪያ ጊዜ የወሰደ ዶኩመንታሪ ሰርቶ ለቀቀ ። ከብር 400,000.00 ( አራት መቶ ሺህ ) በላይ ተሰበሰበ ። በወቅቱ ከተማ መስተዳድሩ በዓልን አስታኮ አቅም ላነሳቸው አርቲስቶች የቤት ስጦታ ያደርግ ስለነበረ የወ/ሮ ሎሚናት ጉዳይ ዶንኪ ቲዩብ ላይ በመቅረቡ ሎሚናትም በክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ መሐል ከተማ ላይ ባለሁለት መኝታ ቤት ፣ አልጋ ፣ ሶፋ እና ቴሌቪዥን ጭምር ተበረከተላቸው ። እሸቱ መለሰ " ስቱዲዮም ቢሆን ቤት እንገዛልሻለን እንጂ እኛ ቤት እያደርን አንቺ መንገድ አትወድቂም " ያለው ተሻሽሎ ወ/ሮ ሎሚናት በስማቸው የተመዘገበ ባለ ሁለት መኝታ ቤት ኖራቸው ። ብሩን ቤቱ ለጎደለው ማሟሟያ እና ለመኖሪያቸው አዋሉት ። ለ16 ዓመት ገደማ 3ሜ. × 4ሜ. በሆነች ቤት ይኖሩ የነበሩት ወ/ሮ ሎሚናት በአንዴ የባለ 2 መኝታ ቤት እና የፌስቡኩ እና የእሸቱ ዩቱዩብ ገቢ አንድ ላይ ተደምሮ ከ600,000.00 ያላነሰ ብር ሆነላቸው ። ይህ ሁሉ ቤትና ገንዘብ ተወስዶ ልጃቸው ይመለስላቸው ቢሆን ሎሚናት በመረጡ ። ይህ ግን የአምላክ ፈቃድ ነው ። ሎሚናት ልጃቸውን ባያገኙ እንኳን ሜዳ ከመውደቅ ዳኑ ። ለዚህ የአንበሳው ድርሻ የኮሜዲያን እሸቱ ነው ። " ዶንኪ ቲዩብ ሰራተኞቹን የማሰናበት አደጋ ተጋርጦበታል ። " ሲባል ፍጹም ደስተኛ የሆኑ ፣ ደስታቸውን ያልደበቁና በአደባባይ ያወጁ ሰዎችን ማየት አሳዛኝ ፣ ማንነታችንን ትዝብት ውስጥ የሚጥል ሆኗል ። " በሚቀጥሉት 8 ቀናት 31 ሰራተኞች እናሰናብታለን ። " ማለት በየትኛው መስፈርት ነው ሊያስደስት የሚችለው ? ሰውን ባልተገባና " ተሳስቷል " በምንለው ተግባሩ መውቀስ ያለ ነው ። እኔም " እሸቱ አጉድሏል " ባልኩ ጊዜ ጽፌ በአደባባይ ወቅሼዋለሁ ፤ ወ/ሮ ሎሚናትን እንዲደገፉ ካስደረገልኝ ( ውለታ ከዋለልኝ ) በኋላ ። በምንም መልኩ እንኳን በቅን ልቡ የብዙዎችን እንባ ያበሰ ሰው ክፉም በክፉ እንዲመለስለት መፈለግ ሰውነት አይደለም ። የሌላው ውድቀት ለማንስ ምን ይበጃል ? ለማንስ ራት ይሆናል ? ሰበብ እየፈለገ የሚወጣ የክፋት ዘር በብዙዎቻችን ልብ ውስጥ አለ ። እሱ ነው ከወዲያ ወዲህ ሲልከሰከስ የነበረው ። ሰው ካጠፋም ቢታረም እንጂ ቢሰበር አናተርፍም ። እሸቱ መለሰ ለብዙዎች የማደግ ተምሳሌት ነው ። አሁን ደግሞ ከየትኛውም የአምልኮ ቤትና በጎ አድራጎት ኮምሽን ሳይቀበል በነጻ እየሰራ መሆኑን ተናግሯል ። " መረጃ ያላችሁ አምጡ " ብሏል ። እስካሁን ያመጣ የለም ። በነገራችን ላይ ኮምሽን ሲቀበል እንደ ዓለማዊ ፣ ነጠላ ሲለብስ እንደ ሀይማኖታዊ አይሁን እንጂ ፣ እንደምናያቸው እንደ አንዳንዶች " አምላክ አጎቴ ነው " አይበልብን እንጂ ኮምሽን ተቀብሎም የሰራውን መስራት ነውርነት የለውም ። ማን ነው እድሉ ሲገጥመው የቤተክርስቲያን ድርሻ ላይ እጁን ያልሰደደ ? አጉል ጻድቅ ጻድቅ ባያጫውተንና ነውራችንን ጣይ ባናስሞቀው መልካም ነው ። በነገራችን ላይ ፦ መምታታችሁ ካልቀረ ለይታችሁ ምቱ ። ዶንኪ ቲዩብ የቱንም ያህል ቢያዘቀዝቅ ሰራተኞቹና ቤተሰቦቻቸው ጉዳት ላይ ይወድቁ ይሆናል እንጂ ሰውየው ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ አንዳች እንኳ አይሆንም ። አሁን እንኳ "ልቀንስ ነው " የሚለው 31 ሰራተኞችን ነው ። ለመሆኑ ስንት ዩቱበሮች ለ31 ሰራተኞች የስራ ዕድል ፈጥራችኋል ? እሸቱ ሰራተኞቹን ቀንሶም ከአመዛኙ ( ምናልባት ከሁሉም ) ዩቱበሮች ይበልጣል ። አንሶ አንሶም ከአመዛኙ ዩቱበር በላይ ነው ። " አንሶና ወድቆ ወደታች አየዋለሁ " የሚል ካለ ሲቃጠል መኖሩ ነው ። አሁን ሕይወት በኢትዮጵያ የአጭር አጭር ብርድ ልብስ ሆኖብናል ። ሰርተንም ፣ ተከፍሎንም አልሆን ብሎናል ። ሰርቶ ያልሞላ ኑሮ ጭራሽ እሱም ሲቀር ምኑ ነው የሚያስደስተው ? ምኑ ነው " እሰይ ! " የሚያስብለው ? በሕይወታችሁ ከስራ ተቀንሳችሁ ታውቃላችሁ ? ነገ ሲነጋ የምትሄዱበት አጥታችሁ ታውቃላችሁ ? የሚቀጥለውን ወር የቤት ኪራይ ፣ የልጆች ት/ቤት ክፍያ ፣ አመት በዓል ፣ ሁሉም ተደምሮ መጥቶባችሁና ለአንዱም መሆን አቅቷችሁ ያውቃል ? ጉዳዩ ከእሸቱ የሰራተኞቹ ነው ። የማታውቁት አንድ ወገናችሁ መጎዳት ምኑ ያስደስታል ? በአጋጣሚው የተረዳሁት እሸቱ መለሰ የተባለ አንድ ትልቅ ተቋም መኖሩ ነው ። እሱ ነው ሊፈርስ የሆነው ። እሸቱን ቃላት እያጠራችሁ ስትገልጹት
254
17
+1
Немає тексту...
256
18
መቐለ ከተማ በራሪ ወረቀት ተበኖ አድሯል‼ በመቐለ ከተማ ጎዳናዎች ላይ ጦርነትን የሚቃወሙ እና ሰላምን የሚጠይቁ በራሪ ወረቀቶች ተበትነው ማደራቸውን የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ወጥቷል። በትግርኛ ቋን+3
መቐለ ከተማ በራሪ ወረቀት ተበኖ አድሯል‼ በመቐለ ከተማ ጎዳናዎች ላይ ጦርነትን የሚቃወሙ እና ሰላምን የሚጠይቁ በራሪ ወረቀቶች ተበትነው ማደራቸውን የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ወጥቷል። በትግርኛ ቋንቋ በተጻፉት በእነዚህ ወረቀቶች ላይ የሰፈሩት ዋና ዋና መልዕክቶች የሚከተሉት ናቸው፦ 📌"ወደ ሌላ ጦርነት እንድትከቱብን አንፈቅድላችሁም፤" 📌"የቀደመው ይበቃል፤ ሰላምን እንመርጣለን፤" 📌"የግዳጅ ውትድርና (መግፈፍ) ወንጀል ነው፤ ወንድምህን አሳልፈህ ሰጥተህ በሰላም አትኖርም፤" 📌አሁን ባለው አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚወሰድ ማንኛውም የኃይል እርምጃ የሕዝቡን ስቃይ ከማባባስ ውጪ እንደማይመረጥ ተገልጿል።
286
19
ግብፅ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ በቀይ ባህር ጉዳይ ላይ የጋራ መግለጫ አውጡ‼ ግብፅ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ ቀይ ባህርን በህገ-ወጥ መንገድ ለመቆጣጠር የሚደረጉ ማናቸውንም ሙከራዎች እንደሚያውግዙ የሚገልጽ
ግብፅ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ በቀይ ባህር ጉዳይ ላይ የጋራ መግለጫ አውጡ‼ ግብፅ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ ቀይ ባህርን በህገ-ወጥ መንገድ ለመቆጣጠር የሚደረጉ ማናቸውንም ሙከራዎች እንደሚያውግዙ የሚገልጽ የጋራ መግለጫ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቻቸው በኩል በጋራ አውጥተዋል። የቀይ ባህር ጉዳይ የሚመለከተው የባህር ዳርቻ ያላቸውን ሀገራት ብቻ እንደሆነና ከእነሱ ውጭ የሚደረጉ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን እንደሚቃወሙ ገልጸዋል። ግብፅ በኤርትራ አንድነትና ሉዓላዊነት ላይ የሚቃጡ ማናቸውንም እርምጃዎች እንደምትቃወም እና ከኤርትራ ጎን እንደምትቆም አስታውቃለች። ይህ መግለጫ ቀጥታ የኢትዮጵያን ባህር በር ፍላጎት የተመለከተ ሲሆን በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በፓርላማና በሀገራዊ ምክክር መድረኮች ላይ ካደረጉት ንግግር ጋር ተያይዞ የተሰጠ ምላሽ መሆኑ ተገልጿል። ጠ/ሚ አብይ "ያልተመረጠ መንግሥት ...ከቀይ ባህር አባረረን"ብለው ነበር አስከትለውም...በቅርቡ ቀይ ባህርን ያጣንበት አጋጣሚ የዚህ እኩይ ታሪካዊ ክስተት አንዱ መገለጫ ነው። ኢትዮጵያ ለሺህ ዘመናት ያስተዳደረችውን፣ በባለቤትነት የያዘችውን፣ ለራሷም ለከባቢውም መጠቀሚያ ያኖረችውን ቀይ ባህር፤ ያልተመረጠ መንግስት፣ ያልተወያየ መንግስት በሸፍጥ ኢትዮጵያን የጂኦግራፊ እስረኛ እንዲያደርግ ያደረገበት ዋናው ምክንያት በውስጥ ያለን ስንፍና እንጂ የኢትዮጵያን መሻትና ጥቅም ማስቆም የሚችል ኃይል ስለነበረ፣ ስላለ፣ ስለሚኖር አይደለም ማለታቸው ይታወሳል።
263
20
🔥🏆 አለም የሚጠብቀው አጓጊ ፍፃሜ! ⚽🌍 የልምድና የመሪነት ምልክት ሊዮኔል ሜሲ የሚመራው አርጀንቲና 🇦🇷 ከወጣት ኮከቡ ላሚን ያማል ጉልበት ጋር የምትመጣው ስፔን 🇪🇸 ጋር ለዋንጫው የሚደ
🔥🏆 አለም የሚጠብቀው አጓጊ ፍፃሜ! ⚽🌍 የልምድና የመሪነት ምልክት ሊዮኔል ሜሲ የሚመራው አርጀንቲና 🇦🇷 ከወጣት ኮከቡ ላሚን ያማል ጉልበት ጋር የምትመጣው ስፔን 🇪🇸 ጋር ለዋንጫው የሚደረገው ፍልሚያ ታሪካዊ ይሆናል! 🏆 ልምድ ወይስ ወጣት ጉልበት? 🤔 የማን ድል ይሆናል? ❤️ ስፔን 🇪🇸 👍 አርጀንቲና 🇦🇷 የመጨረሻ ውጤት ግምትዎን ያስቀምጡ! ⚽🔥
285