የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau
前往频道在 Telegram
2 941
订阅者
+3624 小时
+727 天
+12430 天
帖子存档
በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 3.8 ቢሊዮን ብር ብድር ለኢንተርፕራይዞች ማቅረብ መቻሉ ተገለፀ።
🇪🇹 ሰኔ 27/2018 ዓ.ም 🇪🇹
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝ ልማት ድጋፍና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተአምሩ ደበላ እንዳሉት ፤ በዘርፉ የተከናወኑ ስትራቴጂካል የሪፎርም ስራዎች ትልቅ ፍሬ አፍርተዋል።
በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ኢንተርፕራይዞቻችን በቁጠባ፣ በብድር አቅርቦትና በታማኝነት ብድር በመመለስ ረገድ ከእቅድ በላይ የሆነ እጅግ አበረታች ዉጤት መመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።
ይህ ስኬት ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን ተቋሙ የፋይናንስ ድጋፍን፣ የንግድ ልማት ምክርን፣ የቦታ ማመቻቸትንና የምርታማነት አቅም ልኬትን ያካተቱ 5 አንኳር ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎችን ተጠቅሞ ሌሊትና ቀን በመስራቱ የተገኘ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡
በተለይ ኢንተርፕራይዞች ከመበደራቸው በፊት የቁጠባ ባህላቸውን እንዲያሳድጉ በተደረገው ስልታዊ ስራ 4.8 ቢሊዮን ብር ለመቆጠብ ታቅዶ ወደ 6 ቢሊዮን ብር ገደማ በስኬት ባንክና በሌሎች ባንኮችና በአነስተና ብድርና ቁጠባ ተቋማት መቆጠብ ተችሏል። ከተቋቋመው የተቀናጀ አሰራር አኳያ ከ29 ሺህ የሚጠጉ ኢንተርፕራይዞች የቁጠባው አካል መሆን ችለዋል።
የዲጂታል ብድር አሰራርና ከግል ባንኮች ጋር የተፈጠረው ጠንካራ ትስስር ደግሞ ሌላኛው የስኬት ማማ ነው። በዚህም 3 ቢሊዮን ብር ለመስጠት ታቅዶ 3.8 ቢሊዮን ብር ብድር ማቅረብ ተችሏል፤ የብድር ተጠቃሚ የሆኑት ኢንተርፕራይዞች ቁጥርም ከፍ በማለት 8 ሺህ 176 ደርሷል። እንደ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ያሉ አካባቢዎች ያሳዩትን ጠንካራና ውጤታማ ተሞክሮ ወደ ሌሎች ክፍለ ከተሞች በስፋት በማውረድ ባንኮች በላቀ ተነሳሽነት ብድር እንዲያቀርቡ ማድረግ ተችሏል።
የተሰጠውን የህዝብና የመንግስት ሃብት በአግባቡ የመመለስ አቅምን በተመለከተም፣ መደበኛ ብድር አመላለስን 95 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በተደረገው የቅርብ ክትትልና ታማኝነት አፈጻጸሙ 97 በመቶ ደርሷል፤ ይህም ከእቅድ አንጻር ከ100 በመቶ በላይ ታላቅ ስኬት ነው።
ከዚህ በተጨማሪ ኢንተርፕራይዞች ያሉባቸውን የመያዣ (ኮላተራል) ማነቆዎች ለመቅረፍ ከመሳሪያ ሊዝ ኩባንያዎችና ከአዲስ ካፒታል እቃ ፋይናነስ ንግድ ስራ አ.ማ ጋር በመሆን ያለ ምንም ኮላተራል ማሽነሪዎችንና መሳሪያዎችን ወስደው፣ ሰርተውና ከፍለው በመጨረሻም የባለቤትነት መብት የሚያገኙበት አሰራር በስፋት እየተገበረ ይገኛል። አቅማቸው እያደገ የመጣና ቦታ የጠበባቸውን ኢንተርፕራይዞች ፕሮፖዛል በመገምገም የማስፋፊያ ቦታዎችን የመስጠት ስራ በትኩረት እየተሰራ ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል 10 ምርት ያመርቱ የነበሩ ድጋፉን ተጠቅመው ቢያንስ ወደ 15 በማሳደግ በሂደት ወደ መካከለኛና ሰፋፊ ኢንዱስትሪዎች እንዲሸጋገሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አቶ ተአምሩ ገልጸዋል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 3.8 ቢሊዮን ብር ብድር ለኢንተርፕራይዞች ማቅረብ መቻሉ ተገለፀ።
🇪🇹 ሰኔ 27/2018 ዓ.ም 🇪🇹
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝ ልማት ድጋፍና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተአምሩ ደበላ እንዳሉት ፤ በዘርፉ የተከናወኑ ስትራቴጂካል የሪፎርም ስራዎች ትልቅ ፍሬ አፍርተዋል።
በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ኢንተርፕራይዞቻችን በቁጠባ፣ በብድር አቅርቦትና በታማኝነት ብድር በመመለስ ረገድ ከእቅድ በላይ የሆነ እጅግ አበረታች ዉጤት መመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።
ይህ ስኬት ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን ተቋሙ የፋይናንስ ድጋፍን፣ የንግድ ልማት ምክርን፣ የቦታ ማመቻቸትንና የምርታማነት አቅም ልኬትን ያካተቱ 5 አንኳር ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎችን ተጠቅሞ ሌሊትና ቀን በመስራቱ የተገኘ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡
በተለይ ኢንተርፕራይዞች ከመበደራቸው በፊት የቁጠባ ባህላቸውን እንዲያሳድጉ በተደረገው ስልታዊ ስራ 4.8 ቢሊዮን ብር ለመቆጠብ ታቅዶ ወደ 6 ቢሊዮን ብር ገደማ መቆጠብ ተችሏል። ለዚህም የኦሮሚያ ስኬት ባንክ 4.57 ቢሊዮን ብር በማስቆጠብ አንበሳውን ድርሻ ይዟል። ከተቋቋመው የተቀናጀ አሰራር አኳያ ከ29 ሺህ የሚጠጉ ኢንተርፕራይዞች የቁጠባው አካል መሆን ችለዋል።
የዲጂታል ብድር አሰራርና ከግል ባንኮች ጋር የተፈጠረው ጠንካራ ትስስር ደግሞ ሌላኛው የስኬት ማማ ነው። በዚህም 3 ቢሊዮን ብር ለመስጠት ታቅዶ 3.8 ቢሊዮን ብር ብድር ማቅረብ ተችሏል፤ የብድር ተጠቃሚ የሆኑት ኢንተርፕራይዞች ቁጥርም ከፍ በማለት 8 ሺህ 176 ደርሷል። እንደ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ያሉ አካባቢዎች ያሳዩትን ጠንካራና ውጤታማ ተሞክሮ ወደ ሌሎች ክፍለ ከተሞች በስፋት በማውረድ ባንኮች በላቀ ተነሳሽነት ብድር እንዲያቀርቡ ማድረግ ተችሏል።
የተሰጠውን የህዝብና የመንግስት ሃብት በአግባቡ የመመለስ አቅምን በተመለከተም፣ መደበኛ ብድር አመላለስን 95 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በተደረገው የቅርብ ክትትልና ታማኝነት አፈጻጸሙ 97 በመቶ ደርሷል፤ ይህም ከእቅድ አንጻር ከ100 በመቶ በላይ ታላቅ ስኬት ነው።
ከዚህ በተጨማሪ ኢንተርፕራይዞች ያሉባቸውን የመያዣ (ኮላተራል) ማነቆዎች ለመቅረፍ ከመሳሪያ ሊዝ ኩባንያዎችና ከአዲስ ካፒታል ጋር በመሆን ያለ ምንም ኮላተራል ማሽነሪዎችንና መሳሪያዎችን ወስደው፣ ሰርተውና ከፍለው በመጨረሻም የባለቤትነት መብት የሚያገኙበት አሰራር በስፋት እየተገበረ ይገኛል። አቅማቸው እያደገ የመጣና ቦታ የጠበባቸውን ኢንተርፕራይዞች ፕሮፖዛል በመገምገም የማስፋፊያ ቦታዎችን የመስጠት ስራ በትኩረት እየተሰራ ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል 10 ምርት ያመርቱ የነበሩ ድጋፉን ተጠቅመው ቢያንስ ወደ 15 በማሳደግ በሂደት ወደ መካከለኛና ሰፋፊ ኢንዱስትሪዎች እንዲሸጋገሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አቶ ተአምሩ ገልጸዋል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
የግንቦት እና ሰኔ ክንውኖች የያዘች ወርሀዊ ዜና መጽሔት 📎በቅርብ ቀን ይጠብቁ::
✨ዜና ሥራና ክህሎት
🇪🇹ሰኔ 26/2018 ዓ.ም🇪🇹
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/@bols20116?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1
👉Facebook
https://www.facebook.com/addisababatvetbureau
👉Telegram
https://t.me/AABOLS
👉YouTube
https://youtube.com/@bureauoflaborandskill?si=t9ZklwKzGx9rRyXf
👉website
https://aabols.gov.et
👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ
https://complain.aabols.gov.et
ለጣሊያን ሀገር የሥራ ዕድል የምዝገባ ጥሪ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በገባው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በህጋዊ የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት ፕሮግራም በጣሊያን ሀገር በሆቴልና መስተንግዶ (Hospitality) ዘርፍ የሰው ኃይል ይፈለጋል።
የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም በማስጠበቅ ህጋዊ በሆነ መንገድ ወደ ጣሊያን ሄደው መስራት የሚፈልጉ አመልካቾች እንዲያመለክቱ እናሳውቃለን።
🏨 የሥራ መደቦች፦
🔹ጸሐፊ(Commis de Rang / F&B Server) – 19 ቦታዎች
🔹 የፅዳት ሰራተኛ (Room Attendant / Housekeeping) – 20 ቦታዎች
🔹 ረዳት ሼፍ (Commis Chef) – 13 ቦታዎች
🔹 የእቃ አጣቢ (Kitchen Steward / Dishwasher) – 11 ቦታዎች
🔹 የወለል ረዳት (Floor Porter / Houseperson) – 3 ቦታዎች
🔹 የቢሮ አስተናጋጅ (Front Office Agent / Receptionist) – 4 ቦታዎች
🔹 የጥገና ቴክኒሺያን (Maintenance Technician) – 1 ቦታ
🔹 የስፓ ቴራፒስት / የማሳጅ ባለሙያ (Spa Therapist / Masseuse) – 1 ቦታ
📌 የማመልከቻ መስፈርቶች
✅ ከስራው ጋር ተያያዥ የስራ ልምድ ያላቸው ተመራጭ ናቸው።
✅ ለአብዛኛዎቹ የስራ መደቦች የእንግሊዝኛ እና/ወይም የጣሊያንኛ ቋንቋ እውቀት ያስፈልጋል።
✅ ለአንዳንድ የሙያ መደቦች ተዛማጅ የሙያ ማረጋገጫ ወይም የሆቴል እና መስተንግዶ ትምህርት ተመራጭ ነው።
📅 የሥራ ቆይታ
አብዛኛዎቹ የስራ መደቦች ለ2026/2027 የክረምት የቱሪዝም ወቅት የሚቀጠሩ ሲሆን፣ አንዳንድ የስራ መደቦች ዓመቱን ሙሉ ወይም በበጋና በክረምት ወቅት የሚሰሩ ናቸው።
✅ ለመመዝገብ
1.Labor ID ካሎት በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ያመልክቱ።
2.Labor ID ከሌሎት የሚከተሉትን ሂደቶች ይከተሉ፦
1. በ lmis.gov.et ይመዝገቡ።
በአቅራቢያዎ ባለ የአንድ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ ይስጡ እና የሰራተኛነት መለያ ቁጥር (Labor ID) ይያዙ።
1. Labor ID ካገኙ በኋላ በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ https://forms.lmis.gov.et/italy-hotel/ገብተው መረጃዎትን በትክክል ሞልተው ያመልክቱ።
ማሳሰቢያ
• ምዝገባም ሆነ ስምሪቲ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ ብቻ የሚከናወን ሲሆን ሚኒስቴሩ ለየትኛውም አካል ውክልናም ሆነ ፈቃድ አለመስጠቱን እንገልፃለን።
• ምንም አይነት ክፍያም የለውም
የሰልጣኞችን የብቃት ማረጋገጫ ምጣኔ ለማሳደግ የሚያስችል አዲስ ሞዴል የምዘና መሣሪያ ሥራ ላይ መዋሉ ተገለጸ፡፡
🇪🇹 ሰኔ 25/2018 ዓ.ም 🇪🇹
በከተማዋ በሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የሚሰጠውን የሥልጠና ጥራት ለማረጋገጥና የሰልጣኞችን የሙያ ብቃት ምዘና (COC) ውጤት ለማሻሻል የሚያስችል አዲስ ዕቅድ መዘጋጀቱን በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የውጤት ተኮር ትምህርትና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ነጋ አረጋዉ ገለጹ።
ቀደም ሲል በነበሩት ዓመታት የሰልጣኞች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና (COC) ውጤት ከ50 በመቶ በታች የነበረ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት ከኮሌጆች አመራሮችና ከባለድረሻ አካላት ጋር እቅድን ካስኬድ በማድረግ ይህንን ምጣኔ ወደ 81 በመቶ ከፍ ለማድረግ ታቅዶ በንቅናቄ እየተሰራ ይገኛል።
ዳይሬክተሩ እንደገለጹት ይህንን ተጨባጭ ዕቅድ መሬት ላይ ለማውረድ እና በሀገር አቀፍ የብቃት ማረጋገጫ ምዘና ወቅት የሚታዩትን የሥልጠና ክፍተቶች ለመፍታት የከተማዋ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ከ9ኙ የቅንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች እና ከ15ቱ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ጋር በጋራ በመሆን አዲስ አሰራር ዘርግቷል።
በዚህም መሠረት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የ"ሞዴል ምዘና" መሣሪያ በቢሮው ተዘጋጅቶ ወደ ኮሌጆች እንዲሰራጭ ተደርጓል። ይህም በ2018 ዓ.ም ሥልጠናቸውን የሚያጠናቅቁ 8,514 ሰልጣኞች በቀጥታ ወደ ሥራው ዓለም ከመሰማራታቸው በፊት አስቀድመው በተቋም ደረጃ እና በሞዴል ምዘናዎች እንዲለማመዱና ብቃታቸውን እንዲያረጋግጡ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
ባለፉት ወራት በማዕከልና በቢሮ መካከል በተደረገው የተቀናጀ አሰራር የምዘና ጣቢያዎች እጥረት የምዘና መቋረጥና የግብዓት እጥረት ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ የተደረገ ሲሆን ይህም የሰልጣኞችን የመብቃት ምጣኔ ደረጃ በደረጃ ለማሳደግ በከፍተኛ ሁኔታ እያገዘ እንደሚገኝ ከዳይሬክቶሬቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
ከ132 ሺ በላይ ለሚሆኑ የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔትና የሥራ ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ከ2.6 ቢሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ መተላለፉ ተገለፀ።
🇪🇹 ሰኔ 24/2018 ዓ.ም 🇪🇹
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔትና የሥራ ፕሮጀክት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የከተማዋ ነዋሪዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር እየሰራ ያለውን የሴፍቲኔት ፕሮጀክት በማጠናከር በ2017 በጀት ዓመት በመንግስት ማቺንግ ፈንድ እና በራይዘን ለታቀፉ ተጠቃሚዎች ከ2 ቢሊዮን 630 ሚሊየን 716ሺ 930 ብር ከስምንት ሳንቲም ድጋፍ ለ40ሺ225 የቤተሰብ ተወካዮች ማድረሱን የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ስምሪትና ምግብ ዋስትና ዘርፍ የምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሞላ ገልጸዋል።
ዳይሬክተሩ እንደተናገሩት ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ በመንግስት ማቺንግ ፈንድ እና በአለም ባንክ ድጋፍ የተገኘ ሲሆን፣ አላማውም ተጠቃሚዎች በራሳቸው አቅም እንዲተዳደሩ እና የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ ማድረግ ነው።
እንደ አቶ ሰለሞን ሞላ ማብራሪያ፣ በፕሮጀክቱ በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በአጠቃላይ 132 ሺ 944 ተጠቃሚዎች (ከዚህ ውስጥ 129 ሺህ 441 የመንግስት ማቺንግ ፈንድ እና 3 ሺህ 503 በከተማዋ የሚገኙ የውጭ አገር ስደተኞች) ተካተዋል።
ዳይሬክተሩእንደገለጹት ፕሮጀክቱ ፍትሃዊነትን መሰረት ያደረገ የልየታ አሰራርን በመከተል፣ ትክክለኛውን ተረጂ በመለየት ሂደት ላይ ከፍተኛ ትኩረት አድርጓል። በዚህም መሰረት ከ80 በመቶ በላይ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች ሴቶች መሆናቸውን የጠቀሱት አቶ ሰለሞን ይህም ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስረድተዋል።
የገንዘብ ድጋፉ የመጨረሻ ግብ እንዳልሆነ የገለጹት አቶ ሰለሞን ሞላ፣ አሰራሩ ተጠቃሚዎች ከሚከፈላቸው ክፍያ 20 በመቶ እንዲቆጥቡ እና ይህንንም ቁጠባ ከመንግስት ከሚሰጣቸው ተጨማሪ መነሻ ካፒታል (Grant) ጋር በማቀናጀት ወደ ስራ እንዲሰማሩ የሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም፣ ተጠቃሚዎች በዘላቂነት ኑሯቸውን እንዲያሻሽሉ ከገንዘብ ድጋፍ ባሻገር በመረጡት የሥራ መስክ እንዲሰማሩ በማድረግ፣ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር ክትትል የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል።
ተጠቃሚዎቹን የማሸጋገር ስራው መንግስት ድህነትን ለመቀነስ እና ከልመና ለመላቀቅ የያዘው የ"ዜሮ ግብ " ስትራቴጂ ዋና አካል መሆኑን ዳይሬክተሩ በማብራሪያቸው ጠቁመዋል።
ዳይሬክተሩ እንዳሉት ይህ በጣም ቁርጠኛ እና ጀግንነት የሚጠይቅ ውሳኔ በመሆኑ ሁሉም የዘርፉ አመራሮች እና ባለሙያዎች በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ አለባቸው ብለዋል። አቶ ሰለሞን አያይዘውም ተረጂነትንና ልመናን ለመላቀቅ የሁላችንም የጋራ ሀላፊነት በመሆኑ ሁሉም ተጠቃሚዎች የደረሳቸውን ድጋፍ በአግባቡ በመጠቀም ለራሳቸውና ለሀገራቸው ኩራት እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
በአዋጅ ቁጥር 87/2017 ላይ ለሰራተኞች የስልጠና እና የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሄደ ።
🇪🇹 ሰኔ 24/2018 ዓ.ም 🇪🇹
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ሳምንታዊው የወርቃማ ሰኞ የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር በአዲሱ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ዙሪያ ተካሂዷል ።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ቢሮ ክትትል፣ ድጋፍና ኦዲት ዳይሬክተር አቶ መላኩ ተመስገን ሲሆኑ አዲሱ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ 87/2017 ባለፈው በጀት ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የጸደቀ ሲሆን፣ ይህ አዋጅ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግስት ሰራ ላይ ለሚገኙ 180 ሺህ ያህል ዜጎች የሚመሩበት ትልቁ የህግ ወይም የሰው ሃብት አስተዳደር የህግ ማዕቀፍ ነው ብለዋል።
ስለሆነም፣ ሰራተኛውን ማሳወቅ እና በአዋጁ ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን የጠቀሱት አቶ መላኩ፣ የስልጠና መድረኩ የተዘጋጀው ይህንን ዓላማ ለማሳካት እንደሆነ ገልጸዋል። አዋጁ በዋናነት የመንግስት አገልግሎት አስተዳደርን ውጤታማ ለማድረግ እና የሰው ሃብት ብቃትን በሚፈለገው ደረጃ ለማሳደግ የታለመ ሲሆን፣ ለህብረተሰቡ የሚቀርበውን የአገልግሎት አሰጣጥ በተፈለገው ደረጃ ውጤታማ ለማድረግ እንደታለመ አብራርተዋል።
መርሀ ግብሩ በዋናነት በአዲሱ አዋጅ ዙሪያ የሰራተኞችን ግንዛቤ ለማሳደግ የታለመ ቢሆንም፣ ከሰራተኞች የተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ተደርጓል፣ አቶ መላኩም ለጥያቄዎቹ ምላሽ በመስጠት በአዋጁ ላይ ግልጸኝነት እንዲፈጠር አድርገዋል።
አቶ መላኩ በንግግራቸው ማጠቃለያ ላይ፣ ቢሮው ሰራተኛውን በአዋጁ ዙሪያ ለማሳወቅ እና ግንዛቤ ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት ገልጸው፣ ይህ መድረክ ሰራተኞች አዋጁን በተሻለ ሁኔታ ተረድተው ወደ ስራ እንዲገቡ እንደሚረዳ እምነታቸውን ገልጸዋል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
መንግሥታዊ አገልግሎትን ቀልጣፋ ለማድረግ ትኩረት የሰጠ የሪፎርም ስልጠና ለሥራና ክህሎት ቢሮ ተጠሪና የዘርፍ ተቋማት ተሰጠ።
🇪🇹 ሰኔ 23/2018 ዓ.ም 🇪🇹
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ከስራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር በመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ላይ ለቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ አመራሮች፣ አሰልጣኞች እንዲሁም ለክፍለ ከተማና ወረዳ ስራና ክህሎት ጽህፈት ቤት አመራሮችና ቡድን መሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል。
በስልጠናው ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስ እና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ የማስፈጸም ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ፍቅርተ አበራ እንደገለጹት የሪፎርሙ ዋና ዓላማ ተቋማትን በቴክኖሎጂ በማደራጀት ቀልጣፋ፣ ነጻ እና ገለልተኛ የሆነ የአገልግሎት አሰጣጥ መዘርጋት ነው።
ኃላፊዋ አክለውም የአገልግሎት አሰጣጡ በብቃት ላይ የተመሰረተ እና ለተጠቃሚው ምቹ እንዲሆን በዘመናዊ የሪፎርም ስራዎች መታገዝ እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
በሌላ በኩል በአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ የቢሮ ኃላፊ አማካሪ አቶ ዮሐንስ ምትኩ የሪፎርም ስራው የተቋማቱን አቅም በመገንባት እና ከተለመደው የአሰራር አካሄድ በመውጣት ዘመናዊ እና ውጤት ተኮር አሰራርን የመፍጠር ተልዕኮ እንዳለው ገልጸዋል።
የሪፎርሙ አተገባበር ተቋማዊ አቅምን በማሳደግ የሰው ኃይልን ውጤታማ ማድረግ ላይ እንደሚያተኩርም አቶ ዩሐንስ ጨምረው ገልፀዋል ።
የስልጠናው መድረክ ላይ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ሪፎርሙ ሲካሄድ የሚፈጠሩ የአሰራር ክፍተቶችን ለመሙላት እና ለውጡ ስር እንዲሰድ ጥብቅ የክትትል እና የድጋፍ ስራዎች ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ሪፎርሙ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደግፎ እንዲቀጥል እና የአገልግሎት አሰጣጡን ግልጽነት ባለው መልኩ ማከናወን እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
የከተማ አስተዳደሩ በሪፎርም ስራው የተገኘውን ውጤት ዘላቂ ለማድረግ እና የአገልግሎት አሰጣጡን በላቀ ደረጃ ለማከናወን ቁርጠኛ መሆኑ በስልጠናው መድረክ ተመላክቷል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
ቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች ለማጠናከርና የተሻለ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ አራትዮሽ የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ።
🇪🇹 ሰኔ 19/2018 ዓ.ም 🇪🇹
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ የከተማዋን የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች ለማጠናከርና የተሻለ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ ከዩኤን ሀቢታት (UN-Habitat) እና ከመስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ጋር የአራትዮሽ የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ።
ስምምነቱ በተለይም በከተማዋ ለስደተ ተመላሾች፣ ለስደተ ተጋላጮች እንዲሁም ለሴቶች እና ወጣቶች የኢኮኖሚ አቅማቸውን የሚያሳድጉ የስራ ዕድሎችን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሏል።
በዩኤን ሀቢታት የገንዘብ ድጋፍ በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አስተግባሪነት 100 ኪዮስክ ሱቆችን በመስራት በከተማዋ በ11 ክፍለ ከተሞች በተመረጡ ወረዳዎች 200 ከስደት ተመላሽ የሆኑና የከተማዋ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ስምምነቱን በተፈራረሙበት ወቅት እንደተናገሩት ስምምነቱ የከተማዋን ኢኮኖሚ ከማሳደግ ባሻገር በመንግስትና በግል ዘርፍ መካከል ያለውን ትብብር ወደ ተሻለ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ጠቁመዋል።
የልማት አጋሮቹ በ15ቱ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች እያደረጉት ያለው ድጋፍ በከተማዋ ውስጥ አዳዲስ የስራ ዕድሎችን ለመፍጠር እና የክህሎት ስልጠናን በማስፋፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ወሳኝ እንደሆነም ቢሮ ኃላፊው ገልጸዋል።
የከተማ አስተዳደሩ በተለይም በሼድ አስተዳደር ስርዓት እና መሰል የኢኮኖሚ ድጋፍ ማዕቀፎች የዜጎችን ህይወት ለመለወጥ የያዘውን ዕቅድ እውን ለማድረግ ከእነዚህ አጋሮች ጋር በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ዋና ኃላፊ ዶ/ር አንዱዓለም አድማሴ እንደገለጹት ኩባንያቸው በተለያዩ የኢትዮጵያ የልማት ስራዎች ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በማድረግ ላይ ይገኛል።
በተለይም በስድስት ዋና ዋና ባለድርሻ አካላት አማካኝነት እየተከናወኑ ባሉ ፕሮጀክቶች የሞባይል ኔትወርክ አቅርቦትን ጨምሮ በማህበራዊ እና ዲጂታል ፋይናንሻል አገልግሎቶች ላይ የላቀ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዶ/ር አንዱዓለም አክለውም በዘላቂነት ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች፣ የሳፋሪኮም ፋውንዴሽን ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመተባበር አስፈላጊውን የገንዘብ እና የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ ላይ አዎንታዊ ለውጥ ለማምጣት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የዩኤን ሀቢታት ፕሮጀክት ፕሮግራም መሪ አቶ ፍፁም ፀጋዬ በበኩላቸው የዚህ ፕሮግራም ዋነኛ ትኩረት ከመካከለኛው ምስራቅ የተመለሱ ስደት ተመላሾችን በማቋቋም እና በከተማዋ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ እንዲሳተፉ ማድረግ እንደሆነ አስታውቀዋል።
ይህ ፕሮግራም ከተማዋ እያከናወነች ያለችውን የከተማ ልማት እና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ለማሳደግ የሚረዱ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን እና የቴክኒክ ድጋፎችን በማካተት በጤና እና ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ድጋፎች ላይ ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሮግራሙ በዋናነት የመኖሪያ ቤቶችን፣ የጤና ባለሙያዎችን ስልጠና እና የተሻለ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ለመገንባት የሚያስችሉ ድጋፎችን ለከተማው አስተዳደር እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ አራትዮሽ ስምምነት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዓለም አቀፍ ተቋማት እና ከግል ዘርፍ ጋር በመተባበር የከተማዋን የልማት እና የስራ እድል ፈጠራ አቅም ለማሳደግ የያዘውን ስትራቴጂያዊ ግብ መሆኑ በመድረኩ ተመላክቷል።
በጋራ በሚከናወኑ እነዚህ ፕሮጀክቶች የዜጎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በአስተማማኝ ሁኔታ መረጋገጥ እንደሚችል በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
"ከዘመኑ ጋር የሚራመድ ስልጡን አመራር፤ የምርታማነትና የልህቀት ማዕከል የስትራቴጂክ ስልጠና ማጠቃለያ
🇪🇹ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም🇪🇹
ቢሾፍቱ (ደብረዘይት)፦ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራትንና የዘርፉን የአመራር አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፤ የአመራር ክህሎትን በማሳደግ ተቋማዊ ተወዳዳሪነትን እና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ያለመ የ"ስትራቴጂክ ሊደርሺፕ" (Strategic Leadership) ስልጠና በስኬት ተጠናቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የምርታማነትና የልህቀት ማዕከል ዋና አዘጋጅነት ሰኔ 14/2015 ዓ.ም የተጀመረው ይህ የአቅም ግንባታ መርሃ-ግብር፤ በጥናት በተለዩ የአመራር ክፍተቶች መነሻነት የተዘጋጀ ነው። ስልጠናው ይበልጥ ውጤታማ እና ተደራሽ እንዲሆን በሁለት ዙር ተከፍሎ የተሰጠ ሲሆን፣ የመጀመሪያው ዙር ስልጠና ለ45 ሰልጣኞች በተሳካ ሁኔታ መሰጠቱ ይታወሳል። በዛሬው ዕለት ደግሞ የሁለተኛው ዙር ለ 39 ሰልጣኞች ስልጠና በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ባለሙያዎች አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን፤ በስትራቴጂክ ሊደርሺፕ (Strategic Leadership)፣ በቼንጅ ማኔጅመንት (Change Management) እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን (Digital Transformation) ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። በሁለቱም ዙሮች የመድረኩ ተሳታፊዎች የኮሌጅ ዲኖችና ምክትል ዲኖች፣ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመጡ ተወካዮች እንዲሁም የቢሮው የዘርፉ የዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሮች ነበሩ።
የማዕከሉ ምክትል ዲን አቶ መክብብ አሰፋ በሰጡት መረጃ፣ ተቋማት አመራሩን ስለሚመስሉ የታዩትን የአመራር ክፍተቶች በጥናት ለይቶ ይህንን ስልጠና ማዘጋጀት ማስፈለጉን ገልጸው፤ ማዕከሉ በሁለት ዙር ይሄን መድረክ በኃላፊነት መምራቱንና ወደፊትም የክትትልና የአፈጻጸም ግምገማ (Impact Assessment) ስራዎች እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
በማጠቃለያው መርሃ-ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት በቢሮ ሃላፊ ደረጃ ምክትል ቢሮ ሃላፊና የኢንተርፕራይዝና የቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሜዲቅሳ ከበደ በበኩላቸው፣ አዲስ አበባ ፈጣን እድገት የምታሳይ "ስማርት ሲቲ" በመሆኗ ይህንን ፈጣን እድገት መሸከም የሚችል ተወዳዳሪ መሪ ማፍራት ግድ ይላል ብለዋል። "ትላንት በነበረን ክህሎት እና ልምድ ብቻ ቆመን ነገ ተወዳዳሪ መሆን አንችልም" ያሉት አቶ ሜዲቅሳ፣ ሰልጣኞች ያገኙትን እውቀት ወደ ተቋሞቻቸው በመውሰድ በተግባር ሊለውጡትና እራሳቸውን በየጊዜው ሊያዘምኑ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በቢሮ ሃላፊ ደረጃ ምክትል ቢሮ ሃላፊና ዉጤት ተኮር ስልጠና እና ተቋማት አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ የሆኑት ወይዘሮ ዳግማዊት ግርማ በማጠቃለያው መድረክ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የምርታማነትና የልህቀት ማዕከል የተቋቋመበትን ዓላማ ለማሳካት በትግል ውስጥ እያለፈ እያከናወናቸው ያሉትን ስኬታማ ስራዎች አድንቀዋል። ቢሮውም ተቋማዊ መዋቅሩ እንዲሻሻልና የአመራሩ ዓቅም እንዲገነባ ሙሉ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ወይዘሮ ዳግማዊት አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት በ14ቱ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ ከ55 ሺህ በላይ ተማሪዎች (ትውልድ) እንደሚገኙ ጠቁመው፣ "ይህ ትውልድ ከእኛ ይልቅ በቴክኖሎጂው ረገድ የገፋ (Advanced) ስለሆነ፣ እኛ መራመድና እራሳችንን ማሻሻል ካልቻልን ጥሎን ይሻገራል፤ ስለዚህ እራሳችንን ከዘመኑ ጋር ማዘመንና ሼፕ ማድረግ ይጠበቅብናል" ሲሉ አስገንዝበዋል።
ስልጠናውን በንቃት የተከታተሉት የአቃቂ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ፀጋዬ ዱኛ እና የአሰልጣኝ ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተክለወይኒ ወልደጊዮርጊስ፣ ስልጠናው ወቅታዊና ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበ፣ በተለይም በአዲስ አበባ የተጀመረውን የ"ዞኒንግ እና ዲፈረንሼሽን" አሰራር ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ አቅም የፈጠረ መሆኑን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
ይህ አመራሩ የወደፊት ዕቅዶችን በስትራቴጂክ እይታ እንዲመራ፣ ተቋማዊ ለውጦችን በብቃት እንዲያስተዳድሩ እና በየደረጃው ምርታማነትን እንዲያሳድጉ ታስቦ የተዘጋጀው የአቅም ግንባታ ስልጠና፣ ስልጠናዉን ላጠናቀቁ አመራሮች የሰርተፍኬት አሰጣጥ ስነ-ስርዓት በመከናወን በደመቀ ሁኔታ ፍጻሜውን አግኝቷል።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
