ch
Feedback
የቅዱሳን ታሪክ

የቅዱሳን ታሪክ

前往频道在 Telegram

በዚህ ቻናል ውስጥ፦ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ የሚገኙ ስዕላትን የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ስዕላት የአድባራት እና የገዳማት ፎቶዎችን ያገኛሉ የተለያዩ ስዕለ አድዕኖ ለመላክ @kidanemiherat_bot

显示更多
8 632
订阅者
-124 小时
-87
-5930

数据加载中...

吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+55
在0个频道中
五月 '26
+69
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+77
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+70
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+77
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+55
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+67
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+84
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+66
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+62
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+104
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+93
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+83
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+115
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+115
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+99
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+114
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+149
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+155
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+155
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+119
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+107
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+140
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+132
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+103
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+135
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+140
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+181
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+19
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+21
在1个频道中
Get PRO
十二月 '230
在0个频道中
Get PRO
十一月 '230
在1个频道中
Get PRO
十月 '230
在0个频道中
Get PRO
九月 '230
在0个频道中
Get PRO
八月 '230
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+33
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+73
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+42
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+59
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+68
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+38
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+100
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+68
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+73
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+54
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+89
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+73
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+65
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+57
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+63
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+42
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+20
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+27
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+26
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+18
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+27
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+30
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+42
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+51
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+31
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+28
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+133
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+100
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+149
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+146
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+16 134
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
21 六月+2
20 六月+2
19 六月+6
18 六月+5
17 六月0
16 六月+2
15 六月+1
14 六月+3
13 六月+5
12 六月+5
11 六月+3
10 六月+1
09 六月+2
08 六月+2
07 六月+1
06 六月+2
05 六月+3
04 六月+4
03 六月+2
02 六月+3
01 六月+1
频道帖子
ንግስናን : ከቅድስና : አዋድዶ : የያዘ : ቅዱስ : ላልይበላ !!! #ሰኔ_12_ቀን የተባረከና የተመሰገነ በሰማያት ያለ ምሥጢርን ያየ የኢትዮጵያ ንጉሥ የነበረ በመላአክት አብሳሪነተ በላስታ ሮሃ የተወለደው የቅዱስ ላልይበላ የዕረፍቱ መታሰቢያው ቀን ነው ። በአንድ ወቅትም የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት ወደ ሰማያት አወጣው አብያተ ክርስቲያናትንም እንዴት መሥራት እንደሚችል አሳየው ወደ ምድርም ተመልሶ መንፈስ ቅዱስ እንዳረቀቀው በአስደናቂ ጥበብ ብዙ አብያተ ቤተ ክርስቶያናትን ሰራ ። ቤተ ጎልጎታ ፣ ቤተ ሊባኖስ ፣ ቤተ ደናግል ፣ ቤተ ማርያም ፣ ቤተ መስቀል ፣ ቤተ ሚካኤል ፣ ቤተ ጊዮርጊስ ቤተ ገብርኤል ፣ ቤተ አማኑኤል ፣ ቤተ መርቆሬዎስ ፣ ቤተ መድኃኔዓለምን ያነጸ ደገኛ ንጉሥ ነው ። አብያተ ክርስቲያነቱንም አንጾ ከጨረሰ በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በብርሃን ሠረገላ ተቀምጦ የሚስፈራ መብረቅን የተጎናጸፉ አእላፍት ሠራዊቶቹ ዙሪያውን ሆነው ወደርሱ መጥቶ እንዲህ አለው፤ ‹‹ ወዳጄ ላሊበላ ሆይ ሰላም ይሁንልህ እኔ በማይታበል ቃሌ እነግርሃለሁ፤ ማደሪያህ በክብር ሁሉ ከከበሩ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያቶቼ ጋር ይሁን፡፡ በጸሎትህና በቃል ኪዳንህ ለሚታመን እምነቱ እንደ ጴጥሮስና ጳውሎስ ደም መፍሰስ ይሆንለታል ፡፡ ወደ ቤተ መቅደስህም የሄደ በኢየሩሳሌም ወዳለው ቤተ መቅደሴ እንደ ሄደ ይሆንለታል ። መቃብርህንም የተሳለመ የሥጋዬን መቃብር እን ተሳለመ ይሆንለታል ፡፡ በዓመታቱ ወሮች ሁሉ የተራቡትን እያጠገበ የተጠመቁትንም እያጠጣ መታሰቢያህን ለሚያደርግ እኔ የተሠወረ መና እመግበዋለሁ ፤ የሕይወት ጽዋንም አጠጣዋለሁ፡፡ በመታሰቢያህ ቀንም ዕጣን ወይም ስንዴ የሚያገባውን እኔ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት በውስጠኛው መጋረጃ አስቀምጬ ከተቆረሰው ሥጋዬ አቆርበዋለሁ ። በአማላጅነትህም እየታመነ የገድልህንና የቃል ኪዳንህን መጽሐፍ የሚጽፈውን ያንተ ስም በተጻፈበት ቦታ  እኔ ስሙን እጽፋለሁ ። በፍጹም ልቡ ለሚያምን ይህን የማይታበል ቃል የተናገርኩ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ እኔ ነኝ ፡፡ ›› ቅዱስ ላሊበላም ይህን ቃል ኪዳን በተሰጠው ጊዜ ጌታችን እያመሰገነ በምድር ወድቆ ሰገደ፡፡ ጌታችንም ሰላምታ ከሰጠው በኋላ በክብርና በምስጋና ወደ ሰማያት ዐረገ ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ ከዚህ በኋላ ጥቂት ታሞ በሰላም ዐረፈ፤ የብርሃን መላእክትም ነፍሱን ተቀብለው የዘለዓለም ሕይወት ማደሪያ ወደሆነው ማረፊያው ገነት አስገቡት ፡፡ እግዚአብሔር : አምላክ : በቅዱስ : ላሊበላ ጸሎት : ነፍሳችንን : ይማርልን : አሜን፡፡

2
没有文字...
376
3
የቀን : እረኛ : የሌሊት : ጠባቂ : ቅዱስ : ሚካኤል #ሰኔ_12_ቀን ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎሚያን ከዲያብሎስ መንጋጋ ያስጣለበት እንዲሁም የባሕራንን የሞቱን ጦማር ቀዶ ሠርግ ያደረገበትን እለት
የቀን : እረኛ : የሌሊት : ጠባቂ : ቅዱስ : ሚካኤል #ሰኔ_12_ቀን ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎሚያን ከዲያብሎስ መንጋጋ ያስጣለበት እንዲሁም የባሕራንን የሞቱን ጦማር ቀዶ ሠርግ ያደረገበትን እለት ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ልጆቿን ሰብስባ በዓልን ሰርታ በታላቅ ድምቀት ከዓመት ዓመት ታከብረዋለች። መጋቤ ብሉይ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በተአምራቱ ዘወትር እንደሚጠብቀን ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ እንዲህ እያለ ይመሰክራል ፦ « የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የቀን እረኛ የሌሊት ጠባቂ ክንፎቹ የእሳት የሆነ ዘወትር የሚጠብቀን ቅዱስ ሚካኤል የእውነት የድንኳን ከተማ ነው። » በማለት ተናግሯል። በዚህ መሠረት ድንኳን ከቀን ሐሩር ከሌሊት ቁር እንደሚከለሉበት ሁሉ #ቅዱስ_ሚካኤልም በቃል ኪዳኑም የሚታመኑትን ሁሉ ከምሕረት አልባው ከዲያብሎስ ደባ ከአጋንንት ድብደባ ከዚህ ዓለም ፈተና ያድነናል ይታደገናል።
483
4
#እግዚአብሔርም በሰማያዊ ዜማ በምድራውያን ሰዎች ሊመሰገን በወደደ ጊዜ ቅዱስ ያሬድን ሦስት አዕዋፍ ግእዝ፣ ዕዝል እና አራራይ የሚባሉን የዜማ ስልቶች በመንፈስ ቅዱስ መሪነት አስተማረው ፡፡ ወደ ሰማ
#እግዚአብሔርም በሰማያዊ ዜማ በምድራውያን ሰዎች ሊመሰገን በወደደ ጊዜ ቅዱስ ያሬድን ሦስት አዕዋፍ ግእዝ፣ ዕዝል እና አራራይ የሚባሉን የዜማ ስልቶች በመንፈስ ቅዱስ መሪነት አስተማረው ፡፡ ወደ ሰማይም በመንፈስ ቅዱስ በመነጠቅ ቅዱሳን መላእክት እግዚአብሔርን ልዩ በሆነ ጣዕመ ዜማ ሲያመሰግኑ ሰምቶ ወደ ምድር ተመለሰ፡፡ ከዚያም በአክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ከታቦተ ጽዮን ፊት ቆሞ አምላኩን እግዚአብሔርን ‹‹ በሰማያት የሰማሁት የመላእክት ምስጋና ምን ይደንቅ! ምን ይረቅ!›› በማለት በዜማው አመሰገነ ፡፡ ይህንንም በሰማያዊት ኢየሩሳሌም የሰማውን የመላእክትን ዜማ ለደቀ መዛሙርቶቹ አስተማረ ፡፡ ከ ቅ ዱ ስ : ያ ሬ ድ : በ ረ ከ ት : ረ ድ ኤ ት : ያ ሳ ት ፈ ን !!!
607
5
ልዑል ሰምራ ዳዊት ዘመራ በቤተ መቅደስ ተወክፍዋ ልዑል ወደዳት ዳዊትም ዘመረላት በቤተ መቅደስ ተቀበሏት መቅደሰ ኦሪት ዘቦዕኪ ኦ ማርያም እምነ፤ ወእሙ ለእግዚእነ፤ በሕፅነ ሐና ተማኅፀነ፤ ፈንዊዮ ለ
ልዑል ሰምራ ዳዊት ዘመራ በቤተ መቅደስ ተወክፍዋ ልዑል ወደዳት ዳዊትም ዘመረላት በቤተ መቅደስ ተቀበሏት መቅደሰ ኦሪት ዘቦዕኪ ኦ ማርያም እምነ፤ ወእሙ ለእግዚእነ፤ በሕፅነ ሐና ተማኅፀነ፤ ፈንዊዮ ለፋኑኤል ይዕቀብ ኪያነ፤ በረምኃ መስቀል ረጊዞ ሰይጣነ፤ ወደ ኦሪት መቅደስ የገባሽ የጌታችን እናቱ እናታችን ማርያም ሆይ አንቺን በታቀፈ በሃና ጭን ተማፅነናል፤ ሰይጣንን በመስቀል ጦር ወግቶ እኛን ይጠብቀን ዘንድ ፋኑኤልን ላኪልን። (ነግሥ ዘማኅሌት) በአታ ለማርያም 🙏 እንኳን አደረሳችሁ
1 090
6
ቅ ድ መ : ዓ ለ ም : የ ታ ሰ በ ች #መላእክት ቢታሰቡ ድንግል ማርያምን ከበው በእርስዋ መንበርነት የተገለጠውን ንጉሠ ነገሥት እግዚአ አጋእዝት ሊያመሰግኑ ነው። #ነቢያት ቢታሰቡ ትንቢታቸው በድ
ቅ ድ መ : ዓ ለ ም : የ ታ ሰ በ ች #መላእክት ቢታሰቡ ድንግል ማርያምን ከበው በእርስዋ መንበርነት የተገለጠውን ንጉሠ ነገሥት እግዚአ አጋእዝት ሊያመሰግኑ ነው። #ነቢያት ቢታሰቡ ትንቢታቸው በድንግል ማርያም ተፈጽሞ በእርስዋ ምክንያት መርገም ሊወገድላቸው ነው። #ሐዋርያት ቢታሰቡ በእመቤታችን ከብረው እርስዋ ያወጣችላቸውን ፀሐይ ለብሰው ለዓለም ብርሃን ሊሆኑ ነው። #ሰማዕታት ቢታሰቡ አክሊለ ሰማዕት ክርስቶስን ወልዳላቸው በእርሱ ስም አንበሳ ሊሰግድላቸው እሳት ሊቀዘቅዝላቸው ኃይል ሊያስታጥቃቸው ድል ሊነሡ ነው። #መነኮሳት ቢታሰቡ አክሊለ ሦክ ተቀዳጅቶ የምንኩስና ቆብን ከለሜዳ ለብሶ የምንኩስና ቀሚስን በበረሃ ጹሞ የበረሃው ውስጥ ከዋክብት እንዲሆኑ ገዳምን ባርኮ የሰጣቸውን ብርሃናቸው ጌታን ብትወልድላቸው ነው። ስለዚህ “ እመቤታችን ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር” እንላለን።
1 024
7
በ ዓ ተ ፡ ግ ብ ጽ #ነገ_ግንቦት_24 ቀን እመቤታችን ከተወዳጅ ልጅዋ ጋር በስደት ግብጽ የገባችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው ። አበው የአበባን በዓል በአበባ ዘመን ብለው ማኅሌቱንም በዓሉን በወር
በ ዓ ተ ፡ ግ ብ ጽ #ነገ_ግንቦት_24 ቀን እመቤታችን ከተወዳጅ ልጅዋ ጋር በስደት ግብጽ የገባችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው ። አበው የአበባን በዓል በአበባ ዘመን ብለው ማኅሌቱንም በዓሉን በወርኃ ጽጌ በጥቅምት ቢወስዱትም ጥንተ መሠረቱ ግን ግንቦት 24 ቀን ነው ። እመቤታችን ቀጥኖ ከሚያመነምን ክፉ ዘመን ትሰውረን እፎይ ከምንልበት ዘመን በምልጃዋ ታድርሰን!
1 301
8
ጾም ሙሽሪትን ትመስላለች፤ ሙሽሪትን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች ቤቱን ያስጌጡታል፤ ይሸልሙታል፡፡ ወደ ሰርጉ አዳራሽ የሚገባውን ሰው የሰርግ ልብስ ለብሶ እንደኾነ፣ የቆሸሸ እንዳልኾነ አይ
ጾም ሙሽሪትን ትመስላለች፤ ሙሽሪትን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች ቤቱን ያስጌጡታል፤ ይሸልሙታል፡፡ ወደ ሰርጉ አዳራሽ የሚገባውን ሰው የሰርግ ልብስ ለብሶ እንደኾነ፣ የቆሸሸ እንዳልኾነ አይተው ያስገቡታል፡፡ እኛም እንዲኽ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ልቡናችንን በማንጻት፣ ልል ዘሊል ከመኾን በመራቅ፣ የክፋት እርሾን በማስወገድ፣ ከጾም ጋር አብረው የሚመጡትን የሚያጅቧትን መልካም ምግባራትንም ለመቀበል የልቡናችንን ውሳጤ በመክፈት የምግባር እናት፣ የማስተዋል እንዲኹሉም ለሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትኾን ጾምን ልንቀበላት ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ይኽን ያደረግን እንደኾነ ታላቅ ሐሴት እናደርጋለን፤ ርሷም ቁስለ ነፍሳችንን ትፈውስልናለች፡፡ በሌላ አገላለጽ ብነግራችኹ ሐኪሞች በአንድ ታማሚ ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻ፣ መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ታማሚው ምግብ ከመውሰድ እንዲቈጠብ ነው፡፡ ታማሚው ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከለ ሓኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት እንደተፈለገው ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም ቁስለ ነፍስ ቁስለ ሥጋ የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚኽ በላይ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስን የምንሻ ከኾነ ልቡናችንን ንጹሕና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል፡፡ እንዲኽ ካልኾነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንኳን ለጾመ ሐዋርያት በሰላም አደረሳችሁ 🥰
1 069
9
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : አሸናፊ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የስጦታ ምንጭ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ለሰማዕታት መመኪያ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የተሰበሩትን የሚጠግን ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : አሸናፊ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የስጦታ ምንጭ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ለሰማዕታት መመኪያ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የተሰበሩትን የሚጠግን ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የማይዳሰስ የእሳት ነበልባል ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የንጽሕናና የቅድስና መንፈስ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ዕድፍን የሚያነጻ ውኃን የሚቀድስ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የጻድቃን የባለሟልነታቸው የራስ ወርቅነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ተቀድቶ የሚጠጣ የዕውቀት መጠጥ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ድንጋዮችን የሚፈረካክስ የእሳት መዶሻ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : በጨለማ ላይ የሚያበራ የይቅርታ ብርሃን ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ሐዋርያትን የወይን ጠጅ ሳይጠጡ ያሰከረ ነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የወርቅ የሐር ግምጃ የቅዱሳን የጌጣቸው ልብስ ነው! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ፍጹም የከበረ የአብና የወልድ የባሕርይ ሕይወትነው ! ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የሃይማኖት አልጫነትን የሚያጣፍጥ የልቡና ጨው ነው ጰ ራ ቅሊጦ ስ : መጉደል መጨመር ሳይኖርበት በህልውናው አምላክነው ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ :የይሁዳ ኮረብቶች በጽዮን አዳራሽ የሚጠጡት እሳት ነው ጰራቅሊጦስ : በምሥጢረ ቁርባን ላይ የሚረብ ፀዐዳ መለኮታዊርግብነው እ ን ደ : አ ብ ና : እ ን ደ : ወ ል ድ : በ ሰ ማ የ : ሰ ማ ያ ት : በ ም ድ ር ም : ሁ ሉ : ላ ይ : መ ን ግ ሥ ቱ : የ መ ላ : ነ ው : ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ ። !!!
1 103
10
ደ ብ ረ : ም ጥ ማ ቅ ከሠላሳ ሶስት የእመቤታችን በዓላት አንዱ ግንቦት 21 ቀን የሚከበረው የእመቤታችን በዓል ነው ። በግብጽ ደብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን የወር
ደ ብ ረ : ም ጥ ማ ቅ ከሠላሳ ሶስት የእመቤታችን በዓላት አንዱ ግንቦት 21 ቀን የሚከበረው የእመቤታችን በዓል ነው ። በግብጽ ደብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን የወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ጻድቃንን መልአክትን አስከትላ ለአምስት ቀን የታየችበት የተገለጸችበት ነው ። እመቤታችን በስደት ሳለች ጌታ በዚህ ቦታ በስምሽ ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል ስሙንም ደብረ ምጥማቅ ይሉታል ብሎ ነግሯት ነበር ይኸውም አልቀረም በዚሁ ቦታ በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን ታንጾ ስሙ ደብረ ምጥማቅ ተብሏል ። በዚህ ዕለት እመቤታችን ከፀሐይ ሰባት እጅ አብርታ ከጉልላቱ ላይ በመንበር ብርሃን ተቀምጣ መላእክት ሊቃነ መላእክት ከበው ሲያመሰግኗት ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት እጅ ሲነሣት ታይታለች ። እስከ አምስት ቀንም ምእመናኑን አረማውያኑን አንድ ወገን አድርጋ ስትባርክ ሰንብታለች ከዚህም በኋላ ምእመናንም አረማውያንም በየዓመቱ እነዚህን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 25 ለአምስት ዕለታት በደብረ ምጥማቅ ተሰብስበው የሚያከብሩ ሆነዋል ። ለኛም ለልጆቿ በሕይወታችን ሁሉ እየተገለጠች በረድኤት በበረከት ትባርከን !!!
1 212
11
እ ን ዲ ህ : እ ን ላ ታ ለ ን ለጉድለታችን ምልዓት ናት ። ላለመውደቃችን ጽናት ቅናት ናት ። ለጥፋታችን አንቀጸ መድኀኒት ናት ። ለመነሣታችን ምርጉዘ ዕፀ ሕይወት ናት ። የእመቤታችን የኪዳነ ም
እ ን ዲ ህ : እ ን ላ ታ ለ ን ለጉድለታችን ምልዓት ናት ። ላለመውደቃችን ጽናት ቅናት ናት ። ለጥፋታችን አንቀጸ መድኀኒት ናት ። ለመነሣታችን ምርጉዘ ዕፀ ሕይወት ናት ። የእመቤታችን የኪዳነ ምሕረት ቃል ኪዳኗ በንስሐ እየቀሰቀሰ ወደ ርእሰ ሕይወት ክርስቶስ የሚያደርሰን የምሕረት ገመድ ነው እንላታለን ። በዚህም ልጅዋ ራሱ እኔ ከፍ ብዬ እስባችኟለሁ እንዳለ ኪዳነ ምሕረት ወደ ልጅዋ የምትመራን ብርህት ደመና የልጅዋን የምሕረቱን የወይራ ዝንጣፊ ይዛ ወደ እኛ የምትፋጠን ርግብ መንፈሳዊት ናት እንላታለን ። ዘመን የማይገድባት ለሁሉ የሚበቃ ረድኤት ያላት ምልዕተ ጸጋ በምድርም በሰማይም በነፍስም በሥጋም ጥግ የምትሆነን መለኮት የመሠረታት ነውራችን የምትሸፍንልን ሰፊ አዳራሽ ናት ። ሰለዚህም እመቤታችን ሆይ ቃል ኪዳንሽ ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ስካርም እንደለቀቀው በነፍስ በሥጋ ያነቃናል እንላታለን ። እመቤታችን ሆይ ከሕማም ያስነሣናል ከድካም ያበረታታናል እመቤታችን ሆይ ቃል ኪዳንሽ ከቡሩካን ጋር በቀኝ ያቆመናል እንላታለን ። እመቤታችን የአዳም አባታችን ርስት ከምትሆን ከገነት ከመንግሥተ ሰማያት ገብተን ለመኖር የሚያበቃን ዘላለም ጸንቶ የሚያኖረው ኪዳንሽ ነው እንላታለን ።
1 519
12
‹‹ ወደ : አባቴ : ወደ : አባታችሁ : ዐርጋለሁ ... ›› ያረገው ከሰማይ የወረደው ከድንግል ማርያም የተወለደው የፍጥረ አስገኚ የዓለም ሠራኢ መጋቢ እግዚአብሔር ነው ። በዓለ ዕርገትን ስናከብር አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ በዚህ ዓለም ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ኖረ ። ከማኅበረ መላእክት ተለይቶ ይኖር ለነበረ ለአዳም ጽንዐ ነፍስ ልጅነት ስጥቶ ከማኅበረ መላእክት ጋር አንድ አድርጎ ዐረገ ስንል ነው ። ጌታችን ወደ ሰማይ ሲያርግ የነበረውን ድባብ ምን ይመስላል ቢሉ ፦ ቢታንያ ሲደርስ መሄዱን ትቶ ቆመ ደቀ መዛሙርቱም ከበውት ቆሙ ጌታም በፍቅር ዐይን አያቸው ። እጆቹንም አንሥቶ ሲባርካቸው ከማንኛውም ምድራዊ ስበት በበለጠ ኀይል ከመካከላቸው ተነሥቶ ወደ ሰማይ ዐረገ ‹‹ ወደ አባቴ ወደ አባታችሁ ዐርጋለሁ ›› ይህን እየተናገረ ሳለ ደመና ነጠቀው ከዐይኖቻቸውም ሠወረው ። ዳግመኛ መብረቅ የለበሱ መላእክት ታይዋቸው እናንት የገሊላ ሰዎች ቆማችሁ ሰማይ ሰማይን ለምን ትመለከታላችሁ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያርግ እንዳያችሁ ዳግመኛም በክብር ወደ እናንተ ይመጣል ። ደቀ መዛሙርቱም ጌታቸውን ከዐይናቸው እስኪሰወርና አይኖቻቸው እስኪፈዙ ድረስ በአድናቆትና በፍቅር ወደ ላይ ተመለከቱ ወዲያውኑ የክብር ደመና ከዐይናቸው ሰወረው ። መላእክትም የደመና ሰረገላም መስለው በተቀበሉት ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ጥዑም የሆነውን የመላእክትን ዝማሬ ሰምተዋል። መላእክትም ትኩር ብለው የጌታን ዕርገት ለሚመለከቱ ሐዋርያት ‹‹ እናንተ የገሊላ ሰዎች ሰማይ ሲወጣ ያያችሁት ተመልሶ ይመጣል ›› የሚል ተስፋ አበሠሩአቸው ። ደቀ መዛሙርቱም ‹‹ እነሆ እኔ እስከ ዓለም መጨረሻ ድረስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ ›› ሲል የሰጣቸውን ተስፋ እያስታወሱ ከቢታንያ ተመለሱ ። እንኳን ለብርሃነ ትርገቱ በሰላም አደረሳችሁ
1 476
13
没有文字...
1 204
14
ለኢትዮጵያዊቷ ጻድቅ ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ ክብረ በዓል (ግንቦት 12) እንኳን በሰላምና በጤና በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ። ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ዓለምንና ክብሯን፣ ትዳሯንና
ለኢትዮጵያዊቷ ጻድቅ ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ ክብረ በዓል (ግንቦት 12) እንኳን በሰላምና በጤና በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ። ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ዓለምንና ክብሯን፣ ትዳሯንና ንብረቷን ንቃ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ሙሉ ሕይወቷን ለጸሎትና ለተጋድሎ የሰጠች፤ በተለይም ደግሞ ስለ ሰው ልጆች ሁሉ ድኅነትና ምሕረት ሌሊትና ቀን በጣና ባሕር ውስጥ ቆማ በመጸለይ የምሕረት ቃል ኪዳን የተቀበለች ታላቅ የፍቅርና የንሥሐ እናት ናት። የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ቅዱስ ጸሎቷ፣ ትሕትናዋ፣ ረድኤትና በረከቷ ከሁላችን ጋር ይሁን።
986
15
ሥ ጋ ህ ን : አ ፍ ል ሰ ው : በ ው ስ ጡ : ያ ኖ ራ ሉ ግንቦት 12 ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅዱስ ዐፅማቸው ቀድሞ ካረፉበት (ከተቀበረበት) ሥፍራ (ደብረ አስቦ) አሁን ወዳ
ሥ ጋ ህ ን : አ ፍ ል ሰ ው : በ ው ስ ጡ : ያ ኖ ራ ሉ ግንቦት 12 ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅዱስ ዐፅማቸው ቀድሞ ካረፉበት (ከተቀበረበት) ሥፍራ (ደብረ አስቦ) አሁን ወዳለበት ሥፍራ (ደብረ ሊባኖስ) የተዘዋወረበት ቀን ነው፡፡ ስለ ቀናች ሃይማኖትህ ስለ ልብህ ንጽሕናና ቅድስና ስለ ብዙ ጾም ጸሎት ስግደትህ ሃይማኖትን ለማስተማር መላዋን ኢትዮጵያን ስለመዞርህ በሰባት ዓመታት ቁመት የአንዱ አገዳ እግርህ ስለ መሰበሩ ወደ ኢየሩሳሌም ወርደህ ልዩ ልዩ የቅዱሳን ቦታዎች ስለ መሳለምህ ከአረማውያን ሕዝብ ጋር በሃይማኖት ስትታገል ደምህን ስለ ማፍሰስህ በማለት የሕይወት አክሊላትን ካቀዳጃቸው በኋላ ዝክራቸውን በማዘከር መታሰቢያቸውን የሚያደርጉ ሁሉ በዚህ ዓለምም ሆነ በወዲያኛው ዓለም ፍጹም ዋጋና ፍጹም ክብር እንደሚሰጣቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቃል ኪዳን ከገባላቸው ። #ግንቦት_12_ቀን « በስምህ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ልጆችህ ሠርተው ሥጋህን አፍልሰው በውስጡ ያኖራሉ ›› አላቸው ። የጻድቁ ምልጃ ጸሎት አይለየን🥰🙏
1 057
16
አ ፈ : ወ ር ቅ የቅዱስ ዮሐንስ የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል በየዓመቱ ግንቦት 12 ቀን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዓልን ሰርታ በስሙ ጽላት ቀርጻ ቤተክርስቲያን አንፃ ታዘክረዋለች ። ቅዱስ ዮሐንስ አ
አ ፈ : ወ ር ቅ የቅዱስ ዮሐንስ የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል በየዓመቱ ግንቦት 12 ቀን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዓልን ሰርታ በስሙ ጽላት ቀርጻ ቤተክርስቲያን አንፃ ታዘክረዋለች ። ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ቤተ ክርስቲያን ካፈራቻቸው ሰባክያንና መተርጉማን ታላቁና ደገኛው አባት ነው ፡፡ ዛሬም ድረስ በመላው የክርስትና ዓለም ከፍተኛውን ክብር ይዞ ይገኛል እንከን የለሽና ደስ የሚያሰኝ የሕይወት አሻራ ትቶ ያለፈ ነው ። በሰባክያንና በመተርጉማን ተዘውትሮ የሚነበብና የሚጠቀስ፣ በሁሉም ዘንድ በፍቅር የሚታወስ እንደ እርሱ ያለ የለም፡፡ ከዕረፍቱ በኋላ በተጋድሎው፤ በትምህርቱና በሕይወቱ ቅድስና የሚያደንቁትና የሚወዱት ከዕረፍቱ በኋላ ክርስቲያኖች “አፈ ወርቅ” የሚለውን ቅጽላዊ መጠሪያ ሰጡት ፡፡ “አፈ ወርቅ" የሚለው ስም ከመጠሪያ ስሙ (ዮሐንስ) በላይ ጎልቶ የሚታወቅበትና የሚጠራበት እስኪሆን የደረሰ ነው ። ለቤተ ክርስቲያን ላበረከተው ሁለ ገብ የሆነ ታላቅ አስተዋጽዖም ተገቢ የሆነ የግብሩ መገለጫ ስም ነው፡፡ ቅድስት በረከቱ ትደርብን🥰🙏
1 012
17
ከሰው ዐይን ተሰወረ አኗኗሩም ከሰማይ መላእክት ጋር ሆነ #ግንቦት_11_ቀን_ቅዱስ_ያሬድ ደብረ ሐዊ ከተባለው በሰሜን ተራራና ጫካ ውስጥ ብዙ ዓመታትን በምናኔ ካሳለፈ በኋላ ሞትን ሳይቀምስ ከዚህ ዓለም የተሠወረበት ቀን ነው። ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዓለም የኖረበት ጠቅላላ ዕድሜው ሰባ ዐምስት ዓመት ነዉ በቅዱስ ያሬድ ታሪክ ውስጥ አከራካሪ ትረካዎች አሉ ይህውም በዕረፍቱና በዕርገቱ መካከል የሚነገረው ትረካ ነው። አንዳንድ ሊቃውንት ቅዱስ ያሬድ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ መቃብሩም እንደተሠወረ ሲናገሩ ሌሎች ሊቃውንት ደግሞ እንደ ሄኖክና እንደ ኤልያስ ሞትን ሳይቀምስ እንደተሠወረ ይናገራሉ፡፡ ሞቷል የሚሉት ሊቃውንት በስንክሣሩ ላይ "በዚች ዕለት የሱራፌል አምሳያቸው የሆነ ማሕሌታይ ያሬድ ዐረፈ ፤ ከዚህ በኋላ ወደ ሰሜን ገዳም ሔዶ በዚያ በሰላምም ተቀመጠ" የሚለውን ገጸ ንባብ ይዘው ሞቷል የሚሉ አሉ ነገር ግን ይሄ ገጸ ንባብ በሞት መለየቱን አያመለክትም። ምክንያቱም "ጌታችን ከሥራው ሁሉ ዐረፈ" እንደሚለው ፤ ቅዱስ ያሬድም በድጓው "በጎዳና ካገኘኝ ድካም ሰውነቴ ዐረፈች" ብሎ በተናገረው መሠረት ሰው እንደሚያርፍ ቅዱስ ያሬድም ማስተማሩን ፤ ከሰው ጋር መለየቱን ፤ ከዓይነ ሞት መሠወሩንና ከተጋድሎው ማረፉን የሚያመለክት ነው እንጂ መሞቱን አያመለክትም ብለው የሚከራከሩ ሊቃውንት አሉ። ስለዚህ ቅዱስ ያሬድ ሞቷል ብለው የሚከራከሩ ሊቃውንት ከሞተ መቃብሩ የት ነው ሲባሉ መቃብሩ ተሠውሯል ይላሉ ፤ የመቃብሩ መሠወር ለምን አስፈለገ ተብለው ሲጠየቁ ልክ እንደ ሙሴ መቃብር ተሠውሯል ይላሉ ነገር ግን የሙሴ መቃብር የተሠወረበት የራሱ የሆነ ዓላማና ምክንያት ነበረው። እርሱም ምንድነው ቢሉ እስራኤላውያን ቅዱስ ሙሴን በብዙ ይወዱት ነበርና እንዳያመልኩት ምክንያት ለማሳጣት እግዚአብሔር ይህን እንዳደረገ ሊቃውንት ይናገራሉ ፤ የቅዱስ ያሬድ መቃብር መሠወሩ ግን ምሥጢሩ ምንድ ነው ? ለሚለው ጥያቄ በቂ መልስ ስለሌለ ሞትን ሳይቀምስ እንደነ ኤልያስ ተሠውሯል የሚለው አብላጫውን ድምፅ ይዞ በብዙ ቤተ ጉባኤዎች የሚነገረው መሠወሩ ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤልም "ከሰው ዐይን ተሰወረ ፤ አኗኗሩም ከሰማይ መላእክት ጋር ሆነ" በማለት እንደነ ኤልያስ ከነሥጋው ማረጉን አስረግጦ ይናገራል፡፡( የሰኔ ድርሳነ ዑራኤል ምዕራፍ 2 ፥ 50 ) ስለዚህ ሊቁ ቅዱስ ያሬድን ከሃይማኖታዊ ሚዛን ወጥተን ስንመለከተው ሀገራዊ ፣ ባህላዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ሥልጣኔያዊ ፋይዳና ፍልስፍናዊ ድርሻ ያለው እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሃይማኖታዊ እሴት ያበረከተ ዘማሪ ብቻ ሳይሆን እጅግ ብዙ መጠነ ሰፊ ጉዳዮች የጻፈ የቀመረ ያረቀቀ ሊቅ ነው ፤ ስለሆነም ብሔራዊ መኩሪያችን ነው። እንኳን አደረሳችሁ
1 212
18
没有文字...
1 057
19
ከሰው ዐይን ተሰወረ አኗኗሩም ከሰማይ መላእክት ጋር ሆነ #ግንቦት_11_ቀን_ቅዱስ_ያሬድ ደብረ ሐዊ ከተባለው በሰሜን ተራራና ጫካ ውስጥ ብዙ ዓመታትን በምናኔ ካሳለፈ በኋላ ሞትን ሳይቀምስ ከዚህ ዓለም የተሠወረበት ቀን ነው። ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዓለም የኖረበት ጠቅላላ ዕድሜው ሰባ ዐምስት ዓመት ነዉ በቅዱስ ያሬድ ታሪክ ውስጥ አከራካሪ ትረካዎች አሉ ይህውም በዕረፍቱና በዕርገቱ መካከል የሚነገረው ትረካ ነው። አንዳንድ ሊቃውንት ቅዱስ ያሬድ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ መቃብሩም እንደተሠወረ ሲናገሩ ሌሎች ሊቃውንት ደግሞ እንደ ሄኖክና እንደ ኤልያስ ሞትን ሳይቀምስ እንደተሠወረ ይናገራሉ፡፡ ሞቷል የሚሉት ሊቃውንት በስንክሣሩ ላይ "በዚች ዕለት የሱራፌል አምሳያቸው የሆነ ማሕሌታይ ያሬድ ዐረፈ ፤ ከዚህ በኋላ ወደ ሰሜን ገዳም ሔዶ በዚያ በሰላምም ተቀመጠ" የሚለውን ገጸ ንባብ ይዘው ሞቷል የሚሉ አሉ ነገር ግን ይሄ ገጸ ንባብ በሞት መለየቱን አያመለክትም። ምክንያቱም "ጌታችን ከሥራው ሁሉ ዐረፈ" እንደሚለው ፤ ቅዱስ ያሬድም በድጓው "በጎዳና ካገኘኝ ድካም ሰውነቴ ዐረፈች" ብሎ በተናገረው መሠረት ሰው እንደሚያርፍ ቅዱስ ያሬድም ማስተማሩን ፤ ከሰው ጋር መለየቱን ፤ ከዓይነ ሞት መሠወሩንና ከተጋድሎው ማረፉን የሚያመለክት ነው እንጂ መሞቱን አያመለክትም ብለው የሚከራከሩ ሊቃውንት አሉ። ስለዚህ ቅዱስ ያሬድ ሞቷል ብለው የሚከራከሩ ሊቃውንት ከሞተ መቃብሩ የት ነው ሲባሉ መቃብሩ ተሠውሯል ይላሉ ፤ የመቃብሩ መሠወር ለምን አስፈለገ ተብለው ሲጠየቁ ልክ እንደ ሙሴ መቃብር ተሠውሯል ይላሉ ነገር ግን የሙሴ መቃብር የተሠወረበት የራሱ የሆነ ዓላማና ምክንያት ነበረው። እርሱም ምንድነው ቢሉ እስራኤላውያን ቅዱስ ሙሴን በብዙ ይወዱት ነበርና እንዳያመልኩት ምክንያት ለማሳጣት እግዚአብሔር ይህን እንዳደረገ ሊቃውንት ይናገራሉ ፤ የቅዱስ ያሬድ መቃብር መሠወሩ ግን ምሥጢሩ ምንድ ነው ? ለሚለው ጥያቄ በቂ መልስ ስለሌለ ሞትን ሳይቀምስ እንደነ ኤልያስ ተሠውሯል የሚለው አብላጫውን ድምፅ ይዞ በብዙ ቤተ ጉባኤዎች የሚነገረው መሠወሩ ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤልም "ከሰው ዐይን ተሰወረ ፤ አኗኗሩም ከሰማይ መላእክት ጋር ሆነ" በማለት እንደነ ኤልያስ ከነሥጋው ማረጉን አስረግጦ ይናገራል፡፡( የሰኔ ድርሳነ ዑራኤል ምዕራፍ 2 ፥ 50 ) ስለዚህ ሊቁ ቅዱስ ያሬድን ከሃይማኖታዊ ሚዛን ወጥተን ስንመለከተው ሀገራዊ ፣ ባህላዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ሥልጣኔያዊ ፋይዳና ፍልስፍናዊ ድርሻ ያለው እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሃይማኖታዊ እሴት ያበረከተ ዘማሪ ብቻ ሳይሆን እጅግ ብዙ መጠነ ሰፊ ጉዳዮች የጻፈ የቀመረ ያረቀቀ ሊቅ ነው ፤ ስለሆነም ብሔራዊ መኩሪያችን ነው። እንኳን አደረሳችሁ
0
20
#፩)#የቅዱስ_ያሬድ_ልደትና_የስሙ_ትርጓሜ ꔰ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች
#፩)#የቅዱስ_ያሬድ_ልደትና_የስሙ_ትርጓሜ ꔰ  ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች ልደቱን 493 ዓ.ም. ነው ይላሉ፤ እንዲሁም አባቱ ኖኅ ነው ይሉና መሪጌታ ይስሐቅ የቀለም አባቱ /መመህሩ/ ነው ይላሉ፡፡) ꔰ  የስሙም ትርጓሜም ያሬድ ማለት እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው ፡፡ እነዚህ መሣሪያዎች በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ የያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥቱ ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክትን፥ ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና፡፡ ፨ አንድም ያሬድ ርደት፣ ወሪድ፤ መውረድ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጵያ አውርዷልና፡፡ ፨ አንድም ያሬድ ማለት ንብ ማለት ነው፤ ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከመጻሕፍት የማይጠቅሰው የማይቀሰመው የለም፤ ፨ አንድም ያሬድ ማለት ረአዬ ምሥጢር፥ ነጻሬ ኅቡአት ማለት ነው፤ የመላእክት ምሥጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፣ ነጻሬ ኅቡአት አለ፥ ኅቡእ (ስውር) የሆነ የጻድቃን፣ የሰማዕታት የነቢያት የሐዋርያትን ገድል አምልቶ አስፍቶም ይናገራልና፡፡ -ዐፄ ካሌብ ቤተ እስራኤል፣ ገብረክርስቶስና ገብረ መስቀል የሚባሉ ልጆች ነበሩት፤ ቅዱስ ያሬድ የተነሳው ከእነዚህ ውስጥ በዓፄ ገብረመስቀል ዘመን ነው፡፡ ቅድስት በረከቱ ትደርብንና በሰፊዉ ግንቦት 11 ቀን እንመለስበታለን🥰
1 258