ch
Feedback
የቅዱሳን ታሪክ

የቅዱሳን ታሪክ

前往频道在 Telegram

በዚህ ቻናል ውስጥ፦ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ የሚገኙ ስዕላትን የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ስዕላት የአድባራት እና የገዳማት ፎቶዎችን ያገኛሉ የተለያዩ ስዕለ አድዕኖ ለመላክ @kidanemiherat_bot

显示更多
8 582
订阅者
无数据24 小时
-157 天
-3830 天

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+6
在0个频道中
八月 '26
+96
在0个频道中
Get PRO
七月 '26
+105
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+87
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+69
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+77
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+70
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+77
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+55
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+67
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+84
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+66
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+62
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+104
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+93
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+83
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+115
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+115
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+99
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+114
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+149
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+155
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+155
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+119
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+107
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+140
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+132
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+103
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+135
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+140
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+181
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+19
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+21
在1个频道中
Get PRO
十二月 '230
在0个频道中
Get PRO
十一月 '230
在1个频道中
Get PRO
十月 '230
在0个频道中
Get PRO
九月 '230
在0个频道中
Get PRO
八月 '230
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+33
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+73
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+42
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+59
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+68
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+38
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+100
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+68
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+73
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+54
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+89
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+73
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+65
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+57
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+63
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+42
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+20
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+27
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+26
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+18
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+27
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+30
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+42
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+51
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+31
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+28
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+133
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+100
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+149
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+146
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+16 134
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
04 九月0
03 九月+2
02 九月+1
01 九月+3
频道帖子
Story

2
没有文字...
600
3
⏳ 3 ቀን ብቻ ቀረው!! የምድር ጌጥ ኢትዮጵያ በሆላንድ ፓርክ ከነሐሴ 28 እስከ መስከረም 3 ለተከታታይ 10 ቀናት ከልጆችዎ እና ከቤተሰብዎ ጋር በአክብሮት ጋበዝንዎ! 🎫 የመግቢያ ትኬትዎን በኦን
⏳ 3 ቀን ብቻ ቀረው!! የምድር ጌጥ ኢትዮጵያ በሆላንድ ፓርክ ከነሐሴ 28 እስከ መስከረም 3 ለተከታታይ 10 ቀናት ከልጆችዎ እና ከቤተሰብዎ ጋር በአክብሮት ጋበዝንዎ! 🎫 የመግቢያ ትኬትዎን በኦንላይን ይቁረጡ!! 👇👇👇 https://tickets.hamereberhan.org/e/jewel-of-the-world-ethiopia-r2xu 📍ሆላንድ ፓርክአድራሻ 👇👇👇 https://maps.app.goo.gl/zHL3ZeXVNFWRV4dq6
600
4
ንዒ ርግብየ ሠናይት ነሐሴ ፳፩.mp3
833
5
እጅግ : ትሑቷ : ድንግል : ማርያም ቅድስት ፣ ድንግል ፣ ንፅህት የሆነች ድንግል ማርያም ትንቢተ ኢሳይያስን ስታነብና « ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች» በሚለው አንቀጽ ስትደርስ
እጅግ : ትሑቷ : ድንግል : ማርያም ቅድስት ፣ ድንግል ፣ ንፅህት የሆነች ድንግል ማርያም ትንቢተ ኢሳይያስን ስታነብና « ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች» በሚለው አንቀጽ ስትደርስ « ምነው እኔ በሆንኩኝ? » አላለችም « ምነው በዘመኗ ደርሼ ይህቺን ድንግል ባገለገልኳት? » አለች እንጂ፡፡ መልዐኩ « ተፈስሒ » ደስ ይበልሽ ሲላት « ይገባኛል » አላለችም « የእግዚአብሔር ገረዱ እነሆኝ » አለች እንጂ / ሉቃ.1 ፡ 38 /፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ « የጌታዬ እናቱ እመቤቴ ወደኔ ትመጭ ዘንድ እኔ ምንድነኝ? » ስትላት « ልክ ነሽ ይገባኛል አምላክን ፀንሻለሁና » አላለችም « የባርያይቱን ውርደት ተመልክቷልና » አለች እንጂ ፡፡ እመቤታችን ኤልሳቤጥ እንዳረገዘች ሰምታ ትጠይቃት ዘንድ መሔዷ የትሕትናዋን ጥልቀት ያሳያል ለልማዱ ባርያ ወደ ጌታው ይሔዳል እንጂ ፡፡ የሆነው ግን እንዲህ አይደለም የመጣችው ኤልሳቤጥ አይደለችምና ወላዲተ አምላክ እመቤታችን ሔደች እንጂ ። ያውም በዚያ ተራራማው ስፍራ የእመቤታችን ትሕትናዋ ግሩም ነው፡፡ ትሕትና ሰዎችን አማልክት ዘበጸጋ ታደርጋለች ትዕቢት ደግሞ ቅዱሳን መላዕክትን ታዋርዳለች ምክንያቱም ትዕቢት እጅግ ክፉ ነውና ።
1 025
6
ፍ ል ሰ ታ ፡ ሥ ጋ ሁ ፡ ለ ቅ ዱ ስ ፡ ጊ ዮ ር ጊ ስ #ነሐሴ_16_ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋው ከፋርስ አገር ወደ አገሩ ልዳ በክብር የፈለሰበት ዕለት ነው ። የልዳው ፀሐይ የ
ፍ ል ሰ ታ ፡ ሥ ጋ ሁ ፡ ለ ቅ ዱ ስ ፡ ጊ ዮ ር ጊ ስ #ነሐሴ_16_ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋው ከፋርስ አገር ወደ አገሩ ልዳ በክብር የፈለሰበት ዕለት ነው ። የልዳው ፀሐይ የኢትዮጵያ ገበዝ ቅዱስ ጊዮርጊስ ክርስቶስን አልክድም የሚል አንድ እንኳን በጠፋበት በዚያ ጊዜ በክርስቶስ አምላክነት የጣዖትን ከንቱነት በመመስከር ጌታውን የወደደና ያስከበረ ታላቅ ሰማዕት ነው ። ጌታችንም እንደወደደው ወዶታልና እንዳከበረው አክብሮታልና ዕረፍቱን እሱ ለቤዛ ብዙኃን በመስቀል ተሰቅሎ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ባረፈባት በዕለተ ዓርብ አድርጎለታል ። ፍልሰተ ሥጋውንም ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገተ ሥጋ ጋር አንድ አድርገው እንዲያከብሩት በዚሁ ዕለት በስሙ ወዳነጹለት ቤተ ክርስቲያን አንዲያፈልሱት አድርጓለታል ፡፡ ድንግል ፡ ሆይ ! ፍልሰተ ፡ ዐፅሙ ፡ ከፍልስትሸ ፡ ጋር ፡ ለኾነ ፡ ስለ ፡ ሕማሙ ፡ ስለ ፡ ድካሙ ፡ ፈንታ ፡ የስሙ ፡ ሞገስ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ ላለ ፡ ለቅዱስ ጊዮርጊስ፡ ሰላምታ ፡ ይገባል ፡፡ አስቀድሞ፡ እመቤቴ : ሆይ ከፍልስተሸ ፡ ጋር ፡ ደምሪኝ ፡ ብሎ ፡ ጸልዮአልና ። እንደምርኮ ፡ ልብን ፡ የምታስደስት ፡ ደስ ፡ የተሰኝህ ፡ ቅዱስ ፡ ጊዮርጊስ : ሆይ ፤ የሰማዕትነትህን ፡ ሥቃይ ፡ ከፈጸመክባት : ከፋርስ ፡ ወደ ፡ ልዳ ፡ ለተደረገው ፡ የሥጋህ : ፍልሰት ፡ ሰላምታ : ይገባል ። የሥጋህ : ፍልሰት ፡ ከድንግል ፡ ማርያም፡ ፍልሰት ጋር አንድ ሆነ።
1 201
7
ማ ር ያ ም : አ ር ጋ ለ ች : ወ ደ : ገ ነ ት !!! ለተረገመችው : ምድር : ካሣ : የሆነች ፦ ቅድስት ምድር የእግዚአብሔር ማደሪያው (እናት) የሆነች ድንግል ማርያም እንደ ምንጭ ውኃ የጠራ
ማ ር ያ ም : አ ር ጋ ለ ች : ወ ደ : ገ ነ ት !!! ለተረገመችው : ምድር : ካሣ : የሆነች ፦ ቅድስት ምድር የእግዚአብሔር ማደሪያው (እናት) የሆነች ድንግል ማርያም እንደ ምንጭ ውኃ የጠራች በኀይለ መለኮቱ የጸናች ንጹሕ ዘር የሆነች #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታለች። የጳውሎስ : ፍጽምት : ድንኳን : የሆነች ፦ ደሀውም ባለጠጋውም ሴቱም ወንዱም ጌታውም ባርያውንም ካህኑም ምእመኑም የሚጠለልባት ከድካመ ሥጋ ከድካመ ነፍስ የሚያርፉባት #እሷም_እንደልጇ_ተነስታልች ። የሕይወት : ደምግባት : የሆነች ፦ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሕይወት የታደገባት፤ በፍዳ በመርገም ተጎሳቁሎ የነበረውን ባሕርያችንን ያደሰባት የሕይወታችን ደምግባት የሆነች #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታለች ። ፍጥረት : የዳነባት : የኖኅ : ታቦት ፡ የሆነች ፦ ከጥፋት ውኃ የዳንባት መርከባችን በድንግልና የታተመች ማርያም የሐዲስ ፍጥረት ቅርንጫፍ መዳኛ መርከብ የሆነች በዚህም ዓለም በወዲያኛው ዓለም በገነት ፣ በመንግሥተ ስማያት የምትመሰገን #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታልች ። ዝምተኛ : መልካሚቱ : እመቤት : የሆነች ፦ በሰውነቷ ውስጥ የተከናወነውን ምሥጢር በማኅፀኗ የተፈጸመውን መለኮታዊ ኀይል ዝም ብላ በልቧ ትጠብቀው ነበር እንጂ ስለክብሯ እዩልኝ ስሙልኝ ብላ ለማንም ያልተናገረችው ቅድስት እመቤት #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታልች ። ከወርኅ : መስከረም : አበቦች : ይልቅ : የተመሰገንሽ : ማርያም : ሆይ ከአላፊው : ከጠፊው : ከታችኛው : ዓለም : በሰማይ : በኪሩብ : ጉባኤ : ትኖር : ዘንድ : ሱራፊ : ለሚጠብቃት : የሥጋሽ : ፍልሰት : ሰላምታ : ይገባል።
826
8
没有文字...
904
9
የ እ መ ቤ ታ ች ን : ሰ በ ን እመቤታችን ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ባገኝችው ጊዜ ለሐዋርያት ምልክት እንዲሆን እንካ ብላ ሰበኗን የመግነዝ ጨርቋን ሰጥታው ነበር።
የ እ መ ቤ ታ ች ን : ሰ በ ን እመቤታችን ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ባገኝችው ጊዜ ለሐዋርያት ምልክት እንዲሆን እንካ ብላ ሰበኗን የመግነዝ ጨርቋን ሰጥታው ነበር። እናም ቅድስት ቤተ ክርስትያንም ይህንን ምሳሌ ይዛ በቅዳሴ ጊዜ ሠራዒ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ በመጾር ላይ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው፡፡ እንዲሁም አባቶቻችንም በእጅ መስቀላቸው እጄታ ላይ የሚይዙት መሐረብ መሰል ሱቲ የሰበኗ ምሳሌ ነው። ቅዱሳን ሐዋርያትም በሰበኗ ድውይ ሲፈውሱበት ሙት ሲያሥነሱበት ኖረዋል።
955
10
የሚለውን አያውቅም ነበር” ማር. 9፥6 ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ስለ ደብረ ታቦር በጻፈበት ምዕራፍ ውስጥ ይህንን ዐረፍተ ነገር እናገኛለን። ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታን ያየው ዓሣ በሚያጠምድበት የገሊላ ባሕር ላይ ነው። ዛሬ ያየውን በብርሃን የተሞላ ፊቱን ግን አላየውም። ያን ጊዜ ግብረ መለኮቱን ዛሬ ደግሞ ገጸ መለኮቱን አየ። ያ የመጀመሪያው ቀን በሁለት ጀልባ ሙሉ ዓሣ ያጠመደበት ቀን ነበር በሕይወቱ ትልቁን ትርፍ ያተረፈበት ቀን ነው። ባሕር የታዘዘችለት መሆኑን ሲያይ እርሱ እግዚአብሔር እንደሆነ አውቆ “ጌታ ሆይ” ብሎ ጠራው ሉቃ. 5፥3-11። ዛሬ ደግሞ ገጸ መለኮቱን አየ። በዚህ ምክንያት መደንገጡን የገለጠው ወንጌላዊ ከመደንገጡ የተነሳ የሚናገረውን አያውቅም ነበር አለ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን ይዞ ወደ ተራራው የወጣው ከተራራው እግርጌ “አንተ የሕያው እግዚ አብሔር ልጅ ነህ” ማቴ. 16፥16 ብለውት ስለነበር በትክክልም የሕያው እግዚ አብሔር ልጅ እንደሆነ ከባሕርይ አባቱ ከአብ የምስክርነትን ቃል እንዲሰሙ ለማድረግ ነበር። አንዳንዶቹ ኤርምያስ ነው፣ ኤልያስ ነው ወይም ሌላ ስም እየጠሩ “ዕገሌ” ነው ይሉት ስለነበር የአይሁድ ሊቃነ ካህናት የሚሉት እንዳልሆነ እንዲያስተውሉ ነበር። ጴጥሮስ ግን ከዚህ በተቃራኒ በታቦር ተራራ ላይ መኖር አሰኘውና “በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው” አለ። ጴጥሮስ ሆይ! ለእኛስ መልካም የሚሆነው በሰማይ ባለች ነጻ በምታወጣ በኢየሩሳሌም መኖር ነው። በዚህ ተራራ የጥንት ሰዎች ሰልፍ ሰርተውበታል፤ ደም ፈሶበታል ጦርነት ተደርጎበታል መሳ. 4፥12። ለእኛስ ጦርነት የሌለባት የእግዚአብሔር መንግሥት ትሻለናለች። “ሞትም ከእንግዲህ አይሆንም ኃዘንም ቢሆንም ወይም ጩኸትወይም ስቃይ ከእንግዲህ አይሆንም” ራእ. 21፥4 የተባለላት ከተማ የት አለች? እሷን ሳናገኝ “በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው” ማለት የሚሉትን እንዳለማወቅ ይቆጠራል። ከሰማይ በታች ያለው ነገር ሁሉ ከንቱ ነው ለእኛስ መልካም የሚሆንልን ከክርስቶስ ጋር ወደ ሰማይ መውጣት ነው። ከሰማይ በታች የማያረጅ ውበት የማያልቅ ሀብት የለም ዛሬ የወደድነውን ነገ እንጠላዋለን። መንግሥተ ሰማያት ግን “ለባሏ እንደተሸለመች ሙሽራ ናት” አታረዥም። በእርግጥም ጴጥሮስ የሚለውን አያውቅም ነበር፥ የሰማይና የምድሩን ባለቤት ሰቀላ ሠርቶ ሊያኖረው አስቦ ነበርና። ፈጣሪን ከፍጡራን ጋር አስተካክሎ “ሦስት ዳስ እንሥራ አንዱን ለአንተ፣ አንዱን ለሙሴ፣ አንዱን ለኤልያስ” አለ። ክርስቶስ ከሙሴ ከኤልያስ ጋር ጎረቤት ሆኖ ሊኖር የሚገባው ነውን? በሙሴ አድሮ ባሕር የከፈለ፣ መና ያወረደ፤ በኤልያስ አድሮ አክዓብን የገሰጸ፣ ሰማይን የዘጋ ምድርንም ደረቅ ያደረገ እርሱ አይደለምን? ሙሴን በብርሃን ድንኳን ውስጥ ተገልጦ ዐሥሩ ቃላትን በሁለት ጽላት ላይ የጻፈለት፣ ለኤልያስም የእሳት ሰረገላና ፈረሶችን የላከለት እርሱ ከሙሴና ከኤልያስ ጋር በዚህ ተራራ ሊኖር እንዴት ይችላል? ጴጥሮስ “የሚለውን አያውቅም ነበር” ጴጥሮስ ሆይ ሙሴና ኤልያስ ወደዚህ ተራራ የተጠሩት በኢየሩሳሌም ሊሆን ስላለው የክርስቶስ መስቀል ከክርስቶስ ጋር ሊነጋገሩ እንጂ ሰቀላ አሠርተው ሊኖሩ አይደለም። ዐርባ ዓመታትን ያለ ሰቀላ ያገለገለው ሙሴ፣ በኮሬብ ፈፋ ውስጥ ተሰውሮ ዘመኑን የጨረሰው ኤልያስ ዛሬ ሰቀላ አስፈልጓቸው የመጡ ይመስልሃልን? ቅዱስ ወንጌል የመጡበትን ጉዳይ “በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር” ሉቃ. 9፥31 ብሎ ያብራራዋል። ስለ ክርስቶስ መስቀል በሚነገርበት መድረክ ስለ ሦስቱ ዳሶች ማውራት በእርግጥም የሚሉትን አለማወቅ ነውና ቅዱስ ማርቆስ “የሚለውን አያውቅም ነበር” አለ። ክርስቶስ ካልሞተ ምዕመናን በምን ነጻ ይወጣሉ? “እሞታለሁ እሰቀላለሁ” ያለበት ቦታ ይህ አይደለም፤ በኢየሩሳሌም ነው። ጌታ መቃብራችንን ባዶ የሚያስቀርበት፣ ሞታችንን የሚገድልበት፣ ስለበደላችንም ካሳ ሆኖ የሚቀርብበት ስፍራ ይህ ሳይሆን ያኛው ነው። ጴጥሮስ ሆይ ለእኛስ የሚሻለን በዚህ ሳይሆን በዚያ መኖር ነው። “አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” ብሎ በደላችንን ካላስቀረልን፤ “ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ” ብሎ ወደ ገነት ካልመለሰን፤ “እነሆ እናትህ” ብሎ በሔዋን ፋንታ ድንግል ማርያምን እናት አድርጎ ካልሰጠን፤ “ተራብሁ” ብሎ ማቴ. 4፥2 ረሀባችንን እንዳስቀረልን “ተጠማሁ” ብሎ መጠማታችንን ካላስቀረልን ሰው መሆኑ ለምንድነው? ጴጥሮስ ሆይ በደብረ ታቦር ሰቀላ ሠርተህ ብታኖረው ይህ ሁሉ ይቀርብናል። ሙሴና ኤልያስ የመጡት አይሁድ ክርስቶስን የሙሴን ሕግ ሻረ ብለውት ነበርና ሕግን የሚፈጽም እንጂ ሕግን የሚሽር እንዳልሆነ ለማስረዳት ነው ማቴ. 5፥17። እነሱ ለሕግ የሚቀኑ መስሏቸው ሰንበትን እንደሻረ አስበው ይቃወሙት ነበር፤ “ይህ ሰው ሰንበትን አያከብርምና ከእግዚአብሔር አይደለም” ዮሐ. 9፥16 ያሉት ብዙዎች ናቸው። ከእነሱ በላይ ለእግዚ አብሔር ሕግ የሚቀናው ኤልያስ ዛሬ ወደ እርሱ መጥቶ ታየ። ለምስክርነት የመጡትን ሙሴንና ኤልያስን ዳስ ጥሎ ማኖር አይቻልምና “የሚለውን አያውቅም ነበር” እንኳን አደረሳችሁ ለነቢያት ለሐዋርያት የገለጠውን የጌትነቱን ምሥጢር ለእኛም ይግለጥልን። ©️ ስምዓኮነ መልአከ / Simakone Melak
1 043
11
ደብረ ታቦር በዓለ ደብረ ታቦር ከ9ኙ ዓበይት በዓላት መካከል 1ዱ ነው። ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ «ከነቢያት አንዱ ነህ» ብለውት ነ
ደብረ ታቦር በዓለ ደብረ ታቦር ከ9ኙ ዓበይት በዓላት መካከል 1ዱ ነው። ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ «ከነቢያት አንዱ ነህ» ብለውት ነበርና የነቢያት አምላካቸው እንደሆነ ለማጠየቅ ቅዱስ ጴጥሮስን ቅዱስ ያዕቆብንና ቅዱስ ዮሐንስን ወደ ተራራ ይዟቸው ወጣ። ጴጥሮስን ያዕቆበንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ደብረ ታቦር ተራራ ላይ ከወጣ በኋላ መልኩም በፊታቸው ተለወጠ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ እንደ ፀሐይም አበራ። እነሆ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሊነጋገሩ ወደ እርሱ መጡ ሲነጋገሩም ብሩህ ደመና መጥቶ ጋረዳቸው «የምወደው ልጄ ይህ ነውና እርሱን ስሙት» የሚል ቃል ከደመና መጣ ብርሃነ መለኮቱም ከደብረ ታቦር እስከ አርሞንኤም ተራራ ድረስ ላሉት ሁሉ ተገለጠ። የተራራው አናት ላይ የተገለጠው ብርሃነ መለኮቱ በተራራ ግርጌ ላሉት ሁሉ ለስምንቱ ሐዋርያት ተገለጠላቸው። ሐዋርያቱ የክርስቶስን የክብሩን ብርሃን ሲያዩ ፊቱ ሲለወጥባቸው በሐዋርያት ልብ ያደረው ሥጋዊ መንፈስ ራቀ በውስጣቸው ያለው ጨለማ ተወገደ የእግዚአብሔርን ክብር እንዲያስተውሉ አእምሯቸው ብሩህ ሆነ። ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ «በፊታቸው ተለወጠ ልብሶቹም እንደ በረዶ ነጭ ሆኑ ጴጥሮስ ኢየሱስን እንዲህ አለው ሊቅ ሆይ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው ከዚህ ሦስት ዳስ እንሥራ አንዱን ላንተ አንዱን ለሙሴ አንዱን ለኤልያስ አለው» ሲል ዘምሯል። ጌታችን ሙሴን ከመቃብር ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ አስተዋወቃቸው ጌታችን በደብረ ታቦር ተራራ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን ሰዎችን ነቢያትንና ሐዋርያትን አንድ አደረጋቸው እርሱ አምላካችን ሠራኤ ብሉይ ወሐዲስ ነውና። ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን የብርሃነ መለኮቱን ምስጢር ለኛም ይግለፅልን🙏 እንኳን አደረሳችሁ!
921
12
没有文字...
1 097
13
没有文字...
1 125
14
❝የምሥጢረ ሥላሴ አጭር መግለጫ ❞ °በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ° °°አብ በመንፈስ ቅዱስ ይመሰገናል፡፡ ወልድም በአብና በመንፈስ ቅዱስ ይመሰገናል፡፡ መንፈስ ቅዱስም በአብና በወልድ ይመሰገናል፡፡ °°ከወ
❝የምሥጢረ ሥላሴ አጭር መግለጫ ❞ °በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ° °°አብ በመንፈስ ቅዱስ ይመሰገናል፡፡ ወልድም በአብና በመንፈስ ቅዱስ ይመሰገናል፡፡ መንፈስ ቅዱስም በአብና በወልድ ይመሰገናል፡፡ °°ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ አስቀድመው ለአብ ምስጋና በመስጠታቸውም ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ይልቅ ለአብ ክብርን እንደስጡ አታስብ፡፡ እንዲህ አይደለምና፡፡ °°በአብ ያለ በወልድ ግን የሌለ ክብር የለም፡፡ በወልድ ያለ በአብና በመንፈስ ቅዱስ የሌለ ገናናነት የለም፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ያለ በአብና በወልድ ግን የሌለ ክብር የለም፡፡ °°አብ ወልድ ባልነበረበት ወቅት አልነበረም፡፡ ወልድም መንፈስ ቅዱስ ባልነበረበት ወቅት አልነበረም፡፡ መንፈስቅዱስም አብና ወልድ ባልነበ ሩበት ዘመን አልነበረም፡፡ °°አብ ከወልድ አይበልጥም። ወልድም ከአባቱ አይበልጥም፡፡ መንፈስ ቅዱስም እንደ እነርሱ ነው፡፡ °°አብ ልጁን ይህ የእኔ ነው፣ ያ የአንተ ነው፤ ይህ የመንፈስ ቅዱስ ነው የሚለው አይደለም፡፡ ወልድም አባቱን ይህ የእኔ ነው ይህ የአንተ ነው ይህም የመንፈስ ቅዱስ ነው የሚለው አይደለም፡፡ መንፈስ ቅዱስም አብን ይህ የአንተ ነው ይህ የወልድ ነው አይለውም፡፡ °°መጀመሪያችን ርስታችን የሆነ ወልድ ከአብ የሚለይ አይደለም፡፡ ወልድም በሀብትና በርስት ከአብ አይለ ይም፡፡ መንፈስ ቅዱስም እንዲሁ፡፡ በሥላሴ የተለያየ መንግሥት የለም፡፡ በአንዲት አምልኮት ያመልኳቸዋል፡፡ አንዲት ስግደትም ይሰግዱላቸዋል። °°ሰውን በአርያችንና በምሳሌ ያችን እንፍጠር በማለት ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ የተናገረው የአብ ምክር ምን ይደንቅ፡፡ በዚህ ምክር የተሰማማ የወልድ ምክርም ዕፁብ ነው፡፡ በእጆቹ ሥራ የተደሰተ የመንፈስ ቅዱስ ፈቃድም ምን ይደንቅ!
1 483
15
ሥላሴ በዕለተ ቀናቸው ሦስት የነገረ ድኅነት ማግኛ የመሠረት ድንጋዮችን ጣሉ። በዛሬዋ ዕለት የተጣሉ 3 የመሠረት ድንጋዮችም ❖ ፅንሰተ ማርያም ሚ ቡርክት ወቅድስት ይእቲ ሰዓተ ትፍሥሕት ሐና ዘጸገየተ
ሥላሴ በዕለተ ቀናቸው ሦስት የነገረ ድኅነት ማግኛ የመሠረት ድንጋዮችን ጣሉ። በዛሬዋ ዕለት የተጣሉ 3 የመሠረት ድንጋዮችም ❖ ፅንሰተ ማርያም ሚ ቡርክት ወቅድስት ይእቲ ሰዓተ ትፍሥሕት ሐና ዘጸገየተኪ ባቲ" እንዳለ ደራሲው በዛራዋ ዕለት የድኅነት መሠረት የሆነችዋ እናታችን ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነውና የነገረ ድኅነት ሕንፃው የመሠረት ድንጋዩ ተቀመጠ። ❖ ፅንሰተ ቤተ ክርስቲያን (በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራታለሁ) ቅዱስ ጴጥሮስ ሐዋርያትን ወክሎ አንተ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ በመመለሱ ይህንን ነገረ ሃይማኖት የምትመሰከር ቤተ ክርስቲያን በዚህ አስተምህሮት የጸናች ቤተ ክርስቲያን የመሠረት ድንጋይዋ በቂሳርያ ተመሠረተ። ❖ፅንሰተ ክህነት(የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻ ቁልፍ እሰጥሃለሁ በማለት ጌታችን መድኃኒታችን ቅዱስ ጴጥሮስ አስቀድሞ ለመለሰው መልስ የክህነት ሽልማት በሐዋርያት በኩል ለቤተ ክርስቲያን ተሰጠ። እንኳን አደረሳችሁ
1 068
16
ይህቺን : ዕለት : ያልናፈቀ : ትውልድ : የለም #ነሐሴ_ሰባት_ቀን የባሕርያችን መመኪያ የምትሆን ንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነው ፡፡ ጽ
ይህቺን : ዕለት : ያልናፈቀ : ትውልድ : የለም #ነሐሴ_ሰባት_ቀን የባሕርያችን መመኪያ የምትሆን ንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነው ፡፡ ጽድቃቸው እንደ መርገም ጨርቅ ለሆነባቸው ቅዱሳን አበውና ቅዱሳን አንስት ተስፋቸው የሚፈጸመው በዛሬው ዕለት በተጸነሰችው በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ነውና ፡፡ ቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችንም ከእግዚአብሔር ቀጥሎ እንደ እመቤታችን ከፍ ከፍ የምታደርገው ፍጥረት የሌለው ስለዚሁ ነው ፡፡ ሊቃውንቱ፡- « ሐና አንቺን የጸነሰችበት የደስታ ቀን ምን ያህል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤ ሟች ኢያቄምም ለሕይወት አንቺን ያፈራባት ቀን ምን ያህል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤ » ብለው የሚዘምሩላትም ይህን ምሥጢር በልቡናቸው ቋጥረው ነው ። እንኳን ፡ ለዓለም ፡ ሁሉ ፡ ደስታን ፡ ወዳመጣችው ዕለት ፡ አደረሳችሁ ፡ አደረሰን
940
17
#ማርያም_መግደላዊት #ነሐሴ_6_ቀን ማርያም መግደላዊት ሽሙጥን፣ ስድብን፣ መንገላታትንና ግርፋትን ታግሣ መልካሙን ገድል ተጋድላ ሰማዕትነትን ፈጽማ ያረፈችበት ቀን ነው። ይቺ ሴት ቀድሞ ሰባት አጋንን
#ማርያም_መግደላዊት #ነሐሴ_6_ቀን ማርያም መግደላዊት ሽሙጥን፣ ስድብን፣ መንገላታትንና ግርፋትን ታግሣ መልካሙን ገድል ተጋድላ ሰማዕትነትን ፈጽማ ያረፈችበት ቀን ነው። ይቺ ሴት ቀድሞ ሰባት አጋንንት ተቆራኝተዋት ሰባት አይነት ኀጢት ያሠሯት የነበረች ኋላ ግን ክርስቶስ ሰባቱን አጋንንት አስወጥቶላት ከሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት ጋር የቀላቀላት ቅድስት ሴት ናት። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ በተነሣ ጊዜም ትንሣኤውን ለመጀመሪያ ጊዜ የገለጸው ለማርያም መግደላዊት ነበር። ማርያም መግደላዊት ባደረባት እርኩስ መንፈስ ብዙዎችን ስታታልል ስትሸነግል የኖረችና በሐሰት ወጥመድ ጠልፋ የጣለቻቸው ብዙዎች ነበሩ። ማርያም መግደላዊት በእንዲህ ያለ ግብር ጸንታ ለዘመናት ከኖረች በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ወራት አጋንንትንም በሥልጣኑ ያወጣል ብለው ነገሯት። ጥሪው የእግዚአብሔር ነውና ማርያም መግደላዊት ፈጥና ወደ እርሱ ሄደች ጌታችንም ባያት ጊዜ ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ነውና በፍቅር አቀረባት። በቸርነቱም ከራስ ጸጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ የሞሉትን ሰባት ነገደ አጋንንትን ጠራርጎ አስወጣላት። በዚያች ሰዓት ዕለቱኑ እንደተወለደ ሕፃን ከነበረባት ችግር ሁሉ ንጹሕ ሆነች ከዚህች ቀን ጀምሮ ፍጹም ተቀየረች እርምጃዋ ሁሉ የተባረከና የንጽሕና ሆነ። በሃምሳኛው ቀንም መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ «በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮቹ ላይ ቅዱስ መንፈሴን አሳድራለሁ» ብሎ በኢዩኤል ላይ አድሮ ትንቢት እንደ ተናገረ ከሐዋርያት ጋር ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ጸጋና በረከት የተካፈለች ቅድስት ሴት ናት። በመጨረሻም ማርያም መግደላዊት የሐዲስ ኪዳን ዲያቆናዊት ሴት ስትሆን ክርስትናንም ተዟዙራ ሰብካለች። የቅድስት መግደላዊት ማርያም ጸሎቷና በረከቷ አይለየን!🙏
1 048
18
#ወንጌላዊ_ቅዱስ_ዮሐንስ ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን በጌታችን እግረ መስቀል ስር እስከ መጨረሻው በመጽናት የተገኝ ታማኝ ሐዋርያ ነው ። ለዚህም እንደሽልማት ከኃዘኑም ይጽናና ዘንድ ጌታችን
#ወንጌላዊ_ቅዱስ_ዮሐንስ ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን በጌታችን እግረ መስቀል ስር እስከ መጨረሻው በመጽናት የተገኝ ታማኝ ሐዋርያ ነው ። ለዚህም እንደሽልማት ከኃዘኑም ይጽናና ዘንድ ጌታችን በመስቀል ላይ ሆኖ እመቤታችንን ለቅዱስ ዮሐንስ በእናትነት ሰቶታል ለእሱም ብቻም አይደለም ለእኛም ለሁላችንም በእሱ ምሳሌነት እናት ትሆነን ዘንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰቶናል ። ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን ወደ ቤቱ ከወሰዳት በኃላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከጌታችን ጋር የነበራትን ታሪክ ስትነግረው እሱም ሲያገለግላት 15 ዓመት በእሱ ቤት ቆይታለች ። በቆይታቸውም እንደ ሰኔ ጎለጎልታ እና ራዕይ ማርያም ያሉ መጽሐፍትን ከእሷ እየሰማ እንደጻፈ ብዙ የቤተ ክርስቲያናችን መጸሐፍት ይናገራሉ ። ፍ ቁ ረ : እ ግ ዚ እ : የ ተ ባ ለ : የ ቅ ዱ ስ : ዮ ሐ ን ስ : ወ ን ጌ ላ ዊ : በ ረ ከ ቱ : ረ ድ ኤ ቱ : ከ ሁ ላ ች ን : ጋ ር : አ ድ ሮ : ለ ዘ ላ ለ ም : ይ ኑ ር ።
1 094
19
没有文字...
1 236
20
"+የአንቺን ደም ግባት ማመስገን እንዴት ይቻለኛል+" ❤አንቺ ሙሽራ ነሽ፡፡ ዐይኖችሽም እንደሚያንጸባርቅ የኮከብ አወጣጥ ያስደስታሉ፡፡ ❤ጉንጮችሽም በሰሜናዊ ምሥራቅ በወጣ ጊዜ እንደሚያበራ እንደ ሚያ
"+የአንቺን ደም ግባት ማመስገን እንዴት ይቻለኛል+" ❤አንቺ ሙሽራ ነሽ፡፡ ዐይኖችሽም እንደሚያንጸባርቅ የኮከብ አወጣጥ ያስደስታሉ፡፡ ❤ጉንጮችሽም በሰሜናዊ ምሥራቅ በወጣ ጊዜ እንደሚያበራ እንደ ሚያዝያ ፀሐይ ናቸው፡፡ ❤አንገ ትሽም በዝሆን ቀንድ እንደተሠራ እንደዳዊት ቤት ነው፡፡ ❤ሆድ ሽም ሥንዴ የተጨመረበት በአበባም የታጠረ ነው፤ ❤ጣቶች ሽም የሚያማምሩ፣ በወርቅም የተለበጡ ናቸው፡፡ .......ያንችን ደምግባት የአንቺን ማማር ማመስገን እንዴት ይቻለኛል፡፡ የፊትሽ ደም ግባት ቀይ ነው፡፡ ድንግል ሆይ በውዳሴ አመሰግንሻለሁ፡፡ የአፍሽ ሽታ ከሽቱ መዓዛ ይልቅ ያስደስታል፡፡ =======አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ====
1 241