ch
Feedback
የቅዱሳን ታሪክ

የቅዱሳን ታሪክ

前往频道在 Telegram

በዚህ ቻናል ውስጥ፦ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ የሚገኙ ስዕላትን የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ስዕላት የአድባራት እና የገዳማት ፎቶዎችን ያገኛሉ የተለያዩ ስዕለ አድዕኖ ለመላክ @kidanemiherat_bot

显示更多
8 561
订阅者
+224 小时
-27 天
-4930 天
帖子存档
photo content
+4

« አ ሁ ን ፡ አ ረ ፈ ች ፡ እ ህ ት ሽ ፡ ኤ ል ሳ ቤ ጥ » #መስከረም_ሰባት_ቀን_ቅድስት_ኤልሳቤጥ_ዐረፈች ቅድስት ኤልሳቤጥ የቅዱስ ዮሐንስ እናት የጽድቅ እመቤት ከመሆኗም በላይ የቅድስት ድንግል ማርያም የቅርብ ዘመድ በትሕትናዋ የምትወደድ ደገኛ ሴት ናት ። ሰውነቷ ከኀጢአት ንግግሯ ከትዕቢትና ከስሕተት የታረመ በመንፈስ ቅዱስ የተቀመመ ከቅዱስ ገብርኤል ቀጥላ ስለወላዲተ አምላክ ስለ ድንግል ማርያም ማንነት የመሰከረች በዘመኑ ለነበሩ ማኅበረሰብ ወንጌልን የሰበከች የመጀመሪያዋ የሴት ሐዋርያ የሆነች ክብርት ሴት ናት ቅድስት ኤልሳቤጥ ። በዝምድና አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የእናቷ እኅት ልጅ ናት ይችንም ቅድስት ኤልሳቤጥ ካህኑ ዘካርያስ አገባት የከበረ ወንጌልም ኹለቱም ያለ ነውር ያለ ነቀፋ በእግዚአብሔር ሕግ ጸንተው የሚኖሩ እውነተኞችና ጻድቃን ሆነው እንደኖሩ መስክሮላቸዋል ። ኤልሳቤጥ መካን ስለሆነች ወደ እግዚአብሔር የሚለምኑና የሚማልዱ ሆኑ አርጅተውም የመውለጃቸው ዘመን ባለፈ ጊዜ እግዚአብሔር መልአኩን ገብርኤልን ወደ ዘካርያስ ልኮ ልመናቸው እንደ ተሰማና ዮሐንስን እንደሚወልዱ አበሠረው ። ከዚህም በኋላ ቅድስት ኤልሳቤጥ መጥምቁን ዮሐንስን ፀንሳ ወለደች ከሰዎችም የሚደርስባት ሽሙጥ ተወግዶ እጅግ ደስ አላት ሕፃኑም በማሕፀኗ እያለ እመቤታችን ድንግል ማርያም ሰላምታ በሰጠቻት ጊዜ እንዲህ ብላ ጮኸች ፦ « አንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሸ የተባረክሽ ነሽ የማኅፀንሽም ፍሬ ቡሩክ ነው የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እኔ ምንድን ነኝ እነሆ እንዴት ነሽ ስትይኝ የሰላምታሽን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ልጁ በማኅፀኔ ውስጥ በደስታ ዘለለ»ብላ የእመቤታችንን ወላዲተ አምላክነትን መሰከረች ። ከዚህም በኋላ ጌታችንን አየችው በአምላክነቱም አመነች የሚያምኑበት በመዳናቸው ደስ አላት ስትል መስክራለች ኤልሳቤጥ ልጅዋን ዮሐንስን ከሄሮድስ ሰይፍ ለማሸሽ በስደት በሐቅለ ዮሳፍጥ እንዳለች ከዚህ ዓለም #መስከረም_ሰባት_ቀን_ዐርፋለች። እመቤታችን ተወዳጅ ልጇን አዝላ አረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜን አስከትላ ሦስት ዓመት ከመንፈቅ በስደት ኖራ ከኢትዮጵያ ተነሥታ በመስከረም ወር ግብፅ ገባች ፤ በሐቅለ ዮሳፍጥ አቋርጠው ሲሄዱ ሕፃኑ ኢየሱስ ክርስቶስ #አሁን_አረፈች_እህትሽ_ኤልሳቤጥ እያለ በሕፃን አንደበቱ እየደጋገመ ቅድስት ኤልሳቤጥ ወዳረፈችበት ቦታ በጣቱ እየጠቆመ ያሳያቸው ጀመር ። እነርሱም ወደ ጠቆማቸው ቦታ ቢሄዱ ቅድስት ኤልሳቤጥ አርፋ ልጇ ዮሐንስ ሙት የሆነውን የእናቱን ጡት ሲገጠግጥ አገኙት ፤ ዮሐንስ ሰው አይቶ ስለማያውቅ ምን መጣብኝ ብሎ ደንግጦ ከዱር ገባ ፤ እመቤታችን አረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜ አልቅሰው መቃብሩን የታዘዘ አንበሳ መጥቶ ቆፍሮላቸው በዚያ በዮሳፍጥ በረሃ አጥበው ገንዘው ቀብረዋት ሔደዋል ። እመቤታችን አረጋዊ ዮሴፍን ዮሐንስን አባብለው ከተደበቀበት ዱር ጫካ እንዲያመጣው ልትልከው ስትል ሕፃኑ ክርስቶስ « ተውት እሺ አይላችሁም ጊዜው አልደረሰም ሠላሳ ዘመን ሲሞላው እርሱ ራሱ በክብር ይገለጣል ከፊቴ እየቀደመ የንስሐ ትምህርትን እያስተማረ መንገዴን የሚጠርገው እርሱ ነው » አላቸው ከዚያም ትተውት ሔደዋል ። ዮሐንስም ሠላሳ ዘመን እስኪሞላው ድረስ በዚያው በተሰደደበት በረሃ አድጓል ኤልሳቤጥ የቅድስት ድንግል ማርያምን ወላዲተ አምላክነትን በማብሠር የመጀመሪያ ሴት ሐዋርያዊት ስትሆን ልጇ ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ የክርስቶስን የባሕርይ አምላክነትን በማብሠር የመጀመሪያ ሐዋርያ ሆኗል ። በዚህም እናትና ልጅ በተመሳሳይ ሰዓት ተመሳሳይ ምስክርነትን በመስጠት ከመላእክት ቀጥሎ ከሰው ዘር አስቀድሞ የሥጋዌን ምሥጢር ገበታ በመቅመስ የመጀመሪያና ብቸኛ ናቸው ። ቅዱስ ያሬድ የእናትና የልጅን ሕይወት እንዲሁም የሰጡትን ምስክርነት በድጓው እንዲህ ሲል ዘምሮላቸዋል « ኤልሳቤጥ ማርያምን ቃልሽን በሰማሁ ጊዜ በማኅፀኔ ያለው ልጅ በደስታ ዘለለ አንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሸ የተባረክሽ ነሽ አለቻት መልአኩም ኤልሳቤጥን ተናገራት የዮሐንስን እናት እንዲህ አላት ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ የሚያሰክር ወይንና ጠጅን አይጠጣም መንፈስ ቅዱስ በላዩ ላይ ያድርበታል ( ይመላበታል ) የሙሽራው ወዳጅ ይባላል » በማለት ቅድስት ኤልሳቤጥ የወለደችው የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነ ጻድቅና ነቢይ መሆኑን በድጓው ዘምሯል ።

Story

ር እ ሰ : ዐ ው ደ : ዓ መ ት ና : ቅዱስ : ዮ ሐ ን ስ የቅዱስ ዮሐንስ መታሰቢያ በዓል ከርእሰ ዐውደ ዓመት በዓል ጋር በአንድ ቀን እንዲከበር የተደረገበት ምክንያት የርእሰ ዐውደ ዓመት ወይም የዘመን መለወጫ በዓል ለአሮጌው ዓመት መጨረሻ፣ ለአዲሱ ዓመት መነሻ በመሆን ለጊዜ አቆጣጠር የሚያገለግል ስለሆነ ነው ። ከዚህ መሠረታዊ ተግባር የተነሣ የቅዱስ ዮሐንስ ታሪክ ከዘመን መለወጫ ጋር በንጽጽራዊ ምሥጢር ብዙ የሚያመሳስለው ነገር ስላለ ነው ። ቅዱስ ዮሐንስ የተፀነሰው መስከረም ወር ውስጥ መሆኑ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ « በስድስተኛው ወር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደ ድንግል ማርያም ተላከ» ብሎ ነግሮናል ( ሉቃ 1፥ 26 ) ። ቅዱስ ገብርኤል መጋቢት 29 ቀን ድንግል ማርያም በድንግልና እንደምትፀንስ ባበሠራት ጊዜ እመቤታችን እንደምን ይሆንልኛል ባለችው ሰዓት ኤልሳቤጥ እንኳ ካረጆች ከሸመገለች በኋላ ከፀነሰች 6 ወር ሆኗታል›› በማለት ዮሐንስ በተፀነሰ በስድስት ወሩ እመቤታችንን እንዳበሠራት እንረዳለን ፡፡ ይህ ከሆነ ከመጋቢት 29 ቀን ጀምረን ወደ ኋላ ብንቆጥር 6ኛው ወር መስከረም ስለሆነ ዮሐንስ የተፀነሰው በመስከረም ወር እንደሆነ እንገነዘባለን ። ከዚህ በመነሣት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመስከረም 1 ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም 8 ቀን የቅዱስ ዮሐንስ መታሰቢያ በዓል ብላ ታከብራለች ። የዮሐንስ መፀነስ በወርኃ መስከረም መሆኑን ለማስገንዘብ መስከረም 8 ቀን የወላጆቹን የካህኑ ዘካርያስና የቅድስት ኤልሳቤጥን በዓል ከፅንሰተ ዮሐንስ ጋር በማስተባበር ታከብራለች ፡፡ ስለዚህ መስከረም አንድ ቀን ለአሮጌው ዘመን መጨረሻ ለአዲሱ ዓመት ደግሞ መጀመሪያ ከመሆኑ አንጻር በሕዝብ የሚያሳድረውን ደስታ በማነጻጸር ‹‹ በልደቱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል ›› በተባለለት በቅዱስ ዮሐንስ እለቱን ሰይማ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታከብረዋለች ። እንዲሁም ቅዱስ ዮሐንስ የብሉይ ኪዳን ሥርዓት ማክተሙንና የሐዲስ ኪዳን ሥርዓት መተካቱን በስብከቱ ማወጅ የጀመረበት ወርኃ መስከረም ነው ። መስከረም አንድ ቀን ደግሞ የአሮጌው ዓመት ማብቂያ የአዲሱ ዓመት ደግሞ መጀመሪያ እንደሆነ ሁሉ የብሉይ ኪዳን ሥርዓት እንዳከተመና በምትኩ የሐዲስ ኪዳን ሥርዓት እንደተተካ የሚያበሥረው የቅዱስ ዮሐንስ ስብከት በመሆኑ በይዘቱና በምሥጢሩ ከርእሰ ዐውደ ዓመት ጋር እንዲከበር ሆኖአል ። በእግዚአብሔር : ፊት : የምትሔድ : ዮሐንስ : ሆይ : አንተ : ንዑድ : ክቡር ነህ : ስለእኛ : ጸልይ : መታስቢያህ : በርእሰ : ዐውደ : ዓመት : ተጻፈ (ታሰበ) በረከትህን : እንቀበል : ዘንድ : ባርከን ።

ቅ ዱ ስ : ራ ጉ ኤ ል ን #መስከረም_አንድ_ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ራጉኤል ከዘጠኙ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን በክብርና በጸጋ ልቆ የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመበት በዓለ ሲመቱ ሲሆን በኢት
ቅ ዱ ስ : ራ ጉ ኤ ል ን #መስከረም_አንድ_ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ራጉኤል ከዘጠኙ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን በክብርና በጸጋ ልቆ የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመበት በዓለ ሲመቱ ሲሆን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዘንድ በታላቅ ድምቀት ይከበራል። ይህ ቅዱስ መልአክ የፀሐይን ሥነ ፍጥረት ለነቢዩ ለሄኖክ እንደተረጎመለት በመጽሐፈ ሄኖክ ምእራፍ 6 ላይ በግልጽ ተመልክቶ እናገኛለን። ቅዱስ ራጉኤል በብርሃናት አሠራርና ዑደት ላይ ሥልጣን የተሰጠው መጋቤ ብርሃናት ከመሆኑም በላይ የዚህን ዓለም የጨለማው ገዢ ዲያብሎስን ለመበቀልና ለመቅጣት ፍፁም ሥልጣን የተሰጠው ታላቅ መላእክ ነው ። ቅዱስ ራጉኤል ታላቅ ሥልጣን ያለው፣ ከክብሩ፣ ከብርሃነ-ረድኤቱና ከጸጋው ምልዓት የተነሳ ምድርን ሁሉ ለማብራት ማለትም ለማዳን የሚችል መሆኑን እንረዳለን ፡፡ ከታላቅ ሥልጣኑና ከብርሃነ ክብሩ ተካፋይ ለመሆን በተሰጠው ቃል ኪዳን ከሰው ልጆች ጠላት ከዲያብሎስ ስውር ወጥመድ ለመዳን በክንፈ ረድኤቱ ጠብቆ በንስሐ ወደ እግዚአብሔር የምሕረት ዙፋን እንድንቀርብ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤልን ፍጹም ተራዳኢነት አይለየን።

🌼🌼🌼🌼🌼🌼አሥርቆት🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ሃሌ ሉያ በዘንዜከር ሐሳባተ ሕጉ ወዓመታቲሁ ወትእዛዛቲሁ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ 🌼ሐሳበ ነቢያት ወሐዋርያት🌼 🌼ሐሳበ ጻድቃን ወሰማዕት🌼 🌼ሐሳበ ደናግል ወመነኮሳት🌼 🌼ሐሳበ ኄራን ወትጉሃን መላእክት🌼 እንዘ ሀሎነ በዘመነ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ቡሩክ ያብጽሐነ እስከ ዘመነ ቅዱስ ዮሐንስ ዜናዊ በፍስሓ ወበሐሴት በሰላመ እግዚአብሔር አሜን ሐምሳ ምዕት ወሐምስቱ ምዕት ኮነ ዓመተ ፍዳ ዓመተ ኩነኔ ዕሥራ ምዕት አሠርቱ ወተሥዓቱ ኮነ ዓመተ ምሕረት ወሥጋዌ ሰብዓ ምዕት ወሐምስቱ ምዕት አሠርቱ ወተሥዓቱ ኮነ ዓመተ ዓለም ዮም ሠረቀ ለነ ወርኃ መስከረም በዕለተ ዓርብ ቡሩክ ያብጽሐነ እስከ ወርኃ ጥቅምት በሰላመ እግዚአብሔር አብ አሜን 🌻ዕሥራ ወሐሙሱ ሠርቀ ሌሊት 🌻ዕሥራ ወተሥዑ ሠርቀ ወርህ 🌻ሰዱሱ ጥንተ ዕለት 🌻ረቡዑ ጥንተ ቀመር 🌻ሠሉሱ ጥንተ ዖን 🌻አሚሩ ሠርቀ መዓልት ዮም ትዕርግ ጸሎትነ በኩሉ ጊዜ ወበኩሉ ሰዓት ዝ ጸሎት ወዝ ሥዕለት ወዝ አስተብቊዖት ይዕርግ በእንተ ስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ 🌞ዝ ጸሎት ወዝ ሥዕለት ወዝ አስተብቊዖት ይዕርግ በእንተ ስማ ለእግትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ 🌞ዝ ጸሎት ወዝ ሥዕለት ወዝ አስተብቊዖት ይዕርግ በእንተ ስሙ ለቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት 🌞ዝ ጸሎት ወዝ ሥዕለት ወዝ አስተብቊዖት ይዕርግ በእንተ ተዝካረ ኲሎሙ ቅዱሳን 💥አዋጅ🎺📢 አዋጅ🎺📢 አዋጅ🎺📢 ማርቆስ ተሻረ ሉቃስ ተሾመ 💥አዋጅ🎺📢 አዋጅ🎺📢 አዋጅ🎺📢 ማርቆስ ተሻረ ሉቃስ ተሾመ 💥አዋጅ🎺📢 አዋጅ🎺📢 አዋጅ🎺📢 ማርቆስ ተሻረ ሉቃስ ተሾመ እግዚአብሔር ሆይ የሚሳንህ ነገር የለምና የራቀውን አቅርበህ የረቀቀውን አጉልተህ እየሰማነው ካለነው መርዶና ሰቀቀን ዕረፍተ ሥጋንና ዕረፍተ ነፍስን አትንሣን ስለ ሰላም፣ ሀገራችን፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ በጭንቅ በመከራ ስላሉት፣ በረሀብ በስደት ስላሉት፣ በጽኑ ሕመም ተይዘው ስለሚሰቃዩት፣ ሃይማኖት መሪዎች፣ ሀገር መሪዎች እንጸልይ የሰላም የምሕረት የቸርነት ባለቤት እግዚአብሔር ሰላሙን ምሕረቱን ቸርነቱን አይንሳን 🤲አቡነ ዘበሰማያት......ይቆየን🤲

፩፦ ከነነዌ ጾም እስከ ዐቢይ ጾም 14 ቀናት አሉ። ስለዚህ የዐቢይ ጾም ተውሳክ 14 ይሆናል፡፡ ፪፦ ከነነዌ እስከ ደብረዘይት 41 ቀናት አሉ፡፡ 41 ፥ 30 = 1 ደርሶ ቀሪው 11 የደብረ ዘይት ተውሳክ ይሆናል፡፡ ፫፦ ከነነዌ እስከ ሆሣዕና 62 ቀናት አሉ፡፡ 62 ፥ 30 = 2 ደርሶ ቀሪው 2 የሆሣዕና ተውሳክ ይሆናል፡፡ ፬፦ ከነነዌ እስከ እስከ ስቅለት 67 ቀናት አሉ፡፡ 67 ፥ 30 = 2 ደርሶ ቀሪው 7 የስቅለት ተውሳክ ይሆናል፡፡ ፭፦ ከነነዌ እስከ ትንሣኤ 69 ቀናት አሉ፡፡ 69 ፥ 30 = 2 ደርሶ ቀሪው 9 የትንሣኤ ተውሳክ ይሆናል፡፡ ፮፦ ከነነዌ እስከ ርክበ ካህናት 93 ቀናት አሉ፡፡ 93 ፥ 30= 3 ደርሶ ቀሪው 3 የርክበ ካህናት ተውሳክ ይሆናል፡፡ ፯፦ ከነነዌ እስከ ዕርገት 108 ቀናት አሉ፡፡ 108 ፥ 30 = 3 ደርሶ ቀሪው 18 የዕርገት ተውሳክ ይሆናል፡፡ ፰፦ ከነነዌ እስከ ጰራቅሊጦስ 118 ቀናት አሉ፡፡ 118 ፥ 30 = 3 ደርሶ ቀርው 28 የጰራቅሊጦስ ተውሳክ ይሆናል፡፡ ፱፦ ከነነዌ እስከ ጾመ ሐዋርያት 119 ቀናት አሉ፡፡ 119 ፥ 30 = 3 ደርሶ ቀሪው 29 የጾመ ሐዋርያት ተውሳክ ነው፡፡ ፲፦ ከነነዌ እስከ ጾመ ድኅነት 121 ቀናት አሉ፡፡ 121 ፥ 30 = 4 ደርሶ ቀሪው 1 ሲሆን የጾመ ድኅነት ተውሳክ 1 ይሆናል፡፡ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ከዚህ ተነስተን አጽዋማትንና በዓላትን ተውሳኮቻቸውን ከነነዌ ጋር (ከዘመኑ መባጃ ሐመር) ጋር እየደመርን እናገኛለን፡፡ ስለዚህ የ2019 የነነዌ ጾም መግቢያ የካቲት 15 ቀን ይሆናል፡፡ 7 + 8 = 15 ስለሆነ ነው፡፡ 🌼ዐቢይ ጾም ተውሳኩ 14 ነው = 14 + 15 = 29 ይህ ከ30 ያነሰ ቁጥር ስለሆነ ሳንገድፍ እንዳለ እንወስደዋለን ስለዚህ ዘንድሮ በዘመነ ሉቃስ ዐቢይ ጾም የካቲት 29 ሰኞ ይገባል ማለት ነው፡፡ 🌼ደብረ ዘይት ተውሳኩ 11 ነው፡፡ 11 + 15 = 26 ይህ ከ30 ያነሰ ቁጥር ስለሆነ ሳንገድፍ እንዳለ እንወስደዋለን ነገር ግን የካቲትን በዐቢይ ጾም መግቢያ "29" ስላለፍን በመጋቢት 26 እሑድ ደብረ ዘይት ይሆናል። 🌼ሆሣዕና ተውሳኩ 2 ነው፡፡ = 2 + 15 = 17 ይህ ከ30 ያነሰ ቁጥር ስለሆነ ሳንገድፍ እንዳለ እንወስደዋለን ነገር ግን መጋቢትን በደብረ ዘይት ስላለፍን ሚያዚያ 17 በቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ🥰 እሑድ ሆሳዕና ይሆናል፡፡ 🌼ስቅለት ተውሳኩ 7 ነው፡፡ 7 + 15 = 22 ይህ ከ30 ያነሰ ቁጥር ስለሆነ ሳንገድፍ እንዳለ እንወስደዋለን ስለዚህ ዘንድሮ በሚያዝያ 22 ዓርብ ስቅለት ይሆናል፡፡ 🌼ትንሣኤ ተውሳኩ 9 ነው፡፡ 9 + 15 = 24 ይህ ከ30 ያነሰ ቁጥር ስለሆነ ሳንገድፍ እንዳለ እንወስደዋለን ስለዚህ ሚያዝያ 24 በጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት🥰 በዓለ ትንሣኤ ይውላል። 🌼ርክበ ካህናት ተውሳኩ 3 ነው፡፡ 3 + 15 = 18 ይህ ከ30 ያነሰ ቁጥር ስለሆነ ሳንገድፍ እንዳለ እንወስደዋለን ነገር ግን ሚያዝያን ስለጨረስን በግንቦት 18 ረቡዕ ርክበ ካህናት ይሆናል። 🌼ዕርገት ተውሳኩ 18 ነው፡፡ 18 + 15 = 33 ይህ ከ30 የሚበልጥቁጥር ስለሆነ በ30 እንገድፈዋለን 33 ፥ 30 = 1 ይደርስና 3 ይቀራል ስለዚህ ግንቦትን ሰለጨረስን ዘንድሮ ሰኔ  3 በታላቁ መልአክ በቅዱስ ፋኑኤል🥰🥰 ወርኀዊ በዓል ሐሙስ በዓለ ዕርገት ይሆናል። 🌼ጰራቅሊጦስ ተውሳኩ 28 ነው፡፡ 28 + 15 = 43 ይህ ከ30 የሚበልጥ ቁጥር ስለሆነ በ30 እንገድፈዋለን 43 ፥ 30 = 1 ይደርስና 13 ይቀራል ስለዚህ ሰኔ 13 በቅዱስ ሩፋኤል🥰😍 እሑድ በዓለ ጰራቅሊጦስ ይውላል። 🌼ጾመ ሐዋርያት ተውሳኩ 29 ነው፡፡ 29 + 15 = 44 ይህ ከ30 የሚበልጥ ቁጥር ስለሆነ በ30 እንገድፈዋለን 44 ፥ 30 = 1 ይደርስና 14 ይቀራል በሰኔ 14 ሰኞ የሐዋርያት ጾም ይገባል። 🌼ጾመ ድኅነት ተውሳኩ 1 ነው፡፡ 1 + 15 = 16 በመሆኑ ጾመ ድኅነት (የረቡዕና ዓርብ ጾም) ሰኔ 16 ረቡዕ ይገባል። ከላይ እንዳየነዉ የ2019 ዓ.ም የበዓላት እና አጽዋማት ሰንጠረዥ እንደሚከተለዉ ተለይቶ ቀርቧል። ፩, ዓመተ ዓለም =7519 ፪, ወንጌላዊ = ቅዱስ ሉቃስ ፫, ዕለተ ቀመር = ዓርብ መስከረም ፩ ፬, መደብ = ፲፬ ፭, ወንበር = ፲፫ ፮, አበቅቴ = ፳፫ ፯, መጥቅዕ = ፰, መባጃ ሐመር = ፲፭ ፱, ጾመ ነነዌ = የካቲት ፲፭ዐቢይ ጾም = የኳቲት ፳፱ ፲፩, በዓለ ደብረ ዘይት= መጋቢት ፳፮ ፲፪, በዓለ ሆሳዕና = ሚያዝያ ፲፯ ፲፫, በዓለ ስቅለት = ሚያዝያ ፳፪ ፲፬, በዓለ ትንሳኤ = ሚያዝያ ፳፬ ፲፭, ርክበ ክህናት = ግንቦት ፲፰ ፲፮, በዓለ ዕርገት = ሰኔ ፫ ፲፯, በዓለ ጰራቅሊጦስ = ሰኔ ፲፫ ፲፰, ጾመ ሐዋርያት = ሰኔ ፲፬ ፲፱, ጾመ ድኅነት = ሰኔ ፲፮ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 አምላካችን እግዚአብሔር በአዲሱ ዓመት አዲስ ልብና ቀና መንፈስ ያድለን የስደት፣ የርኃብ፣ የጦርነት፣ የሞት፣ የዕልቂት እና የጭንቅ ጊዜያትን ያሳጥርልን የፍሥሓ የሰላም የይቅርታ የንሥሓ ዘመን ያድርግልን። "#ባርክ_ለነ_እግዚኦ_ዘንተ_ዓመተ_ምሕረትከ_በብዛኅ_ኂሩትከ_ለሕዝብከ_ኢትዮጵያ_ከመ_ንግነይ_ለስምከ_ቅዱስ_በከመ_ይኩን_ንብረተነ_በሰላም_ወበዳኅና_በዝንቱ_ዓመት" እንኳን አደረሳችሁ መልካም አውደ ዓመት መምህር ሳዶር ሲሳይ ጳጒሜ ፭ ፳፻፲፰ ዓ.ም አ.አ ኢትዮጵያ

🌼🌼🌼የ2019 ዓ.ም ባሕረ ሐሳብ🌼🌼🌼 #የበዓላት_እና_አጽዋማት_ስሌት_ሰሌዳ #ዓመተ_ዓለም = ዓመተ ኩነኔ (ፍዳ) + ዓመተ ምሕረት 5500 + 2019 = 7519 ዓ.ዓ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #ወንጌላዊ = በዓመቱ የሚሾመዉ ወንጌላዊ ዓመተ ዓለም ፥ 4 7519 ፥ 4 = 1879 ደርሶ 3 ይቀራል 1879 = መጠነ ራብዒት ይባላል 1879 × 4 =7516 ፤ 7519 - 7516 = ቀሪ 3 ይሆናል ስለዚህ 7519 ፥ 4 1879 ደርሶ ቀሪ 3 ይሆናል ቀሪው ' 1 ' ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ማቴዎስ ቀሪው ' 2 ' ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ማርቆስ ቀሪው ' 3 ' ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ሉቃስ ቀሪው ' 0 ' ከሆነ (ያለ ቀሪ ከተካፈለ)ዘመኑ ዘመነ ዮሐንስ ይሆናል። 🌼ስለዚህ ቀሪው '3' ስለሆነ የዘንድሮው ወንጌላዊ ሉቃስ ሲሆን ዘመኑ ዘመነ ሉቃስ ይባላል። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #ዕለተ_ቀመር = መስከረም አንድ የሚውልበት ቀን ነው፡፡ ዕለተ ቀመር = ዓመተ ዓለም + መጠነ ራብዒት ፥ 7 = 7519 + 1879 = 9398 = 9398 ፥ 7 = 1342 ደርሶ ቀሪ 4 ይሆናል ቀሪው '0 'ከሆነ ሰኞ ቀሪው '1' ከሆነ ማክሰኞ ቀሪው '2 'ከሆነ ረቡዕ ቀሪው '3 'ከሆነ ሐሙስ ቀሪው '4 'ከሆነ ዓርብ ቀሪው '5 'ከሆነ ቅዳሜ ቀሪው '6 'ከሆነ እሑድ መባቻ ይሆናል። በመሆኑም ዘንድሮ ቀሪው '4' ስለሆነ ዕለተ ቀመር ዓርብ ይሆናል። ( አዲስ ዓመት በዓል ዓርብ ነው) 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #መደብ = ዓመተ ዓለምን በዐቢይ ቀመር (532) በማዕከላዊ ቀመር (76) እና በንዑስ ቀመር (19) በማካፈል ማግኘት እንችላለን ፩. 7519 ፥ 532= 14 ደርሶ ቀሪ 71 ፪. 69 ለ ማዕከላዊ ቀመር ወይም ለ 76 መካፈል ስለማይችል ቀጥታ ለንዑስ ቀመር (19) ይካፈላል። 71 ፥19 = 3 ደርሶ 14 ይቀራል። ስለዚህ #መደብ 14 ይሆናል፡፡ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #ወንበር = መደብ ሲቀነስ አንድ ነው (አሐደ አእትት ለዘመን የሚል አዋጅ አለና ላለፈው መሸኛ ለሚመጣው መቀበያ) ነው። መደብ - 1= ወንበር (14 - 1= 13) ይሆናል። በዚህም መሠረት #ወንበር 13 ነው እንላለን። #አበቅቴ = ጥንተ አበቅቴን በዘመኑ ወንበር አባዝተን ከ 30 በላይ ከሆነ በ30 ገድፈን ቀሪውን ከ30 በታች ከሆነ ደግሞ የመጣውን ቁጥር በመጠቀም እናገኛለን። አበቅቴ =11 × 13 =143፤ 143 ፥ 30 = 4 ደርሶ ቀሪው 23 ይሆናል ስለዚህ የዘንድሮው አበቅቴ 23 ነው እንላለን። አበቅቴን ለማግኘት ሌላው አማራጭ  ያለፈው ዘመን አበቅቴ ላይ ጥንተ አበቅቴን  (11) በመጨመር የሚገኘው ቁጥር ከ30 በላይ ከሆነ ለ 30 በማካፈል ቀሪውን ከ30 በታች ከሆነ ደግሞ የመጣውን ቁጥር በመጠቀም ማግኘት እንችላለን። ይህም ማለት የ2018 ዓ.ም አበቅቴ 12 ነበር፤ ስለዚህ የ2019 ዓ.ም አበቅቴን ለማግኘት 12 + 11= 23 ይህንም ከ30 በታች ስለሆነ እንዳለ እንወስደዋለን በዚህም አበቅቴ '23' ይሆናል ማለት ነው። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #መጥቅዕ = ጥንተ መጥቅዕን በዘመኑ ወንበር አባዝተን በ 30 በመግደፍ (በማካፈል) እናገኛለን። መጥቅዕ = 19×13 = 247 247 ፥ 30 = 8  ደርሶ ቀሪው '7' ይሆናል ስለዚህም መጥቅዕ ዘንድሮ '7' ወጥቷል። መጥቅዕን ለማግኘት ሌላው አማራጭ ያለፈውን ዘመን መጥቅዕ ከጥንተ መጥቅዕ ላይ ( 19 ) በመጨመር የሚገኘው ቁጥር ከ30 በታች ከሆነ ራሱ ከ30 በላይ ከሆነ ለ 30 ተካፍሎ ቀሪው የዘመኑ መጥቅዕ ይሆናል። ይህም ማለት የ2018 ዓ.ም መጥቅዕ 18 ነበር ስለዚህ የ2019 ዓ.ም መጥቅዕን ለማግኘት 18 + 19 = 37  ከሰላሳ በላይ ስለመጣ እንገድፈዋለን 37 ፥ 30 =1 ደርሶ ቀሪ 7 ይመጣል ስለዚህ የ2019 ዓ.ም መጥቅዕ '7' ይሆናል ማለት ነው። “አበቅቴ ወመጥቅዕ ክልዔሆሙ ኢይበዝኁ እም ሠላሳ ወኢይወርዱ እም ሠላሳ ወትረ ይከዉኑ ሠላሳ ፤ አበቅቴ ቢበዛ መጥቅዕ ቢያንስ መጥቅዕ ቢበዛ አበቅቴ ቢያንስ ከሠላሳ አይበዙም ከሠላሳ አያንሱም” ይህም ማለት በሌላ አገላለጽ መጥቅዕና አበቅቴ ተደምረዉ ውጤቱ ከሠላሳ መብለጥና ማነስ የለበትም፤ ሁልጊዜ ሠላሳ ይሆናል የሚለዉን አዋጅ ማስታወስ ይገባል፡፡ የዘንድሮዉ የ2019 ዓ.ም = 23 + 7 = 30 መጥቷል። መጥቅዕ ከ14 በላይ ከሆነ በመስከረም ይዉላል፤ መጥቅዕ ከ14 በታች ከሆነ በጥቅምት ይዉላል፤ መጥቅዕ በመስከረም ቢዉል ጾመ ነነዌ በጥር፣ መጥቅዕ በጥቅምት ቢዉል ጾመ ነነዌ በየካቲት ይውላል። ስለዚህ በዚህ ዓመት መጥቅዕ 7 ስለሆነ ከ14 ያንሳል፤ ስለዚህም መጥቅዕ በጥቅምት ውሏል። ስለዚህ የ2019 መጥቅዕ ጥቅምት 7 ሲሆን መጥቅዕ የሚወድቅበት ዕለት (ዕለተ መጥቅዕ) ቀዳሚት ሰንበት (ዕለተ ቅዳሜ) ይሆናል፡፡ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #መባጃ_ሐመር = የዘመኑ መጥቅዕ + መጥቅዕ የወደቀበት የዕለት ተውሳክ  በመጠቀም የሚገኘው ቁጥር ከ 30 በላይ ከሆነ ለ 30 በማካፈል ቀሪውን መባጃ ሐመር እንላለን፡፡ ልብ ይበሉ የዕለታት ተውሳክ ከቅዳሜ ይጀምራል፡፡ የቅዳሜ---8 ፤ የእሑድ---7 ፤ የሰኞ------6 ፤ የማክሰኞ--5 ፤ የረቡዕ------4 ፤ የሐሙስ----3 ፤ የዓርብ ------2 ነው። የዕለታት ተውሳክ የአወጣጥ ስሌቱም የሚከተለውን ይመስላል። ከዕለተ መጥቅዕ ጀምረን እስከ ነነዌ ጾም መግቢያ ስንቆጥር 128 ቀን ይሆናል፡፡ በ30 ብንገድፈዉ 4 ደርሶ ቀሪ 8 ይሆናል፡፡ ይህም የቅዳሜ ተውሳክ ነው። በዚህ ዓይነት ስሌት ስንሄድ መጥቅዕ የሚወድቅበት ዕለት 🌼ቅዳሜ ከሆነ፡- 128፥30= 4 ቀሪ 8 🌼እሑድ ከሆነ፡- 127፥30= 4 ቀሪ 7 🌼ሰኞ  ከሆነ፡- 126፥30=4 ቀሪ 6 🌼ማግሰኞ ከሆነ፡- 125 ፥30= 3 ቀሪ 5 🌼ረቡዕ ከሆነ፡- 124 ፥30= 2 ቀሪ 4 🌼ሐሙስ ከሆነ፡- 123፥ 30= 2 ቀሪ 3 🌼ዓርብ ከሆነ፡- 122፥ 30= 2 ቀሪ 2 ስለዚህ የዕለታት ተውሳክ ቀሪዎቹን በመያዝ ይታወቃል። መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን የዕለት ተውሳክ በመደመር ነው። መባጃ ሐመር= 7 + 8 = 15 ስለዚህ የ2019 ዓ.ም #መባጃ_ሐመር '15' ይሆናል መጥቅዕ ጥቅምት ላይ ስለወደቀና መጥቅዕ የወደቀበት ዕለት ቀዳሚት ሰንበት ስለሆነ የዘመኑ መጥቅዕ 7 እና የቅዳሜ ተውሳክ 8 ድምር  በ15 ስለሆነ 2019 ዓ.ም  ጾመ ነነዌ የካቲት 15 ቀን በዕለተ ሰኞ ይውላል ማለት ነው። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #ጾመ_ነነዌ = መጥቅዕና የዕለቱን ተውሳክ በመደመር በ30 ገድፈን እናገኛለን ይህ ጾም ተውሳክ የለውም የሚወጣውም በደረቅ መባጃ ሐመር ነው። ሌሎችን አጽዋማትና በዓላት ተውሳካቸውን ጾመ ነነዌ የዋለበትን የቀን ቁጥር (መባጃ ሐመር) ደምረን ከ30 ከበለጠ ለ30 እያካፈልን ከ30 በታች ከሆነ ደግሞ ራሱን በመጠቀም እናገኛለን። ስለዚህህ

Story

Story

⏳ 3 ቀን ብቻ ቀረው!! የምድር ጌጥ ኢትዮጵያ በሆላንድ ፓርክ ከነሐሴ 28 እስከ መስከረም 3 ለተከታታይ 10 ቀናት ከልጆችዎ እና ከቤተሰብዎ ጋር በአክብሮት ጋበዝንዎ! 🎫 የመግቢያ ትኬትዎን በኦን
⏳ 3 ቀን ብቻ ቀረው!!
የምድር ጌጥ ኢትዮጵያ በሆላንድ ፓርክ ከነሐሴ 28 እስከ መስከረም 3 ለተከታታይ 10 ቀናት
ከልጆችዎ እና ከቤተሰብዎ ጋር በአክብሮት ጋበዝንዎ! 🎫 የመግቢያ ትኬትዎን በኦንላይን ይቁረጡ!! 👇👇👇 https://tickets.hamereberhan.org/e/jewel-of-the-world-ethiopia-r2xu 📍ሆላንድ ፓርክአድራሻ 👇👇👇 https://maps.app.goo.gl/zHL3ZeXVNFWRV4dq6

ንዒ ርግብየ ሠናይት ነሐሴ ፳፩.mp342.88 MB

እጅግ : ትሑቷ : ድንግል : ማርያም ቅድስት ፣ ድንግል ፣ ንፅህት የሆነች ድንግል ማርያም ትንቢተ ኢሳይያስን ስታነብና « ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች» በሚለው አንቀጽ ስትደርስ
እጅግ : ትሑቷ : ድንግል : ማርያም ቅድስት ፣ ድንግል ፣ ንፅህት የሆነች ድንግል ማርያም ትንቢተ ኢሳይያስን ስታነብና « ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች» በሚለው አንቀጽ ስትደርስ « ምነው እኔ በሆንኩኝ? » አላለችም « ምነው በዘመኗ ደርሼ ይህቺን ድንግል ባገለገልኳት? » አለች እንጂ፡፡ መልዐኩ « ተፈስሒ » ደስ ይበልሽ ሲላት « ይገባኛል » አላለችም « የእግዚአብሔር ገረዱ እነሆኝ » አለች እንጂ / ሉቃ.1 ፡ 38 /፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ « የጌታዬ እናቱ እመቤቴ ወደኔ ትመጭ ዘንድ እኔ ምንድነኝ? » ስትላት « ልክ ነሽ ይገባኛል አምላክን ፀንሻለሁና » አላለችም « የባርያይቱን ውርደት ተመልክቷልና » አለች እንጂ ፡፡ እመቤታችን ኤልሳቤጥ እንዳረገዘች ሰምታ ትጠይቃት ዘንድ መሔዷ የትሕትናዋን ጥልቀት ያሳያል ለልማዱ ባርያ ወደ ጌታው ይሔዳል እንጂ ፡፡ የሆነው ግን እንዲህ አይደለም የመጣችው ኤልሳቤጥ አይደለችምና ወላዲተ አምላክ እመቤታችን ሔደች እንጂ ። ያውም በዚያ ተራራማው ስፍራ የእመቤታችን ትሕትናዋ ግሩም ነው፡፡ ትሕትና ሰዎችን አማልክት ዘበጸጋ ታደርጋለች ትዕቢት ደግሞ ቅዱሳን መላዕክትን ታዋርዳለች ምክንያቱም ትዕቢት እጅግ ክፉ ነውና ።

ፍ ል ሰ ታ ፡ ሥ ጋ ሁ ፡ ለ ቅ ዱ ስ ፡ ጊ ዮ ር ጊ ስ #ነሐሴ_16_ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋው ከፋርስ አገር ወደ አገሩ ልዳ በክብር የፈለሰበት ዕለት ነው ። የልዳው ፀሐይ የ
ፍ ል ሰ ታ ፡ ሥ ጋ ሁ ፡ ለ ቅ ዱ ስ ፡ ጊ ዮ ር ጊ ስ #ነሐሴ_16_ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋው ከፋርስ አገር ወደ አገሩ ልዳ በክብር የፈለሰበት ዕለት ነው ። የልዳው ፀሐይ የኢትዮጵያ ገበዝ ቅዱስ ጊዮርጊስ ክርስቶስን አልክድም የሚል አንድ እንኳን በጠፋበት በዚያ ጊዜ በክርስቶስ አምላክነት የጣዖትን ከንቱነት በመመስከር ጌታውን የወደደና ያስከበረ ታላቅ ሰማዕት ነው ። ጌታችንም እንደወደደው ወዶታልና እንዳከበረው አክብሮታልና ዕረፍቱን እሱ ለቤዛ ብዙኃን በመስቀል ተሰቅሎ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ባረፈባት በዕለተ ዓርብ አድርጎለታል ። ፍልሰተ ሥጋውንም ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገተ ሥጋ ጋር አንድ አድርገው እንዲያከብሩት በዚሁ ዕለት በስሙ ወዳነጹለት ቤተ ክርስቲያን አንዲያፈልሱት አድርጓለታል ፡፡ ድንግል ፡ ሆይ ! ፍልሰተ ፡ ዐፅሙ ፡ ከፍልስትሸ ፡ ጋር ፡ ለኾነ ፡ ስለ ፡ ሕማሙ ፡ ስለ ፡ ድካሙ ፡ ፈንታ ፡ የስሙ ፡ ሞገስ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ ላለ ፡ ለቅዱስ ጊዮርጊስ፡ ሰላምታ ፡ ይገባል ፡፡ አስቀድሞ፡ እመቤቴ : ሆይ ከፍልስተሸ ፡ ጋር ፡ ደምሪኝ ፡ ብሎ ፡ ጸልዮአልና ። እንደምርኮ ፡ ልብን ፡ የምታስደስት ፡ ደስ ፡ የተሰኝህ ፡ ቅዱስ ፡ ጊዮርጊስ : ሆይ ፤ የሰማዕትነትህን ፡ ሥቃይ ፡ ከፈጸመክባት : ከፋርስ ፡ ወደ ፡ ልዳ ፡ ለተደረገው ፡ የሥጋህ : ፍልሰት ፡ ሰላምታ : ይገባል ። የሥጋህ : ፍልሰት ፡ ከድንግል ፡ ማርያም፡ ፍልሰት ጋር አንድ ሆነ።

ማ ር ያ ም : አ ር ጋ ለ ች : ወ ደ : ገ ነ ት !!! ለተረገመችው : ምድር : ካሣ : የሆነች ፦ ቅድስት ምድር የእግዚአብሔር ማደሪያው (እናት) የሆነች ድንግል ማርያም እንደ ምንጭ ውኃ የጠራ
ማ ር ያ ም : አ ር ጋ ለ ች : ወ ደ : ገ ነ ት !!! ለተረገመችው : ምድር : ካሣ : የሆነች ፦ ቅድስት ምድር የእግዚአብሔር ማደሪያው (እናት) የሆነች ድንግል ማርያም እንደ ምንጭ ውኃ የጠራች በኀይለ መለኮቱ የጸናች ንጹሕ ዘር የሆነች #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታለች። የጳውሎስ : ፍጽምት : ድንኳን : የሆነች ፦ ደሀውም ባለጠጋውም ሴቱም ወንዱም ጌታውም ባርያውንም ካህኑም ምእመኑም የሚጠለልባት ከድካመ ሥጋ ከድካመ ነፍስ የሚያርፉባት #እሷም_እንደልጇ_ተነስታልች ። የሕይወት : ደምግባት : የሆነች ፦ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሕይወት የታደገባት፤ በፍዳ በመርገም ተጎሳቁሎ የነበረውን ባሕርያችንን ያደሰባት የሕይወታችን ደምግባት የሆነች #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታለች ። ፍጥረት : የዳነባት : የኖኅ : ታቦት ፡ የሆነች ፦ ከጥፋት ውኃ የዳንባት መርከባችን በድንግልና የታተመች ማርያም የሐዲስ ፍጥረት ቅርንጫፍ መዳኛ መርከብ የሆነች በዚህም ዓለም በወዲያኛው ዓለም በገነት ፣ በመንግሥተ ስማያት የምትመሰገን #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታልች ። ዝምተኛ : መልካሚቱ : እመቤት : የሆነች ፦ በሰውነቷ ውስጥ የተከናወነውን ምሥጢር በማኅፀኗ የተፈጸመውን መለኮታዊ ኀይል ዝም ብላ በልቧ ትጠብቀው ነበር እንጂ ስለክብሯ እዩልኝ ስሙልኝ ብላ ለማንም ያልተናገረችው ቅድስት እመቤት #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታልች ። ከወርኅ : መስከረም : አበቦች : ይልቅ : የተመሰገንሽ : ማርያም : ሆይ ከአላፊው : ከጠፊው : ከታችኛው : ዓለም : በሰማይ : በኪሩብ : ጉባኤ : ትኖር : ዘንድ : ሱራፊ : ለሚጠብቃት : የሥጋሽ : ፍልሰት : ሰላምታ : ይገባል።

Story

የ እ መ ቤ ታ ች ን : ሰ በ ን እመቤታችን ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ባገኝችው ጊዜ ለሐዋርያት ምልክት እንዲሆን እንካ ብላ ሰበኗን የመግነዝ ጨርቋን ሰጥታው ነበር።
የ እ መ ቤ ታ ች ን : ሰ በ ን እመቤታችን ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ባገኝችው ጊዜ ለሐዋርያት ምልክት እንዲሆን እንካ ብላ ሰበኗን የመግነዝ ጨርቋን ሰጥታው ነበር። እናም ቅድስት ቤተ ክርስትያንም ይህንን ምሳሌ ይዛ በቅዳሴ ጊዜ ሠራዒ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ በመጾር ላይ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው፡፡ እንዲሁም አባቶቻችንም በእጅ መስቀላቸው እጄታ ላይ የሚይዙት መሐረብ መሰል ሱቲ የሰበኗ ምሳሌ ነው። ቅዱሳን ሐዋርያትም በሰበኗ ድውይ ሲፈውሱበት ሙት ሲያሥነሱበት ኖረዋል።