የቅዱሳን ታሪክ
رفتن به کانال در Telegram
በዚህ ቻናል ውስጥ፦ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ የሚገኙ ስዕላትን የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ስዕላት የአድባራት እና የገዳማት ፎቶዎችን ያገኛሉ የተለያዩ ስዕለ አድዕኖ ለመላክ @kidanemiherat_bot
نمایش بیشتر8 596
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-107 روز
-2430 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
اوت '26
اوت '26
+91
در 0 کانالها
ژوئیه '26
+105
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '26
+87
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+69
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+77
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '26
+70
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+77
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+55
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+67
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+84
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+66
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+62
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '25
+104
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+93
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+83
در 0 کانالها
Get PRO
مه '25
+115
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+115
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '25
+99
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '25
+114
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+149
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+155
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+155
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+119
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+107
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '24
+140
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+132
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+103
در 0 کانالها
Get PRO
مه '24
+135
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+140
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '24
+181
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+19
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+21
در 1 کانالها
Get PRO
دسامبر '230
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '230
در 1 کانالها
Get PRO
اکتبر '230
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '230
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '230
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '23
+33
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '23
+73
در 0 کانالها
Get PRO
مه '23
+42
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '23
+59
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '23
+68
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '23
+38
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '23
+50
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '22
+100
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '22
+68
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '22
+73
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '22
+54
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '22
+89
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '22
+73
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '22
+65
در 0 کانالها
Get PRO
مه '22
+57
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '22
+63
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '22
+42
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '22
+20
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '22
+27
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '21
+26
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '21
+18
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '21
+27
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '21
+30
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '21
+42
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '21
+51
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '21
+31
در 0 کانالها
Get PRO
مه '21
+28
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '21
+133
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '21
+100
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '21
+149
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '21
+146
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '20
+16 134
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 29 اوت | +2 | |||
| 28 اوت | +4 | |||
| 27 اوت | +3 | |||
| 26 اوت | +1 | |||
| 25 اوت | +1 | |||
| 24 اوت | +2 | |||
| 23 اوت | +1 | |||
| 22 اوت | +3 | |||
| 21 اوت | +4 | |||
| 20 اوت | +3 | |||
| 19 اوت | 0 | |||
| 18 اوت | +1 | |||
| 17 اوت | +3 | |||
| 16 اوت | +2 | |||
| 15 اوت | +1 | |||
| 14 اوت | +2 | |||
| 13 اوت | +4 | |||
| 12 اوت | +3 | |||
| 11 اوت | +6 | |||
| 10 اوت | +5 | |||
| 09 اوت | +2 | |||
| 08 اوت | +3 | |||
| 07 اوت | +8 | |||
| 06 اوت | +4 | |||
| 05 اوت | +6 | |||
| 04 اوت | +4 | |||
| 03 اوت | +4 | |||
| 02 اوت | +5 | |||
| 01 اوت | +4 |
پستهای کانال
| 2 | እጅግ : ትሑቷ : ድንግል : ማርያም
ቅድስት ፣ ድንግል ፣ ንፅህት የሆነች ድንግል ማርያም ትንቢተ ኢሳይያስን ስታነብና « ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች» በሚለው አንቀጽ ስትደርስ « ምነው እኔ በሆንኩኝ? » አላለችም « ምነው በዘመኗ ደርሼ ይህቺን ድንግል ባገለገልኳት? » አለች እንጂ፡፡
መልዐኩ « ተፈስሒ » ደስ ይበልሽ ሲላት « ይገባኛል » አላለችም « የእግዚአብሔር ገረዱ እነሆኝ » አለች እንጂ / ሉቃ.1 ፡ 38 /፡፡
ቅድስት ኤልሳቤጥ « የጌታዬ እናቱ እመቤቴ ወደኔ ትመጭ ዘንድ እኔ ምንድነኝ? » ስትላት « ልክ ነሽ ይገባኛል አምላክን ፀንሻለሁና » አላለችም « የባርያይቱን ውርደት ተመልክቷልና » አለች እንጂ ፡፡
እመቤታችን ኤልሳቤጥ እንዳረገዘች ሰምታ ትጠይቃት ዘንድ መሔዷ የትሕትናዋን ጥልቀት ያሳያል ለልማዱ ባርያ ወደ ጌታው ይሔዳል እንጂ ፡፡
የሆነው ግን እንዲህ አይደለም የመጣችው ኤልሳቤጥ አይደለችምና ወላዲተ አምላክ እመቤታችን ሔደች እንጂ ።
ያውም በዚያ ተራራማው ስፍራ የእመቤታችን ትሕትናዋ ግሩም ነው፡፡
ትሕትና ሰዎችን አማልክት ዘበጸጋ ታደርጋለች ትዕቢት ደግሞ ቅዱሳን መላዕክትን ታዋርዳለች ምክንያቱም ትዕቢት እጅግ ክፉ ነውና ። | 544 |
| 3 | ፍ ል ሰ ታ ፡ ሥ ጋ ሁ ፡ ለ ቅ ዱ ስ ፡ ጊ ዮ ር ጊ ስ
#ነሐሴ_16_ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋው ከፋርስ አገር ወደ አገሩ ልዳ በክብር የፈለሰበት ዕለት ነው ።
የልዳው ፀሐይ የኢትዮጵያ ገበዝ ቅዱስ ጊዮርጊስ ክርስቶስን አልክድም የሚል አንድ እንኳን በጠፋበት በዚያ ጊዜ በክርስቶስ አምላክነት የጣዖትን ከንቱነት በመመስከር ጌታውን የወደደና ያስከበረ ታላቅ ሰማዕት ነው ።
ጌታችንም እንደወደደው ወዶታልና እንዳከበረው አክብሮታልና ዕረፍቱን እሱ ለቤዛ ብዙኃን በመስቀል ተሰቅሎ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ባረፈባት በዕለተ ዓርብ አድርጎለታል ።
ፍልሰተ ሥጋውንም ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገተ ሥጋ ጋር አንድ አድርገው እንዲያከብሩት በዚሁ ዕለት በስሙ ወዳነጹለት ቤተ ክርስቲያን አንዲያፈልሱት አድርጓለታል ፡፡
ድንግል ፡ ሆይ ! ፍልሰተ ፡ ዐፅሙ ፡ ከፍልስትሸ ፡ ጋር ፡ ለኾነ ፡ ስለ ፡ ሕማሙ ፡ ስለ ፡ ድካሙ ፡ ፈንታ ፡ የስሙ ፡ ሞገስ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ ላለ ፡ ለቅዱስ ጊዮርጊስ፡ ሰላምታ ፡ ይገባል ፡፡ አስቀድሞ፡ እመቤቴ : ሆይ ከፍልስተሸ ፡ ጋር ፡ ደምሪኝ ፡ ብሎ ፡ ጸልዮአልና ።
እንደምርኮ ፡ ልብን ፡ የምታስደስት ፡ ደስ ፡ የተሰኝህ ፡ ቅዱስ ፡ ጊዮርጊስ : ሆይ ፤ የሰማዕትነትህን ፡ ሥቃይ ፡ ከፈጸመክባት : ከፋርስ ፡ ወደ ፡ ልዳ ፡ ለተደረገው ፡ የሥጋህ : ፍልሰት ፡ ሰላምታ : ይገባል ። የሥጋህ : ፍልሰት ፡ ከድንግል ፡ ማርያም፡ ፍልሰት ጋር አንድ ሆነ። | 888 |
| 4 | ማ ር ያ ም : አ ር ጋ ለ ች : ወ ደ : ገ ነ ት !!!
ለተረገመችው : ምድር : ካሣ : የሆነች ፦ ቅድስት ምድር የእግዚአብሔር ማደሪያው (እናት) የሆነች ድንግል ማርያም እንደ ምንጭ ውኃ የጠራች በኀይለ መለኮቱ የጸናች ንጹሕ ዘር የሆነች #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታለች።
የጳውሎስ : ፍጽምት : ድንኳን : የሆነች ፦ ደሀውም ባለጠጋውም ሴቱም ወንዱም ጌታውም ባርያውንም ካህኑም ምእመኑም የሚጠለልባት ከድካመ ሥጋ ከድካመ ነፍስ የሚያርፉባት #እሷም_እንደልጇ_ተነስታልች ።
የሕይወት : ደምግባት : የሆነች ፦ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሕይወት የታደገባት፤ በፍዳ በመርገም ተጎሳቁሎ የነበረውን ባሕርያችንን ያደሰባት የሕይወታችን ደምግባት የሆነች #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታለች ።
ፍጥረት : የዳነባት : የኖኅ : ታቦት ፡ የሆነች ፦ ከጥፋት ውኃ የዳንባት መርከባችን በድንግልና የታተመች ማርያም የሐዲስ ፍጥረት ቅርንጫፍ መዳኛ መርከብ የሆነች በዚህም ዓለም በወዲያኛው ዓለም በገነት ፣ በመንግሥተ ስማያት የምትመሰገን #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታልች ።
ዝምተኛ : መልካሚቱ : እመቤት : የሆነች ፦ በሰውነቷ ውስጥ የተከናወነውን ምሥጢር በማኅፀኗ የተፈጸመውን መለኮታዊ ኀይል ዝም ብላ በልቧ ትጠብቀው ነበር እንጂ ስለክብሯ እዩልኝ ስሙልኝ ብላ ለማንም ያልተናገረችው ቅድስት እመቤት #እሷም_እንደ_ልጇ_ተነስታልች ።
ከወርኅ : መስከረም : አበቦች : ይልቅ : የተመሰገንሽ : ማርያም : ሆይ ከአላፊው : ከጠፊው : ከታችኛው : ዓለም : በሰማይ : በኪሩብ : ጉባኤ : ትኖር : ዘንድ : ሱራፊ : ለሚጠብቃት : የሥጋሽ : ፍልሰት : ሰላምታ : ይገባል። | 616 |
| 5 | بدون متن... | 661 |
| 6 | የ እ መ ቤ ታ ች ን : ሰ በ ን
እመቤታችን ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ባገኝችው ጊዜ ለሐዋርያት ምልክት እንዲሆን እንካ ብላ ሰበኗን የመግነዝ ጨርቋን ሰጥታው ነበር።
እናም ቅድስት ቤተ ክርስትያንም ይህንን ምሳሌ ይዛ በቅዳሴ ጊዜ ሠራዒ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ በመጾር ላይ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው፡፡
እንዲሁም አባቶቻችንም በእጅ መስቀላቸው እጄታ ላይ የሚይዙት መሐረብ መሰል ሱቲ የሰበኗ ምሳሌ ነው።
ቅዱሳን ሐዋርያትም በሰበኗ ድውይ ሲፈውሱበት ሙት ሲያሥነሱበት ኖረዋል። | 749 |
| 7 | የሚለውን አያውቅም ነበር” ማር. 9፥6
ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ስለ ደብረ ታቦር በጻፈበት ምዕራፍ ውስጥ ይህንን ዐረፍተ ነገር እናገኛለን።
ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታን ያየው ዓሣ በሚያጠምድበት የገሊላ ባሕር ላይ ነው። ዛሬ ያየውን በብርሃን የተሞላ ፊቱን ግን አላየውም።
ያን ጊዜ ግብረ መለኮቱን ዛሬ ደግሞ ገጸ መለኮቱን አየ።
ያ የመጀመሪያው ቀን በሁለት ጀልባ ሙሉ ዓሣ ያጠመደበት ቀን ነበር በሕይወቱ ትልቁን ትርፍ ያተረፈበት ቀን ነው።
ባሕር የታዘዘችለት መሆኑን ሲያይ እርሱ እግዚአብሔር እንደሆነ አውቆ “ጌታ ሆይ” ብሎ ጠራው ሉቃ. 5፥3-11።
ዛሬ ደግሞ ገጸ መለኮቱን አየ። በዚህ ምክንያት መደንገጡን የገለጠው ወንጌላዊ ከመደንገጡ የተነሳ የሚናገረውን አያውቅም ነበር አለ።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን ይዞ ወደ ተራራው የወጣው ከተራራው እግርጌ “አንተ የሕያው እግዚ አብሔር ልጅ ነህ” ማቴ. 16፥16 ብለውት ስለነበር በትክክልም የሕያው እግዚ አብሔር ልጅ እንደሆነ ከባሕርይ አባቱ ከአብ የምስክርነትን ቃል እንዲሰሙ ለማድረግ ነበር።
አንዳንዶቹ ኤርምያስ ነው፣ ኤልያስ ነው ወይም ሌላ ስም እየጠሩ “ዕገሌ” ነው ይሉት ስለነበር የአይሁድ ሊቃነ ካህናት የሚሉት እንዳልሆነ እንዲያስተውሉ ነበር።
ጴጥሮስ ግን ከዚህ በተቃራኒ በታቦር ተራራ ላይ መኖር አሰኘውና “በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው” አለ።
ጴጥሮስ ሆይ! ለእኛስ መልካም የሚሆነው በሰማይ ባለች ነጻ በምታወጣ በኢየሩሳሌም መኖር ነው። በዚህ ተራራ የጥንት ሰዎች ሰልፍ ሰርተውበታል፤ ደም ፈሶበታል ጦርነት ተደርጎበታል መሳ. 4፥12። ለእኛስ ጦርነት የሌለባት የእግዚአብሔር መንግሥት ትሻለናለች።
“ሞትም ከእንግዲህ አይሆንም ኃዘንም ቢሆንም ወይም ጩኸትወይም ስቃይ ከእንግዲህ አይሆንም” ራእ. 21፥4 የተባለላት ከተማ የት አለች? እሷን ሳናገኝ “በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው” ማለት የሚሉትን እንዳለማወቅ ይቆጠራል።
ከሰማይ በታች ያለው ነገር ሁሉ ከንቱ ነው ለእኛስ መልካም የሚሆንልን ከክርስቶስ ጋር ወደ ሰማይ መውጣት ነው። ከሰማይ በታች የማያረጅ ውበት የማያልቅ ሀብት የለም ዛሬ የወደድነውን ነገ እንጠላዋለን። መንግሥተ ሰማያት ግን “ለባሏ እንደተሸለመች ሙሽራ ናት” አታረዥም።
በእርግጥም ጴጥሮስ የሚለውን አያውቅም ነበር፥ የሰማይና የምድሩን ባለቤት ሰቀላ ሠርቶ ሊያኖረው አስቦ ነበርና። ፈጣሪን ከፍጡራን ጋር አስተካክሎ “ሦስት ዳስ እንሥራ አንዱን ለአንተ፣ አንዱን ለሙሴ፣ አንዱን ለኤልያስ” አለ።
ክርስቶስ ከሙሴ ከኤልያስ ጋር ጎረቤት ሆኖ ሊኖር የሚገባው ነውን?
በሙሴ አድሮ ባሕር የከፈለ፣ መና ያወረደ፤ በኤልያስ አድሮ አክዓብን የገሰጸ፣ ሰማይን የዘጋ ምድርንም ደረቅ ያደረገ እርሱ አይደለምን?
ሙሴን በብርሃን ድንኳን ውስጥ ተገልጦ ዐሥሩ ቃላትን በሁለት ጽላት ላይ የጻፈለት፣ ለኤልያስም የእሳት ሰረገላና ፈረሶችን የላከለት እርሱ ከሙሴና ከኤልያስ ጋር በዚህ ተራራ ሊኖር እንዴት ይችላል? ጴጥሮስ “የሚለውን አያውቅም ነበር”
ጴጥሮስ ሆይ ሙሴና ኤልያስ ወደዚህ ተራራ የተጠሩት በኢየሩሳሌም ሊሆን ስላለው የክርስቶስ መስቀል ከክርስቶስ ጋር ሊነጋገሩ እንጂ ሰቀላ አሠርተው ሊኖሩ አይደለም። ዐርባ ዓመታትን ያለ ሰቀላ ያገለገለው ሙሴ፣ በኮሬብ ፈፋ ውስጥ ተሰውሮ ዘመኑን የጨረሰው ኤልያስ ዛሬ ሰቀላ አስፈልጓቸው የመጡ ይመስልሃልን?
ቅዱስ ወንጌል የመጡበትን ጉዳይ “በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር” ሉቃ. 9፥31 ብሎ ያብራራዋል።
ስለ ክርስቶስ መስቀል በሚነገርበት መድረክ ስለ ሦስቱ ዳሶች ማውራት በእርግጥም የሚሉትን አለማወቅ ነውና ቅዱስ ማርቆስ “የሚለውን አያውቅም ነበር” አለ።
ክርስቶስ ካልሞተ ምዕመናን በምን ነጻ ይወጣሉ? “እሞታለሁ እሰቀላለሁ” ያለበት ቦታ ይህ አይደለም፤ በኢየሩሳሌም ነው። ጌታ መቃብራችንን ባዶ የሚያስቀርበት፣ ሞታችንን የሚገድልበት፣ ስለበደላችንም ካሳ ሆኖ የሚቀርብበት ስፍራ ይህ ሳይሆን ያኛው ነው።
ጴጥሮስ ሆይ ለእኛስ የሚሻለን በዚህ ሳይሆን በዚያ መኖር ነው። “አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” ብሎ በደላችንን ካላስቀረልን፤ “ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ” ብሎ ወደ ገነት ካልመለሰን፤ “እነሆ እናትህ” ብሎ በሔዋን ፋንታ ድንግል ማርያምን እናት አድርጎ ካልሰጠን፤ “ተራብሁ” ብሎ ማቴ. 4፥2 ረሀባችንን እንዳስቀረልን “ተጠማሁ” ብሎ መጠማታችንን ካላስቀረልን ሰው መሆኑ ለምንድነው?
ጴጥሮስ ሆይ በደብረ ታቦር ሰቀላ ሠርተህ ብታኖረው ይህ ሁሉ ይቀርብናል።
ሙሴና ኤልያስ የመጡት አይሁድ ክርስቶስን የሙሴን ሕግ ሻረ ብለውት ነበርና ሕግን የሚፈጽም እንጂ ሕግን የሚሽር እንዳልሆነ ለማስረዳት ነው ማቴ. 5፥17።
እነሱ ለሕግ የሚቀኑ መስሏቸው ሰንበትን እንደሻረ አስበው ይቃወሙት ነበር፤ “ይህ ሰው ሰንበትን አያከብርምና ከእግዚአብሔር አይደለም” ዮሐ. 9፥16 ያሉት ብዙዎች ናቸው።
ከእነሱ በላይ ለእግዚ አብሔር ሕግ የሚቀናው ኤልያስ ዛሬ ወደ እርሱ መጥቶ ታየ።
ለምስክርነት የመጡትን ሙሴንና ኤልያስን ዳስ ጥሎ ማኖር አይቻልምና “የሚለውን አያውቅም ነበር”
እንኳን አደረሳችሁ
ለነቢያት ለሐዋርያት የገለጠውን የጌትነቱን ምሥጢር ለእኛም ይግለጥልን።
©️ ስምዓኮነ መልአከ / Simakone Melak | 785 |
| 8 | ደብረ ታቦር
በዓለ ደብረ ታቦር ከ9ኙ ዓበይት በዓላት መካከል 1ዱ ነው።
ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ «ከነቢያት አንዱ ነህ» ብለውት ነበርና የነቢያት አምላካቸው እንደሆነ ለማጠየቅ ቅዱስ ጴጥሮስን ቅዱስ ያዕቆብንና ቅዱስ ዮሐንስን ወደ ተራራ ይዟቸው ወጣ።
ጴጥሮስን ያዕቆበንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ደብረ ታቦር ተራራ ላይ ከወጣ በኋላ መልኩም በፊታቸው ተለወጠ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ እንደ ፀሐይም አበራ።
እነሆ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሊነጋገሩ ወደ እርሱ መጡ ሲነጋገሩም ብሩህ ደመና መጥቶ ጋረዳቸው «የምወደው ልጄ ይህ ነውና እርሱን ስሙት» የሚል ቃል ከደመና መጣ ብርሃነ መለኮቱም ከደብረ ታቦር እስከ አርሞንኤም ተራራ ድረስ ላሉት ሁሉ ተገለጠ።
የተራራው አናት ላይ የተገለጠው ብርሃነ መለኮቱ በተራራ ግርጌ ላሉት ሁሉ ለስምንቱ ሐዋርያት ተገለጠላቸው።
ሐዋርያቱ የክርስቶስን የክብሩን ብርሃን ሲያዩ ፊቱ ሲለወጥባቸው በሐዋርያት ልብ ያደረው ሥጋዊ መንፈስ ራቀ በውስጣቸው ያለው ጨለማ ተወገደ የእግዚአብሔርን ክብር እንዲያስተውሉ አእምሯቸው ብሩህ ሆነ።
ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ «በፊታቸው ተለወጠ ልብሶቹም እንደ በረዶ ነጭ ሆኑ ጴጥሮስ ኢየሱስን እንዲህ አለው ሊቅ ሆይ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው ከዚህ ሦስት ዳስ እንሥራ አንዱን ላንተ አንዱን ለሙሴ አንዱን ለኤልያስ አለው» ሲል ዘምሯል።
ጌታችን ሙሴን ከመቃብር ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ አስተዋወቃቸው ጌታችን በደብረ ታቦር ተራራ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን ሰዎችን ነቢያትንና ሐዋርያትን አንድ አደረጋቸው እርሱ አምላካችን ሠራኤ ብሉይ ወሐዲስ ነውና።
ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን የብርሃነ መለኮቱን ምስጢር ለኛም ይግለፅልን🙏
እንኳን አደረሳችሁ! | 769 |
| 9 | بدون متن... | 944 |
| 10 | بدون متن... | 1 013 |
| 11 | ❝የምሥጢረ ሥላሴ አጭር መግለጫ ❞
°በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ°
°°አብ በመንፈስ ቅዱስ ይመሰገናል፡፡
ወልድም በአብና በመንፈስ ቅዱስ ይመሰገናል፡፡
መንፈስ ቅዱስም በአብና በወልድ ይመሰገናል፡፡
°°ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ አስቀድመው ለአብ ምስጋና በመስጠታቸውም ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ይልቅ ለአብ ክብርን እንደስጡ አታስብ፡፡ እንዲህ አይደለምና፡፡
°°በአብ ያለ በወልድ ግን የሌለ ክብር የለም፡፡ በወልድ ያለ በአብና በመንፈስ ቅዱስ የሌለ ገናናነት የለም፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ያለ በአብና በወልድ ግን የሌለ ክብር የለም፡፡
°°አብ ወልድ ባልነበረበት ወቅት አልነበረም፡፡
ወልድም መንፈስ ቅዱስ ባልነበረበት ወቅት አልነበረም፡፡ መንፈስቅዱስም አብና ወልድ ባልነበ ሩበት ዘመን አልነበረም፡፡
°°አብ ከወልድ አይበልጥም።
ወልድም ከአባቱ አይበልጥም፡፡
መንፈስ ቅዱስም እንደ እነርሱ ነው፡፡
°°አብ ልጁን ይህ የእኔ ነው፣ ያ የአንተ ነው፤ ይህ የመንፈስ ቅዱስ ነው የሚለው አይደለም፡፡
ወልድም አባቱን ይህ የእኔ ነው ይህ የአንተ ነው ይህም የመንፈስ ቅዱስ ነው የሚለው አይደለም፡፡
መንፈስ ቅዱስም አብን ይህ የአንተ ነው ይህ የወልድ ነው አይለውም፡፡
°°መጀመሪያችን ርስታችን የሆነ ወልድ ከአብ የሚለይ አይደለም፡፡ ወልድም በሀብትና በርስት ከአብ አይለ ይም፡፡ መንፈስ ቅዱስም እንዲሁ፡፡ በሥላሴ የተለያየ መንግሥት የለም፡፡ በአንዲት አምልኮት ያመልኳቸዋል፡፡ አንዲት ስግደትም ይሰግዱላቸዋል።
°°ሰውን በአርያችንና በምሳሌ ያችን እንፍጠር በማለት ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ የተናገረው የአብ ምክር ምን ይደንቅ፡፡ በዚህ ምክር የተሰማማ የወልድ ምክርም ዕፁብ ነው፡፡ በእጆቹ ሥራ የተደሰተ የመንፈስ ቅዱስ ፈቃድም ምን ይደንቅ! | 1 379 |
| 12 | ሥላሴ በዕለተ ቀናቸው ሦስት የነገረ ድኅነት ማግኛ የመሠረት ድንጋዮችን ጣሉ።
በዛሬዋ ዕለት የተጣሉ 3 የመሠረት ድንጋዮችም
❖ ፅንሰተ ማርያም
ሚ ቡርክት ወቅድስት ይእቲ ሰዓተ ትፍሥሕት ሐና ዘጸገየተኪ ባቲ" እንዳለ ደራሲው በዛራዋ ዕለት የድኅነት መሠረት የሆነችዋ እናታችን ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነውና የነገረ ድኅነት ሕንፃው የመሠረት ድንጋዩ ተቀመጠ።
❖ ፅንሰተ ቤተ ክርስቲያን (በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራታለሁ) ቅዱስ ጴጥሮስ ሐዋርያትን ወክሎ አንተ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ በመመለሱ ይህንን ነገረ ሃይማኖት የምትመሰከር ቤተ ክርስቲያን በዚህ አስተምህሮት የጸናች ቤተ ክርስቲያን የመሠረት ድንጋይዋ በቂሳርያ ተመሠረተ።
❖ፅንሰተ ክህነት(የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻ ቁልፍ እሰጥሃለሁ በማለት ጌታችን መድኃኒታችን ቅዱስ ጴጥሮስ አስቀድሞ ለመለሰው መልስ የክህነት ሽልማት በሐዋርያት በኩል ለቤተ ክርስቲያን ተሰጠ።
እንኳን አደረሳችሁ | 958 |
| 13 | ይህቺን : ዕለት : ያልናፈቀ : ትውልድ : የለም
#ነሐሴ_ሰባት_ቀን የባሕርያችን መመኪያ የምትሆን ንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነው ፡፡
ጽድቃቸው እንደ መርገም ጨርቅ ለሆነባቸው ቅዱሳን አበውና ቅዱሳን አንስት ተስፋቸው የሚፈጸመው በዛሬው ዕለት በተጸነሰችው በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ነውና ፡፡
ቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችንም ከእግዚአብሔር ቀጥሎ እንደ እመቤታችን ከፍ ከፍ የምታደርገው ፍጥረት የሌለው ስለዚሁ ነው ፡፡
ሊቃውንቱ፡- « ሐና አንቺን የጸነሰችበት የደስታ ቀን ምን ያህል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤ ሟች ኢያቄምም ለሕይወት አንቺን ያፈራባት ቀን ምን ያህል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤ » ብለው የሚዘምሩላትም ይህን ምሥጢር በልቡናቸው ቋጥረው ነው ።
እንኳን ፡ ለዓለም ፡ ሁሉ ፡ ደስታን ፡ ወዳመጣችው
ዕለት ፡ አደረሳችሁ ፡ አደረሰን | 834 |
| 14 | #ማርያም_መግደላዊት
#ነሐሴ_6_ቀን ማርያም መግደላዊት ሽሙጥን፣ ስድብን፣ መንገላታትንና ግርፋትን ታግሣ መልካሙን ገድል ተጋድላ ሰማዕትነትን ፈጽማ ያረፈችበት ቀን ነው።
ይቺ ሴት ቀድሞ ሰባት አጋንንት ተቆራኝተዋት ሰባት አይነት ኀጢት ያሠሯት የነበረች ኋላ ግን ክርስቶስ ሰባቱን አጋንንት አስወጥቶላት ከሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት ጋር የቀላቀላት ቅድስት ሴት ናት።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ በተነሣ ጊዜም ትንሣኤውን ለመጀመሪያ ጊዜ የገለጸው ለማርያም መግደላዊት ነበር።
ማርያም መግደላዊት ባደረባት እርኩስ መንፈስ ብዙዎችን ስታታልል ስትሸነግል የኖረችና በሐሰት ወጥመድ ጠልፋ የጣለቻቸው ብዙዎች ነበሩ።
ማርያም መግደላዊት በእንዲህ ያለ ግብር ጸንታ ለዘመናት ከኖረች በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ወራት አጋንንትንም በሥልጣኑ ያወጣል ብለው ነገሯት።
ጥሪው የእግዚአብሔር ነውና ማርያም መግደላዊት ፈጥና ወደ እርሱ ሄደች ጌታችንም ባያት ጊዜ ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ነውና በፍቅር አቀረባት።
በቸርነቱም ከራስ ጸጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ የሞሉትን ሰባት ነገደ አጋንንትን ጠራርጎ አስወጣላት።
በዚያች ሰዓት ዕለቱኑ እንደተወለደ ሕፃን ከነበረባት ችግር ሁሉ ንጹሕ ሆነች ከዚህች ቀን ጀምሮ ፍጹም ተቀየረች እርምጃዋ ሁሉ የተባረከና የንጽሕና ሆነ።
በሃምሳኛው ቀንም መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ «በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮቹ ላይ ቅዱስ መንፈሴን አሳድራለሁ» ብሎ በኢዩኤል ላይ አድሮ ትንቢት እንደ ተናገረ ከሐዋርያት ጋር ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ጸጋና በረከት የተካፈለች ቅድስት ሴት ናት።
በመጨረሻም ማርያም መግደላዊት የሐዲስ ኪዳን ዲያቆናዊት ሴት ስትሆን ክርስትናንም ተዟዙራ ሰብካለች።
የቅድስት መግደላዊት ማርያም ጸሎቷና በረከቷ አይለየን!🙏 | 949 |
| 15 | #ወንጌላዊ_ቅዱስ_ዮሐንስ ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን በጌታችን እግረ መስቀል ስር እስከ መጨረሻው በመጽናት የተገኝ ታማኝ ሐዋርያ ነው ።
ለዚህም እንደሽልማት ከኃዘኑም ይጽናና ዘንድ ጌታችን በመስቀል ላይ ሆኖ እመቤታችንን ለቅዱስ ዮሐንስ በእናትነት ሰቶታል ለእሱም ብቻም አይደለም ለእኛም ለሁላችንም በእሱ ምሳሌነት እናት ትሆነን ዘንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰቶናል ።
ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን ወደ ቤቱ ከወሰዳት በኃላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከጌታችን ጋር የነበራትን ታሪክ ስትነግረው እሱም ሲያገለግላት 15 ዓመት በእሱ ቤት ቆይታለች ።
በቆይታቸውም እንደ ሰኔ ጎለጎልታ እና ራዕይ ማርያም ያሉ መጽሐፍትን ከእሷ እየሰማ እንደጻፈ ብዙ የቤተ ክርስቲያናችን መጸሐፍት ይናገራሉ ።
ፍ ቁ ረ : እ ግ ዚ እ : የ ተ ባ ለ : የ ቅ ዱ ስ : ዮ ሐ ን ስ : ወ ን ጌ ላ ዊ : በ ረ ከ ቱ : ረ ድ ኤ ቱ : ከ ሁ ላ ች ን : ጋ ር : አ ድ ሮ : ለ ዘ ላ ለ ም : ይ ኑ ር ። | 1 018 |
| 16 | بدون متن... | 1 167 |
| 17 | "+የአንቺን ደም ግባት ማመስገን እንዴት ይቻለኛል+"
❤አንቺ ሙሽራ ነሽ፡፡ ዐይኖችሽም እንደሚያንጸባርቅ የኮከብ አወጣጥ ያስደስታሉ፡፡
❤ጉንጮችሽም በሰሜናዊ ምሥራቅ በወጣ ጊዜ እንደሚያበራ እንደ ሚያዝያ ፀሐይ ናቸው፡፡
❤አንገ ትሽም በዝሆን ቀንድ እንደተሠራ እንደዳዊት ቤት ነው፡፡
❤ሆድ ሽም ሥንዴ የተጨመረበት በአበባም የታጠረ ነው፤
❤ጣቶች ሽም የሚያማምሩ፣ በወርቅም የተለበጡ ናቸው፡፡
.......ያንችን ደምግባት የአንቺን ማማር ማመስገን እንዴት ይቻለኛል፡፡ የፊትሽ ደም ግባት ቀይ ነው፡፡ ድንግል ሆይ በውዳሴ አመሰግንሻለሁ፡፡ የአፍሽ ሽታ ከሽቱ መዓዛ ይልቅ ያስደስታል፡፡
=======አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ==== | 1 185 |
| 18 | بدون متن... | 1 135 |
| 19 | #ጾመፍልሰታ/ጾመ ማርያም/
#ፍልሰታ ማለት ፈለሰ፤ ተሰደደ፤ ተጓዘ፤ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ሄደ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ቃል ሲሆን ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ «ፈለሰት ማርያም እምዘይበሊ ኀበኢይበሊ፤ ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም፣ ከምድር ሕይወት ወደ ሰማያዊ ሕይወት፣ ተሻገረች» በማለት ፍልሰታ የሚለውን ቃል ትርጓሜ አመሥጥሮ ገልጾታል፡፡
#ጾመ ፍልሰታ ከእመቤታችን ድንግል ማርያም የዕረፍት ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ እመቤታችን በዚህ ዓለም ፷፬ ዓመታትን በሕይወተ ሥጋ ከቆየች በኋላ ጌታችን የእናቱን ተድላ ነፍሷን እንጂ ተድላ ሥጋዋን አይወድምና ጥር ፳፩ ቀን ፵፱ ዓመተ ምሕርት አረፈች፡፡ ዕረፍቷም እንደሌላው ሰው በሕማምና በድካም አይደለም፡፡ በገነት ዕፀዋት መዓዛ ተመስጣ ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይታለች፡፡
#ታሪኩ በነገረ ማርያም እንደተጻፈው ሐዋርያት እመቤታችንን በአጎበር አድርገው አክብረው ወደጌቴሴማኒ መካነ መቃብር ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉም ነበርና ቀድሞ ልጇን ተነሣ ዐረገ እያሉ ሲያውኩ ኖረዋል፤ እርሷን ደግሞ ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን ነውና «ኑ የማርያምን ሥጋ በእሳት እናቃጥለው» ብለው በምቀኝነት ተነሱ፡፡ ከመካከላቸው አንድ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ከሐዋርያት እጅ ለመንጠቅ ዘሎ ሄዶ የአልጋውን ሸንኮር ሲይዝ የታዘዘ መልአክ በረቂቅ ሰይፉ እጆቹን ቆረጠው፡፡ እጆቹም በአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ የምሕረት እናት የሆነችው ድንግል ማርያም ቅዱስ ጴጥሮስ ጸልዮ እጆቹን እንዲመልስለት ነግራው እንደነበረ አድርጎለታል፡፡
#የእመቤታችን ሥጋዋን መላእክት ከዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ወስደው አስቀምጠውታል፡፡ ሥጋዋ ያለበትን ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እነርሱ ባለማየታቸው እመቤታችን ባረፈች በ፮ኛው ወር ከነሐሴ ፩ ቀን እስከ ፲፬ ቀን ድረስ ከጾሙ በኋላ በ፲፬ኛው ቀን ሥጋዋን እንደገና ከጌታ ተቀብለው በጌቴሴማኒ ባለው መቃብር ቀብረውታል፡፡
#ከዚህ በኋላ እንደ ልጇ በ፫ኛው ቀን ተነሥታ መላእክት እየዘመሩላት ወደሰማያት ስታርግ፤ ሐዋርያው ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሰ ዕርገቷን በማየቱ መላእክት «እመቤትህ እርሷ ናት፤ስገድላት» አሉት፤ እርሱም «ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ ይላል፤ከደመናው ሊወድቅ ወደደ» ምክንያቱም ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ፤ ዛሬ ደግሞ የእርሷን ትንሣኤ ለማየት ብሎ ነው፡፡ እመቤታችንም «ትንሣኤየን ያየህ አንተ ነህ ሌሎቹ አላዩም» ብላ ሐዋርያት ገንዘው የቀበሩበትን የሐር ግምጃ ሰጥታ አጽናንታ ሰደደችው፡፡
#ቅዱስ ቶማስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ የእመቤታችን ነገር እንዴት ሆነ ብሎ ጠየቃቸው፤እነርሱም አግኝተው እንደቀበሯት ነገሩት፤ እርሱም ያየውን ምሥጢር በልቡ ይዞ «ሞት በጥር፤ በነሐሴ መቃብር፤ ለሰሚውም አያምር፤ይህ እንዴት ይሆናል?»፤ ቢላቸው ቅዱስ ጴጥሮስ «ድሮም አንተ ተጠራጣሪ ነህ፤ማን ያርዳ የቀበረ፤ ማን ይናገር የነበረ እንዲሉ፤ ገንዘን የቀበረን እኛ እያለን እንዴት ትጠራጠራለህ» ብለው ወደ መቃብሯ ሄደው መቃብሯን ቢከፍቱት ባዶ ሆኖ አገኙት፡፡ በዚህ ተደናግጠው ተያዩ፤ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ «አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችን ተነሣች፤ዐረገች፤ ይኸው ምልክቱ» ብሎ ገንዘው የቀበሩበትን ሰበን አሳያቸው፤ እነርሱም አምነው ሰበኗን ለበረከት ተካፈሉት፡፡
#በዓመቱ ነሐሴ ፩ ቀን ሐዋርያት በመንፈሰዊ ቅናት ተነሳስተው «ቶማስ ትንሣኤዋን አይቶ እኛ ሳናይ እንዴት ይቀርብናል» በማለት ነሐሴ ፩ ቀን ሱባኤ ጀምረው በ፲፮ኛው ቀን የሐዋርያትን ሱባኤ ተቀብሎ እመቤታችንን መንበር ጴጥሮስን ተራዳኢ፣ ካህን እስጢፋኖስን ሠራዔ ዲያቆን አድርጉ ቀድሶ አቁርቧቸዋል፡፡ ከዚያ ጊዜ በኋላም ከነሐሴ ፩ እስከ ፲፭ ቀን ጾመ ፍልሰታ ተብሎ ሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ ይጾመዋል፡፡
የጾሙ እና የትንሣኤዋ በረከት ተካፋይ ያድረገን፤ አሜን | 993 |
| 20 | بدون متن... | 913 |
