የቅዱሳን ታሪክ
الذهاب إلى القناة على Telegram
በዚህ ቻናል ውስጥ፦ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ የሚገኙ ስዕላትን የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ስዕላት የአድባራት እና የገዳማት ፎቶዎችን ያገኛሉ የተለያዩ ስዕለ አድዕኖ ለመላክ @kidanemiherat_bot
إظهار المزيد8 622
المشتركون
-224 ساعات
-147 أيام
-5730 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يونيو '26
يونيو '26
+84
في 0 قنوات
مايو '26
+69
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+77
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+70
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+77
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+55
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+67
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+84
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+66
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+62
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+104
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+93
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+83
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+115
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+115
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+99
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+114
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+149
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+155
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+155
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+119
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+107
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+140
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+132
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+103
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+135
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+140
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '24
+181
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+19
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '24
+21
في 1 قنوات
Get PRO
ديسمبر '230
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '230
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبر '230
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '230
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '230
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+33
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+73
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+42
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+59
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+68
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+38
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+50
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+100
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+68
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+73
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+54
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+89
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+73
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+65
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+57
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+63
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+42
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+20
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+27
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+26
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+18
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+27
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+30
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+42
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+51
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+31
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+28
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+133
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+100
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+149
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+146
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+16 134
في 0 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 29 يونيو | +5 | |||
| 28 يونيو | +3 | |||
| 27 يونيو | +6 | |||
| 26 يونيو | +5 | |||
| 25 يونيو | +2 | |||
| 24 يونيو | +3 | |||
| 23 يونيو | +3 | |||
| 22 يونيو | 0 | |||
| 21 يونيو | +4 | |||
| 20 يونيو | +2 | |||
| 19 يونيو | +6 | |||
| 18 يونيو | +5 | |||
| 17 يونيو | 0 | |||
| 16 يونيو | +2 | |||
| 15 يونيو | +1 | |||
| 14 يونيو | +3 | |||
| 13 يونيو | +5 | |||
| 12 يونيو | +5 | |||
| 11 يونيو | +3 | |||
| 10 يونيو | +1 | |||
| 09 يونيو | +2 | |||
| 08 يونيو | +2 | |||
| 07 يونيو | +1 | |||
| 06 يونيو | +2 | |||
| 05 يونيو | +3 | |||
| 04 يونيو | +4 | |||
| 03 يونيو | +2 | |||
| 02 يونيو | +3 | |||
| 01 يونيو | +1 |
منشورات القناة
Repost from አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
የ አ ሚ ና ዳ ብ : ሠ ረ ገ ላ
አባ ሕርያቆስ እመቤታችንን የአሚናዳብ ሠረገላ አንቺ ነሽ በማለት አመስግኗታል ።
መተርጉማኑ ደግሞ እመቤታችን በአሚናደብ ሠረገላ የተመሰለችበትን ምሥጢራዊ ምክንያት ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ ፦
የአሚናደብ ሠረገላ ልዝብና ፈጣን ምቹ ነበረች እመቤታችንም ለነፍስ ለሥጋ የምትመች በንጽሕና በቅድስና የለዘበች ለምሕረት የፈጠነች አፍጣኒተ ረድኤት ሰአሊተ ምሕረት ምዕራገ ጸሎት ናትና ነው።
« አንቀጸ : ሰላማዊት : ድንግል : ሆይ : ያንቺ : ሰላም ከሁላችን : ጋር : ይሁን : የጌታችን : እናት : እናታችን ማርያም : ሆይ : ለምኚልን : ከደጅ : እንዳንቆም : አማልጂን » !!!
| 2 | ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ሕይወትን እንደሰጠን ሁሉ የእርሱ ባለሟል የሆኑት ቅዱሳን በሞታቸው ቂም በቀል ሳይሆን ወደ ሕይወት ወደ ሃይማኖት ይወስዱናል ።
ሕያው ሥራ ሠርተው ካለፉ ቅዱሳን መካከል አንዱ ደግሞ ቀዳሚ ሰማዕት #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ነው። | 819 |
| 3 | በኃጢአት በተሰነካከልን ጊዜ ሰይጣን ምሕረት አታገኙም አትረቡም አትጠቅሙም ብሎ በቀቢጸ ተስፋ ሰንሰለት እየጎተተ ወደ ጥልቁ እንዳያወርደን የእናት አማላጅ የመስቀል ምርኩዝ #ኪዳነ_ምሕረትን ሰጠን !!!። | 840 |
| 4 | ማ ር : ሚ ና ስ
#ሰኔ_15 የቅዱስ ሚናስ ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት ቀን ነው በተማፀኑትም ጊዜ በምልጃው ፈጥኖ በመድረስ የሚታወቀው ታላቅ ሰምዕት ነው፡፡
ቅዱስ ሚናስ በመላው ዓለም በተለይ በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ልክ እንደ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በእጅጉ የሚወደድና ተአምር አድራጊ « ገባሬ ተአምር ወመንክር » በመባል የሚታወቅ ሰማዕት ነው።
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ፡- (የክርስቶስ ምርጥ ጭፍራ ከገንዘብ ይልቅ ጽድቅን የመረጠ እንደ ምሳሌው እንደጨረቃ ለደመቀና እንደ ፀሓይም ብሩህ ለኾነ ለሚናስ ሰላምታ ይገባል ) በማለት አወድሶታል፡፡
የ ቅ ዱ ስ : ሚ ና ስ : በ ረ ከ ት: ይ ደ ር ብ ን ፡፡ | 811 |
| 5 | ንግስናን : ከቅድስና : አዋድዶ : የያዘ : ቅዱስ : ላልይበላ !!!
#ሰኔ_12_ቀን የተባረከና የተመሰገነ በሰማያት ያለ ምሥጢርን ያየ የኢትዮጵያ ንጉሥ የነበረ በመላአክት አብሳሪነተ በላስታ ሮሃ የተወለደው የቅዱስ ላልይበላ የዕረፍቱ መታሰቢያው ቀን ነው ።
በአንድ ወቅትም የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት ወደ ሰማያት አወጣው አብያተ ክርስቲያናትንም እንዴት መሥራት እንደሚችል አሳየው ወደ ምድርም ተመልሶ መንፈስ ቅዱስ እንዳረቀቀው በአስደናቂ ጥበብ ብዙ አብያተ ቤተ ክርስቶያናትን ሰራ ።
ቤተ ጎልጎታ ፣ ቤተ ሊባኖስ ፣ ቤተ ደናግል ፣ ቤተ ማርያም ፣ ቤተ መስቀል ፣ ቤተ ሚካኤል ፣ ቤተ ጊዮርጊስ ቤተ ገብርኤል ፣ ቤተ አማኑኤል ፣ ቤተ መርቆሬዎስ ፣ ቤተ መድኃኔዓለምን ያነጸ ደገኛ ንጉሥ ነው ።
አብያተ ክርስቲያነቱንም አንጾ ከጨረሰ በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በብርሃን ሠረገላ ተቀምጦ የሚስፈራ መብረቅን የተጎናጸፉ አእላፍት ሠራዊቶቹ ዙሪያውን ሆነው ወደርሱ መጥቶ እንዲህ አለው፤
‹‹ ወዳጄ ላሊበላ ሆይ ሰላም ይሁንልህ እኔ በማይታበል ቃሌ እነግርሃለሁ፤ ማደሪያህ በክብር ሁሉ ከከበሩ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያቶቼ ጋር ይሁን፡፡
በጸሎትህና በቃል ኪዳንህ ለሚታመን እምነቱ እንደ ጴጥሮስና ጳውሎስ ደም መፍሰስ ይሆንለታል ፡፡
ወደ ቤተ መቅደስህም የሄደ በኢየሩሳሌም ወዳለው ቤተ መቅደሴ እንደ ሄደ ይሆንለታል ።
መቃብርህንም የተሳለመ የሥጋዬን መቃብር እን ተሳለመ ይሆንለታል ፡፡
በዓመታቱ ወሮች ሁሉ የተራቡትን እያጠገበ የተጠመቁትንም እያጠጣ መታሰቢያህን ለሚያደርግ እኔ የተሠወረ መና እመግበዋለሁ ፤ የሕይወት ጽዋንም አጠጣዋለሁ፡፡
በመታሰቢያህ ቀንም ዕጣን ወይም ስንዴ የሚያገባውን እኔ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት በውስጠኛው መጋረጃ አስቀምጬ ከተቆረሰው ሥጋዬ አቆርበዋለሁ ።
በአማላጅነትህም እየታመነ የገድልህንና የቃል ኪዳንህን መጽሐፍ የሚጽፈውን ያንተ ስም በተጻፈበት ቦታ እኔ ስሙን እጽፋለሁ ።
በፍጹም ልቡ ለሚያምን ይህን የማይታበል ቃል የተናገርኩ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ እኔ ነኝ ፡፡ ››
ቅዱስ ላሊበላም ይህን ቃል ኪዳን በተሰጠው ጊዜ ጌታችን እያመሰገነ በምድር ወድቆ ሰገደ፡፡ ጌታችንም ሰላምታ ከሰጠው በኋላ በክብርና በምስጋና ወደ ሰማያት ዐረገ ፡፡
ቅዱስ ላሊበላ ከዚህ በኋላ ጥቂት ታሞ በሰላም ዐረፈ፤ የብርሃን መላእክትም ነፍሱን ተቀብለው የዘለዓለም ሕይወት ማደሪያ ወደሆነው ማረፊያው ገነት አስገቡት ፡፡
እግዚአብሔር : አምላክ : በቅዱስ : ላሊበላ
ጸሎት : ነፍሳችንን : ይማርልን : አሜን፡፡ | 925 |
| 6 | لا يوجد نص... | 673 |
| 7 | የቀን : እረኛ : የሌሊት : ጠባቂ : ቅዱስ : ሚካኤል
#ሰኔ_12_ቀን ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎሚያን ከዲያብሎስ መንጋጋ ያስጣለበት እንዲሁም የባሕራንን የሞቱን ጦማር ቀዶ ሠርግ ያደረገበትን እለት ነው።
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ልጆቿን ሰብስባ በዓልን ሰርታ በታላቅ ድምቀት ከዓመት ዓመት ታከብረዋለች።
መጋቤ ብሉይ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በተአምራቱ ዘወትር እንደሚጠብቀን ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ እንዲህ እያለ ይመሰክራል ፦
« የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የቀን እረኛ የሌሊት ጠባቂ ክንፎቹ የእሳት የሆነ ዘወትር የሚጠብቀን ቅዱስ ሚካኤል የእውነት የድንኳን ከተማ ነው። » በማለት ተናግሯል።
በዚህ መሠረት ድንኳን ከቀን ሐሩር ከሌሊት ቁር እንደሚከለሉበት ሁሉ #ቅዱስ_ሚካኤልም በቃል ኪዳኑም የሚታመኑትን ሁሉ ከምሕረት አልባው ከዲያብሎስ ደባ ከአጋንንት ድብደባ ከዚህ ዓለም ፈተና ያድነናል ይታደገናል። | 785 |
| 8 | #እግዚአብሔርም በሰማያዊ ዜማ በምድራውያን ሰዎች ሊመሰገን በወደደ ጊዜ ቅዱስ ያሬድን ሦስት አዕዋፍ ግእዝ፣ ዕዝል እና አራራይ የሚባሉን የዜማ ስልቶች በመንፈስ ቅዱስ መሪነት አስተማረው ፡፡
ወደ ሰማይም በመንፈስ ቅዱስ በመነጠቅ ቅዱሳን መላእክት እግዚአብሔርን ልዩ በሆነ ጣዕመ ዜማ ሲያመሰግኑ ሰምቶ ወደ ምድር ተመለሰ፡፡
ከዚያም በአክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ከታቦተ ጽዮን ፊት ቆሞ አምላኩን እግዚአብሔርን ‹‹ በሰማያት የሰማሁት የመላእክት ምስጋና ምን ይደንቅ! ምን ይረቅ!›› በማለት በዜማው አመሰገነ ፡፡
ይህንንም በሰማያዊት ኢየሩሳሌም የሰማውን የመላእክትን ዜማ ለደቀ መዛሙርቶቹ አስተማረ ፡፡
ከ ቅ ዱ ስ : ያ ሬ ድ : በ ረ ከ ት : ረ ድ ኤ ት : ያ ሳ ት ፈ ን !!! | 1 026 |
| 9 | ልዑል ሰምራ
ዳዊት ዘመራ
በቤተ መቅደስ ተወክፍዋ
ልዑል ወደዳት
ዳዊትም ዘመረላት
በቤተ መቅደስ ተቀበሏት
መቅደሰ ኦሪት ዘቦዕኪ ኦ ማርያም እምነ፤
ወእሙ ለእግዚእነ፤
በሕፅነ ሐና ተማኅፀነ፤
ፈንዊዮ ለፋኑኤል ይዕቀብ ኪያነ፤
በረምኃ መስቀል ረጊዞ ሰይጣነ፤
ወደ ኦሪት መቅደስ የገባሽ የጌታችን እናቱ እናታችን ማርያም ሆይ
አንቺን በታቀፈ በሃና ጭን ተማፅነናል፤
ሰይጣንን በመስቀል ጦር ወግቶ እኛን ይጠብቀን ዘንድ ፋኑኤልን ላኪልን።
(ነግሥ ዘማኅሌት)
በአታ ለማርያም 🙏
እንኳን አደረሳችሁ | 1 423 |
| 10 | ቅ ድ መ : ዓ ለ ም : የ ታ ሰ በ ች
#መላእክት ቢታሰቡ ድንግል ማርያምን ከበው በእርስዋ መንበርነት የተገለጠውን ንጉሠ ነገሥት እግዚአ አጋእዝት ሊያመሰግኑ ነው።
#ነቢያት ቢታሰቡ ትንቢታቸው በድንግል ማርያም ተፈጽሞ በእርስዋ ምክንያት መርገም ሊወገድላቸው ነው።
#ሐዋርያት ቢታሰቡ በእመቤታችን ከብረው እርስዋ ያወጣችላቸውን ፀሐይ ለብሰው ለዓለም ብርሃን ሊሆኑ ነው።
#ሰማዕታት ቢታሰቡ አክሊለ ሰማዕት ክርስቶስን ወልዳላቸው በእርሱ ስም አንበሳ ሊሰግድላቸው እሳት ሊቀዘቅዝላቸው ኃይል ሊያስታጥቃቸው ድል ሊነሡ ነው።
#መነኮሳት ቢታሰቡ አክሊለ ሦክ ተቀዳጅቶ የምንኩስና ቆብን ከለሜዳ ለብሶ የምንኩስና ቀሚስን በበረሃ ጹሞ የበረሃው ውስጥ ከዋክብት እንዲሆኑ ገዳምን ባርኮ የሰጣቸውን ብርሃናቸው ጌታን ብትወልድላቸው ነው።
ስለዚህ “ እመቤታችን ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር” እንላለን። | 1 303 |
| 11 | በ ዓ ተ ፡ ግ ብ ጽ
#ነገ_ግንቦት_24 ቀን እመቤታችን ከተወዳጅ ልጅዋ ጋር በስደት ግብጽ የገባችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው ።
አበው የአበባን በዓል በአበባ ዘመን ብለው ማኅሌቱንም በዓሉን በወርኃ ጽጌ በጥቅምት ቢወስዱትም ጥንተ መሠረቱ ግን ግንቦት 24 ቀን ነው ።
እመቤታችን ቀጥኖ ከሚያመነምን ክፉ ዘመን ትሰውረን እፎይ ከምንልበት ዘመን በምልጃዋ ታድርሰን! | 1 581 |
| 12 | ጾም ሙሽሪትን ትመስላለች፤ ሙሽሪትን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች ቤቱን ያስጌጡታል፤ ይሸልሙታል፡፡ ወደ ሰርጉ አዳራሽ የሚገባውን ሰው የሰርግ ልብስ ለብሶ እንደኾነ፣ የቆሸሸ እንዳልኾነ አይተው ያስገቡታል፡፡ እኛም እንዲኽ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡
ልቡናችንን በማንጻት፣ ልል ዘሊል ከመኾን በመራቅ፣ የክፋት እርሾን በማስወገድ፣ ከጾም ጋር አብረው የሚመጡትን የሚያጅቧትን መልካም ምግባራትንም ለመቀበል የልቡናችንን ውሳጤ በመክፈት የምግባር እናት፣ የማስተዋል እንዲኹሉም ለሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትኾን ጾምን ልንቀበላት ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ይኽን ያደረግን እንደኾነ ታላቅ ሐሴት እናደርጋለን፤ ርሷም ቁስለ ነፍሳችንን ትፈውስልናለች፡፡
በሌላ አገላለጽ ብነግራችኹ ሐኪሞች በአንድ ታማሚ ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻ፣ መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ታማሚው ምግብ ከመውሰድ እንዲቈጠብ ነው፡፡ ታማሚው ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከለ ሓኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት እንደተፈለገው ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም ቁስለ ነፍስ ቁስለ ሥጋ የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚኽ በላይ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስን የምንሻ ከኾነ ልቡናችንን ንጹሕና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል፡፡ እንዲኽ ካልኾነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
እንኳን ለጾመ ሐዋርያት በሰላም አደረሳችሁ 🥰 | 1 185 |
| 13 | ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : አሸናፊ ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የስጦታ ምንጭ ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ለሰማዕታት መመኪያ ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የተሰበሩትን የሚጠግን ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የማይዳሰስ የእሳት ነበልባል ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የንጽሕናና የቅድስና መንፈስ ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ዕድፍን የሚያነጻ ውኃን የሚቀድስ ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የጻድቃን የባለሟልነታቸው የራስ ወርቅነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ተቀድቶ የሚጠጣ የዕውቀት መጠጥ ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ድንጋዮችን የሚፈረካክስ የእሳት መዶሻ ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : በጨለማ ላይ የሚያበራ የይቅርታ ብርሃን ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ሐዋርያትን የወይን ጠጅ ሳይጠጡ ያሰከረ ነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የወርቅ የሐር ግምጃ የቅዱሳን የጌጣቸው ልብስ ነው!
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : ፍጹም የከበረ የአብና የወልድ የባሕርይ ሕይወትነው !
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ : የሃይማኖት አልጫነትን የሚያጣፍጥ የልቡና ጨው ነው
ጰ ራ ቅሊጦ ስ : መጉደል መጨመር ሳይኖርበት በህልውናው አምላክነው
ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ :የይሁዳ ኮረብቶች በጽዮን አዳራሽ የሚጠጡት እሳት ነው
ጰራቅሊጦስ : በምሥጢረ ቁርባን ላይ የሚረብ ፀዐዳ መለኮታዊርግብነው
እ ን ደ : አ ብ ና : እ ን ደ : ወ ል ድ : በ ሰ ማ የ : ሰ ማ ያ ት : በ ም ድ ር ም : ሁ ሉ : ላ ይ : መ ን ግ ሥ ቱ : የ መ ላ : ነ ው : ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ ። !!! | 1 271 |
| 14 | ደ ብ ረ : ም ጥ ማ ቅ
ከሠላሳ ሶስት የእመቤታችን በዓላት አንዱ ግንቦት 21 ቀን የሚከበረው የእመቤታችን በዓል ነው ።
በግብጽ ደብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን የወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ጻድቃንን መልአክትን አስከትላ ለአምስት ቀን የታየችበት የተገለጸችበት ነው ።
እመቤታችን በስደት ሳለች ጌታ በዚህ ቦታ በስምሽ ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል ስሙንም ደብረ ምጥማቅ ይሉታል ብሎ ነግሯት ነበር ይኸውም አልቀረም በዚሁ ቦታ በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን ታንጾ ስሙ ደብረ ምጥማቅ ተብሏል ።
በዚህ ዕለት እመቤታችን ከፀሐይ ሰባት እጅ አብርታ ከጉልላቱ ላይ በመንበር ብርሃን ተቀምጣ መላእክት ሊቃነ መላእክት ከበው ሲያመሰግኗት ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት እጅ ሲነሣት ታይታለች ።
እስከ አምስት ቀንም ምእመናኑን አረማውያኑን አንድ ወገን አድርጋ ስትባርክ ሰንብታለች ከዚህም በኋላ ምእመናንም አረማውያንም በየዓመቱ እነዚህን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 25 ለአምስት ዕለታት በደብረ ምጥማቅ ተሰብስበው የሚያከብሩ ሆነዋል ።
ለኛም ለልጆቿ በሕይወታችን ሁሉ እየተገለጠች በረድኤት በበረከት ትባርከን !!! | 1 330 |
| 15 | እ ን ዲ ህ : እ ን ላ ታ ለ ን
ለጉድለታችን ምልዓት ናት ።
ላለመውደቃችን ጽናት ቅናት ናት ።
ለጥፋታችን አንቀጸ መድኀኒት ናት ።
ለመነሣታችን ምርጉዘ ዕፀ ሕይወት ናት ።
የእመቤታችን የኪዳነ ምሕረት ቃል ኪዳኗ በንስሐ እየቀሰቀሰ ወደ ርእሰ ሕይወት ክርስቶስ የሚያደርሰን የምሕረት ገመድ ነው እንላታለን ።
በዚህም ልጅዋ ራሱ እኔ ከፍ ብዬ እስባችኟለሁ እንዳለ ኪዳነ ምሕረት ወደ ልጅዋ የምትመራን ብርህት ደመና የልጅዋን የምሕረቱን የወይራ ዝንጣፊ ይዛ ወደ እኛ የምትፋጠን ርግብ መንፈሳዊት ናት እንላታለን ።
ዘመን የማይገድባት ለሁሉ የሚበቃ ረድኤት ያላት ምልዕተ ጸጋ በምድርም በሰማይም በነፍስም በሥጋም ጥግ የምትሆነን መለኮት የመሠረታት ነውራችን የምትሸፍንልን ሰፊ አዳራሽ ናት ።
ሰለዚህም እመቤታችን ሆይ ቃል ኪዳንሽ ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ስካርም እንደለቀቀው በነፍስ በሥጋ ያነቃናል እንላታለን ።
እመቤታችን ሆይ ከሕማም ያስነሣናል ከድካም ያበረታታናል እመቤታችን ሆይ ቃል ኪዳንሽ ከቡሩካን ጋር በቀኝ ያቆመናል እንላታለን ።
እመቤታችን የአዳም አባታችን ርስት ከምትሆን ከገነት ከመንግሥተ ሰማያት ገብተን ለመኖር የሚያበቃን ዘላለም ጸንቶ የሚያኖረው ኪዳንሽ ነው እንላታለን ። | 1 555 |
| 16 | ‹‹ ወደ : አባቴ : ወደ : አባታችሁ : ዐርጋለሁ ... ››
ያረገው ከሰማይ የወረደው ከድንግል ማርያም የተወለደው የፍጥረ አስገኚ የዓለም ሠራኢ መጋቢ እግዚአብሔር ነው ።
በዓለ ዕርገትን ስናከብር አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ በዚህ ዓለም ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ኖረ ።
ከማኅበረ መላእክት ተለይቶ ይኖር ለነበረ ለአዳም ጽንዐ ነፍስ ልጅነት ስጥቶ ከማኅበረ መላእክት ጋር አንድ አድርጎ ዐረገ ስንል ነው ።
ጌታችን ወደ ሰማይ ሲያርግ የነበረውን ድባብ ምን ይመስላል ቢሉ ፦ ቢታንያ ሲደርስ መሄዱን ትቶ ቆመ ደቀ መዛሙርቱም ከበውት ቆሙ ጌታም በፍቅር ዐይን አያቸው ።
እጆቹንም አንሥቶ ሲባርካቸው ከማንኛውም ምድራዊ ስበት በበለጠ ኀይል ከመካከላቸው ተነሥቶ ወደ ሰማይ ዐረገ ‹‹ ወደ አባቴ ወደ አባታችሁ ዐርጋለሁ ›› ይህን እየተናገረ ሳለ ደመና ነጠቀው ከዐይኖቻቸውም ሠወረው ።
ዳግመኛ መብረቅ የለበሱ መላእክት ታይዋቸው እናንት የገሊላ ሰዎች ቆማችሁ ሰማይ ሰማይን ለምን ትመለከታላችሁ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያርግ እንዳያችሁ ዳግመኛም በክብር ወደ እናንተ ይመጣል ።
ደቀ መዛሙርቱም ጌታቸውን ከዐይናቸው እስኪሰወርና አይኖቻቸው እስኪፈዙ ድረስ በአድናቆትና በፍቅር ወደ ላይ ተመለከቱ ወዲያውኑ የክብር ደመና ከዐይናቸው ሰወረው ።
መላእክትም የደመና ሰረገላም መስለው በተቀበሉት ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ጥዑም የሆነውን የመላእክትን ዝማሬ ሰምተዋል።
መላእክትም ትኩር ብለው የጌታን ዕርገት ለሚመለከቱ ሐዋርያት ‹‹ እናንተ የገሊላ ሰዎች ሰማይ ሲወጣ ያያችሁት ተመልሶ ይመጣል ›› የሚል ተስፋ አበሠሩአቸው ።
ደቀ መዛሙርቱም ‹‹ እነሆ እኔ እስከ ዓለም መጨረሻ ድረስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ ›› ሲል የሰጣቸውን ተስፋ እያስታወሱ ከቢታንያ ተመለሱ ።
እንኳን ለብርሃነ ትርገቱ በሰላም አደረሳችሁ | 1 476 |
| 17 | لا يوجد نص... | 1 204 |
| 18 | ለኢትዮጵያዊቷ ጻድቅ ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ ክብረ በዓል (ግንቦት 12) እንኳን በሰላምና በጤና በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ።
ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ዓለምንና ክብሯን፣ ትዳሯንና ንብረቷን ንቃ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ሙሉ ሕይወቷን ለጸሎትና ለተጋድሎ የሰጠች፤ በተለይም ደግሞ ስለ ሰው ልጆች ሁሉ ድኅነትና ምሕረት ሌሊትና ቀን በጣና ባሕር ውስጥ ቆማ በመጸለይ የምሕረት ቃል ኪዳን የተቀበለች ታላቅ የፍቅርና የንሥሐ እናት ናት።
የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ቅዱስ ጸሎቷ፣ ትሕትናዋ፣ ረድኤትና በረከቷ ከሁላችን ጋር ይሁን። | 986 |
| 19 | ሥ ጋ ህ ን : አ ፍ ል ሰ ው : በ ው ስ ጡ : ያ ኖ ራ ሉ
ግንቦት 12 ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅዱስ ዐፅማቸው ቀድሞ ካረፉበት (ከተቀበረበት) ሥፍራ (ደብረ አስቦ) አሁን ወዳለበት ሥፍራ (ደብረ ሊባኖስ) የተዘዋወረበት ቀን ነው፡፡
ስለ ቀናች ሃይማኖትህ
ስለ ልብህ ንጽሕናና ቅድስና
ስለ ብዙ ጾም ጸሎት ስግደትህ
ሃይማኖትን ለማስተማር መላዋን ኢትዮጵያን ስለመዞርህ
በሰባት ዓመታት ቁመት የአንዱ አገዳ እግርህ ስለ መሰበሩ
ወደ ኢየሩሳሌም ወርደህ ልዩ ልዩ የቅዱሳን ቦታዎች ስለ መሳለምህ
ከአረማውያን ሕዝብ ጋር በሃይማኖት ስትታገል ደምህን ስለ ማፍሰስህ
በማለት የሕይወት አክሊላትን ካቀዳጃቸው በኋላ
ዝክራቸውን በማዘከር መታሰቢያቸውን የሚያደርጉ ሁሉ በዚህ ዓለምም ሆነ በወዲያኛው ዓለም ፍጹም ዋጋና ፍጹም ክብር እንደሚሰጣቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቃል ኪዳን ከገባላቸው ።
#ግንቦት_12_ቀን « በስምህ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ልጆችህ ሠርተው ሥጋህን አፍልሰው በውስጡ ያኖራሉ ›› አላቸው ።
የጻድቁ ምልጃ ጸሎት አይለየን🥰🙏 | 1 057 |
| 20 | አ ፈ : ወ ር ቅ
የቅዱስ ዮሐንስ የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል በየዓመቱ ግንቦት 12 ቀን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዓልን ሰርታ በስሙ ጽላት ቀርጻ ቤተክርስቲያን አንፃ ታዘክረዋለች ።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ቤተ ክርስቲያን ካፈራቻቸው ሰባክያንና መተርጉማን ታላቁና ደገኛው አባት ነው ፡፡
ዛሬም ድረስ በመላው የክርስትና ዓለም ከፍተኛውን ክብር ይዞ ይገኛል እንከን የለሽና ደስ የሚያሰኝ የሕይወት አሻራ ትቶ ያለፈ ነው ።
በሰባክያንና በመተርጉማን ተዘውትሮ የሚነበብና የሚጠቀስ፣ በሁሉም ዘንድ በፍቅር የሚታወስ እንደ እርሱ ያለ የለም፡፡
ከዕረፍቱ በኋላ በተጋድሎው፤ በትምህርቱና በሕይወቱ ቅድስና የሚያደንቁትና የሚወዱት ከዕረፍቱ በኋላ ክርስቲያኖች “አፈ ወርቅ” የሚለውን ቅጽላዊ መጠሪያ ሰጡት ፡፡
“አፈ ወርቅ" የሚለው ስም ከመጠሪያ ስሙ (ዮሐንስ) በላይ ጎልቶ የሚታወቅበትና የሚጠራበት እስኪሆን የደረሰ ነው ።
ለቤተ ክርስቲያን ላበረከተው ሁለ ገብ የሆነ ታላቅ አስተዋጽዖም ተገቢ የሆነ የግብሩ መገለጫ ስም ነው፡፡
ቅድስት በረከቱ ትደርብን🥰🙏 | 1 012 |
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
