በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ደህንነትን ለማጠናከር የሚያስችል የአንድ ጤና የቴክኒክ የሥራ ቡድኖች ማነቃቂያ አውደጥናት ተካሄደ::
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በብሔራዊ የአንድ ጤና (One Health) ሴክሬታሪያት አማካኝነት በኢትዮጵያን ያሉ የጤና ስጋቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የዝግጁነትና ምላሽ አቅም ለማጠናከር ያለመ የቴክኒክ የሥራ ቡድኖች (TWGs) ማነቃቂያ ወርክሾፕ ከግንቦት 20–21 ቀን 2018 ዓ. ም አካሂዳል ።
በአውደጥናቱ የመንግሥት ተቋማትን፣ የልማት አጋሮችን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በአንድ ጤና አቀራረብ በማሰባሰብ ከአስተዳደር፣ ከቅንጅት፣ ከተጠያቂነት እና ዘላቂነት ጋር የተያያዙ ችግሮች ላይ ተወያይቷል።
በዝግጅቱ ላይ የብሔራዊ የአንድ ጤና ጽህፈት ቤት ሀላፊ ዶ/ር ፈይሳ ረጋሳ የሰው፣ የእንስሳት እና የአካባቢ ጤና ሥርዓቶችን በተቀናጀ መንገድ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
“ዋና ግባችን ለጊዜው ለሚከሰቱ የጤና ችግሮች መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ፣ ከወረርሽኞች ውጪም በየዕለቱ የሚሰራ እና ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ ጠንካራ የሥራ ሥርዓት መገንባት ነው” ብለዋል።
የአውደ ጥናቱ ቁልፍ ውጤቶች የመመሪያ ሰነዶችን (Terms of Reference - TORs) በማሻሻል የሥራ ኃላፊነቶችንና የሪፖርት ማቅረቢያ መዋቅሮችን ግልጽ ማድረግ፣ የተጠያቂነት ሥርዓቶችን ማጠናከር፣ እንዲሁም ለቴክኒክ የሥራ ቡድኖች ቋሚ ሰብሳቢዎችና ምክትል ሰብሳቢዎችን በመሾም እና መደበኛ የመግባቢያ መድረኮችን በመፍጠር እንደገና ማነቃቃትን ያካትታሉ።
በአውደ ጥናቱ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከሕብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ከግብርና ሚኒስቴር፣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ከኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን እንዲሁም እንደ FAO፣ Resolve to Save Lives፣ UKHSA፣ JSI፣ Core Group Partners Project፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር እና Project HOPE ያሉ አለማቀፍ አጋሮች ተሳትፈውበታል::
ተሳታፊዎች በሰው፣ በእንስሳት እና በአካባቢ ጤና መስኮች መካከል የሚከሰቱ አዳዲስ የጤና ስጋቶችን ለመቋቋም በቅጽበት የመረጃ ልውውጥን ማሻሻል፣ ሀብት ማሰባሰብ እና የተቀናጀ ምላሽ መስጠትን ለማጠናከር ቃል ገብተዋል።
ይህ የተሳካ አውደጥናት የአንድ ጤና አቀራረብን በኢትዮጵያ ውስጥ ተቋማዊ ለማድረግ እና የዘርፎች መካከል ትብብርን ለሰዎች፣ ለእንስሳት እና ለአካባቢው ጤና መደበኛ የሥራ ባህል ለማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ታይቶበታል::
EPHI Concludes One Health TWGs Revitalization Workshop to Strengthen Ethiopia’s Health Security
The Ethiopian Public Health Institute (EPHI), through the National One Health Secretariat, has successfully concluded a two-day Technical Working Groups (TWGs) Revitalization Workshop held from May 28–29, 2026, aimed at strengthening Ethiopia’s preparedness and response to interconnected health threats.
The workshop brought together government institutions, development partners, and stakeholders to address challenges related to governance, coordination, accountability, and the sustainability of the One Health approach.
Speaking at the event, Dr. Feyisa Regassa, Chairperson of the National One Health Secretariat, emphasized the need to integrate human, animal, and environmental health systems.
“Our ultimate objective is to pivot away from temporary fixes and build a resilient, everyday operational mechanism that endures well beyond active outbreaks,” he said.
Key achievements of the workshop included refining draft Terms of Reference (TORs) to clarify mandates and reporting structures, strengthening accountability mechanisms, and revitalizing Technical Working Groups through the appointment of dedicated chairs and co-chairs and the establishment of regular communication platforms.
The workshop also reinforced collaboration among key stakeholders, including the Ministry of Health, Ministry of Agriculture, Environmental Protection Authority, Ethiopian Wildlife Conservation Authority, and international partners such as FAO, Resolve to Save Lives, UKHSA, JSI, core group partners project , Ethiopia Red Cross Society and Project HOPE.
Participants committed to enhancing real-time information sharing, resource mobilization, and coordinated responses to emerging health threats at the human-animal-environment interface.
The successful workshop marks an important step toward institutionalizing the One Health approach in Ethiopia, making cross-sector collaboration a routine practice for protecting the health of people, animals, and the environment.