uz
Feedback
DARU-TEWHID [ዳሩ-ተውሒድ]

DARU-TEWHID [ዳሩ-ተውሒድ]

Kanalga Telegram’da o‘tish

በፍትህ ላይ ቀጥ ያልክ ሰለፊ ሁን ለአስተያየትና ጥቆማ 👉 @AbuNuhibnufedlu

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali DARU-TEWHID [ዳሩ-ተውሒድ] analitikasi

DARU-TEWHID [ዳሩ-ተውሒድ] (@darutewhide) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 11 462 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 7 919-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 914-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 11 462 obunachiga ega bo‘ldi.

27 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -122 ga, so‘nggi 24 soatda esa -2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.74% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 10.98% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 953 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 260 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 8 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
በፍትህ ላይ ቀጥ ያልክ ሰለፊ ሁን ለአስተያየትና ጥቆማ 👉 @AbuNuhibnufedlu

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 28 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

11 462
Obunachilar
-224 soatlar
-217 kunlar
-12230 kunlar
Postlar arxiv
አዒሻ ቢንት አቡበክር ክፍል ሶስት ነቢዩ በመዲና ሳሉ ከሚስቶቻቸው ሁሉ አዒሻን ይበልጥ ይወዱ እንደነበር ግልፅ ነው።አንዳንድ ባልደረባዎቻቸው አዘውትረው « የአላህ ልዑክ ሆይ ! በዓለም ላይ እጅግ በጣም የሚወዱት ማንን ነው ? » ሲሉ ይጠይቋቸው ነበር ። ለዚህም ጥያቄ የሚሰጡት ምላሽ እንደ ጥያቄው ባህሪ የሚለያይ ነበር ። ለሴት ልጆቻቸውና ለነርሱም ልጆች ፥ ሌላ ጊዜ ለአቡበክር ፥ ለዓሊ ፣ ለዘይድና ለልጁ ለኡሳማ ) ውዴታ እንዳላቸው አሳውቀዋል ። ነገር ግን ከሚስቶቻቸው መሃል ከኸዲጃ ቀጥሎ ማንን ይበልጥ እንደሚወዱ ሲጠየቁ ምላሻቸው « አዒሻ ናት » የሚል ነበር ። እርሷም እጅግ አድርጋ ትወዳቸዋለች ። ዘወትር ውዴታቸውን የሚያረጋግጥላት ነገርም ከእርሳቸው ትፈልጋለች ። አንድ ወቅት « ለኔ ያለህ ፍቅር እንዴት ነው ? » ስትል ጠይቃቸው « እንደ ቋጠሮ ሲሉ መለሱላት ። ትርጓሜውም እንደብረት የጠነከረና በቀላሉ የማይፈታ ማለት ነው ። ለነብዩ ያላት ፍቅር ቅናት የታከለበት ስለነበር ከርሷ የበለጠ ትኩረት ለሌሎች ሚስቶቻቸው እንዲሰጡ አትፈቅድም ነበር ። ከዚህም የተነሳ « የአላህ ልዑክ ሆይ ! እባክዎን ይንገሩኝ ! ለመሆኑ በሁለት ሸለቆዎች መሃከል ቢሆኑና አንዱ ሸለቆ የተጋጠ ሌለኛው ልምላሜው ያማረ ጨፌ ቢኖረው በየትኛው ላይ ከብቶችዎን ሊያሰማሩ ይሻሉ ? » ስትል ጠየቀቻቸው።ነቢዩም « ባልተጋጠጠው ሸለቆ ላይ » ሲሉ መለሱላት ። አዒሻም « ታዲያ እኔኮ እንደሌሎቹ ሚስቶችዎ አይደለሁም ። ምክንያቱም ሁሉም ቢሆኑ ሌላ ባል አግብተው የነበሩ ናቸው ። » በማለት የርሷን ማንነት ልታስታውስ ትሞክራለች ። በዚህን ጊዜም ነቢዩ ድርበብ የተላበሰ ፈገግታቸውን በማሳየት ዝም ይላሉ ። አዒሻ በኸዲጃ በጣም ትቀና ነበር ። አዒሻ እንዲህ ትላለች : - « ዘወትር ስሟን ስለሚጠሩ ፣ እንዲሁም ከከበረ ድንጋይ የተገነባ ቤት በጀነት እንደተዘጋጀላት ብሥራት ይነግሩ ዘንድ ከአላህ በመታዘዛቸው ፥ በኸዲጃ ( ረ.ዐ ) እንደቀናሁት በማናቸውም የነቢዩ ሚስቶች አልቀናሁም ። በግ ባረዱ ቁጥር የሥጋውን የተወሰነ ክፍል የልብ ወዳጆቿ ለነበሩ ይልካሉ ። በዚህም ምክንያት ‹ በርስዎ ቤት ከኸዲጃ በስተቀር ሌላ ሴት በዓለም ላይ የለም › እያልኩ አዘውትሬ እነግራቸው ነበር ። »ሙሐመድ ኢብኑ ፈድሉ     【 📚ሃያቱ ሶሃባ 】       “ ኢንሻ አላህ ይቀጥላል ”       ¤ t.me/Darutewhide/2852

አዒሻ ቢንት አቡበክር ክፍል ሁለት የነቢዩ ሚስት የሆነችው የ 10 ዓመት ልጅ ሳለች በመካ ሲሆን ፥ እስከ ሁለተኛው ዓመተ – ሂጅራና በግምት የ 14 ና የ 15 ዓመት ወጣት እስከሆነችበት ጊዜ ድረስ ሰርጓ አልተከናወነም ። የሰርጓን ስነ ሥርዓት በተመለከተ እንዲህ ስትል ተርካልናለች : - « አንድ ቀን እየተጫወትኩ ነበር ። ረጅሙና ዘንፋላው ፀጉሬ በወጉ አልተጐነጐነም ። ቤተሰቦቼ ከምጫወትበት ቦታ መጥተው ወደቤት በመውሰድ ለሰርግ እንድዘጋጅ አደረጉኝ ። በባህሬይን የተሠራ ቀይ ሰረዝ ያለው የሙሽራ ልብስ አለበሱኝ ። እናቴም ጥቂት የመዲና ሴቶች ከበር ላይ ቆመው ወደሚጠብቁባት አዲሱ ጐጆዬ ወሰደችኝ ። ( ጋብቻሽ ለመልካምና ለደስታ ይበለው ! ሁሉም ያማረ ይሁንልሽ › ሲሉም በደስታ ተቀበሉኝ ። ከዚያም በፈገግታ የተሞሉት ነቢይ በተገኙበት የዋንጫ ወተት ቀረበ ። ነቢዩ ( ሶ.ዐ.ወ ) ከወተቱ ተጐንጭተው ሰጡኝ ። እኔም ስላፈርኩኝ በእጄ እንደያዝኩት ቀረሁ ። ቢሆንም እንድጠጣ ስላደፋፈሩኝ ጠጣሁ ። ቀሪውን ከአጠገቤ ተቀምጣ ለነበረችው እህቴ– ለአስማ– አሳለፍኩ ። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ሁሉም እየተቀባበሉ ተጐነጩለት ። በዚህ እጅግ ቀላልና የተባረከ በሆነ መልክ ነበር የጋብቻ ሥነ ሥርዓቱ የተካሄደው ። ” የነቢዩ ሚስት መሆኗ የጨዋታ ሕይወቷን አልገታውም ። ወጣት ጓደኞቿ ከቤት ሊጐበኟት አዘውትረው ይመጡ ነበር ። ስለዚህም ሁኔታ እንዲህ ስትል ተናግራለች : - « ጓደኞቼ ከሆኑ ልጃገረዶች ጋር በመጫወት ላይ ሳለሁ ነቢዩ በሚገቡበት ጊዜ ጓደኞቼ ቤቱን ለቀው ይወጣሉ ። ነቢዩም የእነርሱ ከኔ ጋር መሆን እንደሚያስደስተኝ ስለሚያውቁ ለኔ ውዴታ ሲሉ እንዲመለሱ ያደርጓቸዋል ። አንዳንድ ጊዜም ቤቱን ከመልቀቃቸው በፊት ‹ ባላችሁበት ሁኑ › በማለት ያረጓጓቸዋል ። እንዲያም ሲል በጨዋታቸው ላይ ይሳተፋሉ ። » የአዒሻ የመጀመሪያው የመዲና ሕይወቷ ትጋትና ጥንካሬን የሚጠይቅ ፈታኝ አጋጣሚ ነበር ። በአንድ ወቅት አባቷና ከርሱ ዘንድ ያረፉ ሁለት አስሃባዎች በመዲና በተወሰኑ ወቅቶች የተለመደ በሆነ አደገኛ ትኩሳት ታመሙ ። በዚያን ጊዜ አዒሻ አንድ ጠዋት አባቷን ለመጐብኘት እንደሄደች ሦስቱም በሽተኞች ተዳክመውና ሰውነታቸው ሟሾ ስላገኘቻቸው ከባድ ድንጋጤና ተስፋ የመቁረጥ ስሜት አደረባት ። በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ አባቷ ምን እንደሚሰማቸው ስትጠይቅ ፥ ትርጓሜው ባልገባት የቁርኣን ምዕራፍ መለሱላት ። በሁኔታው እጅግ ተረብሻ ወደቤቷ በመመለስ ለነቢዩ ፥ « በሽታው ስለጠናባቸው ይቃዣሉ ። » አለቻቸው።ነቢዩም ምን ምን እንዳሉ ጠየቋት ። ምንም እንኳ ትርጓሜው ባይገባትም የሰማችውን ንግግር ቃል በቃል ነገረቻቸው።ከንግግሯም ነቢዩ የበሽተኞቹን ሁኔታ ለመረዳት ቻሉ።ይህ ገጠመኝ እጅግ አስደናቂ የሆነውን የማስታወስ ችሎታዋን ያሳየናል ።ይህም ችሎታዋ ጊዜ እየገፋ በሄደ ቁጥር በዋጋ ሊተመኑ የማይችሉ የነቢዩን ንግግሮች እንድታከማች አግዟታል ። ✍ ሙሐመድ ኢብን ፈድሉ     【 📚ሃያቱ ሶሃባ 】       “ ኢንሻ አላህ ይቀጥላል ”       ¤ t.me/Darutewhide/2852

ክፍል 2⃣ ይቀጥላል

አዒሻ ቢንት አቡበክር ክፍል አንድ « በእርግጥ እኔ የምሻው አላህን ፣ መልዕክተኛውን ፣ አንዲሁም ዘውታሪ የሆነውን የመጭውን ሕይወት መኖሪያ ( ጀነት ) ነው ፡፡ » 【ዓኢሻ 】 የዓኢሻ የሕይወት ታሪ
አዒሻ ቢንት አቡበክር ክፍል አንድ « በእርግጥ እኔ የምሻው አላህን ፣ መልዕክተኛውን ፣ አንዲሁም ዘውታሪ የሆነውን የመጭውን ሕይወት መኖሪያ ( ጀነት ) ነው ፡፡ » 【ዓኢሻ 】 የዓኢሻ የሕይወት ታሪክ ሴት ልጅ እንደ ተቃራኒ ፆታዋ አዋቂና የምሁራን መምህር ለመሆን ብቃት እንዳላት ያረጋግጥልናል ። በተጨማሪም ሴት ልጅ በወንዶች አስተሳሰብ ላይ ተፅዕኖ በመፍጠር የአመለካከትና የአመራር ምንጭ መሆን እንደምትችል ፥ አልፎ ተርፎም በእንስትነቷ ለባልተቤቷ የደስታና የምቾት ምንጭ ለመሆን ብቃት እንዳላት ግልፅ ማስረጃነት አለው ። ዓኢሻ የአንድም ዩኒቨርስቲ ምሩቅ አልነበረችም ። እንዲያውም በዘመኗ ዩኒቨርስቲም አልነበረም ።ግና እንደማር ያንቆረቆረቻቸው ንግግሮቿ በቋንቋ መካነ ጥናቶች እየተጠኑ ነው ።ህግን በሚመለከት የተናገረቻቸው በህግ ኮሌጆች ይጠናሉ ። እንዲሁም ከሕይወት ታሪኳ የሚነበቡ ድርጊቶችዋ የሙስሊሞችን ታሪክ በሚያጠኑ ተማሪዎችና ምሁራን ከሺህ ዓመታት በላይ እየተዳሰሱ ነው ። ዓኢሻ የዕውቀት ባህር ለመሆን የበቃችው ገና በወጣትነት ዕድሜዋ ነው ።ልጅ ሆና ያደገችው በአዋቂነታቸውና በመልካም ሥነ ምግባራቸው በሚታወቁት በአባቷ በአቡበክር ቤት ነው ።ዐኢሻ በማራኪ ውበቷና በአስደናቂ የማስታወስ ችሎታዋ የታወቀች ነበረች ። በወጣትነት ጊዜዋ የነቢዩ የልብ ተፈቃሪና ታሳቢ ለመሆን በቅታለች ።በሚስትነትም የቅርብ ወዳጃቸው ለመሆን በመታደሏ ሌሎች ሴቶች ሊያካብቱት ያልቻሉትን ዕውቀት ከርሳቸው ለማግኘት ችላለች። ✍ ሙሐመድ ኢብን ፈድሉ     【 📚ሃያቱ ሶሃባ 】       “ ኢንሻ አላህ ይቀጥላል ”       ¤ t.me/Darutewhide/2852

ላለንበት ወቅትና ግርግር ለህይወታችን ስንል ወደ ኃላ እየተመለስን የሶሃቦችን ታሪክ ብናነብና ብናስተነትን ከነሱ ህይወት ብዙ መማረ እንችላለን።ከዚህ ጋር በተያያዘ ፦ የእናታችን ዐኢሻ እና አንዳንድ
ላለንበት ወቅትና ግርግር  ለህይወታችን ስንል ወደ ኃላ እየተመለስን የሶሃቦችን ታሪክ ብናነብና ብናስተነትን ከነሱ ህይወት ብዙ መማረ እንችላለን።ከዚህ ጋር በተያያዘ ፦ የእናታችን ዐኢሻ እና አንዳንድ የሌሎች ሶሃቦች የህይወት ታሪክ ለአንባቢያን በሚመች መልኩ በዚሁ ቻናል ከነጌ ጀምሮ  አጠር አጠር እያደረኩ የማቀርብላችሁ ይሆናል። እስከዛ ሌሎችም ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ  ሊንኩን ለጓዶቻችሁ እያጋራችሁ ጠብቁኝ።  " ወቢላሂ ተውፊቅ " ✍ ወንድማችሁ ሙሐመድ ኢብን ፈድሉ ⤵️⤵️⤵️ t.me/Darutewhide t.me/Darutewhide

ኡስታዝ  ኢብኑ  ሙነወር  (አቡ  ሁዘይፋ) ሴትን ልጅ ለገንዘቧ ብሎ ማግባት!      t.me/NABAWITUBE

ረድ የሸሪዓ አንድ መሰረት ነው ! ከመሆኑም ጋር....... 🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሓፊዘሁላህ        ~ t.me/Darutewhide

"ዛሬ ደርስ አይኖርም" ብዬ ስፅፍ ይጨንቀኛል። የሰዎች የመማር ፍላጎት ላይ ቀዝቃዛ ውሃ የምቸልስ ነው የሚመስለኝ። ግን ደግሞ አንዳንዴ ሁኔታዎች ያስገድዳሉ። በሑዘይፋ መስጂድ ከመግሪብ በኋላ የሚቀርበው የኪታቡ ተውሒድ ደርስ ላይ መገኘት እንደማልችል ለማስታወስ ፈልጌ ሲከብደኝ ነው ይህን ማለቴ። ዛሬም ነገም የኪታቡ ተውሒድ ደርስ አይኖርም። ከትልቅ ይቅርታ ጋር! ከሩቅ የሚታደሙ ስለሚኖሩ በማሰራጨት አግዙኝ፣ ለምታውቋቸውም አድርሱልኝ። ባረከላሁ ፊኩም።

የደርስ ማስታወቂያ የሚቀሩ ኪታቦች፦ ① ተዕሊሙል አጥፋልሙኽተሶሩል አዝካር ወልአዳብመንዙመቱ ተውሒድ ወልኢማን በተስሚዕ ለመቅራት በዚህ ይመዝገቡ፦ +251919993634

https://www.tiktok.com/@daru.tewhid5?_r=1&_t=ZM-92IIFvhEgmG አልፎ አልፎም ቢሆንም የተለያዩ የኡስታዞቻችን አጫጭር ነሲሃዎች ምናሰራጭበት ሌላኛው ቤታችን ስለሆነ እዛ መንደር ያላችሁ ተጎራበቱን።

የዒልም ደረጃ ! ታላቁ የኢስላም ሊቅና ሶሃባ አብዳላህ ኢብኑ አባስ ! ከጓደኞቻቸው ነገሮችን ፈጥኖ የመረዳት ልዩ ችሎታ ፣ የላቀ ዕውቀት ፣ ጥበብንና ብልሃትን የተላበሱ እንደነበሩ ከሶሃቦች የተመሰከረላችው ድንቅ የነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ) ባልደረባ ነበሩ።ከመሆኑም ጋር አንድ ጊዜ እሳቸው የማያውቁትን ሓዲስ አንድ የነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ባልደረባ እንደሚያውቅ ወሬ ሰምተው ስላደረጉት ጥረት እንዲህ ሲሉ ዘግበዋል።    በቀትር የመኝታ ሰአት ❨ቀይሉላ❫ ወደ እሱ ቤት ሄድኩ።ከቤቱ በር ላይ ካባዬን አንጥፌ እስኪነቃ ጠበቅኩት።ንፋሱ አቧራውን እያነሳ ያለብሰኝ ነበር።ብፈልግ ኖሮ እንዲፈቅድልኝ በጠየቅሁትና ያለምንም ጥርጥር ያስገባኝ ነበር። እኔ ግን እንቅልፉን መጨረስ ይችል ዘንድ መጠበቁን መረጥኩ።ሰውየውም ከቤቱ ሲወጣ እንደዚያ ሆኜ ሲያየኝ ’ አንተ የነብዩ አጎት ልጅ ! ምን ነካህ ? ብትልክብኝ ኖሮ እኔው ራሴ እመጣ አልነበር ?! አለ።ወደ አንተ መምጣት ያለብኝ እኔ ነኝ።እውቀት ተፈልጎ እንጂ እንዲሁ ራሱ አይመጣም ! አልኩት።ከዚያም ስለሐዲሱ ጠይቄው ከእሱ ተማርኩ ይላሉ።ታላቁ ሶሃቦ አብደላህ ኢብኑ አባስ። ሶሃቦች ስንትና ስንት የዕውቀት ጥግ ላይ ደርሰው ፣ ስንትና ስንት ሐዲሶችን ለዑማው አስተላልፈው ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ደረሶች ሰብስበው እያስተማሩ እንኳን ለዒልም ከነበራቸው ጉጉትና ክብር እነሱ ማውቁትን የነብዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ) ንግግር አለ ከተባሉ ስንት ስንት ኪሎ ሜትሮች ሄደው ያቺን አንዲትን ሓዲስ ተምረው ይመለሱ ነበር።ባለንበት ዘመን ዒልምን ላለመማር  ምንም ምናቀርበው ዑዝር በሌለበት አላህ በያዝነው ሞባይል ዐለም ላይ ካሉ ዑለማዎች አገናኝቶን ሲያበቃ የኛ በዚህ ልክ ከኢልም መራቅና አለመማራችን የሚያሳዝን ነው።አላህ ያግራልን። ከተጨማሪ ንግግሮች ጋር ከሐያቱ ሶሃባ መፅሐፍ የተወሰደ። ✍ ሙሐመድ ኢብን ፈድሉ ~ https://t.me/Darutewhide

በትልቅ በትንሹ አትዋሽ ! 🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሓፊዘሁላህ        ~ t.me/Darutewhide

ደሊልን መከተል እንጂ የማንም ጭፍራ አጫፋሪ መሆን የለብንም ! 🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሓፊዘሁላህ        ~ t.me/Darutewhide

አሰላሙአለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ። ኢንሻ አላህ ዘውትር እሁድ ረፋድ ላይ በሑዘይፋ መስጂድ ከነገ ጀምሮ ሚን ኡሱሊ አቂደቲ አህሊ ሱነቲ ወል ጀመዓ የሸይኽ ፈውዛንን ኪታብ እንማማራለን። አድራሻ ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ፣ አዲሱ ሸገር ሲቲ።

ሶሻል ሚዲያ ላይ የኡለማዕ ንግግሮች ሆነ በሌሎች የተፃፉ ፁሑፎች የራስ አስመስሎ ማሰራጨት አማና አይደለም ! 🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሓፊዘሁላህ        ~ t.me/Darutewhide

photo content
+4

ዳዕዋ ላይ ስትሰማራ አቃቂር ይፈለግልሃል ! ያለ ብቻ ሳይሆን የሌለም ይለጠፍብሃል ! 🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሓፊዘሁላህ        ~ t.me/Darutewhide

😵🤔🙁😝😤☹️🙁☹️ 🛜የመጀመሪያው ፕሮግራማችን ▶️ 🙁☹️😭🙁😭🙁☹️🙁 🎤ስለ ሒጃብ   ግዴታነት       ተ🎁              ጀ▶️                   መ ▶️                           ረ▶️ ➡️አቡ ሂበቲላህ ሁሰይን ✅ ገባ ገባ በሉ ባረከሏሁ ፊኩም! ‼  ➘  ➘ ➘ ➘➘ ➘ ➘ ➘  ➘ ➘ ➘ t.me/tdarna_islam?livestream t.me/tdarna_islam?livestream

DARU-TEWHID [ዳሩ-ተውሒድ] - Telegram kanali @darutewhide statistikasi va tahlili