ፍሬ ሃይማኖት
Kanalga Telegram’da o‘tish
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የአ/አ ሐገረ ሥብከት የመ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኤል ካ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና ሥርዓት የጠበቁ መዝሙሮች እና ወረቦች ግጥማቸው ከነዜማ የሚገኝበት ቻናል ነው፡፡ ® ለማናኛውም ሃሳብ አስተያየት ጥያቄና ጥቆማ @Frehaymanoteebot
Ko'proq ko'rsatish1 826
Obunachilar
-124 soatlar
+17 kunlar
+1430 kunlar
Postlar arxiv
1 826
+3
በምስጋና የታጀበው የሰንበት ትምህርት ቤታችን የምርጫ ሂደት በሰላም ተጠናቀቀ!!
በዛሬው ዕለት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የሦስት ዓመት የሥራ ዘመን የሚያገለግሉ አዳዲስ የሥራ አመራር አባላትን በመምረጥ በታላቅ መንፈሳዊ ድባብ ጉባዔውን አካሂዷል።
በዚህም መሠረት፡-
· አሥር (10) የሥራ አመራር አባላት በምርጫ ተለይተዋል፤
· ከእነዚህ ውስጥ የሥራ አስፈጻሚ እና ፀሐፊ ተመርጠዋል፤
· ሦስት (3) የኦዲትና ኢንስፔክሽን ፣
· አንድ (1) የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ተወካይ ተመርጠዋል።
በመጨረሻም፣ ከአጥቢያችን ካህናት የተወከሉ ሁለት አባቶች እና ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ የመጡ ታዛቢዎች የተገኙበት የባረኩበትና የንግግር መድረክ ተካሂዷል። ጉባዔው በአባቶች ቡራኬና በጸሎት ተጠናቋል።
አዲሶቹን አገልጋዮች አምላክ በጥበቡ ይምራቸው፤ እኛም በጋራ በመቆም አብረን እናገልግል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ ወለወላዲቱ ድንግል፣ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
1 826
+7
በምስጋና የታጀበው የሰንበት ትምህርት ቤታችን የምርጫ ሂደት በሰላም ተጠናቀቀ!!
በዛሬው ዕለት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የሦስት ዓመት የሥራ ዘመን የሚያገለግሉ አዳዲስ የሥራ አመራር አባላትን በመምረጥ በታላቅ መንፈሳዊ ድባብ ጉባዔውን አካሂዷል።
በዚህም መሠረት፡-
· አሥር (10) የሥራ አመራር አባላት በምርጫ ተለይተዋል፤
· ከእነዚህ ውስጥ የሥራ አስፈጻሚ እና ፀሐፊ ተመርጠዋል፤
· ሦስት (3) የኦዲትና ኢንስፔክሽን ፣
· አንድ (1) የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ተወካይ ተመርጠዋል።
በመጨረሻም፣ ከአጥቢያችን ካህናት የተወከሉ ሁለት አባቶች እና ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ የመጡ ታዛቢዎች የተገኙበት የባረኩበትና የንግግር መድረክ ተካሂዷል። ጉባዔው በአባቶች ቡራኬና በጸሎት ተጠናቋል።
አዲሶቹን አገልጋዮች አምላክ በጥበቡ ይምራቸው፤ እኛም በጋራ በመቆም አብረን እናገልግል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ ወለወላዲቱ ድንግል፣ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
1 826
"ምግባቸውን በየጊዜው ይሰጣቸው ዘንድ ጌታው በቤተሰቡ ላይ የሚሾመው ደግ ታማኝና ብልህ መጋቢ ማን ነው ?"
ሉቃስ 12÷42
አስመራጭ ኮሚቴ
1 826
✝️ 12ተኛ ዙር የሥራ አመራር ምርጫ የጸሎት መርሐ ግብር ✝️
የተወዳችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ፤
ለ12ተኛ ዙር የሰንበት ት/ቤታችን የሥራ አመራር ምርጫ በተዘጋጀው የጸሎት መርሐ ግብር ላይ በመገኘት፤ ስለ ቤተክርስቲያናችን፣ ስለ ፍጹም ሃይማኖታችን፣ ስለ አንድነታችንና ስለ አገልግሎታችን እያሳሰብን፣ እስከዛሬ በቸርነቱ ጠብቆ ለዚህ ያደረሰን አምላክ ለቀጣዩ ዘመን የተሻለ ራእይ ያላቸውን አባላት እንዲሰጠን እንጸልያለን።
ሁላችሁም በፍቅር ተጋብዛችኋል!!
🗓 ቀን፦ 28/10/2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፦ ከጥዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ 📍 ቦታ፦ ደጀ ሰላም
✨ መ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኤል ፍ/ሃ ሰ/ት/ቤት ✨
1 826
✝️ አንድነት ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት!
የመካኒሳ ደብረገነት ቅዱስ ሚካኤል ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት፤
የሰንበት ትምህርት ቤታችን የ12ኛ ዙር የሥራ አመራር ምርጫን እና የጸሎት መርሐ ግብርን በታላቅ ድምቀት ለማከናወን ተዘጋጅተናል። በዚህ መንፈሳዊ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት የአገልግሎት አሻራችሁን እንድታኖሩ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
"የመጣነው ለመማር፣ የቆምነው ለማገልገል ነው!"
🗓 ቀን፡ 28/10/2018 🕒 ሰዓት፡ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጀምሮ 📍 ቦታ፡ ደጀሰላም
1 826
🚨 የሥራ ማስታወቂያ 🚨
የድርጅት ስም: የየረር አጠቃላይ ሆስፒታል (Yerer General Hospital)
የሥራ ቦታ: ጎሮ፣ አዲስ አበባ
የሥራ ዓይነት: ሙሉ ሰዓት (Full Time)
📌 የሥራ መደብ ዝርዝር
የሥራ መደብ: ነርስ (Nurse)
የትምህርት ደረጃ: በክሊኒካል ነርሲንግ (Clinical Nursing) የቢኤስሲ (BSc) ዲግሪ የተመረቁ።
የሥራ ልምድ: አግባብ ባለው የሙያ ዘርፍ 1 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሥራ ልምድ ያለው/ላት።
📞 ማመልከቻ እና አድራሻ
ለበለጠ መረጃ እና ለመመዝገብ ከዚህ በታች ባለው ስልክ ቁጥር በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።
ስልክ ቁጥር: +251911462331
1 826
.
✝️ ታሪክ በዛሬዋ ዕለት ✝️
✝️ የመጀመርያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ ሹመት ✝️
በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ)
ሰላም ለኩልክሙ ኦ ውሉደ ፍሬ ሃይማኖት
እንደ ምን ከረማችሁ???
ተወዳጆች ሆይ!!!
በቀጥታ ወደ ዕለቱ ታሪክ ከመግባታችን በፊት ለመንደርደሪያ ይሆነን ዘንድ እስኪ ይህንን ጥያቄ መልሱ።
👉 ፓትርያርክ ማለት ምን ማለት ነው?ቃሉስ የምን አገር ነው?
ወደ ዕለቱ ታሪክ ስናመራ በረከታቸው በሁላችንም ላይ ይደርብንና በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ በአገራችን ታሪክ የመጀመርያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ በመሆን ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ የተሾሙት በዛሬዋ ዕለት ሰኔ ሃያ አንድ ቀን 1951ዓ.ም የዛሬ ስድሳ ሰባት ዓመት ነበረ ።
በነገራችን ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለ1600 ዓመታት ጳጳሳት ይላኩላት የነበረው ከግብጽ ነበር። በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ከራሷ ልጆች አራት ኢትዮጵያውያን መነኮሳት ወደ ግብጽ ተልከው ጵጵስና የተሾሙት ግንቦት 25 ቀን 1921ዓ.ም ሲሆን ከሃያ ሁለት ዓመታት በኋላም ጥር 6 ቀን 1943ዓ.ም መንፈሳዊ ማዕረጉ(ሥልጣኑ) ከጵጵስና ወደ ሊቀ ጵጵስና ከፍ ለማለት በቅቷል።
የመጀመርያው ሊቀ ጳጳስም የወደፊቱ ፓትርያርክ ብጹዕ አቡነ ባስልዮስ ነበሩ።
መጋቢት 14 ቀን 1884ዓ.ም በሰሜን ሸዋ አገረ ስብከት በመርሐ ቤቴ አውራጃ የተወለዱት ቅዱስነታቸው በተለያዩ ቦታዎች በተለይም በታላቁ የደብረ ሊባኖስ ገዳም የቤተክርስቲያናችንን ትምሕርትና የአባቶችን መንፈሳዊ ሕይወት በቃልም በተግባርም በሚገባ ሲያጠኑ ከኖሩ በኋላ በሃያ አንድ ዓመታቸው ሥርዓተ ምንኩስናን ፈጽመዋል።
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ፍጹም መናኝ እና ተሐራሚ፤ በዚያውም ላይ ትጉህ አገልጋይ ስለነበሩ መልካም ሥራቸው በመናንያኑና በአካባቢው ሕዝበ ክርስቲያን ከመታወቅ አልፎ እስከ ቤተ መንግሥት ለመድረስ ቻለ።በንጉሠ ነገሥቱም መልካም ፈቃድ የመናገሻ አምባ ማርያም ቤተክርስቲያን መምሕር(አስተዳዳሪ)፣ የግቢ ገብርኤል አለቃ፣በቅድስት አገር ኢየሩሳሌም የገዳማቱ የበላይ ኃላፊ(ራይስ) በመሆን ተመድበው የተጣለባቸውን መንፈሳዊ አደራ በትጋት የተወጡ ቅዱስ አባት ነበሩ።
ከሁለት ዓመታት የኢየሩሳሌም ቆይታ በኋላም በግርማዊነታቸው መልካም ፈቃድ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው "ብጹዕ ዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ ዘነበረ በመንበረ ተክለ ሃይማኖት" ተብለው የታላቁ የደብረ ሊባኖስ ገዳም 59ኛ እጨጌ ሆነው በመሾም በማገልገል ላይ ሳሉ ፋሽስት ኢጣልያ አገራችንን በመውረሯ ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር የምስካዬ ሕዙናን መድኃኔ ዓለምን ታቦት በመያዝ ወደ ኢየሩሳሌም ተሰደዋል። ጠላት ከአገራችን እስከ ሚወጣ ድረስ እንደ መንፈሳዊ አባትነታቸው በጾም በጸሎት እንደ ኢትዮጵያዊነታቸው ደግሞ አገራችን በጠላት ላይ ድልን ትቀዳጅ ዘንድ አርበኞችን በማበረታታት ብዙ ተግባራትን ፈጽመዋል።
ከነጻነት መመለስ በኋላም በነበራቸው የዕጨጌነት ሥልጣን በጠላት የተጎዳውን ሕዝብ በማጽናናት የፈረሱ አብያተ ክርስቲያናትን በማሳደስ ቆዩ።በፈቃደ እግዚአብሔር ሐምሌ 18 ቀን 1940ዓ.ም ወደ ካይሮ ተጉዘው "ብጹዕ አባ ባስልዮስ ጳጳስ ዘሸዋ ወዕጨጌ ዘደብረ ሊባኖስ" ተብለው በእስክንድርያው ፓትርያርክ አንብሮተ ዕድ ተሾሙ።
ከአራት ዓመት በኋላም በኢትዮጵያ የነበሩት ግብጻዊው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ ሲያርፉ ወደ ግብጽ ሔደው ጥር 6 ቀን 1943ዓ.ም የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳሳት በመሆን ተሾሙ።
በሊቀ ጳጳሳትነት ቤተ ክርስቲያንን በስፋት ሲያገለግሉ የቆዩት ቅዱስነታቸው በርሳቸው መልካም አስተዳደርና በቤተ መንግሥቱ ድጋፍ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ ነጻነቷን እንድታውጅ በመፍቀዷ ከ11 ዓመታት የሊቀ ጵጵስና አገልግሎት በኋላ ሰኔ 21 ቀን 1951ዓ.ም ብጹዕ ወቅዱስ ተብለው የመጀመርያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ ሆነው ተሾሙ።
ታላቋን የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን ለ12 ዓመታት በፓትርያርክነት ከመሩ በኋላ ጥቅምት 2 ቀን 1963ዓ.ም በተወለዱ በ79 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።እረፍታቸው እንደተሰማም በመላ አገሪቱ 12 ብሔራዊ የሐዘን ቀናት ታወጀ።
አቤት ያ መልካም ዘመን እንዴት ይናፍቃል?የቤተ ክርስቲያናችን ልዕልና፣ የንጉሠ ነገሥቱ ደግነት፣የሕዝቡ ቅንነት፣.....ሁሉም ነገር ምን አለ ተመልሶ ቢመጣ ያሰኛል።
የቅዱስነታቸው ሥርዓተ ቀብር ንጉሠ ነገሥቱ፣ብጹዓን አባቶች፣መኳንንቱና መሳፍንቱ፣ሕዝበ ክርስቲያኑ በምልዓት በተገኘበት ፊደል ቆጥረው ባደጉበት በደብረ ሊባኖስ ገዳም ጥቅምት 4 ቀን 1963ዓ.ም ተፈጽሟል።
በስማቸው የሚጠራ ትምሕርት ቤትም በዚሁ በአቅራቢያችን ከቆሼ(china camp) አጠገብ ይገኛል።
የሚያሳዝነው ግን አብዛኞቹ ሠራተኞች፣መምሕራን እና ተማሪዎች ባስልዮስ ማነው??? ተብለው ቢጠየቁ አያውቁትም።
ታሪኩን አለማወቃቸው ብቻ ሳይሆን ስማቸውን አስተካክለው መጥራት እንኳን አያውቁበትም።
ባስልዮስ በማለት ፈንታ ፓስልዮስ ይላሉ።
ለነገሩ ምን ይገርማል እኛስ አለን አይደል? ዕድሜ ልካችንን "ሰንበት" ማለት አቅቶን "ሰምበት" የምንል ልባችንን አብሮን የሌለ።በድናችን ብቻ የሚመላለስ። ማስተዋሉን ይስጠን።
የቅዱስነታቸው በረከት በሁላችንም ላይ ይደር።
ያን ተናፋቂና ደግ ዘመን አምላካችን መልሶ ያምጣልን።
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን
ተጻፈ ሰኔ 21 ቀን 2018ዓ.ም ከቀኑ በ10:00 ሰዓት።
1 826
የሥራ አመራሩን ቀንበር የሚሸከሙ ዕቅዶችን ወደ መሬት ዘርተው የሚያበቅሉ
ለተልኮ የሚፋጠኑ የሰንበት ት/ቤታችን ክንፉ ከመ መላክ የተባሉ የስራ አስፈፃሚ አደረጃጀት መልክ ደግሞ ይህን መሳይ ነው::
የሚመርጣቸውና የሚያዝባቸውም የመልካቸውን ፀዳል የሚወስነው የስራ አመራሩ ብቻ ነው::
አስመራጭ ኮሚቴ
1 826
አዲሱ የስራ አመራር በማስተባበርያ ደረጃ ያለው አደረጃጀት መልኩ ይህን ይመስላል::
የመልኩን ፀዳል ለመወሰን ሰኔ 21 በፍፁም አይቀርም::
አስመራጭ ኮሚቴ
1 826
ይህ ጉባኤ በ3ወር አንዴ እየተገናኘ ትልልቅ ውሳኔዎች የሚያሳልፍ ከጠቅላላ ጉባኤ ቀጥሎ በሰንበት ት/ቤት ውስጥ ትልቁ የአገልግሎት ዘርፍ ነው::
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
