ch
Feedback
ፍሬ ሃይማኖት

ፍሬ ሃይማኖት

前往频道在 Telegram

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የአ/አ ሐገረ ሥብከት የመ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኤል ካ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና ሥርዓት የጠበቁ መዝሙሮች እና ወረቦች ግጥማቸው ከነዜማ የሚገኝበት ቻናል ነው፡፡ ® ለማናኛውም ሃሳብ አስተያየት ጥያቄና ጥቆማ @Frehaymanoteebot

显示更多
1 815
订阅者
无数据24 小时
+17
-830
帖子存档
.             ✝️ ታሪክ በዛሬዋ ዕለት ✝️ ❤️‍🩹❤️‍🩹❤️‍🩹 ቀዳሚዋ(የመጀመሪያዎቹ መጀመሪያ) ዕለት በደብረ ገነት ❤️‍🩹❤️‍🩹❤️‍🩹         ✝️ ሰኔ 4  ቀን 1984 ዓ.ም ✝️       በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ) "ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር" "እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት" መዝ.117፥24 ሰላም ለኩልክሙ ኦ ውሉደ ደብረ ገነት( ፍሬ ሃይማኖት) በሩቅና በቅርብ፣በአገር ውስጥና ከባሕር ማዶ የምትገኙ የደብረ ገነት(የፍሬ ሃይማኖት) ልጆች በሙሉ እንደምን ከረማችሁ??? ሰላምና ጤና፣ ጸጋና በረከት ለሁላችሁ ይሁን። ተወዳጆች ሆይ‼️ ይህንን ልዩ የሆነ ታሪክ ለመጻፍ ስነሳ አንድ ነገር ከፊት ለፊቴ መጥተቶ ድቅን እያለ ቢያስቸግረኝ  ከታሪኩ በማስቀደም ለእናንተ ለክቡራን አንባብያን ላወጋችሁ ወደድኩ። ይኸውም ምንድነው የዚህ ድንቅና ዘመን አይሽሬ ታሪክ ባለቤቶች የነበሩ ሰዎች በሙሉ ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ በሕይወተ ሥጋ ቢኖሩና ዘመናትን ተሻግረው  ለዛሬዋ ቀን ቢደርሱ፤ ብሎም ብዙ ዋጋ የከፈሉለትን ቤተ ክርስቲያን ዕድገቱን እና ለውጡን ቢመለከቱ፤ በተጨማሪም የአካባቢውን መቀየር የሕዝቡንም መብዛት ማየት ቢችሉ እንዴት መልካም ነበር❓❓❓ አሁን በቀጥታ ሠላሳ አራት ዓመታትን የኋሊት በምናብ ይዘናችሁ እንጓዝ እናንተም በእግረ ልቡና ተከተሉን። ዕለቱ ዕለተ ሐሙስ፣ ወሩ አሰረኛው ወር ወርኃ ሰኔ ሲሆን ዓመተ ምሕረቱ ደግሞ 1984ዓ.ም ነው።ልክ የዛሬ ሠላሳ አራት ዓመት መሆኑ ነው።ሰዓቱ ማለዳ ሁለት ሰዓት ገደማ ሲሆን ለጥ ባለውና አሁን የደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በተተከለበት ስፍራ ጥቂት አበው ካሕናትና ቁጥራቸው ብዙም ያልሆነ ምዕመናን ተሰባስበዋል።በመሃከላቸውም  ስፋቱ በግምት አምስት በአምሰት (25 ካሬ) የሆነ  አነስተኛ ቦታ ዙርያው ተቆፍሮ ይታያል። ከተቆፈረው ስፍራ ጥቂት ራቅ ብሎም ሁለትና ሶስት ቦታ ላይ ጥርብ ድንጋይ ተገልብጦ ይታያል። ይህም ድንጋይ ቤተ ክርስቲያኑን ለመትከል የተቋቋመው ኮሚቴ የአካባቢውን ሕዝበ ክርስቲያን በማስተባበር ባሰባሰበው ገንዘብ ለአዲሡ መቃኞ ግንባታ የተገዛ ማቴሪያል ነበር።        በነገራችን ላይ አሁን ቤተክርስቲያኑ የተተከለበት ስፍራ በንጉሡ(በአጼ ኃይለ ሥላሴ) ጊዜ የመንበረ መንግሥት(ግቢ) ገብርኤል ርስት እንደነበረ አንጋፋ የአገር ሽማግሌ የነበሩት አቶ ኃይለ ኢየሱስ ገብረ ሚካኤል በአንድ ወቅት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።ኋላም በደርግ ጊዜ አሁን በግቢው የሚገኘው ቀይ ባሕር ዛፍ ተተክሎበት ጥቅጥቅ ያለ ጫካ ሆኖ ቆይቷል። ከ1977ዓ.ም ጀምሮም የሕዝብ ደሕንነት መሥሪያ ቤት ዙርያ መለሱን አጥሮት ውስጡ የአራዊት መናኸሪያ ሆኖ ቆይቷል።በኋላም በ1983ዓ.ም የተከሰተውን የመንግሥት ለውጥ ተከትሎ ጫካው አንዳንድ ኃላፊነት በጎደላቸው ሰዎች አማካይነት ተመንጥሮ  በጥቂት ቀናት ውስጥ በተምች እንደተወረረ መስክ  ምድረ በዳ(አውላላ ሜዳ) ሆነ። ወደ ታሪኩ ስንመለስ ሰኔ 4 ቀን 1984ዓ.ም ኮሚቴውና አባቶች በዕለቱ ሥራና ትምሕርት ዝግ መሆኑን ተከትሎ ባደረጉት ቅስቀሳ ሕዝበ ክርስቲያኑ ነገ የሚጸልይበትን እና ሥጋ ወደሙ የሚቀበልበትን ልጆቹንም ክርስትና የሚያስነሳበትን መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ለመገንባት ሲል በንቃትና በጉጉት በአጭር ታጥቆ ማልዶ ወጥቷል።የአየር ጸባዩም ሆነ ምድሩ ደስ የሚያሰኙ ሲሆን ቀደም ብሎ የጣለው የበልግ ዝናምም ምድሪቱን አለምልሟት አረንጓዴ መጎናጸፊያን አልብሷታል።ፀሐይቱም የማለዳ ጮራዋን ፈንጥቃለች። በእንዲሕ ያለ ሁናቴ የተሰባሰቡት  ምዕመናን አብዛኞቹ  አዲስ ቤት ሠርተው የገቡ በመሆናቸው አይተዋወቁም።ካሕናቱም ከጥቂቶቹ በስተቀር ለአካባቢው እንግዶች  ስለሆኑ ትውውቅ የላቸውም ነበር።ሆኖም ግን አንድ የተቀደሠ ዓላማ ርስ በርስ  እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ነጋሪ  አስተሳስሯቸዋል። በሰዓቱ ወንድ ሴት፣ካህን ምዕመን፣ትልቅ ትንሽ፣...... ሳይሉ ሲተጉ ለተመለከተ እውነትም ነገሩ ከልዑል እግዚአብሔር እንደሆነ ይረዳል።ግንበኞች ድንጋይ ይጠርባሉ፣ ሕዝቡ የተጠረበውን ድንጋይ ጥንድ ጥንድ በመሆን  በባሬላ ወደተቆፈረው ስፍራ ያጓጉዛል። ግማሹ ሲሚንቶና አሸዋውን ያዋሕዳል(ያቦካል)፣ እናቶችና እህቶች ውሃ ከየመንደሩ ይቀዳሉ።እንዲህ እንዲህ እያለ ሥራው ቀጥሎ ግንበኞቹ እጅ በእጅ የመቃኞ ቤተ ክርስቲያኑን መሠረት ገነቡትትትትትትት። በዚያች ቅጽበትም አሁን የሠላሳ ሶስት ዓመት ጎልማሳ የሆነው የመካኒሳው ቅዱስ ሚካኤል አካልን በመንሳት ተወለደ።ይህች ቀን ምን ያህል የተወደደችና የተባረከች ቀን ናት።  በዕለቱ የዚህ  ታሪክ ፀሐፊ ግን ሥራውን እየሠራ(ባሬላውን እንደተሸከመ) አንድ ጥያቄ በልጅነት አዕምሮው እየተመላለሰ ያስጨንቀው ነበር።ይኸውም ጥያቄ ምንድነው የሰኔ ዓመታዊ ክብረ በዓል ስምንት ቀን ብቻ ነው የቀረው። ቤተ ክርስቲያኑ እንዴት በዚች አጭር ቀን ይደርሳል???አይ ልጅነት(የዋሕነት)። ድንገትም ሳያስበው ድምጽ አውጥቶ አብሮት ባሬላ የተሸከመውን ሰው እንዲህ ሲል ጠየቀው በአንድ ሳምንት እንዴት ይደርሳል??? የሰውየውም ምላሽ አጭርና ግልጽ ነበር "እኔ እንጃ‼️" የሚል። ‼️አሁንስ ብዙዎቻችን ስለደብረ ገነትና ስለ ፍሬ ሃይማኖት ስንጠየቅ መልሳችን ምን ይሆን❓❓❓ እኔ እንጃ‼️ይሆንን❓❓❓ እነሆ ለ1984ቱ የሰኔ ሚካኤል ያልደረሠው መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ክረምቱን ተሻግሮ፣ እንዲፈርስ የተበየነበትንም ብያኔ አሸንፎ፣ አሮጌውን ዓመት(1984ን) ሸኝቶ፣.......ቅዱስ ሚካኤል በአዲሡ ዓመት(1985) ለህዳር ሚካኤል ከች አለ። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን ተጻፈ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ረፉድ 4:00 ሰዓት።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። የመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን "ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት" አባላት በሙሉ፦ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። የመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን "ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት" አባላት በሙሉ፦ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የተላከውን አጠቃላይ የመዋቅር ስልጠና ለመውሰድ ቀጠሮ ተይዟል። በመሆኑም፡- ·         ቀን፦ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ·         ሰዓት፦ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ ·         ቦታ፦ በቤተክርስቲያናችን ደጀ ሰላም አዳራሽ ይህ ስልጠና የመንፈሳዊ ህይወታችንን እና የአገልግሎታችንን ጥራት የሚያሳድግ በመሆኑ፣ ከመስራች አባላት ጀምሮ እስከ አዲሱ አባል ድረስ ያላችሁ ሁሉ በሰዓቱ ተገኝታችሁ በረከቱን እንድትካፈሉ በእግዚአብሔር ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። "አገልግሎታችን ለእግዚአብሔር፤ ህይወታችን ለቤተክርስቲያን!"     ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት

የፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ዛሬ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤታችን የተካሄደው ሁሉን አቀፍ የአንድነት ጉባዔ፣ በእግዚአብሔር ቸርነት እና በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት በ
+5
የፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ዛሬ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤታችን የተካሄደው ሁሉን አቀፍ  የአንድነት ጉባዔ፣ በእግዚአብሔር ቸርነት እና በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት በታላቅ ድምቀት ተጠናቋል። በጉባዔው የተከናወኑ ዋና ዋና ኩነቶች፡ ✨ መንፈሳዊ ትምህርት፡ በተጋባዥ መምህራን አማካኝነት የተሰጠውን ጥልቅ ትምህርተ ወንጌል እንዲሁም በበገና ዝማሬና በግጥሞች የታጀበውን መርሐ ግብር በመከታተል መንፈሳችንን ያደስንበት፣ በቃለ እግዚአብሔር የታነጽንበት በረከት የሞላበት ጊዜ ነበር። 🗳 የአመራር ምርጫና ግንዛቤ፡ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ባወረደው መዋቅርና መመሪያ መሠረት፤ የስራ አመራር አስመራጭ ኮሚቴ ተዋቅሮ ቀጣዩን የአመራር ምርጫ በስርዓት እና በግልጽነት ለማካሄድ የሚያስችል አቅጣጫ ተቀምጧል። በዚህም መሠረት ስለ መዋቅሩ አስፈላጊነት እና አተገባበር ለአባላት ሰፊ ግንዛቤ ተሰጥቷል። በመጨረሻም፣ ጉባዔውን በጸሎት እና በምስጋና አጠናቀናል። በዕለቱ የተሳተፋችሁ አባላት ሁሉ የእግዚአብሔር ቸርነት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።🙏🙏

photo content
+4

photo content
+9

🙏 አይቀርም! የአንድነት ጉባዔ ✨ ልብን የሚያድስ ትምህርት፣ ዝማሬ እና ውይይት በአንድ ላይ! በኅብረት የምንቆይበት ይህ ታላቅ ጉባዔ ለነፍስዎ በረከት ይዞ ይመጣል። ፕሮግራሙ የጠዋቱን ጊዜ ስለምን
🙏 አይቀርም! የአንድነት ጉባዔ ✨ ልብን የሚያድስ ትምህርት፣ ዝማሬ እና ውይይት በአንድ ላይ! በኅብረት የምንቆይበት ይህ ታላቅ ጉባዔ ለነፍስዎ በረከት ይዞ ይመጣል። ፕሮግራሙ የጠዋቱን ጊዜ ስለምንጠቀም በሰዓቱ ተገኝተው በረከቱን ይሳተፉ። 📅 ግንቦት 30ከጠዋቱ 3:00 - 6:00 📍 በደጀሰላም!!

🌟 የእሁድ ጠዋት ቀጠሮዎትን በፍሬ ሃይማኖት ያድርጉ! 🌟 የመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ባዘጋጀው ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
🌟 የእሁድ ጠዋት ቀጠሮዎትን በፍሬ ሃይማኖት  ያድርጉ! 🌟 የመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ባዘጋጀው ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል። 📅 ቀን፦ እሑድ ግንቦት 30 / 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፦ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ 📍 ቦታ፦ መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በዕለቱ ምን ይጠብቅዎታል? ✅ ነፍስን የሚያረካ መንፈሳዊ ትምህርት ✅ ልብን የሚያርሱ ድንቅ መዝሙራት ✅ ልዩ የኪነ-ጥበብ ዝግጅቶችና ያልተሰሙ መርሃ ግብሮች

በወንድሞች መተባበር መልካም ነው!" የፊታችን እሑድ ወርሀዊ የጽዋ እና የአጠቃላይ የጉባዔ ቀናችን ነው። እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነን በጋራ የምንጸልይበትና በረከትን የምን
በወንድሞች መተባበር መልካም ነው!" የፊታችን እሑድ ወርሀዊ የጽዋ እና የአጠቃላይ የጉባዔ ቀናችን ነው። እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነን በጋራ የምንጸልይበትና በረከትን የምንካፈልበት ዕለት በመሆኑ፣ ማንም ሳይቀር ሁላችሁም በፍቅር ተጠርታችኋል። 📌 ቀን፦ እሑድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፦ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ 📍 ቦታ፦ በፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ "የሁላችንም መገኘት ለጉባዔው ጥንካሬ ነውና በሰዓቱ እንገናኝ!" 🙏✨

የ2018 የዕርገት ክብረ በዓል በደብራችን በመካኒሳ ደብረገነት ቅዱስ ሚካል በከፊል
+4
የ2018 የዕርገት ክብረ በዓል በደብራችን በመካኒሳ ደብረገነት ቅዱስ ሚካል በከፊል

photo content
+9

photo content
+9