es
Feedback
ፍሬ ሃይማኖት

ፍሬ ሃይማኖት

Ir al canal en Telegram

በኢ/ኩ/ተ/ቀ/ክ ዹአ/አ ሐገሹ ሥብኚት ዹመ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኀል ካ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቀት ዚቀተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና ሥርዓት ዹጠበቁ መዝሙሮቜ እና ወሚቊቜ ግጥማ቞ው ኹነዜማ ዚሚገኝበት ቻናል ነው፡፡ ® ለማናኛውም ሃሳብ አስተያዚት ጥያቄና ጥቆማ @Frehaymanoteebot

Mostrar más
1 826
Suscriptores
-124 horas
+17 días
+1430 días
Archivo de publicaciones
"ምግባ቞ውን በዹጊዜው ይሰጣ቞ው ዘንድ ጌታው በቀተሰቡ ላይ ዚሚሟመው ደግ ታማኝና ብልህ መጋቢ ማን ነው ?" ሉቃስ 12÷42 አስመራጭ ኮሚ቎
"ምግባ቞ውን በዹጊዜው ይሰጣ቞ው ዘንድ ጌታው በቀተሰቡ ላይ ዚሚሟመው ደግ ታማኝና ብልህ መጋቢ  ማን ነው ?"                    ሉቃስ 12÷42                     አስመራጭ ኮሚ቎

ኑ ኚእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር አብሚን እንስራ አስመራጭ ኮሚ቎
ኑ ኚእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር አብሚን እንስራ        አስመራጭ ኮሚ቎

✝ 12ተኛ ዙር ዚሥራ አመራር ምርጫ ዚጞሎት መርሐ ግብር ✝ ዚተወዳቜሁ ዚሰንበት ትምህርት ቀታቜን አባላት በሙሉፀ ለ12ተኛ ዙር ዚሰንበት ት/ቀታቜን ዚሥራ አመራር ምርጫ በተዘጋጀው ዚጞሎት መርሐ ግብር ላይ በመገኘትፀ ስለ ቀተክርስቲያናቜን፣ ስለ ፍጹም ሃይማኖታቜን፣ ስለ አንድነታቜንና ስለ አገልግሎታቜን እያሳሰብን፣ እስኚዛሬ በ቞ርነቱ ጠብቆ ለዚህ ያደሚሰን አምላክ ለቀጣዩ ዘመን ዚተሻለ ራእይ ያላ቞ውን አባላት እንዲሰጠን እንጞልያለን። ሁላቜሁም በፍቅር ተጋብዛቜኋል!! 🗓 ቀን፩ 28/10/2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓትፊ ኚጥዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ 📍 ቊታፊ ደጀ ሰላም ✹ መ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኀል ፍ/ሃ ሰ/ት/ቀት ✹

✝ አንድነት ለቀተ ክርስቲያን አገልግሎት! ዚመካኒሳ ደብሚገነት ቅዱስ ሚካኀል ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቀት አባላትፀ ዚሰንበት ትምህርት ቀታቜን ዹ12ኛ ዙር ዚሥራ አመራር ምርጫን እና ዚጞሎት መርሐ ግብርን በታላቅ ድምቀት ለማኹናወን ተዘጋጅተናል። በዚህ መንፈሳዊ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት ዚአገልግሎት አሻራቜሁን እንድታኖሩ ጥሪያቜንን እናስተላልፋለን። "ዚመጣነው ለመማር፣ ዹቆምነው ለማገልገል ነው!" 🗓 ቀን፡ 28/10/2018 🕒 ሰዓት፡ ኚጠዋቱ ሊስት ሰዓት ጀምሮ 📍 ቊታ፡ ደጀሰላም

🚚 ዚሥራ ማስታወቂያ 🚚 ዚድርጅት ስም: ዹዹሹር አጠቃላይ ሆስፒታል (Yerer General Hospital) ዚሥራ ቊታ: ጎሮ፣ አዲስ አበባ ዚሥራ ዓይነት: ሙሉ ሰዓት (Full Time) 📌 ዚሥራ መደብ ዝርዝር ዚሥራ መደብ: ነርስ (Nurse) ዚትምህርት ደሹጃ: በክሊኒካል ነርሲንግ (Clinical Nursing) ዚቢኀስሲ (BSc) ዲግሪ ዚተመሚቁ። ዚሥራ ልምድ: አግባብ ባለው ዚሙያ ዘርፍ 1 ዓመት እና ኚዚያ በላይ ዚሥራ ልምድ ያለው/ላት። 📞 ማመልኚቻ እና አድራሻ ለበለጠ መሹጃ እና ለመመዝገብ ኹዚህ በታቜ ባለው ስልክ ቁጥር በመደወል መጠዹቅ ይቜላሉ። ስልክ ቁጥር: +251911462331

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ እኚህ ነበሩ።
+1
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ እኚህ ነበሩ።

.              ✝ ታሪክ በዛሬዋ ዕለት ✝ ✝ ዚመጀመርያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ ሹመት ✝           በደሹጀ እሞ቎(ወልደ ሥላሎ) ሰላም ለኩልክሙ ኩ ውሉደ ፍሬ ሃይማኖት እንደ ምን ኚሚማቜሁ???    ተወዳጆቜ ሆይ!!!    በቀጥታ ወደ ዕለቱ ታሪክ ኚመግባታቜን በፊት ለመንደርደሪያ ይሆነን ዘንድ  እስኪ ይህንን ጥያቄ መልሱ። 👉 ፓትርያርክ ማለት ምን ማለት ነው?ቃሉስ ዹምን አገር ነው?       ወደ ዕለቱ ታሪክ ስናመራ በሚኚታ቞ው በሁላቜንም ላይ ይደርብንና በኢትዮጵያ ቀተ ክርስቲያንም ሆነ በአገራቜን  ታሪክ ዚመጀመርያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ በመሆን ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ዚተሟሙት  በዛሬዋ ዕለት ሰኔ ሃያ አንድ ቀን 1951ዓ.ም  ዚዛሬ ስድሳ ሰባት ዓመት ነበሹ ።         በነገራቜን ላይ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ለ1600 ዓመታት ጳጳሳት ይላኩላት ዹነበሹው ኚግብጜ ነበር። በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ኚራሷ ልጆቜ አራት ኢትዮጵያውያን መነኮሳት ወደ ግብጜ ተልኹው ጵጵስና ዚተሟሙት ግንቊት 25 ቀን 1921ዓ.ም ሲሆን ኚሃያ ሁለት ዓመታት በኋላም ጥር 6 ቀን 1943ዓ.ም መንፈሳዊ ማዕሹጉ(ሥልጣኑ) ኚጵጵስና ወደ ሊቀ ጵጵስና ኹፍ ለማለት በቅቷል።       ዚመጀመርያው ሊቀ ጳጳስም ዚወደፊቱ ፓትርያርክ ብጹዕ አቡነ ባስልዮስ ነበሩ።    መጋቢት 14 ቀን 1884ዓ.ም በሰሜን ሾዋ አገሹ ስብኚት በመርሐ ቀ቎ አውራጃ ዚተወለዱት ቅዱስነታ቞ው በተለያዩ ቊታዎቜ በተለይም በታላቁ ዚደብሚ ሊባኖስ ገዳም ዚቀተክርስቲያናቜንን ትምሕርትና ዚአባቶቜን መንፈሳዊ ሕይወት በቃልም በተግባርም  በሚገባ ሲያጠኑ ኚኖሩ በኋላ በሃያ አንድ ዓመታ቞ው ሥርዓተ ምንኩስናን ፈጜመዋል።       ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ፍጹም መናኝ እና ተሐራሚፀ በዚያውም ላይ ትጉህ አገልጋይ ስለነበሩ መልካም ሥራ቞ው በመናንያኑና በአካባቢው ሕዝበ ክርስቲያን ኚመታወቅ አልፎ እስኚ ቀተ መንግሥት ለመድሚስ ቻለ።በንጉሠ ነገሥቱም መልካም ፈቃድ ዚመናገሻ አምባ ማርያም ቀተክርስቲያን መምሕር(አስተዳዳሪ)፣ ዚግቢ ገብርኀል አለቃ፣በቅድስት አገር ኢዚሩሳሌም ዚገዳማቱ ዹበላይ ኃላፊ(ራይስ) በመሆን ተመድበው ዚተጣለባ቞ውን መንፈሳዊ አደራ  በትጋት ዚተወጡ  ቅዱስ አባት ነበሩ።     ኚሁለት ዓመታት ዚኢዚሩሳሌም ቆይታ በኋላም በግርማዊነታ቞ው መልካም ፈቃድ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው "ብጹዕ ዕጹጌ ገብሚ ጊዮርጊስ ዘነበሹ በመንበሹ ተክለ ሃይማኖት" ተብለው ዚታላቁ ዚደብሚ ሊባኖስ ገዳም 59ኛ እጚጌ ሆነው  በመሟም በማገልገል ላይ ሳሉ ፋሜስት ኢጣልያ አገራቜንን በመውሚሯ  ኹንጉሠ ነገሥቱ ጋር  ዚምስካዬ ሕዙናን መድኃኔ ዓለምን ታቊት በመያዝ ወደ ኢዚሩሳሌም ተሰደዋል። ጠላት ኚአገራቜን እስኚ ሚወጣ ድሚስ እንደ መንፈሳዊ አባትነታ቞ው በጟም በጞሎት እንደ ኢትዮጵያዊነታ቞ው ደግሞ አገራቜን በጠላት ላይ ድልን ትቀዳጅ ዘንድ አርበኞቜን በማበሚታታት ብዙ ተግባራትን ፈጜመዋል።       ኚነጻነት መመለስ በኋላም በነበራ቞ው ዚዕጚጌነት ሥልጣን በጠላት ዚተጎዳውን ሕዝብ በማጜናናት ዚፈሚሱ አብያተ ክርስቲያናትን በማሳደስ ቆዩ።በፈቃደ እግዚአብሔር  ሐምሌ 18 ቀን 1940ዓ.ም ወደ ካይሮ ተጉዘው "ብጹዕ አባ ባስልዮስ ጳጳስ ዘሾዋ ወዕጹጌ ዘደብሚ ሊባኖስ" ተብለው በእስክንድርያው ፓትርያርክ አንብሮተ ዕድ ተሟሙ።        ኚአራት ዓመት በኋላም በኢትዮጵያ ዚነበሩት ግብጻዊው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ ሲያርፉ ወደ ግብጜ ሔደው ጥር 6 ቀን 1943ዓ.ም ዚኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳሳት በመሆን ተሟሙ።      በሊቀ ጳጳሳትነት ቀተ ክርስቲያንን በስፋት ሲያገለግሉ ዚቆዩት ቅዱስነታ቞ው በርሳ቞ው መልካም አስተዳደርና በቀተ መንግሥቱ ድጋፍ ዚግብጜ ቀተ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ቀተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ ነጻነቷን እንድታውጅ በመፍቀዷ ኹ11 ዓመታት ዹሊቀ ጵጵስና አገልግሎት በኋላ ሰኔ 21 ቀን 1951ዓ.ም ብጹዕ ወቅዱስ ተብለው ዚመጀመርያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ  ሆነው ተሟሙ።     ታላቋን ዚኢ/ኩ/ተ/ቀ/ያን ለ12 ዓመታት በፓትርያርክነት ኚመሩ በኋላ ጥቅምት 2 ቀን 1963ዓ.ም በተወለዱ በ79 ዓመታ቞ው ኹዚህ ዓለም ድካም አሚፉ።እሚፍታ቞ው እንደተሰማም በመላ አገሪቱ 12 ብሔራዊ ዹሐዘን ቀናት ታወጀ።        አቀት ያ መልካም ዘመን እንዎት ይናፍቃል?ዚቀተ ክርስቲያናቜን ልዕልና፣ ዹንጉሠ ነገሥቱ ደግነት፣ዚሕዝቡ ቅንነት፣.....ሁሉም ነገር  ምን አለ ተመልሶ ቢመጣ ያሰኛል።     ዚቅዱስነታ቞ው ሥርዓተ ቀብር ንጉሠ ነገሥቱ፣ብጹዓን አባቶቜ፣መኳንንቱና መሳፍንቱ፣ሕዝበ ክርስቲያኑ በምልዓት በተገኘበት ፊደል ቆጥሚው ባደጉበት በደብሚ ሊባኖስ ገዳም ጥቅምት 4 ቀን 1963ዓ.ም ተፈጜሟል።     በስማ቞ው ዚሚጠራ  ትምሕርት ቀትም በዚሁ በአቅራቢያቜን ኚቆሌ(china camp) አጠገብ ይገኛል።      ዚሚያሳዝነው ግን አብዛኞቹ ሠራተኞቜ፣መምሕራን እና ተማሪዎቜ ባስልዮስ ማነው??? ተብለው ቢጠዚቁ አያውቁትም።       ታሪኩን አለማወቃቾው ብቻ ሳይሆን ስማ቞ውን  አስተካክለው መጥራት እንኳን አያውቁበትም። ባስልዮስ በማለት ፈንታ ፓስልዮስ ይላሉ። ለነገሩ ምን ይገርማል እኛስ አለን አይደል? ዕድሜ ልካቜንን "ሰንበት" ማለት አቅቶን "ሰምበት" ዹምንል ልባቜንን አብሮን ዚሌለ።በድናቜን ብቻ ዚሚመላለስ። ማስተዋሉን ይስጠን። ዚቅዱስነታ቞ው በሚኚት በሁላቜንም ላይ ይደር። ያን ተናፋቂና ደግ ዘመን አምላካቜን መልሶ ያምጣልን። ሰላመ እግዚአብሔር ኚሁላቜን ጋር ይሁን ተጻፈ ሰኔ 21 ቀን 2018ዓ.ም ኹቀኑ በ10:00 ሰዓት።

አስመራጭ ኮሚ቎
አስመራጭ ኮሚ቎

ዚሥራ አመራሩን ቀንበር ዹሚሾኹሙ ዕቅዶቜን ወደ መሬት ዘርተው ዚሚያበቅሉ ለተልኮ ዹሚፋጠኑ ዚሰንበት ት/ቀታቜን ክንፉ ኹመ መላክ ዚተባሉ ዚስራ አስፈፃሚ አደሚጃጀት መልክ ደግሞ ይህን መሳይ ነው:: ዹ
ዚሥራ አመራሩን ቀንበር ዹሚሾኹሙ ዕቅዶቜን ወደ መሬት ዘርተው ዚሚያበቅሉ ለተልኮ ዹሚፋጠኑ ዚሰንበት ት/ቀታቜን ክንፉ ኹመ መላክ ዚተባሉ ዚስራ አስፈፃሚ አደሚጃጀት መልክ ደግሞ ይህን መሳይ ነው:: ዚሚመርጣ቞ውና ዚሚያዝባ቞ውም ዚመልካ቞ውን ፀዳል ዚሚወስነው ዚስራ አመራሩ ብቻ ነው:: አስመራጭ ኮሚ቎

አዲሱ ዚስራ አመራር በማስተባበርያ ደሹጃ ያለው አደሚጃጀት መልኩ ይህን ይመስላል:: ዚመልኩን ፀዳል ለመወሰን ሰኔ 21 በፍፁም አይቀርም:: አስመራጭ ኮሚ቎
አዲሱ ዚስራ አመራር በማስተባበርያ ደሹጃ ያለው አደሚጃጀት መልኩ ይህን ይመስላል:: ዚመልኩን ፀዳል ለመወሰን ሰኔ 21 በፍፁም አይቀርም:: አስመራጭ ኮሚ቎

ይህ ጉባኀ በ3ወር አንዮ እዚተገናኘ ትልልቅ ውሳኔዎቜ ዚሚያሳልፍ ኹጠቅላላ ጉባኀ ቀጥሎ በሰንበት ት/ቀት ውስጥ ትልቁ ዚአገልግሎት ዘርፍ ነው::
ይህ ጉባኀ በ3ወር አንዮ እዚተገናኘ ትልልቅ ውሳኔዎቜ ዚሚያሳልፍ ኹጠቅላላ ጉባኀ ቀጥሎ በሰንበት ት/ቀት ውስጥ ትልቁ ዚአገልግሎት ዘርፍ ነው::

ዚሰንበት_ትምህርት_ቀቱ_ነባር_አፈፃፀም_መሙያ_ቅፅ_አሁን_ባለው_ስራ_አምራር_ዹሚሞላ.pdf1.13 MB

1_አንድ_ዚጥናትና_ምርምሩ_ሊይዘው_ዚሚገባ_ዋና_ዋና_ሃሳብ.pdf1.26 KB

ነገሹ ቀተ ክርስቲያን.pdf2.17 MB

✝✝✝ ዝክሹ ቅዱሳን ✝✝✝ በደሹጀ እሞ቎(ወልደ ሥላሎ) ✝ አባ ይስሐቅ( አባ ገሪማ) ✝ አባ ይስሐቅ (አባ ገሪማ) አባቱ ዚሮም ንጉሥ መስፍንያኖስ እናቱ ንግሥተ ሮማ ሰፍንግያ ይባላሉ፡፡እናቱ መክና ስትኖር እመቀታቜንን ተማጜና ልጅ ወለደቜ ስሙንም ይሰሐቅ ብለው ሰዚሙት፡፡ ዕድሜው ለትምህርት ሲደርስም ዚቀተ ክርስቲያንን ትምሕርት ተምሮ ዲቁናን ተቀብሏል፡፡አባቱ ሲሞት በሮም 7 ዓመት በንጉሥነት ተቀመጠ፡፡ አባ ጰንጠሌዎንም ለአባ ገሪማ " አንተስ ዚክርስቶስን መንግሥት ትሻ ዘንድ ወደ እኔ ና" ብሎ መልዕክት ላኚበት፡፡ መልእክቱ እንደ ደሹሰው ቅዱስ ገብርኀል ዹ10 ወር ዚእግር ጎዳና ዹነበሹውን በክንፉ ተሾክሞ በ3 ሰዓት ወደ ኢትያጵያ በማምጣት በአክሱም ኹጰንጠሌዎን ጋር ጚመሚው፡፡ጰንጠሌዎንም በደስታ ተቀብሎ አልባሰ ምንኩስና አለበሰው፡፡ ኚተሰዓቱ(ኹዘጠኙ) ቅዱሳን በመጚሚሻ ወደ ኢትዮጵያ ዚመጣው አባ ይስሐቅ(አባ ገሪማ) ነው። ኹዚህም በኋላ በቀተ ቀጢን ዚሀገሪቱን ቋንቋና ባሕል ኹአጠና በኋላ ኚአድዋ በስተምስራቅ 10 ኪ/ሜ ያህል ርቆ ዹሚገኘውን ዚመደራን ገዳም መሥርቷዋል፡፡ በገዳሙም በጟም በጞሎት፣ በገድል በትሩፋት ተወሰኖ ሥጋው ኚአጥንቱ እሰኪጣበቅ ድሚስም በመጋደል አጋንንትን ያወጣ፣ ሕሙማንን ይፈውስ፣ ዚተለያዩ ተአምራትን ያደርግ ነበር፡፡ ኚተአምራቶቹ ውስጥ ጥቂቶቜን እንኳን ብንመለኚት፣ 👉 በአንድ ቀን ስንዎ ዘርቶ ማታ ለቁርባን አድርሷል፡፡ 👉 እንዲሁ በማግስቱ ነዶውን ኚግራር ላይ በማውጣት በበሬ አበራይቶ ምርትን አምርቷል፡፡ 👉 ዹወይን ሐሹግ ኚዐለት ላይ ተክሎ አብባ አፍርታ ለመሥዋዕት ደርሳለታለቜ፡፡ 👉 አንድ ቀን ሲጜፍ ፀሐይ እንዳትገባ ገዝቶ ጜሕፈቱን አስቲጚሚስ ድሚስ አቁሟታል፡፡ 👉 ምራቁን ዚተፋበት ቊታ ፈውስ ኹኖ እስኚ ዛሬ ድሚስ ያገለግላል፡፡ 👉 ዚሚጜፍበት ብርዕ ወድቆበት ወዲያው በቅሎ ለምልሞ ዐድጓል፡፡ ✝ ገሪማ ገሹምኹኒ ✝ ኚዕለታት በአንድ ቀን ለተግባር ወጥቶ ነበር። ኚመነኮሳቱ ጋር ምግብ ለመብላት ተቀምጠው ሳለ እነርሱ ሲመገቡ እርሱ ግን ኚሄደበት ሲመለስ ቅዳሎ እንደ ሚታጎል ስላወቀ ዹበላ በመምሰል ሳይመገብ ቀሚ።ኚተመለሰ በኋላም ቅዳሎ ገብቶ ቀደሰ፡፡ መነኮሳቱ ወደ አባ ጰንጀሌዎን መጥተው አባ ይስሐቅ ኹበላ በኃላ ቀደሰ ብለው ኚሰሱት፡፡ እሱም ሊመሹምሹው ፈልጎ "ልጄ ይሰሐቅ ሰዎቜህን ኚአጠገብህ አስገልል(አርቅ)" አለው፡፡ ይሰሐቅም "ሰዎቜን ተውና ዕንጚቶቜና ድንጋዮቜ ይገለሉ" ሲል ተናገሚ፡፡ በዚያን ጊዜ ዕንጚቶቜና ድንጋዮቜ አንድ ምዕራፍ ሞሜተው ተገለሉ፡፡ አባ ጰንጠሌዎንም እጅግ ተገሚሙ። "ልጄ ይስሐቅ ገሹምኾኝ(ገሹምኹኒ)" አለ። ኚዚያቜ ዕለት ጀምሮም ገሪማ ተባለ፡፡ መልካም ተጋድሎ ኹፈጾመ በኃላ ጌታቜን ተገልጟ ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡ "ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውን ለሚያደርግ መጜሐፈ ገድሉን ያነበበውን ዹተሹጎመውን በሕይወት መጜሐፍ ስሙን እንደሚጜፍለትፀ እንደ ገና በስሙ ለተራበ ላበላ ለተጠማ ላጠጣ ኚሕይወት እንጀራ አጠግበዋለሁ ኚሕይወት ጜዋዕ አሚካዋለሁ አለው፡፡ መካነ መቃብርህን ዚሚያኚብሚውን አክብሚዋለሁ፡፡ በቀተ ክርስቲያንህ ውስጥ ማኅሌት ዹቆመውን ጞሎት ያደሚሰውን ዝማሬ መላዕክት አሰማዋለሁ፡፡ ኚዚያም ዚሞት ጥላ እንደ ማያገኘህ ታላቅ ዚምስራቜ እነግርሃለኹ" ብሎ ተስፋውን ነግሮት ኚእሱ ተሰወሚ፡፡ አባ ገሪማም በጣም ተደሰተ፡፡ ያን ጊዜ በሠሹገላ ብርሃን ተነጥቆበ ሰኔ 17 ቀን ወደ ብሔሚ ሕያዋን ተሰወሚ፡፡ ዚጻድቁ አባታቜን ዚአባ ገሪማ ፀሎታ቞ው፣በሚኚታ቞ው አማላጅነታ቞ው አይለዚን፡፡ አሜን። ሰኔ 17 ቀን 2018ዓ.ም ሚፋድ 5:00 ሰዓት

ፍሬ ሃይማኖት - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @frehaymanote