cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ፍሬ ሃይማኖት

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የአ/አ ሐገረ ሥብከት የመ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኤል ካ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና ሥርዓት የጠበቁ መዝሙሮች እና ወረቦች ግጥማቸው ከነዜማ የሚገኝበት ቻናል ነው፡፡ ® ለማናኛውም ሃሳብ አስተያየት ጥያቄና ጥቆማ @Frehaymanoteebot

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
1 707
Obunachilar
-124 soatlar
-17 kunlar
-830 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

#ቄጤማ_ለምን? ============= #የቄጤማ_ታሪኩ ከኖኅ ዘመን ጋር የተያያዘ ነው:: የጥፋት ውሃ መጉደሉን ለማወቅ #ኖህ_ርግብን በላካት ግዜ ለምለም ቄጤማና የወይራ ቀንበጥን ባፏ ይሃ መጥታለች:: ኖህም: ርግብ #ቄጤማና_የወይራ ቀንበጥ ይዛ መምጣት የቻለችው ውሃው በመጉደሉ መሆኑን ተረድቶ ከመርከብ ወጥቷል :: ቄጤማና ወይራ ለጥፋት ውሃ መድረቅ #ምስራች_መንገርያ እንደሆነ ሁሉ : አሁንም በክርስቶስ ሞት : ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ :: የምስራች መሆኑን #ለመግለጥ_ቄጤማ ይታሰራል:: #ሰንበት_ዓባይ / #ቅዱስ_ቅዳሜ ================== #የፊተኛይቱ_ጥንተ ቅዳሜ : ፈጣሪ ሥራውን ሰርቶ ያረፈባት ሰንበት ናት::#ይህች_ደግሞ ጌታችን የማዳን ሥራውን ፈጽሞ በከርሰ #መቃብር_አርፎ የዋለባት ስለሆነች ነው:: #ቅዳሜ_ስዑር ============ በዓመት አንዴ #ስለምትጾም_ስዑር ቅዳሜ ተብላለች:: የተሻረች ቅዳሜ ማለት ነው:: ስዑር የሚለውን ቃል #በመያዝ_ቅዳሜ ሹር ይሏታል:: የተሻረች ቅዳሜ ማለት ነው:: ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ : ተሀጺባ በደመ ክርስቶስ 🤲 🤲 🤲 #አሜን......... 🧡 ......... #አሜን ⊹ #አሜን🙏³
Hammasini ko'rsatish...
#እንኳን_አደረሳቹሁ_የእምየ_ተዋሕዶ_ልጆች ➬#ቅዳሜ_ሥዑር ( ቅዳሜ ሹር)‼ ➬የዓብይ ጾም #የመጨረሻዋ_ቅዳሜ ብዙ ስያሜ አላት:: ሊቃውንቱ ዓባይ ሰንበት ይሏታል:: ቅዱስ #ቅዳሜም_ትባላለች:: ቀዳም ሥዑር የሚለውን ስያሜ ተከትሎም ምዕመናን ቅዳሜ ሹር ይሏታል:: #ለምለሚቱ_ቅዳሜም የዚህች ቅዳሜ መጠርያ ነው:: የነዚህ ሁሉ #ስያሜዎች_ምክንያት ይሄንን ይመስላል:: #ገብረ_ሰላመ_በመስቀሉ ============== #ቅዳሜ_ጠዋት_በቤተ_ክርስትያን ጸሎት ይከናወናል:: ሥርዓተ ጸሎቱ ሲያልቅ " ገብረ ሰላመ በመስቀሉ" ( #በመስቀሉ_ሰላምን አደረገ ማለት ነው) እየተባለ ቄጠማ ይታደላል:: ምዕመኑም ቄጠማውን በመሰንጠቅ በግንባር ላይ ያስራል:: ለምለም ቄጤማ #ስለሚታደልባት " ለምለሚቱ ቅዳሜ ትባለለች::
Hammasini ko'rsatish...
በሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍሬ ሃይማኖት ለነዳያን ማስፈሰኪያ አገልግሎት እየተካሄደ ነው:: ሁላችሁም አባላት መጥታችሁ የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ እንጠይቃለን::
Hammasini ko'rsatish...
የጌታችን የስቅለት በዓል በካቴድራላችን በመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል እየተከበረ ይገኛል:: እንኳን አደረሳችሁ::
Hammasini ko'rsatish...
ሰላም እንዴት ናችሁ የፍሬ ሃይማኖት ልጆች :- እንኳን አደረሳችሁ :: እነሆ የምግባረ ሰናይ ክፍል ለትንሳኤ የነድያን ምገባ እና ጉብኝት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ::በመሆኑም ሐሙስ አርብ ቅዳሜ እና እሁድ የተለያዩ ስራዎችን ያከናውናል :: ስለሆነም ሁላችንም ከላይ በተጠቀሱት ቀናት በመገኘት በአገልግሎቱ ተሳታፊ እና የበረከቱ ተካፋይ እንዲንሆን በእግዚአብሔር ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ። ከሐሙስ ጀምሮ የሚከናወኑ ተግባራት 👉ለነድያን የሚበተኑ አልባሳትን መምረጥ መለየት እና ማስተካከል 👉አካባቢውን ማስተካከል እና ማጽዳት 👉ሽንኩርት መላጥ 👉ከምእመናን የሚመጡ ቁሳቁሶችን መቀበል ✝️ቅዳሜ ለእሁድ አዳር ✝️ 🐂 በሬ ማረድ 🧅 ሽንኩርት ማቁላላት 🥩 ስጋ መክተፍ 🥘 ወጥ መስራት 🥡 ለፀበልተኞች ምግብ መቋጠር 🥡 የተቋጠረው በተመረጡ ቦታዎች መውሰድ እና ማደል ነድያንን ማስፈሰክ ሌሎችም በርካታ አገልግሎቶች ስላሉ ከሐሙስ ጥዋት ጀምሮ ሙሉ ቀን ስላለን እየመጣን ምንተ ንግበር (ምን እናድርግ) እንበል የበዓሉ የበረከት ተሳታፊ እንሁን ሁላችንም እንገኝ በህብረት እናገልግል ። የፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ምግባረ ሰናይ ዋና ክፍል !
Hammasini ko'rsatish...
ሰላም ለእናንተ ይሁን የፍሬ ሃይማኖት አባላት ለትንሳኤ የሚደረገው የነዳያን ምገባ ቅድመ ዝግጅት እየተካሄደ ነው:: ማገዝ እና መርዳት የምትችሉ ሁላችሁም የበረከት ተሳታፊዎች እንደምትሆኑ በትንሳኤው ባለቤት በልዑል እግዚአብሔር ስም አሳስባለሁ::
Hammasini ko'rsatish...
ሰላም ጤና ይስጥልን ውድ የፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ የሐመረ ብርሃን የብራና መፅሀፍት ሥራ ድርጅት "ንፁህ ምንጭ ኢትዮጵያ" በሚል ርዕስ በዘመናችን ትልቅ ታሪካዊ አሻራ አሳርፎ የሚያልፍ ከሚያዝያ4 - ሚያዝያ13 የሚቆይ ልዩ ዓውደ ርይ በግዮን ሆቴሌ እንዳዘጋጁ በተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ ሲያስተዋውቁ የቆዩ ሲሆን ስለሆነም ለዚህ ተከታታይ 10 ቀን የሚቆይ አውደ ርይ ከሰንበት ት/ቤታችን የቀን አበል እየተከፈላቸው የሚያገለግሉ አባል ስለሚፈልጉ በአወደ ርዩ ላይ እንደ ኤግዚቢተር ለመሳተፍ የምትፈልጉ አባላት በሰንበት ት/ቤታችን ፅ/ቤት መታችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ!      ፍ/ሀ/ሰ/ት/ቤት ጽ/ቤት
Hammasini ko'rsatish...