uk
Feedback
ፍሬ ሃይማኖት

ፍሬ ሃይማኖት

Відкрити в Telegram

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የአ/አ ሐገረ ሥብከት የመ/ደ/ገ/ቅዱስ ሚካኤል ካ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና ሥርዓት የጠበቁ መዝሙሮች እና ወረቦች ግጥማቸው ከነዜማ የሚገኝበት ቻናል ነው፡፡ ® ለማናኛውም ሃሳብ አስተያየት ጥያቄና ጥቆማ @Frehaymanoteebot

Показати більше
1 850
Підписники
Немає даних24 години
+77 днів
+1230 день
Архів дописів
.                  ታሪክ በዛሬዋ ዕለት             ነሐሴ 23 ቀን 1968ዓ.ም ✝️ የመናኙ ፓትርያርክ የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ሲመት(ሹመት) ✝️           በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ) በቀድሞ ስማቸው አባ መልአኩ  ወልደ ሚካኤል ይባላሉ።የተወለዱት መስከረም 10 ቀን 1910ዓ.ም በቀድሞው ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ሲሆን፦ ሶስተኛው የኡትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በመሆን የተሾሙት ልክ የዛሬ ሃምሳ ዓመት ነሐሴ 23 ቀን 1968ዓ.ም ነበር። ፍጹም መናኝ የነበሩት አባ መልአኩ(ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ቀደም ብለን እንዳየነው ምንም እንኳን የተወለዱትና ያደጉት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ቢሆንም ከ1926ዓ.ም ጀምሮ ወደ ደቡቡ የአገራችን ክፍል በመጓዝ በወላይታ ሶዶ እና አካባቢው በተለይም በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በተጋደሉበት  ታሪካዊው ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት  ገዳም በአታቸውን በማጽናት በጾም፣በጸሎት፣በስግደትና በትኅርምት ፈጣሪያቸውን በቅድስና ሕይወት ሲያገለግሉ ኖረዋል። ከ1940ዓ.ም ጀምሮም በአታቸውን በዚያው ገዳም አድርገው በመላው ወላይታ አውራጃ እየተዘዋወሩ በማስተማር(ሐዋርያዊ) ተልኳቸውን በማከናወን በርካታ ሕዝብን ካለማመን ወደ ማመን ከአሕዛብነት ወደ ክርስትና የመለሱ ሲሆን በእርሳቸው ትምሕርትም ከ300,000(ከሶስት መቶ ሺህ) በላይ ኢአማንያን አምነው እንደተጠመቁ የክርስቶስ ተከታዮችም እንደሆኑ ይነገራል። በተጨማሪም በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን አሰርተዋል።አያሌ ትምሕርት ቤቶችን አቋቁመዋል።የችግረኞች መርጃ ማዕከላትን መስርተዋል።በዚህ መልካም ሥራቸው የተነሳም  የድሆች አባት በመባል ይታወቃሉ። ቅዱስነታቸው በዚህ ዓይነት መልካም ሥራ ተሰማርተው ሳሉ ወታደራዊው መንግሥት ደርግ ንጉሣዊውን መንግስት በኃይል አስወግዶ በትረ መንግስቱን ጨበጠ።የስልጣን ኮርቻውም ላይ ተፈናጠጠ። ቀጥሎም  ሁለተኛው የቤ ተክርስቲያናችን ፓትርያርክ የነበሩትን ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን አላግባብ አሠራቸው።ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጪም ሌላ ፓትርያርክ እንዲመረጥ አዘዘ። ራሱ ባቋቋመው አስመራጭ ኮሚቴ አማካይነትም ለፓትርያርክነት እንዲመረጡ የሚፈለጉ አባቶችን ከየክፍሉ በእጩነት እንዲጠቆሙ  ካደረገ በኋላ በስተመጨረሻም አባ መልአኩ ከሌሎቹ እጩዎች የበለጠ ድምጽ በማግኘት ተመርጠዋል። ባላሰቡትና ባልጠበቁት ሁኔታ ለዚህ ታላቅ ኃላፊነት እንደታጩ የሰሙት ቅዱስነታቸውም "መንበሩ ለእኔ አይገባም"  ብለው እንደተቃወሙ ይነገራል።በዚህም የተነሳ ቅዱስነታቸው ቤተ ክህነት ውስጥ በምትገኝ አንዲት ጠባብ ክፍል ውስጥ በጥበቃ(በዘበኛ) ይጠበቁ እንደነበር ይነገራል። ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በጣሰ መልኩ በደርግ አስገዳጅነት ሶስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሆነው  የተመረጡት አባ መልአኩ(አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ፓትርያርክ ሆነው ከመሾማቸው አስቀድሞ ሐምሌ 11 ቀን 1968ዓ.ም ብጹዕ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ተብለው በመሰየም  መዓርገ ጵጵስናን ተቀበሉ። ከአንድ ወር በኋላም ነሐሴ 23 ቀን 1968ዓ.ም ሶስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በመሆን ተሾሙ። የቅዱስነታቸውን የአመራረጥ ሒደት የሰሙት የግብጽ ቤተ ክርስቲያን፣የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት፣ እንዲሁም የአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት "አንድን ፓትርያርክ በኃይል ከመንበሩ አንስቶ ሌላ ፓትርያርክ መሾም አይገባም" ሲሉ በመቃወም ለሹመቱ ዕውቅና አንሰጥም በማለት የተቃውሞ መግለጫን አውጥተዋል። በእንዲህ ያለ አወዛጋቢ መንገድ የተመረጡት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዚያ "ፈጣሪ የለም ተብሎ በተካደበት" እና የሰው ልጅ ደም እንደ ከረምት ጎርፍ ይፈስ በነበረበት አስቸጋሪ ወቅት በትዕግስትና በጥበብ ቤተ ክርስቲያንን ማሻገር የቻሉ አባት እንደነበሩ ብዙዎች ይመሰክሩላቸዋል። ፍጹም ባሕታዊና መናኝ የነበሩት ሶስተኛው ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ታላቋ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ለ12(ለአስራ ሁለት) ዓመታት ከመሩ በኋላ ግንቦት 28 ቀን 1980ዓ.ም  ከዚህ ዓለም ድካም አርፈው  ግንቦት 30 ቀን 1980ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሥርዓተ ቀብራቸው በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ስርዓት ተፈጽሟል። ተጨማሪ‼️ ጥቂት ስለ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት መንፈሳዊ ሕይወት እናክልላችሁና ታሪኩን እናጠቃልል። ☦️ ፓትርያርክ ሆነው ሳለ በባዶ እግራቸው ይሄዱ ነበር እንጂ ለእግራቸው መጫሚያ አልነበራቸውም(ጫማን አያደርጉም ነበር)። ☦️ አመጋገባቸውን በተመለከተም ከበሶና ከተቀቀለ ድንች በስተቀር ሌላ የምግብ ዓይነት ቀምሰው አያውቁም ይባላል። ☦️ መቼም ቢሆን መሬት እንጂ አልጋ ላይ ተኝተው እንደማያውቁ በቅርብ የሚያውቋቸው  ሁሉ ይመሰክሩላቸዋል። ☦️ እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሀገረ ሙላድ(የትውልድ ስፍራ) ቢኖራቸውም ተወልጄ ያደግኹበት ቦታ ይህ ነው ብለው ከመናገር ይልቅ በፍጹም ኢትዮጵያዊነታቸው ያምኑ ነበር።በተጨማሪም የሰውን ልጅ በሙሉ በአንድ ዐይን(እኩል) በመመልከት ብቃታቸው ብዙዎችን ሲያስገርሙ የኖሩ አባት ነበሩ። ☦️  ቅዱስነታቸው መላ ዘመናቸውን በጾም፣በጸሎትና በሰጊድ ያሳለፉ በመሆናቸው ምክንያት ባደረባቸው ሕመም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ስትለይ የሰውነታቸው ክብደት 25(ሃያ አምስት) ኪሎ ግራም ደርሶ እንደነበር ይነገራል። የቅዱስነታቸው ረድኤትና በረከት በሁላችነም ላይ ይደርብን። ምንጭ፦ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን መጽሐፍ። በዲያቆን መርሻ አለኸኝ  የተዘጋጀ። ፲፱፻፺፯(1997)ዓ.ም ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። ተጻፈ ነሐሴ 22 ቀን 2018ዓ.ም ረፋድ 5:00 ሰዓት።

photo content
+2

.            የአሸንዳ በዓል የአሸንዳ፣ አሸንድዬ፣ ሻደይ፣ ሶለል በዓል ከየት መጣነት(መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዳራ)።        በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ) ሰላም ለኩልክሙ ኦ ውሉደ ፍሬ ሃይማኖት ውድ ቤተሰቦቻችን እንደምን ከረማችሁ?     ስንቶቻችን የአሸንዳ በዓል ከባህላዊ ገጽታው  ባሻገር መጽሐፍ ቅዱሳዊና መንፈሳዊ እንደሆነ እናውቅ ይሆን??? በመጠኑ እናውጋችሁ። ይጠቅማችኋልና በማስተዋል አንብቡት።      ይህ በዓል ከጊዜ በኋላ ባህላዊ ገጽታው እየጎላ የመጣ ቢሆንም ቅሉ መሠረቱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው።በነገራችን ላይ አሸንዳ በወንዝ ዳር የሚበቅል ቅጠለ ሰፊ ቄጤማ መሳይ የሣር ዓይነት ሲሆን ልጃ ገረዶች በበዓሉ ሰሞን ይህን የሣር ዓይነት አቀጣጥለው፤ እንደ ጉርድ ቀሚስ በወገባቸው ላይ አስረው ስለሚጫወቱ ነው በዓሉ አሸንዳ ተብሎ የተሰየመው።        በዓሉ በሰፊው የሚከበረው በትግራይ በተለይም በተምቤንና በእንደርታ ሲሆን በተጨማሪም በዋግሕምራ፣በላስታ፣በላሊበላና በሰሜን ጎንደር አካባቢዎችም ይከበራል።      የአሸንዳ ጨዋታ(በዓል) ታሪክ ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ በአገረ እሥራኤል ይዘወትር ነበር።መጠርያው ይኽ(አሸንዳ) የሚለው ባይሆንም ቅሉ የጥንት አሥራኤላውያን መንፈሳዊና ባህላዊ ዕሴታቸው ነበር።       አጀማመሩም እንዲህ ነው፦ በመጽሐፈ መሳፍንት ምዕ. 11 ከቁ.1-40 ላይ እንደተጻፈው ዮፍታሔ የተባለ የገለዓድ ልጅ ነበር።ይሁንና ዮፍታሔ የተወለደው ከገለዓድ ሕጋዊ ሚስት ሳይሆን ከሌላ አመንዝራ ሴት ስለነበር፤ ከሕጋዊ ሚስቱ የተወለዱ የገለዓድ ልጆች "የአባታችንን ሥልጣንም ሆነ ኃብት የመውረስ መብት የለህም"። በማለት ወንድማቸው ዮፍታሔን አባረሩት።      ከጊዜ በኋላ ግን በእሥራኤላውያን ላይ ጠላቶች ተነስተው የገለዓድ ልጆችን አሸነፏቸው። በዚህን ጊዜ የእሥራኤል የአገር ሽማግሌዎች ተሰባስበው ከመከሩ በኋላ ዮፍታሔን ለማምጣት ተስማሙ።ምክንያቱም ዮፍታሔ የጦር ሠውና ኃይለኛ ተዋጊ እንደሆነ ያውቁ ነበርና ነው። ሔደውም ጠላቶቻቸውን እንዲወጋላቸው ለመኑት።      ዮፍታሔም ጥያቄያቸውን የሚቀበለው ጠላቶቹን ድል ካደረገ በኋላ መስፍን(ገዥ) አድርገው የሚሾሙት ከሆነ ብቻ እንደሆነ ነገራቸው። ሽማግሌዎቹም በዚህ ተስማምተው ቃላቸውን እንደሚያከብሩ አረጋገጡለት።        ዮፍታሔም  እግዚአብሔር ከጎኑ እንዲቆምለት ከጸለየ በኋላ ጠላቶቹን ድል አድርጎ ሲመለስ ቀድሞ ከቤቱ ወጥቶ የሚቀበለውን መስዋዕት አድርጎ ለማቅረብ ተሳለ። ዮፍታሔ እንደተመኘው ጠላቶቹን ድል አድርጎ ወደ ቤቱ ተመለሰ።ከራሱ አብልጦ የሚወዳት ብቸኛ ሴት ልጅ ነበረችው።ከእርሷ ሌላ ሴትም ሆነ ወንድ ልጅ አልነበረውም።ይህች ብቸኛ ልጁ አባቷ በጦርነት ድል ማድረጉን ስትሰማ የዕድሜ እኩዮቿ የሆኑ ጓደኞቿን ሰብስባ ከበሮ ይዛ እየጨፈረች ልትቀበለው ወጣች።አባቷ ወደ ቤቱ በተቃረበበት ጊዜም እየሮጠች ሄዳ ተጠመጠመችበት።      በዚህን ጊዜ ዮፍታሔ ልጁን እንደታቀፈ ማልቀስ ጀመረ።በሁኔታው ግራ የተጋባችው ልጁ ለምን እንደሚያለቅስ ጠየቀችው።እርሱም ለእግዚአብሔር የተሳለውን ስዕለት ነገራት።እርሷ ግን አልደነገጠችም። ይልቁንም "አባቴ አትዘን በስዕለትህ መሠሰት ሰዋኝ።ከዚያ በፊት ግን አንድ ነገር ብቻ ፍቀድልኝ፤ ይኸውም ከባልንጀሮቼ ጋር ሆኜ በአገሬ ተራሮችና ሸንተረሮች እየዞርኩ ለድንግልናዬ ክብር እንዳለቅስ ለሁለት ወራት አሰናብተኝ"። አለችው።ፈቀደላትና ጓደኞቿን ይዛ ሄደች።     ከሁለት ወራት በኋላ ስትመለስ ዮፍታሔ በስዕለቱ መሠረት ብቸኛ ልጁን መስዋዕት አድርጎ አቀረባት። እዚህ ላይ ዮፍታሔ ልጁን መስዋዕት አድርጎ አቀረባት ሲባል፦  አረዳት ማለት ሳይሆን ዕድሜ ልኳን ባል ሳታገባ በድንግልና እንድትኖር አደረጋት ማለት ነው ብለው የጻፉ ጸሐፍያንም አሉ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እሥራኤላውያን ልጃ ገረዶች በየዓመቱ ለአራት ቀናት ለዮፍታሔ ልጅ መታሰቢያ  ሙሾ የማውጣት ሥርዓትን  እንደ  ልምድ አድርገው ያዙት።      እዚህ ላይ ባህሉ ወደ ኢትዮጵያ እንዴት ሊመጣ ቻለ? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። መልሱም ታቦተ ጽዮን ወደ ኢትዮጵያ ስትመጣ አስራ ሁለት ሺህ ቤተ እሥራኤላውያንም አብረው መጥተው ነበር። እነዚሁ እሥራኤላውያን አሁን ተምቤን እየተባለ ከሚጠራው ስፍራ እንዲሰፍሩ ተደረገ።ከዚያን ጊዜ በኋላ እነዚህ እሥራኤላውያን "አውርስ" የተባለውን የጨዋታ ዓይነት ጨምሮ ለአሸንዳ መሠረት የሆነውን ልማድና አሠራር እንዲስፋፋ አደረጉ።         ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ከተስፋፋ በኋላም ኢትዮጵያውያን የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በዓሉ የደናግል በዓል በመሆኑ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓል ጋር ተየይዞ እንዲከበር አደረጉ።በመሠረቱ አሸንዳ የልጃ ገረዶች በዓል ነው። በመሆኑም፦የዚህ በዓል ተሳታፊዎች የሚሆኑት ያላገቡና ደናግል ብቻ ናቸው።       ልጃ ገረዶቹ የአሸንዳ ሥነ ስርዓታቸውን ሲጀምሩም ሆነ ሲያጠናቅቁ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው የጋራ ጸሎት ያደርሳሉ። በአካባቢው የሌለ ካልሆነ በስተቀር ቤተ ክርስቲያኑ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መሆን አለበት። በአሸንዳ ሰሞን ልጃ ገረዶች ሙሉ ነጻነታቸው የተጠበቀ ነው።በአሸንዳ ወቅት ሌላው ቀርቶ አንዲት ልጃ ገረድ "የማርያም ልጅ እየተባለች" ነው የምትጠራው። በመሆኑም "የማርያምን ልጅ" መምታት ቀርቶ መገላመጥና መቆጣትም ነውር ነው። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን ምንጭ፦ ኅብረ ብዕር መጽሐፍ። (መምሕር ካሕሣይ ገ/እግዚአብሔር)  ተጻፈ ነሐሴ 21ቀን 2018ዓ.ም ምሽት በ4:00 ሰዓት።

photo content

ለሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ፤ ለ2019 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤታችን ውስጥ የየትኛውን ክፍል አገልግሎት መስጠት እንደሚፈልጉ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ በመግባት ምርጫዎን እንዲያሳውቁን እንጋብዛለን። https://script.google.com/macros/s/AKfycbz4VKy5rDMHpZV42UXcL2ZXtti9-u7zJAEXSs_Hfg4GVYtf9lklejLkieT5d8hBt-mBtQ/exec

ለመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት፣ መምህራን እና መላው ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ! ሰንበት ትምህርት ቤታችን በአዲሱ ስርዓተ-ትምህርት መሠረት ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ከፋፍሎ በመስጠት ላይ ባለው ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት ማዕቀፍ፣ በዘንድሮው ዓመት  የ12ኛ ክፍል ፈተና ተቀምጠው የነበሩት ተማሪዎቻችን ሙሉ በሙሉ (100 በመቶ) በማለፍ ታላቅ የድል ምዕራፍ አስመዝግበዋል። ይህ አስደናቂ ውጤት ሰንበት ትምህርት ቤታችን ለትውልድ ግንባታ እያበረከተ ያለው ሁለንተናዊ አስተዋጽኦ ተጨባጭ ማሳያ ነው። ተማሪዎቻችን በክፍል ደረጃዎች እየተከታተሉ ያገኙትን መንፈሳዊ እውቀት ከአካዳሚክ ትምህርታቸው ጋር አስተባብረው ያስመዘገቡት ይህ ስኬት አርዓያ የሚሆን ነው። ለዚህ ድል መሳካት ሁለንተናዊ ድጋፍ የሰጡትን መምህራን፣ ወላጆች እና መላው የሰንበት ት/ቤቱ አባላት ድርሻ ታላቅ ነው። ሰንበት ትምህርት ቤታችን ላበረከታችሁት ትልቅ አስተዋጽኦ ምስጋናውን እያቀረበ፣ ለተማሪዎቻችን ቀጣይ የሕይወት ጎዳና የበረከትና የስኬት ምኞቱን ይልካል።

የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ፤ ለ2019 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቱ የትኛውን ክፍል አገልግሎት መስጠት እንደሚፈልጉ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ በመግባት ይምረጡ!

4_5785121283272350964.mp36.08 MB

.   ☦ ለመላው ውሉደ ፍሬ ሃይማኖት‼️ ✝       እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የትንሣኤና የዕርገት በዐል አደረሳችሁ አደረሰን።       በዐሉን በዐለ ፍስሐ ወሰላም ያድርግላችሁ ያድርግልን።        ትክክለኛ የፍልሰታ ስጦታን እነሆ ብለናችኋል።ተጋበዙልን።               ድንግል ወላዲተ ቃል         ድንግል ድንግል ወላዲተ  ቃል(2×) አሟሟትሽ በጥር ነሐሴ መቃብር   ያንቺ ለብቻ ነው ትንሣኤሽ ሲነገር ሥጋሽ በምድር ላይ የታለ እንደ ፍጡር አርጓል ወደ ሰማይ ከክርስቶስ መንበር ድንግል ድንግል ወላዲተ ቃል(2×) ሥጋሽን ሲያሳርጉ መላእክተ ሰማይ ቶማስ በደመና ሲመጣ መንገድ ላይ መግነዝ ተረከበ ለሐዋርያት ሊያሳይ ድንግል ድንግል ወላዲተ ቃል (2×) ትንሣኤሽን ሽተው ግራ ሲገባቸው ሐዋርያት ጾመው ተገለጽሽላቸው ተቀብራ አልቀረችም በምድር ከደጇ ወደ ላይ አረገች እሷም እንደ ልጇ ድንግል ድንግል ወላዲተ ቃል(2×) ለማየት ሲጓጉ የድንግል ትንሣኤ ዕርገቷን አወቁ በብዙ ሱባኤ እኛም እንጸልይ በራችን እንዝጋ ከወላዲተ አምላክ እንድናገኝ ዋጋ ድንግል ድንግል ወላዲተ ቃል(2×) በኩረ መዘምራን ኪነ ጥበብ ወ/ቂርቆስ የእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሱባኤ ምክንያት በማድረግ አማላጅነቷ ጉልበት ፍቅሯ ብርታት ሆኖኝ ትምሕርታዊ ጽሑፎቹን አዘጋጅቼ ያቀረብኩላችሁ ደካማው ወንድማችኹ፦ ደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ) ነኝ። በጸሎታችኹ አስቡኝ አደራ እንዳትረሱኝ። አነሳስቶ ላስጀመረን አስጀምሮም ላስፈጸመን ለልዑል አምላካችን እግዚአብሔር ክብርና ምሥጋና ይሁን። ጣዕሟን በልቦናችን ፍቅሯን በአንደበታችን ያሳድርብን። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን።

"አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እም ገነት = ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ" አባ ሕርያቆስ(ቅዳሴ ማርያም)
"አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እም ገነት  =  ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ" አባ ሕርያቆስ(ቅዳሴ ማርያም)

የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ፤ ለ2019 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቱ የትኛውን ክፍል አገልግሎት መስጠት እንደሚፈልጉ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ በመግባት ይምረጡ!

የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ፤ ለ2019 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቱ የትኛውን ክፍል አገልግሎት መስጠት እንደሚፈልጉ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ በመግባት ይምረጡ! https://script.google.com/macros/s/AKfycbzDHN8kxUZgR5-HxXhE2WD0XCJfNtUuVA8cM8oyQpozl8iQ5mbixCj5IoNbXoxshO76tQ/exec

      ሰአሊ ለነ ቅድስት(በአልፋው አ ሲጻፍ)                             እና          ሰዐሊ ለነ ቅድስት(በዐይኑ ዐ ሲጻፍ)      በአልፋው አ ሲጻፍ ማለትም "ሰአሊ ለነ ቅድስት" ሲሆን ትርጉሙ "ቅድስት  ሆይ ለምኝልን(አማልጅን) ማለት ነው። ይህ ማለት ግን ሁል ጊዜ ለመለመን(ለመማለድ)  በጌታ ፊት ትቆማለች ማለት ሳይሆን በቀደመ ልመናዋ(ምልጃዋ) ምሕረትን የምታሰጥ ስለሆነች ነው።የሁልጊዜ ልመና እንኳን በእርስዋ አይደለም በሌሎቹም ቅዱሳን የለባቸውም።       በዐይኑ ዐ ሲጻፍ ማለትም "ሰዐሊ ለነ ቅድስት"  ሲሆን ትርጉሙ ቅድስት ሆይ አዕምሮውን ለብዎውን(ማስተዋሉን) ሳይብን አሳድሪብን ማለት ይሆናል።    ቅድስት ማለትም ንጽሕት፣ ጽንዕት፣ ክብርት፣ ልዩ ማለት ነው።፣ 👉 እመቤታችን ንጽሕት ናት ሲባል፦  ሌሎች ሴቶች ቢነጹ ከነቢብ(በንግግር ከሚፈጸም  ኃጢአት)፣ ከገቢር(በተግባር ከሚፈጸም ኃጢአት)  ብቻ ነው። ከኃልዮ(በሃሳብ ከሚፈጸም ኃጢአት) አይነጹም።እርስዋ ግን ከሐልዮ፣ ከነቢብ፣ ከገቢር ንጽሕት ናት። 👉 እመቤታችን ጽንዕት ናት ማለትም፦ ሌሎች ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው።ኋላ ግን ተፈትሖ ማኅጸን አለባቸው።እርሷ ግን ቅድመ ጸኒስ፣ ጊዜ ጸኒስ፣ ድኅረ ጸኒስ፤ ቅድመ ወሊድ፣ ጊዜ ወሊድ፣ ድኅረ ወሊድ ጽንዕት ናት።(ድንግልናዋ አልተለወጠም) 👉 ክብርት ናት ሲባልም፦ ሌሎች ሴቶችን ብናከብራቸው ጻድቃንን፣ ሰማዕታትን፣ጳጳሳትን፣ነገሥታትን  ወለዱ ብለን ነው።እርሷ ግን ወላዲተ አምላክ ስለሆነች ነው በልዩ ሁኔታ የምናከብራት። 👉 ልዩ ናት ሲባልም፦ እናትነትን ከድንግልና አስተባብራ በመያዟ ነው። እናትነትን ከድንግልና አጣምራ የምትገኝ ሴት ከእመቤታችን በቀር  የለችም። ስለዚህ ከተለዩ የተለየች(ቅድስተ ቅዱሳን) እናታችን ናት። ጽንዕት በድንግልና ስርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን። ጣዕሟን በልቦናችን ፍቅሯን በአንደበታችን ይሳልብን ያሳድርብን። ያብጽሐነ ያብሕክሙ አመ ከመ ዮም በፍስሐ ወበሰላም። (ሁላችንንም ከቁጥር ሳያጎለን የከርሞ ሰው ይበለን) ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።

photo content

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሣሌዎች በመጽሐፍ ቅዱስ             ከባለፈ የቀጠለ            መሶበ ወርቅ ንጹሕ          ንጹሕ የወርቅ መሶብ      ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ በውዳሴ ማርያም ዘሰንበተ ክርስቲያን(የእሁድ) ላይ በግእዙ፦ "አንቲ ውእቱ መሶበ ወርቅ ንጹሕ እንተ ውስቴታ መና ኅቡዕ ኅብስት ዘወረደ እም ሰማያት ወሃቤ ሕይወት ለኩሉ ዓለም" ወደ አማርኛ ሲመለስም፦  "የተሰወረ መና ያለብሽ  ንጹሕ የወርቅ መሶብ አንቺ ነሽ።መናም ከሰማይ የወረደውና ለዓለም ሁሉ ሕይወትን የሚያድለው ኅብስት ነው። ቁ.4 በማለት እመቤታችንን አወድሷታል። ትርጓሜው(ምሥጢሩም)፦ መሶበ ወርቅ የእመቤታችን ምሣሌ ሲሆን፤ ወርቁም የንጽሕናዋ የቅድስናዋ  ምሣሌ ነው።ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን ማለትም፦ ከንጹሐን ይልቅ የነጻች፤ ከተለዩትም የተለየች እንደሆነች ይታወቃል፣ ይታመናልም። ከሰማይ የወረደ ኅብስት(መና)  የተባለውም ምግበ ነፍስ ማለትም፦ ዘለዓለማዊ የነፍስ ምግብ  የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።       ይህንንም ራሱ ጌታ በማይሻረው ቃሉ፣ በቅዱስ ወንጌሉ እንዲህ ሲል አስተምሮናል። "የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የሚወርድ ለዓለምም  ሕይወትን የሚሰጥ ነውና" ዮሐ.6፥33  አያይዞም በቁጥር 35 ላይ "የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም።በእኔ የሚያምንም ሁል ጊዜ ከቶ አይጠማም። ዮሐ. 6፥ 35 ሲል ተናግሯል።        ዝቅ ብሎ በዚሁ የወንጌል ክፍል ላይ "የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ። አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱም ።ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው። ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ።ሰው ከዚህ እነጀራ ቢበላ ለዘለዓለም ይኖራል። ዮሐ.6፥ 48-51። አምላካችን ለእኛ ለልጆቹ በሁለት መልክ ነው የነፍስ ምግብ የሆነን፦ ፩ኛው  "ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ኹሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም" ማቴ.4፥4 በማለት ሕይወት የሆነውን ቅዱስ ቃሉን በመስጠት ሲሆን ፪ኛም፦ "እኔ ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው። እውነት እውነት እላችኋለው የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችኹ ደሙንም ካልጠጣችኹ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም።      ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘለዓለም ሕይወት አለው።እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሳዋለው።      ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና።      ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል።እኔም በእርሱ እኖራለሁ"። 51-56     በማለት በልተነው ዳግም የማያስርበንን ጠጥተነውሞ ዳግም የማያስጠማንን የዘለዓለም ምግብ የሆነውን ቅዱስ ሥጋውን እንዲሁም የሕይወት መጠጥ የሆነውን ክቡር ደሙንም በመስጠት ነው።        ይህንን ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚገኝበትን ቅዱስ ሥጋውን እና ክቡር ደሙን ጌታ ይዞት የመጣው ከሰማይ ሳይሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከደምዋ ደምን  በመንሳት(በመውሰድ) ስለሆነ እርስዋ የኅብስት ማኖርያ በሆነው በንጹሕ መሶበ ወርቅ ተመስላለች።   ተወዳጆች ሆይ!!!      እሰሰካሁን ያየናቸውም ሆኑ  ሌሎችም ያልዳሰስናቸው ተምሳሌቶች  በትክክል የእርሷን ክብር፣ታላቅነት፣ንጽሕናና ቅድስና ይገልጻሉ ማለት ግን ፈጽሞ አይደለም።      ስለሆነም እኛም ደካሞቹ ልጆቿ እንደ ደጋጎቹ  አበው "በመኑ ወበአምሳለ መኑ ናስተማስለኪ + በምን እንመስልሻለን? ማንስ በመሰለው ምሳሌ እንመስልሻለን? ብለን ነገራችንን ለጊዜው  እናጠቃል። ጽንዕት በድንግልና ስርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን። ጣዕሟን በልቦናችን ፍቅሯን በአንደበታችን ይሳልብን ያሳድርብን። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።

☦  በዓለ ደብረ ታቦር በአገራችን እና በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ☦       በደረጀ እሸቴ(ወልደ ሥላሴ) "ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌስኁ ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል" መዝ.88፥12 ውድ ቤተሰቦቻችን እንደምን አደራችሁ? የዘመናት ጌታ የጊዜ ባለቤት አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር እንኳን ለበዓለ ደብረ ታቦር በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን።     የደብረ ታቦር በዓል ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከምታከብራቸው ከዘጠኙ የጌታ ዐበይት በዐላት መካከል አንዱ ሲሆን ሙሉ ታሪኩ በማቴዎስ ወንጌል በምዕ. 17፥ከቁ.1-9 ላይ ተመዝግቦልን እናገኘዋለን።       አስቀድሞ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፊልጶስ ቂሣርያ "ሰዎች የሰውን ልጅ(ራሱን ማለት ነው) ማን ነው ይሉታል?" ብሎ በጠየቀ (ማቴ.16፥ከ13-20) ከስድስት ቀን በኋላ (በሰባተኛው ዕለት) ከአስራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት መካከል አዕማድ(የምሥጢር ሐዋርያት)  የሚባሉትን ሶስቱን ማለትም፦ ቅዱስ ጴጥሮስን፣ ቅዱስ ዮሐንስን እና ወንድሙን ቅዱስ  ያዕቆብን ይዞ የተቀሩት ዘጠኙን ሐዋርያት ከእግረ ደብር(በተራራው ግርጌ) በመተው  ወደ ርዕሰ ደብር (ወደ ተራራው ራስ) ወጣ ይለናል።        የተራራውም ስም ደብረ ታቦር ሲሆን በፊታቸው ተለወጠ።ፊቱ እንደ ፀሐይ  በራ።ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ።ተለወጠ ማለት  መልኩ ሌላ፣ ቁመቱ  ሌላ፣ ሆነ። በአጠቃላይ መላ አካሉ ተለውጦ ሌላ አካል ሆነ ማለት ሳይሆን  አስቀድሞ የነበረው ሶስት ክንድ ከስንዝር  የሚሆነው አካሉ ሙሉ ብርሃን ሆነ ማለት ነው።     እነሆም ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ቅዱስ ጴጥሮስም "ጌታ ሆይ  ለእኛ በዚህ መሆን መልካም ነው። ብትወድስ  ሶስት ዳስ አንዱን ለአንተ፣ አንዱን ለሙሴ፣ አንዱን ለኤልያስ እንስራ" አለ።      እርሱም ገና ሲናገር እነሆ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው።እነሆም ከደመናው "ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ወሎቱ ስምዕዎ  + በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" የሚል አስገምጋሚ ድምጽ መጣ።     ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ።እጅግም ፈርተው ነበር።ዐይናቸውንም አቅንተው ሲያዩ ከኢየሱስ በቀር ማንንም አላዩም።      ከተራራውም በወረዱ ጊዜ ኢየሱስ ፦"የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሳ ድረስ ያያችሁትን ለማንም አትንገሩ"  ብሎ አዘዛቸው።        የደብረ ታቦር በዓል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱንና ግርማ መንግሥቱን የገለጸበት በዓል ሲሆን መንፈሳዊና ትውፊታዊ በሆነ ሥነ ሥርዓት በአገራችን በልዩ ሁኔታ ይከበራል።     በቤተ ክርስቲያናችን በማኅሌት፣በቅዳሴ፣በአንዳንድ አድባራት ታቦታቱ ከመንበራቸው ወጥተው በሥርዓተ ንግሥና በመሳሰሉት ሥነ ስርዓቶች በድምቀት ይከበራል።       በሌላ በኩልም በአገራችን በኢትዮጵያ ቡሄ እየተባለ በየቤቱና በየመንደሩ ትውፊቱን በጠበቀ መንገድ የሚከበር ሲሆን  ቡሄ  ማለት ትርጉሙ፦ ብራ፣ገላጣ፣ብርሃን፣ደማቅ ማለት ነው።ይህም መነሻው መጽሐፍ ቅዱስ ሲሆን ጌታ ብርሃነ መለኮቱን በደብረ ታቦር በመግለጡ ከዚያ የመነጨ(የተገኘ) ስያሜ ነው። ችቦ(ደመራ) የሚበራበትም ምክንያት ምሥጢሩ  ከዚሁ ጋር የተየያዘ ነው።        በሌላ በኩልም "ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት፤ ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት" እንዲሉ ጨለማ የሆነው  የክረምቱ ወቅት አልፎ ብርሃን የሚታይበት ወቅት መዳረሻ(መሸጋገሪያ) ስለሆነ በተጨማሪም ከሰማይ ጭጋጉ ተገፎ ብሩህ ሆኖ የሚታይበት ጊዜ እየመጣ ስለሆነ "ቡሄ"  የሚለው ስያሜ ይህንኑ  የሚያስረዳ ነው።      የጂራፉ ድምጽም  በአንድ በኩል ከሰማይ የመጣውን የክርስቶስ የባሕርይ አባት የሆነውን የቅዱስ እግዚአብሔር አብን ነጎድጓዳማ ድምጽ የሚያስታውስ ሲሆን በሌላ በኩልም በዕለተ አርብ ለእኛ ሲል የተገረፈውን ግርፋት ያስታውሰናል።       እናቶች የሚጋግሩት ሙልሙል ዳቦም፦  በወረደው ብርሃን ምክንያት የቀኑን መምሸት ያላወቁ እረኞች(ልጆች)  ወደ የቤታቸው ሳይመጡ በመቆየታቸው  ወላጆቻቸው ከየመንደሩ ዳቦ ጋግረው ችቦ እያበሩ  ለልጆቻቸው ይዘውላቸው ፍለጋ  ሄደዋል። ትውፊቱ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲወርድ ሲዋረድ ቆይቶ እነሆ ከዛሬ ደርሷል።የፍቅር መገለጫም ስለሆነ እናቶች ሙልሙል ዳቦን እየጋገሩ ለልጆቻቸው ይሰጣሉ።      ይህም አገራችን ባህሏና የበዓል አከባበሯ በአብዛኛው መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረትና መንፈሳዊ  ዕሴት  እንዳለው የሚያረጋግጥ ነው። ከበዓሉ፣ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤትና በረከት ይክፈለን። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።

photo content

photo content