uz
Feedback
Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Kanalga Telegram’da o‘tish

Government Organization

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Addis Ababa Design And Construction Works Bureau analitikasi

Addis Ababa Design And Construction Works Bureau (@addiscitycon) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 20 649 obunachidan iborat bo'lib, Siyosat toifasida 2 855-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 629-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 20 649 obunachiga ega bo‘ldi.

07 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 265 ga, so‘nggi 24 soatda esa -5 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 13.40% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.70% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 766 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 796 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 18 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Government Organization

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 08 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Siyosat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

20 649
Obunachilar
-524 soatlar
-67 kunlar
+26530 kunlar
Postlar arxiv
“ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየሰራ ነው!” በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላ
+8
“ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየሰራ ነው!” በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀምበር (ዶ/ር) ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየተሰራ ነው ሲሉ ዶር ጀማሉ ጀንበር ገለፁ። አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አላስፈላጊ የቢሮክራሲ አሰራርን ያስቀረና ተጠያቂነትን ያሰፈነ ነውም ብለዋል። በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት የበቃው የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት የየካ ማዕከል 96 ተገልጋዮችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚያስችል መስኮትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የተሟሉለት መሆኑን አስረድተዋል። ማዕከሉ የ22 ተቋማትን 114 አገልግሎት መስጠት ያስችላል። በቀጣይ ተጨማሪ አገልግሎቶች እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።

ቃል በተግባር በከተማችን ተጠናክሮ ቀጥሏል--- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግ
+9
ቃል በተግባር በከተማችን ተጠናክሮ ቀጥሏል--- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት የካ ማዕከልን መርቀው አስጀመሩ። በም/ከንቲባው የተመረቀው የየካ ማዕከል በከተማችን 9ኛው መሶብ ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት ነው። መሶብ በከተማ አስተዳደሩ የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያሉ የህዝቡን ቅሬታዎችን እየፈታ መሆኑንም አቶ ጃንጥራር አባይ ተናግረዋል። በዚህ ዓመት ቀደም ሲልና አሁን ላይ ወደ ስራ በገቡ የመሶብ ማዕከላት የተገልጋዮች እርካታን 99 በመቶ ማድረስ ተችሏል። ይህን የነዋሪዎችን የአገልግሎት እንግልት ለማስቀረት ከምርጫ ማግስትም አዳዲስ የመሶብ ዲጅታል ማዕከላትን ወደ ስራ የማስገባት ጥረታችንን አጠናክረን በመቀጠል 9ኛው የየካ ማዕከል ላይ ደርሰናል። በቀጣይ ጥቂት ቀናት ደግሞ ግንባታቸው የተጠናቀቁትን የአቃቂና የለሚ ኩራ ማዕከላትን ወደ ስራ የምናስገባ ይሆናል። ተጨማሪ ስራ በመስራት የህዝባችንን እርካታ እንዲጨምር እናደርጋለን ሲሉም አቶ ጃንጥራር ተናግረዋል።

ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው!! ዛሬ 9ኛውን መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ አስጀምረናል። የመንግስት አገልግሎት አሰጣጣችንን ቀልጣፋ
+9
ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው!! ዛሬ 9ኛውን መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ አስጀምረናል። የመንግስት አገልግሎት አሰጣጣችንን ቀልጣፋ፣ ፈጣን፣ ግልፅ እና ተደራሽ ለማድረግ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ስራ በ2018 በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ ለማስጀመር አቅደን ለህዝቡ ቃል በገባነው መሰረት እነሆ የዛሬውን ጨምሮ 9 ማዕከላትን ወደ ስራ አስገብተናል። የአገልግሎት እንግልትን፣ እዚህም እዝያም ጉቦ የመጠየቅ ችግርን ለመቅርፍ፣ ተጠያቂነትን እና የህዝባችንን በክብር የመገልገል መብት ለማረጋገጥ፣ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜውንና ገንዘቡን ሳያባክን ያለውን ሃብት ለልማት እንዲያውለው ለማድረግ ያቀድነውን ግብ በማሳካት የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን ። የየካ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የሰራችሁትን ሁሉ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ውድድር አሸናፊ ሆነች በ19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በሴቶች የአዲስ አበባ ፖሊሷ መሰለች አለማየሁ አሸንፋለች። ዝማም ማራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ ወጥታለች። መነሻ እና መድረሻ
+3
ውድድር አሸናፊ ሆነች በ19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በሴቶች የአዲስ አበባ ፖሊሷ መሰለች አለማየሁ አሸንፋለች። ዝማም ማራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ ወጥታለች። መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ አድርጎ በተከናወነው ውድድር በወንዶች 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች ተሳትፈውበታል፡፡

የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ሩጫ እየተካሄደ ነው 19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድሩ በወንዶች 455
+3
የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ሩጫ እየተካሄደ ነው 19ኛው የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድሩ በወንዶች 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች እየተሳተፉበት እንደሚገኝ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል። በዴንማርክ ኮፐንሀገን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች በውድድሩ እንደሚመረጡ ተገልጿል።

የቀድሞ የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በአዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በምስል!
+9
የቀድሞ የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በአዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በምስል!

አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል! የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎች እና የቀድሞው የክለቡ ተጫዋች አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦችን ጎበኙ። መንግስት የስፖ
+7
አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል! የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎች እና የቀድሞው የክለቡ ተጫዋች አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦችን ጎበኙ። መንግስት የስፖርት ቱሪዝም ለማሳደግ፣ የተለያዩ የስፖርት ማዕከላትን ከመገንባት ባሻገር፥ ሀገራዊ፣ ዓለማቀፉዊና አህጉራዊ ስፖርታዊ ፌስቲቫሎችን እንዲዘጋጁ በማድረግ ህብረተሰቡ እየተዝናና ጤናውን እንዲጠብቅ ምቹ ሁኔታን ተፈጥሯል። የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በከተማችን የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የስፖርት ማዕከላትን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።

ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረገው ጥረት በሕዝብ እና በጸጥታ አካላት ቅንጅት ከሽፏል፡- የሰላም ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የተካሄደውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማደፍረስ ጽንፈኛ ኃይሎችና የውጭ ጠላቶች የከፈቱት ሁለንተናዊ ጥቃት መክሸፉን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ ሀገራዊ ለውጡን የማይቀበሉ አካላት በመሬት ላይ የሽብር ጥቃቶችን ከመፈጸም ጀምሮ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የፕሮፓጋንዳና የሥነ-ልቦና ጦርነት ሲያካሂዱ ቆይተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ምርጫውን የህልውና እና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማረጋገጫ አድርጎ በመውሰድ በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ በአንጻሩ የስልጣን ሽግግርን በድምጽ መስጫ ኮሮጆ ሳይሆን በኃይል ለመጠቅለል የሚሹ የውስጥ ቅጥረኞችና የኢትዮጵያን እድገት የማይፈልጉ የውጭ ኃይሎች ሂደቱን ለማስቆም ከምርጫው በፊት፣ ወቅትና በኋላ ከፍተኛ ሴራዎችን መሸረባቸውን ይፋ አድርጓል። አፍራሽ ኃይሎቹ የመንግሥትን ሕጋዊ ቅቡልነት ለማሳጣትና ኢትዮጵያን ወደ ሥርዓት አልበኝነት ለመክተት ሕዝቡ የምርጫ ካርድ እንዳይወስድ፣ በፖለቲካ ድጋፍ ሰልፎች ላይ እንዳይገኝ እና በምርጫው ቀን ድምጽ እንዳይሰጥ ቅስቀሳ ሲያደርጉ እንደነበር ተጠቅሷል። ሆኖም የኢትዮጵያ ህሕብ ለጥሪዎቻቸው እውቅና ባለመስጠትና የጽንፈኝነትን አጀንዳ ውድቅ በማድረግ፥ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ተሳትፎ የምርጫ ካርድ በመውሰድ፣ በሰልፎች ላይ በነጻነት በመገኘትና በምርጫው ቀን በነቂስ ወጥቶ ድምጽ በመስጠት አፍራሽ ኃይሎቹን ማሸነፉን ሚኒስቴሩ ገልጿል። ይህ የዲሞክራሲ ስኬት ያለመስዋዕትነት እንዳልመጣ የጠቀሰው የሰላም ሚኒስቴር፤ የጸጥታ ተቋማት ባደረጉት ወቅቱን የጠበቀና የተቀናጀ አጸፋዊ እርምጃ የሽብር ዕቅዶቹ ሊከሽፉ መቻላቸውን አስታውቋል። ሆኖም የሕዝቡን አብሮነት ለመስበር የተሞከሩ የሽብር ጥቃቶች እንደነበሩ ጠቅሶ፤ ህዝቡ የከፈለው መስዋዕትነት ጽንፈኝነትን በመቃወም ሀገርን የሚያስቀጥል ሕጋዊ መንግስት ለመመስረት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳየበት መሆኑም ተመልክቷል። AMN

ከአክሞ ማዳን በፊት መከላከል ትኩረት ማድረግ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው በአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራን በተግባራዊ ፖሊሲዎች ለመደገፍ ያለመ አህጉራዊ ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰኔ 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ያዘጋጀው ይህ ጉባኤ በአካዳሚክ ምርምሮች እና በፖሊሲ አፈጻጸሞች መካከል ያለውን ክፍተት መሙላትን ታሳቢ ያደረገ ነው። የአፍሪካ ልማትና የተግባራዊ መፍትሄዎች መድረክ (ADIF 2026) የሚል ስያሜ ያለው ጉባኤ “በአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ የሚረዱ ምርጥ ተሞክሮዎችና የፈጠራ መፍትሔዎች” በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ ነው። ጉባኤው በአፍሪካ በፍጥነት እያደገ የሚገኘውን የወጣት ማኅበረሰብ፣ በዓመት ከ15 ሚሊዮን በላይ የሥራ ዕድል በመፍጠር አህጉራዊው ፍላጎትን ለመመለስ ከተያዘው ውጥን ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው። ይህ አዲስ መድረክ ከተለመዱ አህጉራዊ ስብሰባዎች በተለየ፤ የፖሊሲ አፈጻጸምን በማፋጠን በዘርፉ ያለውን የፖሊሲ እና የአሰራር ሂደት ለማቀለጣፈ ያለመ መሆኑን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በዚህም መሠረት የኢኮኖሚክ ኮሚሽኑ በገንዘብ እጥረት ምክንያት መሬት ያልወረዱ ጥናታዊ ምርምሮችን ወደ ተግባር ለመለወጥ፣ በጥቂት አካባቢዎች ተሞክረው ስኬታማ የሆኑ አነስተኛ የሙከራ ፕሮጀክቶችን ለማስፋት እንዲሁም አህጉር በቀል ምርጥ ተሞክሮዎችን በአገራት አጠቃላይ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ውስጥ በቀጥታ ለማካተት አቅዷል። አሠራሩ በልማት ላይ የሚፈሱ የአህጉሪቱ ኢንቨስትመንቶች አስተማማኝና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጡ ለማድረግ ትልቅ እገዛ ይኖረዋል ተብሏል። የፎረሙን ውጤታማነትና ተጠያቂነት በተረጋገጠ መልኩ ለመከታተልም፣ ከጉባኤው በፊት፣ በጉባኤው ወቅትና ከጉባኤው በኋላ የሚተገበር የአሠራር ሥርዓት ተዘርግቷል። የመድረኩን ቀጣይነትና ትስስር አስተማማኝ ለማድረግ፣ የየዓመቱ መሪ ሀሳቦችን አንዱ ከሌላው ጋር በማስተሳሰር እና ተመጋጋቢ በማድረግ እንደሚዘጋጁ ኮሚሽኑ አስታውቋል። በቀጣይ የሚካሄዱት ፎረሞች፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና (AfCFTA) ትግበራን ከአህጉራዊ የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂዎች ጋር ማስተሳሰር ጨምሮ ሌሎች የልማት የትኩረት መስኮችን ታሳቢ በማድረግ እንደሚካሄድ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት አካሄደ። ለካቢኔው በዛሬው በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡ በዚህ መሰረት፡- 1ኛ. የ
+9
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት አካሄደ። ለካቢኔው በዛሬው በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡ በዚህ መሰረት፡- 1ኛ. የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተዳደር ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ተፈፃሚ እንዲሆን አፅድቋል። 2ኛ. የመሬት ይዞታ ማስለቀቅና ካሳ ጉዳዮች ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ እንደገና ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ አፅድቋል። 3ኛ. በግል ዘርፍ ለህክምና ተቋማት ግንባታ እና ማስፉፍያ የሚውል መሬት ለማስተላለፍ የቀረበ የዉሳኔ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ፣ ተፈፃሚ እንዲሆን አድፅድቋል።

ዛሬ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነ፣ የሕዝባችንን የጤና አገልግሎት በአዲስ ከፍታ ላይ የሚያስቀምጥ አዲስ የዲኤንኤ(DNA)፣ የፎሬንሲክና ስነምረዛ ምርመራ የልህቀት ማዕከል መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል። ሀገራችን ብዙ የውጭ ምንዛሪ የምታጣበት እና የምርመራ ውጤት ለማግኘት በጣም ረጅም ጊዜ ይፈጅ የነበረውን ችግር የሚያስቀር የDNA መረጃ ማከማቻና ማነጻጸሪያ ሲስተም (CODIS)፣ በወንጀል የተጠረጠሩ፣ ወላጅነትን ለማረጋገጥና ተመሳሳይ ምርመራዎችን በዘር መለያ (DNA Profiling) ለመለየት፣ የቤተሰብ ግንኙነትን እስከ ዘር ሀረግ መለየትና ማረጋገጥ እንዲሁም አጠራጣሪ ማንነትን ለማወቅ የሚያስችል የልህቀት ማዕከል ነው። ይህ ማዕከል የሀገሪቱን የፍትሕ ሥርዓት ምርመራን ውጤታማ በማድረግና በማዘመን፣ በሳይንሳዊ ማስረጃ ላይ የተመሰረተ የወንጀል ምርመራ ለማካሄድ፣ የመብት ጥያቄዎችን ለመመለስና ለሕዝብ ጤና ጥበቃ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ብሔራዊ የልህቀት ማዕከል ነው። ሁሌም ቃልን በተግባር ፈፅመን በቁርጠኝነትና በተሻሻለ የስራ ባህል እየሰራን ባለፉት 5 ዓመታት ለጤናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት 4 ዓለም አቀፍ ደረጃ የሚመጥኑ ሆስፒታሎች በመገንባትና ነባሮቹንም ሆስፒታሎች በማደስና በማስፋፋት ሰፊ ስራዎችን ሰርተን አዘምነናቸዋል፡፡ በከተማ አስተዳደራችን በጤናው ዘርፍ የኢትዮጵያን የዕድገት ተምሳሌትነት እና የከፍተኛ ቴክኖሎጂ ምዕራፍ እያበሰርን ነው! ተጠናክሮም ይቀጥላል። ከዚሁ ጎን ለጎን የጤና ባለሙያዎቻችንን ትጋት፣ ብቃት እና እምነት ይበልጥ ለማሳደግ ልዩ ትኩረት እንሰጣለን። ከእቅድ ጀምሮ የልህቀት ማዕከሉ እውን እንዲሆን አስተዋጽኦ ያደረጋችሁትን በሙሉ በራሴ፣ በከተማ አስተዳደሩ እና በተጠቃሚዎች ስም ከልብ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባን የአፍሪካ የከተሞች ልማት ተምሳሌት ያደረገው የ24/7 የመፈጸም አቅም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" በማለት አቅጣጫ ያስቀመጡት ከተማዋ ስሟን የምትመጥን እንድትሆን በማሰብ ነው። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል ዛሬ በከተማዋ ተግባራዊ በሆኑት መዋቅራዊ እና ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች አማካኝነት በተጨባጭ እውን እየሆነ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ ወደ መሬት አውርዶ በተግባር ለመተርጎም ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያሳየው የአፈጻጸም ብቃት ሁነኛ ሚና ተጫውቷል። በከንቲባ አዳነች አቤቤ የሚመራው የከተማዋ አመራር ቁርጠኝነት የለውጡ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ሞተር ሆኖ አዲስ አበባን እንደ ስሟ የፈካች አበባ አድርጓታል። አስተዳደሩ ያሰፈነው የ24/7 (ቀን ከሌሊት) የሥራ ባህል ቀደም ሲል ለዘመናት ስር ሰድዶ የነበረውን ዝግተኛ የመንግሥት ቢሮክራሲ በመስበር፣ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ እና በከፍተኛ ጥራት የማጠናቀቅ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፍቷል። ይህ የሥራ ባህል ለውጥ ከተማዋን የማዘመን ተግባር ብቻ ሳይሆን፣ የከተማዋን ኢኮኖሚ ሌት ተቀን በማንቀሳቀስ ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል የፈጠረ የልማት ኃይል ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። የአመራሩ በቢሮ ከመቀመጥ ይልቅ በምሽት የሥራ እንቅስቃሴዎች ላይ በአካል በመገኘት እና በመከታተል፣ በበዓላት ቀናት ከኮሪደር ልማት ሠራተኞች ጋር ማዕድ በመጋራት፣ እንዲሁም ሠራተኛውን በቅርበት በማበረታታት መሪነትን በተግባር አሳይተዋል። ይህ ዓይነቱ ያልተቋረጠ የአመራር ክትትል እና አብሮነት የሥራ ባህልን በመቀየር ረገድ ትልቅ ሥነ-ልቦናዊ ለውጥ አምጥቷል። የአስተዳደሩ ትጋት ከተማዋ ላይ ያመጣቸው ተጨባጭ ለውጦች ያፈሩት ፍሬ ዛሬ በገሃድ ይታያል፤ በርካቶችንም ተጠቃሚ አድርገዋል። የከተማዋን ገጽታ ሙሉ ለሙሉ የቀየሩት ሰፋፊ የኮሪደር ልማቶች፣ ግዙፉ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የአዲስ አበባ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ ማራኪ የሆኑት የሕዝብ መዝናኛ ስፍራዎች እና ዘመናዊ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የአዲስ አበባን ትክክለኛ ውበት አጉልተው አውጥተውታል። አዲስ አበባን የኪነ ጥበብ እና ፍልስፍና ማዕከል ለማድረግም ዘመናዊ የሲኒማ ኮምፕሌክሶች እና አምፊ ቴአትሮች በስፋት ተሠርተው ለአገልግሎት በቅተዋል። አዲስ አበባ መጪውን ጊዜ ስታስብ ትላንቷንም ሳትረሳ ኢትዮጵያን ላገለገሉት ልጆቿ መታሰቢያ በማቆም ለቅርሶቿ ጥበቃ አድርጋለች። የወንዝ ዳር ልማት፣ ትላንት የበሽታ እና የወንጀል ምንጮች የነበሩ ወንዞችን በማደስ ለከተማዋ አዲስ አስትንፋስ ሰጥቷል። እነዚህ ተከታታይ ስኬቶች አዲስ አበባ ስሟን የሚመጥን ከተማ እንድትሆን ከማድረጋቸውም ባሻገር፣ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫነቷን እና የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በሚመጥን መልኩ የዓለምን ቀልብ በከፍተኛ ሁኔታ እንድትስብ አድርጓታል። ዛሬ ላይ ቱሪስቶችም ሆኑ ዓለም አቀፍ ልዑካን በከተማዋ ንጽህና እና ፈጣን ዕድገት መገረማቸውን በተደጋጋሚ ከመግለጽ አልፈው በአካል መጥተው ለዓለም አረጋግጠዋል። መዲናችንን የጎበኙ ዓለም አቀፍ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችም ከተማዋ ከየትኛውም የዓለማችን ከተማ ጋር የምትወዳደር ውብ ከተማ እንደሆነች አረጋግጠዋል። ከዚህም በላይ የከተማ አስተዳደሩ የጀመረው የኮሪደር ልማት እና የመልሶ ማልማት ሥራ፣ ማንንም ወደ ኋላ የማይተው ሰው-ተኮር መርሕን የተከተለ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያስመዘገበው ይህ አስደናቂ የመፈጸም አቅም እና የልማት አርአያነት በዋና ከተማዋ ብቻ ተወስኖ አልቀረም። ከተማ አስተዳደሩ ይህን ተጨባጭ ለውጥ ወደ ክልል ከተሞችም በተሳካ ሁኔታ እንዲሰርጽ አድርጓል። ባለሙያዎችን በመመደብ እና የቴክኒክ ድጋፎችን በማቅረብ ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ የጀመረችውን የኮሪደር ልማት በፍጥነት እና በጥራት እንድታከናውን ትልቅ አሻራውን አሳርፏል። በተመሳሳይ መልኩ የሐይቆች ከተማ የሆነችውን ቢሾፍቱ ከተማን የኮሪደር ልማት እና የቱሪስት መዳረሻነት ለማጠናከር የተደረጉት የልምድ ልውውጦች፣ የአመራሩን አጋርነት እና ሀገራዊ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩ ናቸው። በአዲስ አበባ የታየው ይህ አስደናቂ ለውጥ በምኞት የመጣ ሳይሆን፣ በጠንካራ መዋቅራዊ ዕቅድ፣ ቀን ከሌሊት በሚተጋ ቁርጠኛ አመራር፣ በተለወጠ የሥራ ባህል እና ከሕዝብ ጋር በተመሠረተ ጠንካራ ትሥሥር የመጣ ውጤት ነው። ይህ ስኬት "የጀመርነውን እናጠናቅቃለን" የሚለውን የይቻላል መንፈስ በዜጎች ልቦና ውስጥ ያሰረጸ እና መላው ኢትዮጵያውያን በመዲናቸው እንዲኮሩ ያደረገ ብሩህ ተስፋ ነው። አዲስ አበባ ዛሬ በአፍሪካ እጅግ ተወዳዳሪ፣ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ለሌሎች ከተሞች ታላቅ የልማት ትምህርት ቤት ሆና በኩራት ቆማለች። EBC

የልማት ስራዎች የአንድ ወቅት ብቻ አይደሉም፥ ዘመን ተሻጋሪ እንጂ! በተለያዩ የልማት ስራዎች ፈር ቀዳጅ የሆነችው አዲስ አበባ፣ ከ7ኛው ሀገራዊ መርጫ ማግስት በተለያዩ የልማት ስራዎች መገለጥዋን ቀጥላለች፡፡ የልማት ስራዎች የአንድ ወቅት ብቻ አለመሆናቸውን የተረዳው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ከዚህ ቀደም በእንግልት እና በኃላ ቀር አሰራር ህዝብ ሲማረርባቸው የነበሩ የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ይስተዋል የነበረውን ችግር በማስቀረት፣ በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ቀልጣፋና የተቀናጀ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ዘመናዊ ተቋማት እየተገነቡ ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። ከዚህም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ዘንድ ለዓመታት የቆየውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ታላቅ ስራ ሲሆን፤ በተለይም በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተደራሽ መሆኑ ነዋሪዎች ከተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚያገኟቸውን አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተቀናጅና በተናበበ እንዲሁም በሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲያገኙ አድርጓል። ቀደም ሲል ቀናትና ሳምንታት ይወስዱ የነበሩ ጉዳዮች፥ ዛሬ በመሶብ የአንድ ማዕከል በደቂቃዎች ውስጥ እልባት ማግኘት ችለዋል፡፡ ከሁሉም በላይ አገልግሎቱ ወደ ነዋሪዎች መቅረቡ ነዋሪዎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ባሉበት ቦታ በተንቀሳቃሽ መሶብ አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል። እነዚህ ማዕከላት በውስጣቸው ከንግድ ፈቃድ ምዝገባ ጀምሮ እስከ መታወቂያና የውልና ማስረጃ አገልግሎቶች ድረስ እጅግ በርካታ ፋይዳ ያላቸውን ዘርፎች አካትተዋል። በተለይም ለአገልግሎት ፈላጊዎች ምቹ የሆኑ የጥበቃ ስፍራዎች፣ ዲጂታል የሰልፍ መቆጣጠሪያዎች፣ የህፃና ማቆያና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ የሆኑ መሰረት ልማቶችን በመያዛቸው ተገልጋዩ የጊዜ ብክነት እና እንግልት እንዳይገጥመው ታድገዋል፡፡ በአዲስ አበባ የተጀመረውና በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተግባራዊ የሆነው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቁጥሩን ወደ ስምንት ከፍ በማድረግ እንዲሁም በተንቀሳቃሽ አውቶብስ አገልግሎቱን በማስፉት ነዋሪው እፎይታን እንዲያገኘ ማድረግ ተቸሏል። የልማት ስራዎች የአንድ ወቅት ብቻ አይደሉም፥ ዘመን ተሻጋሪ እንጂ፥ ይቀጥላል!